cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

የፍቅር ጥቅሶች

Melkam ፍቅር ለአፍቃሪ እንጂ ለተፈቃሪው ------------ !!!!!!-👨----?-----👩-----?----መልሱ ቻናሉ ውስጥ አለ ????????👀👀

Більше
Рекламні дописи
211
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

🌿አፍቅሩ፣ ነገር ግን . . . አንድን ሰው ስታፈቅሩ በዚያ ስሜት ውስጥ ሆናችሁ ረጅም ርቀት ከመጓዛችሁ በፊት እናንተ ያንን ሰው ባፈቀራችሁበት የፍቅር ጥልቀት ልክ እሱም እንደሚያፈቅራችሁ እርግጠኛ መሆናችሁን አትዘንጉ፡፡ እናንተ ላላችሁ ጠሊቅ ፍቅር የሚመጥን ፍቅር የሌለው ሰው የሚሰጣችሁ ቁስል ያንኑ ያህል ጠሊቅ መሆኑን አትርሱ፡፡ አፍቅሩ፣ ነገር ግን ያላችሁን የፍቅር ስሜት መውሰድ በፈለጋችሁት ፍጥነት ያኛውም ሰው መውሰድ መፈለጉን እርግጠኛ ሁኑ፡፡ አፍቅሩ፣ ነገር ግን ልባችሁን አሳልፋችሁ ከመስጠታችሁ በፊት እናንተም መፈቀራችሁን እርግጠኛ ሁኑ፡፡ አፍቅሩ፣ ነገር ግን ፍቅር አውነተኛ ነው እንጂ እውር እንዳልሆነ አትርሱ፡፡ ፍቅር ያስባል፣ ያያል፣ ያመዛዝናል፣ ምላሽ ይጠብቃል፣ በመጨረሻም በትክክለኛው ነገር ላይ ይቆርጣል፡፡ Semir
Показати все...
💡ማነው? ማነው? 🔸ብርሃንና ጨለማን ፥ ሜዳና ተራራን ፥ ፍቅርና ጥላቻን ፥ የሕይወትን ዉጣ ዉረድ በዉስጡ ሳያልፍ ፥ በዉስጡ ጥልቅ የመኖር ግንዛቤ ያገኘው? ማነው? ባለንበት ምድር ያለ አንዳች ችግር ጥበብን ያጠና? ማነው? 🔹በቤተሰብና በሕብረተሰቡ ዉስጥ ቢያንስ ቢያንስ መጠነኛ ግጭት ሳያጋጥመው ፍቅርና ሰላምን ያየ? ማነው? 🔸በዓለም ላይ ፈተና ሳያጋጥመው ከተለመደው የሕይወት ዕርዳታ ሳይወጣ ታላቅ ተግባርን ያከናወነ? __ማንም የለም ! 🔹ሕይወት ማዕበሉንና ወጀቡን ዳር ይዘን ተግ እስኪል እንድንጠብቅ አትፈልግም ፥ ይልቁንስ በዝናቡና በወጀቡ መካከል ሆነን መደነስን እንድንለምድ እንጂ። ደግሞም 🔸አምላክ ስቃይ አልባ ቀናትን ቃል አልገባልንም።ለሃዘን አልባ የፈንጠዝያ ጊዘያትም ቃሉን አልሰጠንም፡፡ዝናብ የሌለባቸዉን ጸሃያማ ቀናትንም ተስፋ አልሰጠንም።ይልቅ ለስቃይና ለመከራችን ጥንካሬን ፥ ለሃዘናችን መጽናናትንና ለመንገዳችን ብርሃንን ነው ቃል የገባልን፡፡ እናም 🔹ፈጣሪያችንን መለመን ያለብን ችግሮችን ከእኛ እንዲያርቅልን ሳይሆን ፥ ችግሮቻችንን ተጋፍጠን በአሻፊነት እንድንወጣ ጥንካሬውን እንዲሰጠን ነው፡፡ እኛ የቻልነዉን ካደረግን ፥ ፈጣሪ ደግሞ ያልቻልነዉን ያደርግልናልና፡፡ ጥንካሬዉን ይለግሰን፣ semir ami ❤️
Показати все...
‍ ❤️ እናት ❤️ Semir ami እልፍ አመት ተወራ  ቅኔም ተዘረፈ ሀገር ሁሉ ሰማ ስለእናት ተፃፈ ሆኖም አልበቃ ሲል ዛሬም ይታወሳል ቃል በቃል ተውቦ  ስሟ  ይወደሳል❤️ ግን እኮ አስተውሎ ላየው ከስር መሰረቱ የሰው ዘር መፍለቂያ እናት ነች  እንብርቱ🤗 ሜዳው ቢለሰልስ ምን ቢያምር መሬቱ ተወላጅ አይስቅም ከሌለች እናቱ‼️ እናት እናት ብየ ልቃኝላት አምሮኝ የትዝታ ፍቅሯ ናፍቆቷ አሰከረኝ☺️ ሀገሩን ብዞረው ቃላትን ፍለጋ ስንኝ ላሰፍርላት መሽቶም እስኪነጋ ልቄ ላሞግሳት ባስብ ልዳብሳት ጥልቅ ነው ሚስጥሩ አልቻልሁም ልደርሳት የእናትነት ፀጋ መች እንዲ ቀላል ነው ብዕር ያለው ሁሉ አድምቆ የሚፅፈው ሆሄያት ቃላት ሰርተው ሀረግም መስርተው ስንኝም ቢሞሉ ሊገልፁት አይችሉም የእናትነት  ፍቅርን እንዲ በቀላሉ።❤️ ✅yefeker_tiksoche
Показати все...
ይወት ቀረ።" ይሄ ግጥም ራሄል ተስፋዋ ሙጥጥ ሲልናራሷን ልታጠፋ በወሰነችበት ቅፅበት የፃፈችዉ እንደሆነ ገመትኩ። "ምን ያህል እንደምወድሽ ብታዉቂ!" አልኩ በልቤ! ግን ህይወት የእዉነታ እንጂ የስሌት ጉዳይ አይደለችምና እዉነቱን ማስተናገዱ ይሻላል። ስለዚህ ነገር አልተነገረኝም ነበር። የሪቾን ግጥሞች በዚህ መልኩ ሳያቸዉ እንድደመም አስባ ይሆናል ሀዩ ያልነገረችኝ። የራሄል ቤተሰቦች ባዩት ነገር በጣም ተደምመዋል። ምን እነሱ ብቻ እኔ ራሱ የሌለ ተደንቄያለሁ። ሌላዉ በጣም የሚገርመዉ ራሄል ለእኔ የፃፈችዉ የስንብት ደብዳቤ በትልቁ ግድግዳዉ ላይ የተፃፈበት ልዩ የመመገቢያ ክፍል መኖሩ ነዉ። ስገምት ሴቶች ባላቸዉን ለመጋበዝ የሚመርጡት ሁነኛ ቦታ የሚሆን ይመስለኛል። ስታጣኝ እዉነቱን ትጋፈጣለህ አይነት ማስፈራሪያ ሲፈልጉ ማለት ነዉ። በሀዩ የአመራር ብቃት ተደመምኩ። በቀጣይ ደግሞ ሆቴሉ የአስጎብኚ ቡድን እንዲኖረዉ ለማድረግ አቅደዋል። ሀዩ ታቅዳለች እኔ እየሳቅኩ እፈርማለሁ። . ጉብኝቱን ጨርሰን ምግብ ልንበላ የምግብ አዳራሹ ዉስጥ ስንገባ ሰዒዶናኢማን ይዘዉኝ ያደረግከዉ ንግግር የፖለቲከኛ ይመስላል ብለዉ ፎገሩኝ። ሰኢዶናኢማን አንድ ወንድ ልጅ ወልደዋል። ሙሀባ ብለዉታል። የራሄል አባት በተሰራዉ ስራ የተሰማቸዉን ደስታ ገለፁልኝ። ወዲያዉ አንድ የራሄል ቤተሰብ የሆነ ልጅ መጥቶ አድናቆቱን ከገለፀልኝና በዚህ እድሜዬ እንደዚህ ለስኬት መብቃቴ እንደገረመዉ ነግሮኝ ጥያቄ አዘነበብኝ። እሱ ሀብቴ ብዙዉን የዉርስ መሆኑን አያዉቅም። ሲቀጥል ሆቴሉን በዚህ መልኩ የማስተዳድረዉ እኔ መስየዋለሁ። ሀዩ እንደሆነች አያዉቅም። "አንድ ቆንጆ ምክር እስኪ ምከረኝ!" አለኝ ከኔናከሀዩ ጋር እየተቀመጠ "በወንድናበሴት መካከል ተፈጥሯዊ መፈላለግ አለ። ስለዚህ ሴት ልጅ ሚስትህ እንጂ የልብ ጓደኛህ አትሁን!" አልኩት። ሀያት ሳቋን ለቀቀችዉ። እኔ ጓደኞቼ ሴቶች በመሆናቸዉ የገባሁበትን ጭንቅ እኔ ነኝ የማዉቀዉ። ራሄል ጓደኝነት በቀደደዉ መንገድ ፍቅር ላይ ወድቃ ነዉ እስከሞት የደረሰችዉ። "አንተ ጓደኛህን አይደል እንዴ ያገባኸዉ?" አለኝ ወደ ሀያት እየጠቆመ "አዎ ግን የሞተችዉም ጓደኛዬ ናት።" አልኩትና ወደ ሀዩ እየጠቆምኩ "እሷም ብትሆን ደስታዬ የሆነችዉ ከተጋባን በኋላ ነዉ።" አልኩት። ልጁ ፈገግ ብሎ ልጃችንን እና ከኛ ቀጥሎ ያለዉ ጠረጴዛ ላይ የተቀመጡትን ቤተሰቦቻችንን እያየ ሳቀና "የናንተ ቤተሰብ በጣም ያስቀናል!" ብሎን እየሳቀ ከመቀመጫዉ ተነስቶ ወደ ቤተሰቦቻችን ጠረጴዛ ሄደ። የልጁ ድፍረት ገረመኝ። ራሄል በወንዱ ነገር ነዉ። ከእናቴ ጋር ማዉራት ጀመረ። ስቀን ዞር አልን። . ከሁለት ቀን በኋላ እኔ መኝታ ክፍል ዉስጥ ጋደም ብያለሁ። ሀዩ ራህማን ስታጫዉት ይሰማኛል። የምትለዉን ራህማ እንድትደግመዉ እያደረገች ትስቃለች። "ረበና" አለች ሀዩ "አፐና" ትላለች ራህማ! ሀዩ በሳቅ ፍርስ ትላለች "ማ ኸለቅተ ሀዛ" "ማተዛ" ትላለች ራህማ! አሁን እኔም በጣም መሳቅ ጀምሬያለሁ። ሀዩ በጣም እያዝናናት ነዉ መሰለኝ ቀጠለች። "ባጢለን ሱብሀነክ!" "ባክነን" አለች ራህሚ! በሷ ቤት ሀዩ ያለችዉን መድገሟ ነዉ። አንደበቷ ይጣፍጣል። ከምር ግን እንደ ልጅ ምንም የሚያስደስት ነገር የለም። ሀያት ራህማን ስታስብላት የነበረዉ የቁርዓን አንቀፅ ነዉ። "ረበና ማ ኸለቅተ ሀዛ ባጢለን ሱብሀነክ!" ነበር ያለችዉ። ትርጉሙ "ጌታችን ሆይ ይህን (ድንቅ አለም) እንዲሁ (ያለ ዓላማ) አልፈጠርከዉም ..." ማለት ነዉ። ፈጣሪ ምድርና ሰማይን እንዲህ ያስዋበዉ የስዕል ጥበቡን ለማሳየት አይሆንም። ስለዚህ በከንቱ ያልተፈጠረ ምድር ላይ ከንቱ መሆን አይገባም። ምድር በከንቱ አልተፈጠረችም። እኛም ለጨዋታ አልተፈጠርንም። ህይወታችን ቁምነገር ሊሆን ይገባል!! "የራሄል አምላክ እዉነት ተናገረ!" አልኩ አልጋዉ ላይ እንደተዘረርኩ። አልረሳት ነገር ከልቤ ታትማ ፤ የኔ አትሆን ነገር ከመቃብር ከትማ! ጌታዬን ራህማን እና ሀያትን ስለሰጠኝ አመሰግናለሁ። የተከለከልናቸዉ ከሚመስሉን ነገሮች ይልቅ የተሰጡን ዋጋ አላቸዉ። . ተፈፀመ!! . ✎የፍቅር ጥቅሶች||™ @Bast_Love_Quotes_Robot
Показати все...
መንታ መንገድ ክፍል አስራአምስት (ፉአድ ሙና) . . ሀዩዬ እንደሷ ቆንጆ ልጅ ወልዳልኝ ሆስፒታል ከተኛች በኋላ በሀኪሞቹ ፈቃድ ወደ ቤተሰቦቿ ቤት ወሰድናት። እናቷ ሁሉንም ነገር አዘጋጅተዉ ጨርሰዉ ነበር። ገንፎ ለሀዩ ይሰራል መግፊ በሷ እያሳበበች ትበላለች። የኔናየመግፊ የሰሞኑ ትርርባችን በገንፎዉ ጉዳይ ላይ ነዉ። ፓምፐርስ ምናምን ከመግፊ ጋር ሆነን ገዝተናል። መግፊ ሆነ ብላ ሴሪፋም አስገዝታ መሳቂያ አደረገችኝ። ለካ እስከ ስድስት ወር ከጡት ሌላ ምንም አይነት ምግብ ለህፃናት አይሰጥም። ሀዩዬን ልጃችንን ስታጠባ አየኋት ፤ የሆነ ልብ የሚይዝ ነገር አለዉ። ልጇን ስትንከባከብ በጣም ደስ ትላለች። . በሰባተኛዉ ቀን ሁለት በግ አርደን ሰደቃ አወጣን። ሰደቃ ማለት ምፅዋት ማለት ነዉ። በሀይማኖታችን መሰረት ልጅ በተወለደ በሰባተኛዉ ቀን የሚደረገዉ ይህ የምፅዋት ዝግጅት አቂቃ ይባላል። በነገራችን ላይ ለልጃችን ስም ለማዉጣት በጣም ብዙ ክርክር ነበር የተፈጠረዉ። መጀመሪያ ራሄል እንድትባል ፈልጌ ነበር። ግን የሀዩም የኔም ቤተሰቦች በራስ ላይ ሀዘንን ማባባስ አያስፈልግም ብለዉ ተቆጡኝና ተዉኩት። እንደዉም የሀዩ እናት "ለሀያትም ስሜት አስብ እንጂ! ማትፈልጋት እንዳይመስላት!" ነበር ያሉኝ። ሀዩ ብዙ ነገር ስላደረገችልኝ ስሜቷን መጠበቅ ይኖርብኛል። ራሄልን ለመዘከር ሆቴሉ ይበቃል። ብዙ የስም ምርጫዎች ከቀረቡ በኋላ መጨረሻ ላይ "ራህማ" የሚለዉ የኔ ምርጫ ተቀባይነት አገኘ። እኔ ራህማ እንድትባል የፈለግኩት ከራሄል ሞት በኋላ የነበርኩበትን መጥፎ ሁኔታ ፣ አልጋ ላይ የነበረብኝን ያለመረጋጋት ችግር እና ጥፊዬን ችላ ለኖረችዉ ዉዷ ሚስቴ ሀያት ስጦታ እንዲሆን በማሰብ ነዉ። ነብዩ አዩብ(እዮብ) በሽታ ሲፈራረቅበት ፣ ሀብቱ ሁሉ ሲወድም እና ሌሎች ሚስቶቹ ትተዉት ሲሄዱ በፅናት ከጎኑ የቆየችዉ አንዷ ሚስቱ ራህማ ብቻ ነበረች። እናም የኔ ልጅ ከብዙ ችግር በኋላ የተገኘች ናትና የሚስቴን ትዕግስት ለመዘከር ራህማ አልኳት። ራህማ ማለት እዝነት ማለት ነዉ። . ሀጅራ ፣ እስክንድር እና የሪቾ ቤተሰቦች ፤ ቤት መጥተዉ ሀዩን አራስ ጠይቀዋታል። በነገራችን ላይ ሀጅራ ታጭታለች። በቅርቡ ማግባቷ አይቀርም። የአክስቴ ልጅ እና የዉዱ ጓደኛዬ ሰዒድ ሚስት ኢማን ሰሞኑን ከነሀያት ቤተሰቦች ቤት ጠፍታ አታዉቅም። ኢስራዕ እና መርየም ቤታቸዉ አድርገዉታል። ከመግፊራ ጋር ሆነዉ ሀዩን ያዳብሯታል። እናቴም ከአባቴ ሞት በኋላ ትንሽ ስርዓት ይዛለች። ከአክስቶቼም ጋር ታርቀዋል። ምግብ እየሰራች ለሀዩ ይዛላት ትመጣለች። ከምር ልጅ ግን የደስታ ምንጭ ነዉ። ስራ ዉዬ ማታ አይኗን እስከማይ እንዴት እንደምጓጓ! በርግጥ ለሀዩዬ ያለኝም ፍቅር በጣም ጨምሯል። . ጊዜዉ በሀዩ ፍቅርና በራህማ ጨዋታ ታጅቦ ነጎደ። ራህማዬ ሁለት አመት ሞላት። የራሄል ሆቴል ግንባታም ተጠናቀቀ። አጠቃላይ እቃዎቹን ሳይጨምር ለግንባታ ብቻ አስር ሚሊየን ብር አዉጥተናል። በርግጥ ቢዝነሱ አስተማማኝ ስለሆነ በአመት ዉስጥ ይመልሰዋል። በዛ ላይ ሀዩን የመሰለች የምርጥ ጭንቅላት ባለቤት ናት የምታስተዳድረዉ። የዉስጥ እቃዎቹን ከዉጭ ካስመጣንናእነሀያት ሰራተኞችን ከቀጠሩ በኋላ የሚመረቅበት ቀን ደረሰ። ሆቴሉ በአክሲዮን የተከፈተ ነዉ። የእኔ ቤተሰብ ፣ የሀያት ቤተሰብ ፣ የራሄል ቤተሰቦች ፣ እስክንድር ፣ ሰዒድ እና ሀጅራ ነን ባለድርሻዎቹ። ትልቁ ድርሻ ግን የኔ እና የሀዩ ቤተሰቦች ነዉ። የሆቴሉ የቦርድ ሰብሳቢ እኔ እንድሆን ተወስኗል። ሆቴሉን በስራ አስኪያጅነት ደግሞ ሀያት ትመራዋለች። ምክትል ስራ አስኪያጁ ልምድ ያለዉ ሰዉ ነዉ። ሀጅራ እና እስክንድርም ዉስጥ ላይ የሀላፊነት ቦታዎችን ይዘዉ ይመራሉ። ከምርቃቱ በፊት የማስታወቂያ ክፍላችን ሆቴላችን በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ እንዲተዋወቅ አደረገ። እነሀያት በስራዉ በጣም ተወጥረዋል። እኔ እንኳ የራሴን ስራ ስለምሰራ በሳምንት አንዴ ነዉ ሪፖርታቸዉን ለማዳመጥ የምሄደዉ። . ጠዋት ቢሮ ስገባ ፀሀፊዬ ሞጆ ደረቅ ወደብ ላይ ስላሉ እቃዎች ካወራችኝ በኋላ አንድ ደብዳቤ ሰጥታኝ ወጣች። ከራሄል ሆቴል ይላል። እነሀያት እንደላኩት ገመትኩ። ከፍቼ አነበብኩት። "የራሄል ሆቴል የምርቃት ስነ ስርዓት በቀጣዩ ሳምንት እንደሚደረግ ይታወቃል። በመሆኑም ሆቴሉ የራሄል መታሰቢያ እንደመሆኑ በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ ስለ ራሄል የሚዳስስ አጭር ፅሁፍ መቅረብ ይኖርበታል። ስለሆነም እንደ ሆቴሉ የቦርድ ሰብሳቢነትዎ በእለቱ ይህን ሀሳብ ባካተተ መልኩ የመክፈቻ ንግግር እንዲያደርጉልን በአክብሮት እንጠይቃለን። ከሰላምታ ጋር!" ይላል። ከስሩ የሀያት ፊርማ አለዉ። ረዥም ሰዓት ብቻዬን ሳቅኩ። ለምን ሳቅኩ? ሀዩ ለኔ ደብዳቤ መፃፏ ገርሞኝ! እሷ ስራ ላይ ቀልድ አታዉቅም። . የሆቴሉ ምርቃት ሲጠጋ ሀያት ስራ ስለበዛባት አንዳንዴ አስፈቅዳኝ እዛዉ ታድራለች። ራህማን ሁሌም ስራ ስትሄድ ይዛት ነዉ የምትሄደዉ። "አንተ እኔን እንጂ እሷን ማቀፍ አትችልበትም!" ትላለች ሀዩ። ለነገሩ ራህማ መራመድ እና ትንሽ ትንሽ መናገር ጀምራለች። ከብዙ ዉጥረት በኋላ የራሄል ሆቴል ምርቃት ደረሰ። የዛን ቀን ሀዩ ሆቴል ስለነበር ያደረችዉ ከኢስራዕናማማ ጋር ሄድኩ። መርየም ከባሏ ጋር ሄዳለች። የሆቴላችን በር ላይ ስደርስ ድባቡ ለየት ያለ ነዉ። መኪናዬን የሆቴሉ ፓርኪንግ ጋር አቁመን ወደ ዉስጥ ገባን። ሱፍ የለበሱ ወጣቶች ወዲያዉ እየተቀላጠፉ ወደ ሆቴሉ አዳራሽ ይዘዉን ሄዱ። ብዙ ሰዉ አለ። አዳራሹ ጋር ስንደርስ ሀዩ በሩ ጋር ቆማ እንግዳ እየተቀበለች አገኘኋት። ሰላም ካለችን በኋላ ኮሌታዬን አስተካክላልኝ ወደ ተዘጋጀልን መቀመጫ ወሰደችን። እንግዳዉ ሁሉ ቦታ ቦታ ከያዘ በኋላ መድረክ መሪዉ ወደ መድረክ ወጥቶ የእለቱን ዝግጅቶች አስተዋወቀ። ከዚያም ሀያትን ወደ መድረክ ጠርቶ እኔን ንግግር እንዳደርግ እንድትጋብዘኝ አደረገ። እንግዲህ የቦርድ ሰብሳቢዉ በስራአስኪያጇ መጋበዙ ነዉ። ሀዩ ስታወራ አንቱ እያለችኝ ነበር። እኔ ሳቄን ለመቆጣጠር እየታገልኩ ነዉ። . መድረኩ ላይ ወጥቼ ንግግሬን ጀመርኩ። ሁሉም አፉን ከፍቶ ያዳምጣል። "ዛሬ በዋናነት በስራ አስፈፃሚዎቻችን ብርታት ሆቴላችንን ለመመረቅ በቅተናል። ግን መረሳት የሌለበት፤ ሆቴሉ ትናንት አብራን በአንድ ጎዳና ላይ ስትጓዝ የነበረችናብዙ ህልም የነበራት ጓደኛችን መታሰቢያ መሆኑ ነዉ። የራሄል ዉበት በሆቴላችን አይነግቡነት ይገለፃል። የሰላ ብዕሯን የማስታወቂያ ቡድናችን ተቋማችንን ያስተዋዉቅበታል። ለሰዉ የነበራትን ፍቅር ሰራተኞቻችን እርስ በእርስ ይዋደዱበታል። እሷን መልሰን ማግኘት ባንችልም ሆቴሉን ትልቅ ደረጃ በማድረስ ከፍ አድርገን እንዘክራታለን። ራሄል ሆቴል በይፋ ተከፍቷል!!" አልኩና ከመድረኩ ወረድኩ። ታዳሚዉ ያጨበጭባል። . የመንግስት ባለስልጣናት ዲስኩራቸዉን ካሰሙ በኋላ ታዳሚዉ ሆቴሉን እንዲጎበኘዉ ተደረገ። በየኮሪደሩ ላይ የራሄል ፎቶ በሚያምር ፍሬም ተሰቅሏል። አንድ ጥግ ላይ ደግሞ የራሄል የተመረጡ ግጥሞች በልዩ ዲዛይን ተሰርተዉ ግድግዳዉ ላይ ተሰቅለዋል። አይኔ አንዱ ግጥም ላይ አረፈ። መንታ መንገድ ይላል አርዕስቱ "መንታ መንገድ ፊት ቆሞ ፈራጁ፣ ምረጥ ተባለ ከመንገዶቹ፣ ግራዉን መንገድ እየወደደዉ ለሀይማኖት ሲል ቀኙን መረጠዉ። ቀኝ በጎ ነዉ ሲባል የሰማ፣ ነገዉን ብሎ ግራዉን ያማ፣ ሚስኪን አፍቃሪ ፍቅሩን ተቀማ። ግራዉ ፈራጁን ማግኘት ቢነፈግ፣ ፈገግታ ሰጡት ለቅሶ ሚሸሽግ። ሳቀ ሳቀና አንብቶ አንብቶ፣ ፈራጅን ሲያልም ዉሎ አምሽቶ፣ ተስፋ ሲቆርጥ ፣ ፈርሶ አደረ፣ ከተጠራበት ፣ ከህ
Показати все...
መመኝ። ከአይኔ እንባ ፈሰሰ። "ኧረ በፀጋ አይለቀስም! አላህን ፍራ!" አሉኝ የሀዩ እናት። ሰዒዶ ከክፍሉ ራቅ ብሎ ወዳለ መቀመጫ ወሰደኝ። ሰዒድ እያየኝ ይስቃል። "ልጅም አባትም አልቅሳችሁ እንዴት ይሆናል!" አለኝ እየሳቀ! ንግግሩ እያሳቀኝ "እሱን ኢማን ስትወልድልህ ትቀምሰዋለህ!" አልኩት። ወዲያዉ የማዋለጃዉ ክፍል በር ሲከፈት አየን። ከተቀመጥንበት ተነሳን። ከክፍሉ አንድ ዉሀ ሰማያዊ የህክምና ልብስ የለበሰች ሴት ወጥታ እነመግፊራን ማናገር ጀመረች። ወደ ክፍሉ በፍጥነት እየተራመድን ተጠጋን። የህፃን ልጅ ለቅሶ ይሰማል። የነመግፊራ ፊት ላይ ደስታ ይነበባል። ወዲያዉ መሬት ላይ በግንባሬ ተደፍቼ ጌታዬን አመሰገንኩ። እነመግፊን ተከትዬ ወደ ማዋለጃ ክፍሉ ገባሁ። ሀዩዬ ፊቷ በላብ ተጠምቆ ተጋድማለች። ስታየኝ ፈገግ አለች። ተንደርድሬ ሄጄ አልጋዉ አጠገብ ተንበርክኬ እጇን ያዝኩት። ጠጋ ብዬ ግንባሯን ሳምኳት። "ደሞ አሁን ቆንጆ የሴት ስም እንፈልግ!" አለች መግፊራ! ልጄ ሴት ነበረች። ደስ አለኝ። ደስታዬ ወደር የለዉም። በጣም ደስስስስ አለኝ። "ያንተንም ጉድ እናየዋለን ሰዒዶ!" አለች ሀዩ ወደ ሰዒድ እያየች። "እስኪ አላህ ያድርሰን!" አለ እየተሽኮረመመ። ወዲያዉ ሀኪሞቹ ግርግሩን እንድንቀንስ እና እንድንወጣ አዘዙን። እናቷ ብቻ ቀሩ። እኔና መግፊራ ለጊዜዉ የሚያስፈልጉ ነገሮችን ለመግዛት ሄድን። . ይቀጥላል... . ✎የፍቅር ጥቅሶች||™ @Bast_Love_Quotes_Robot
Показати все...
መንታ መንገድ ክፍል አስራአራት (ፉአድ ሙና) . . ራሴን ከአንድ ሰዓት ለሚበልጥ ጊዜ አላዉቅም ነበር። አይኔን ስገልጥ ነጭ አምፖል ሰማያዊ ኮርኒስ ላይ ይታየኛል። ወዲያዉ ቀና ስል ከፊት ለፊቴ ሰዒድ እና ቁርዓን ሲቀራብኝ የነበረዉ ሰዉዬ እየተመለከቱኝ ነበር። ቁርዓን ሲቀራብኝ የነበረዉ ሰዉ ወዲያዉ ጌታዬን እንዳመሰግን አዘዘኝ። አመሰገንኩ። ወዲያዉ ወደ ጆሮዬ ተጠግቶ ለስግደት ጥሪ የሚደረገዉን አዛን እያደረገ የማጅራቴን ደምስሮች በጣቱ ነካካቸዉ። "ሴቶች በጣም ይወዱህ ነበር?" አለኝ ኡስታዙ ሰዒድ አጠገብ እየተቀመጠ "እንደዛ ነገር" አልኩት። "ያይኔአበባ የምትባል ሴት ታዉቃለህ?" አለኝ አይን አይኔን እያየ። "አዎ ዩኒቨርሲቲ ስማር የምጠቀምበት ምግብ ቤት አስተናጋጅ ናት።" አልኩት። ሰዒድ በግርምት አንገቱን ነቀነቀ። ኡስታዙ "እዛ ቤት በጣም ጣፍጦህ የበላህበት ቀን ትዝ ይልሀል?" አለኝ። እንደድንገት አንድ ቀን የበዓል ስጦታ ብላ ያይኔአበባ የሰጠችኝ ምግብ ትዝ አለኝ። እንደዉም ብቻዬን ዶርም ነበር የበላሁት። ኡስታዙ ሌሎች ጥያቄዎችንም ጠይቆኝ ከመለስኩለት በኋላ ድግምቱ የተሰራብኝ በያይኔአበባ እንደሆነ ነገረኝ። ያይኔአበባ ወዳኝ እንደነበር ግን ልትፎካከራቸዉ በማትችላቸዉ ቆንጆ ሴቶች ተከብቤ የነበረ በመሆኑ ድግምት እንዳሰራችብኝ ራሴን በሳትኩበት ሰዓት ዉስጤ የነበረዉ ጋኔን መናገሩን አረዱኝ። ኡስታዙ አሁን በፈጣሪ ፈቃድ ድግምቱ መክሸፉንና ዉስጤ የነበረዉ መጥፎ ስሜትም እንደሚወገድ አበሰረኝ። በሀይማኖቴ መጠንከር እንደሚኖርብኝ መክሮ ከግብረስጋ ግንኙነት በፊት ላደርጋቸዉ የሚገቡ ነገሮችን መከረኝ። . በተፈጠረዉ ነገር እኔም ሰዒድም ተገርመናል። መኪና ዉስጥ እንደገባን ሰዒድ "በል እስኪ ዛሬ ሂድና ሞክራት እና ጉዱን እንየዉ!" አለኝ እየሳቀ። እዉነት ለመናገር በጣም ቅልል ብሎኛል። . ማታ ቤት ስገባ ሀዩ አኩርፋ መጅሊሱ ላይ ተቀምጣለች። ደሞ ምን ተፈጠረ? "ሀዩዬ ምን ተፈጠረ?" አልኳት ከጎኗ እየተንበረከክኩ። "አክረሜ ልዉለድልህ ፍቀድልኝ!" አለች እያለቀሰች። የአልጋ ላይ ፀባዬ እስኪስተካከል ላለመዉለድ ወስኜ መድሀኒት እንድትወስድ አዝዣት ነበር። አይ ሀዩ! ከነዚህ የአልጋ ላይ ፀባዬ ምንም ሳትጠላኝ ልትወልድልኝ መጓጓቷ የፈጣሪ ስጦታ እንደሆነች እንዳስብ አደረገኝ። ፈገግ አልኩና "አላህ ካለ ነገ ጠዋት መልሴን እነግርሻለሁ!" አልኳት ዛሬ ማታ ሊፈጠር የሚችለዉን ሰላማዊ ለሊት ተስፋ እያደረግኩኝ። . ማታዉን ኡስታዙ በነገረኝ መልኩ ግንኙነት ከመፈፀማችን በፊት ሰግጄ ፀሎት አደረስኩ። ከዛም የሀዩ ጭንቅላት ላይ መዳፌን አስቀምጬ ጌታዬን ለመንኩ። ዉስጤ በእርጋታ ተሞልቷል። ሀዩን ሳምኳት ፣ እጄ ጥፊ እንዳይቀድመዉ ፈርቼያለሁ። እየተሳሳምን በስሜት ጠፋን። እጆቼ ሰዉነቷ ላይ ተንሸራሸሩ። ልክ እንደሰዉ ተገናኘኋት። ሀዩ ፊቷ በእርካታ ተሞልቶ እየሳቀች "ጌታዬ እንደማያሳፍረኝ አዉቅ ነበር።" አለችኝ። የረዥም ጊዜ ፀሎቷ ይሄ ነበር መሰለኝ። ሁለታችንም መድገም ፈለግን! ሀይል አሰባስበን ደገምነዉ። እርካታ ጣራ ነካ! ማመን ከበደኝ። የምድርን ጣፋጩን ነገር በእርጋታ ማጣጣም ቻልኩኝ። ሀዩ እቅፌ ዉስጥ ቀለጠች። ፍልቅልቅ እያለች "አፈቅርሀለሁ።" አለችኝ። ጌታዬን አመስግኜ ሀዩን እቅፍ አድርጌ ተኛሁ። . በነጋታዉ ጠዋት ሀዩ ከእንቅልፍ እንደተነሳን የወሰደችዉ የመጀመሪያዉ እርምጃ የወሊድ መቆጣጠሪያ ክኒኖችን መጣል ነበር። አሁን ልጅ ያስፈልገናል። ጠዋቱን ሰዒዶ ደወለና "እ ጄኪጃን አደብ ገዝተህ አደርክ ወይስ?" አለኝ። "ኧረ አልሀምዱሊላህ ዛሬ ጥፍጥናን አጣጣምኩት። አሁን ከልቤ እንድትቀምሰዉ ተመኝቼልሀለሁ።" አልኩት። ተገናኝተን ስለጋብቻዉ ለማዉራት ተቀጣጥረን ስልኩን ዘጋዉ። ሀዩን በሙሉ አይኔ ለማየት ደፈርኩ። ግንኙነት የፈፀምን ለሊት ያዉ ስለምመታት ጠዋቱን ቀና ብዬ ላያት በጣም ነበር የምሸማቀቀዉ። ጠዋት ቁርስ እኔ ካልሰራሁ ብላትም ከለከለችኝ። ሁኔታዬ ሁሉ እያሳቃት ነዉ። ወንድነቴ ልኩን መያዙ ከሀዩ ጋር የተሻለ ቅርርብ እንዲኖረኝ አደረገኝ። . ጠዋቱን ሀዩን ወደ ቢሮዋ አድርሼያት እኔ ወደ ስራ ሄድኩ። የራሄል ሆቴልን ጉዳይ በተመለከተ በዋናነት እየመራችዉ ያለችዉ ሀዩ ናት። አሁን ግንባታዉ ተጀምሯል። ሀጅራም አዲስአበባ ሆና ስራዉ እንዲቀላጠፍ ለማድረግ እየጣሩ ነዉ። እስክንድር አዲስ ፍቅረኛ ይዟል። እስክንድርን ካየሁ ሁሌም ራሄል ትዝ ትለኛለች። አሁን እንኳ ሀዘኔ በጣም ደብዝዟል። ግን በጣም የገረመኝ የተሰራብኝ ድግምት ከዝሙት እኔን ለመታደግ ምክንያት መሆኑ ነዉ። ከራሄል ጋር ያደርን ለሊት ስሜቴ ሲግል በጥፊ መታኋት እና አልጋ ላይ ተዘረረች። እዛዉ እንዳለች ልገናኛት ወደ አልጋዉ ስሄድ እንደዉም አብሬያት መተኛት ያልፈለግኩ መስሏት ተፈናጥራ ተነሳች። ለመጥፎ የተደረገብኝ ለጥሩ ጠቀመኝ። ምንም የስድስት ወሩ የስቃይ ጊዜ ባይረሳም ማለት ነዉ። ለሀዩ ትዕግስት ግን ምድር ላይ የሚመጥነዉ ሽልማት አላገኘሁም። . ጊዜዉ ሄዶ የሰዒዶ እና የኢማን ኒካህ ደረሰ። ደስ በሚል ስነ ስርዓት የኒካህ ስነ ስርአቱ ተደረገና ከሁለት ቀን በኋላ ሰርጉ ተደገሰ። ሚዜ ነበርኩኝ። በጣም ደስ የሚል ነበር። የሰርጉ ቀን ማታዉን ሆቴል እንዳደረስናቸዉ ፈገግ ብዬ "በል ፈረስ ያደርሳል እንጂ አይዋጋም!" አልኩት። ሰዒዴ ንግግሬን ጠምዝዞ "ኧረ እኛ ተዋጊ አንፈልግም!" አለኝ እየሳቀ። በጥፊ የሚማታ አንፈልግም ማለቱ እንደሆነ እኔናእሱ ተግባብተናል። . ጊዜዉ ሄዶ የሀዩ ሆድም ገፋ! እየደከማት ስትቸገር የሷን ስራ ከነሀጅራ ጋር እየተደጋገፍን ለመሸፈን ሞክረን እሷ ቤት እንድታርፍ አደረግን። ሀዩዬ ስታረግዝ አንዳንድ የፀባይ መቀያየሮች ቢስተዋሉባትም እንደምንም ታግሼ ተንከባከብኳት። አንዳንዴ ለአይኗ ሁሉ አስጠላታለሁ። አንዳንዴ ድብርት በጣም ይጫጫናታል። የእርግዝናዉ ፀባይ እንደሆነ ስለገባኝ ምንም ሳልበሳጭ የምትፈልገዉን ሁሉ ለማቅረብ ሞከርኩ። . ሀዩ ዘጠነኛ ወሯን ከያዘች በኋላ ብዙም ከሀዩ ቤተሰቦች ቤት አልጠፋም ነበር። ቢሮ ወሳኝ የሆኑ ጉዳዮችን አስተካክዬ ወደሀዩ ወላጆች ቤት እመለሳለሁ። ከሀዩ ጋር ግንኙነት መፈፀም ካቆምን ሁለት ወር ሆነን። የእዉነት አግኝቶ ማጣት ከባድ ነዉ። ወንድነቴ ሀዩን አምጣ ብሎ ሊገለኝ ምንም አልቀረዉም። ገና ወልዳ ደሞ የወሊድ ደም እስከሚቆም ግንኙነት እንደማንፈፅም ሳስበዉ ሰቀጠጠኝ። የሀዩ ገላ ናፍቆኛል። የሀዩ ፅንስ በጣም ስለገፋ ወደ ቤተሰቦቿ ቤት ሄዳ እናቷ በጣም እየተንከባከቧት ነዉ። ጁምዓ(አርብ) ጠዋት ላይ መግፊራ ደወለችልኝ። "እሺ እጩ አክስት!" አልኩ ስልኩን አንስቼ "እጩ አባት! ሚስትዎ እያማጠች ነዉ። ኢትዮ ጠቢብ ሆስፒታል እየሄድን ስለሆነ ቢመጡ!" አለችኝ። መግፊ ቀልዷናምሯ አይለይም። "መግፊ እስኪ ወላሂ በይ!" አልኳት። ወዲያዉ ስልኩን ወደ ሀዩ አስጠግታ ስታምጥ አሰማችኝ። መኪና እንደዚህ በፍጥነት መንዳት እችል ነበር እንዴ? በሀያ ደቂቃ ዉስጥ ሆስፒታል ደረስኩ። መግፊራ ጋር ደዉዬ ወጥታ ይዛኝ ገባች። ሀዩ የማዋለጃ ክፍል ዉስጥ ናት። መግባት እንደማልችል ተነግሮኝ በር ላይ ከነመግፊር ጋር ተቀመጥኩ። ደስ የሚለዉ አዋላጆቹ ሴቶች ናቸዉ። ወንድ የሚስትህን ብልት እየነካካ ሲያዋልዳት በጣም ይቀፋል። በተቻለዉ መጠን ሴቶች ስራዉን በፍጥነት ሊቆጣጠሩት ይገባል። የሀዩ የስቃይ ድምፅ አልፎአልፎ ይሰማኛል። ሀዩ ስትሰቃይ እኔን አመመኝ። ለሰዒዶ መንገድ ላይ እያለሁ ደዉዬ ነግሬዉ ስለነበር ደርሶ ከኛ ጋር ተቀምጧል። የሀዩ እያንዳንዷ ጩኸት በጣም አ
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ከኑረታችን ላይ እየተቀነሰ እንደዛፍ ቅርፊት ከበላያችን እድሜ እየተነሳ ግንዳችንን እያጠነከረ ቡረቃው ፣ ልፊያው ፣ ፀቡ ፣ ድብድቡ ፣ መበሻሸቁ ፣ የጨዋታ ታለንቱ ፣ ደንብና ስርአቱ ፣ እንደ አንድ የህይወት ክፍል የሸመደድናቸው የጨዋታ ህጎች ፣ መዝሙሮቻችን ፣ ችሎታዎቻችን ......እያንዳንዱን አንድ በአንድ እየዘለልን ጉርምስናን ያጠናቀቅን ጊዜ ትልቅነትን ሀ ብለን ስንጀምር ህጎቻችንን በሌላ ህጎች ስንቀይር ድንገት መለስ ያደርጉናል..... ወርቃማ ጊዜያቶቻችን ትውስ.... ፍዝዝ ባለ ትውስታ ወደዃላ ግልቢያ እንጀምራለን... ኑረታችንን ቃኘት አድርገን አጣጥመን ደግሞ ምልስ ከእውነታው ጋር ግጥምጥም........ ልጅነቴ ትላንት ያለፈ ያክል ቅርርብብ ይልብኛል ይዘው አይመልሱት ነገር የህይወት መፈገጊያው ገፃችን.... እንደምን አለህ ልጅነት?!! ©ማኪ 30-2-2015 ✎የፍቅር ጥቅሶች||™ @Bast_Love_Quotes_Robot
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ለምን ትኖራለህ ቢሉኝ ላንቺ ማለቴን ከሞኝነት ቆጥረውት ይሆን?🤔 ብርታቴ ፣ ተስፋዬ ፣ አለኝታዬ ፣ ነገዬ መሆንሽን ባያውቁ ነውና አልፈረድኩባቸውም😊 ብቻ አትልቀቂኝ እንጂ እኖርልሻለው❤️ ©ማኪ ✎የፍቅር ጥቅሶች||™ @Bast_Love_Quotes_Robot
Показати все...
ም አይን ለአይን ተያይተን ሳቅንና እኩል "ኢማን" አልን። ኢማን ሁሌም እኛ ቤት መጥታ እሱ ካለ እኔን ደክሞሀል ምናምን ብሎ ሰበብ ሰጥቶ እሱ ነበር ወደ ቤቷ የሚያደርሳት። "እና አዉርታችኋላ!" አልኩት። "ሁሉም አልቋል። ኒካህ ብቻ!" አለኝ እየሳቀ። ኢማን በጣም የምወዳት የአክስቴ ልጅ ናት። በፀባዩ የምተማመንበትን ጓደኛዬን ስለምታገባ ደስ አለኝ። የሱን ጉዳይ አዉርተን እንደጨረስን የእኔን ጉዳይ በሙሉ ነገርኩት። ሰዒድ ለኔ በጣም አዘነና "አክረሜ ይሄ ነገር ድግምት ሊሆን ይችላል። ብዙ ሴቶች ይወዱህ ስለነበር አስነክተዉህ ይሆናል።" አለኝ። ወደዱኝ ከተባሉት ሴቶች የቀረብኳቸዉ ሀያትንእናራሄልን ነዉ። ሁለቱም ደግሞ እኔን የሚጎዳ ነገር እንደማያደርጉ እርግጠኛ ነኝ። ቢሆንም ነገሮችን ማረጋገጡ ሳይሻል አይቀርም በሚለዉ በቁርዓን ህክምና ጤናዬን ልንፈትሸዉ ወሰንን። . በነጋታዉ ለማንም ሳንናገር እኔናሰዒዶ ወደ አንድ የቁርዓን ህክምና ማዕከል ሄድን። ብዙ ሰዉ ከኔዉ ጋር በተያያዘ ጉዳይ ማለትም በድግምት እና በአጋንንት ተበጥብጦ ህክምና ለማግኘት ተቀምጧል። በመሀል ከተማችን ዉስጥ እንደዚህ ድግምት አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑ አሳዘነኝ። ተራዬ ሲደርስ ወደ ህክምና ክፍሉ ገባሁ። ሰዒድም አብሮኝ ገባ። አንድ ነጭ ጀለቢያ የለበሰ ኡስታዝ ተሽከርካሪ ወንበር ላይ ተቀምጦ ችግሬን ካዳመጠኝ በኋላ ወደ ቀጣዩ ክፍል አስገባኝ። ቀጣዩ ክፍል ሙሉ ለሙሉ ምንጣፍ የተነጠፈበት ክፍል ነበር። የመኪናዬን ቁልፍ እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ የያዝኳቸዉን ነገሮች ለሰዒድ ከሰጠሁት በኋላ ሰዉየዉ ጮክ ብሎ ቁርዓን መቅራት ጀመረ። መጀመሪያ ድምፁ በጣም ያምር ነበር። ከዛም የሆነ ብስጭት ዉርር አደረገኝናድምፁ አስጠላኝ። ከዚህ በኋላ ምን እንደተፈጠረ ነቅቼ ሰዒድ እስኪነግረኝ ድረስ አላዉቅም። . ይቀጥላል... ✎የፍቅር ጥቅሶች||™ @Bast_Love_Quotes_Robot
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.