cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Voa Amharic

መረጃዎችን ለመላክ @Voa_News_Amharic_bot

Більше
Рекламні дописи
16 721
Підписники
+424 години
+1217 днів
+63830 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት እና አራት የፌደራል ግዛቶች በሱማሊያ የሕገመንግሥት ከፊል ማሻሻያዎች ላይ ትናንት ባካሄዱት ውይይት ተስማምተዋል። እስከ ትናንት የፌደራል ግዛቶቹ የፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሃመድ ያቀረባቸውን የሕገመንግስት ማሻሻያዎች ላይቀበሉ ይችላሉ የሚል ስጋት ሰፍኖ ቆይቶ ነበር። ከዚኹ የሕገመንግሥታዊ ማሻሻያ ሂደት ጋር በተያያዘ፣ ከጥቂት ወራት በፊት ከሱማሊያ ፌደራል መንግሥት መውጣቷን ያወጀችው ፑንትላንድ ግን አኹንም በብሄራዊ ውይይቱ ላይ ሳትሳተፍ ቀርታለች። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1
Показати все...
የሥራና ክህሎት ሚንስቴር፣ ባለፉት 10 ወራት 301 ሺህ ዜጎች በውጭ አገራት ሥራ እንዲያገኙ አድርጌያለኹ ማለቱን የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ሚንስቴሩ፣ መንግሥት ተጨማሪ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር ከሦስት አገራት ጋር እየተነጋገረ መኾኑን እንደገለጠ ዘገባዎቹ አመልክተዋል። ኾኖም የአገራቱን ሥም ሚንስቴሩ ስለመጥቀሱ ዘገባዎች አላመለከቱም። እስካሁን መንግሥት ሥልጠና የወሰዱ ሠራተኞችን ባብዛኛው ያሠማራው በመካከለኛው ምሥራቅ አገራት ነው። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
እስራኤል በጥቅምት 7 የሀማስ ጥቃት የተገደሉ ሶስት ታጋቾች አስክሬን በጋዛ ማግኘቷን አስታወቀች። የእስራኤል ጦር ሀይል በኖቫ የመዚቃ ፌስቲቫል ላይ የተገደሉትን ሶስት ግለሰቦች አስከሬን ማግኘቱን አስታዉቋል። ሶስቱ ምርኮኞች በጋዛ ሰርጥ አስክሬናቸው የተገኘ ሲሆን ሀማስ በደቡብ እስራኤል ባደረሰዉ ጥቃት የተገደሉ ናቸዉ። የጦሩ ቃል አቀባይ ዳንኤል ሀጋሪ በትላትናዉ ዕለት በሰጡት መግለጫ የሶስቱ ግለሰቦች አስክሬን በጦር ሀይሉ እና በሀገሪቱ የዉስጥ ደህንነት አገልግሎት በተወሰደ እርምጃ መገኘቱን ተናግረዋል። ሃጋሪ ግለሰቦቹ በጥቅምት 7ቱ የሀማስ ጥቃት በሙዚቃ ፌስቲቫሉ ላይ ተገድለዉ ወደ ጋዛ ተወስደዋል ማለታቸዉን ቢቢቢ ነዉ የዘገበዉ። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1
Показати все...
ጃዋር መሀመድ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአሜሪካ አምባሰደርን የሰላም ጥሪ ማውገዙ አሳዛኝ ነው አሉ የአሜሪካ በኢትዮጵያ አምባሳደር አርቪን ማሲንጋ “የሰጡትን ሃቀኛ እና ድፍረት የተሞላበት መግለጫ” የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማውገዙ ግራ የሚያጋባ እና አሳዛኝ ነው ሲሉ አንጋፋው ፖለቲከኛ ጃዋር መሀመድ ገለጹ። ጃዋር መሀመድ ዛሬ በይፋዊ ፌስቡክ ገጻቸው ላይ አምባሳደሩ የሰጡትን መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ይቀበለዋል ተብሎ የሚጠበቅ ባይሆንም አምባሳደሩ “በተለመደ ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ሳይሸፋፍን ይልቁንም የአገር እውነተኛ ወዳጅ ማድረግ እንዳለበት ሁሉ በግልፅ እና በፍትሃዊነት ሁሉም ተፋላሚ ወገኖች የፖለቲካ ግጭቶችን በትጥቅ ሃይል ለመፍታት የሚያደርጓቸውን አውዳሚ እና የተሳሳተ ሙከራ እንዲተዉ” መጠየቃቸውን አስፍረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በትላንትናው ዕለት አምባሳደር አርቪን ማሲንጋ በሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ ያቀረቡት መግለጫ በሕዝብ የተመረጠን መንግስት ለመገልበጥ የተነሱ ቡድኖችን በመዘርዘር መንግስት እንዴት አገሪቷን መምራት እንዳለበት የሚገልጽ ያልተገባ ምክርን ያዘለ ነው” ሲል ተቃውሞታል። የአምባሳደሩ መግለጫ “ያልተረጋገጡ መረጃዎች ያሉትና የሁለቱን አገራት ግንኙነት የሚጻረር መሆኑን የገለጸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር “ስህተቶች እንዲታረሙ” ከኤምባሲው ጋር በቅርበት እንደሚሰራ አዲስ ማለዳ ከመግለጫው ተመልክታለች። ጃዋር መሀመድ በጽሁፋቸው የፕሪቶሪያ ስምምነት በመፈራረም መንግስት የእርስ በርስ ጦርነቶችን በድርድር ለመፍታት ፍላጎት እንዳለው ቢያሳይም የገባውን ቃል “አሁን ወደኋላ እየተመለሰ ይመስላል” ማለታቸውን አዲስ ማለዳ ተመልክታለች። መንግስት ተቃዋሚዎቹን በወታደራዊ መንገድ ለማጥፋት ወደመሞከር የተመለሰ ሲሆን ይህ የተሞከረ እና ያልተሳካለት ስልት ባለፉት ዓመታት አገሪቱን አውድሟል ሲሉ ፖለቲከኛው ገልጸዋል። በሰላማዊ መንገድ የተገኘውን ውጤት ከማጠናከር ይልቅ ከፍተኛ ወታደራዊ እና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎችን መንግስት እያደረገ፤ ከዚሁ ጎን ለጎን ገዢው ፓርቲ የፖለቲካ ምህዳሩን ዋስትና በማስጠበቅ የምርጫ ቅስቀሳ ማድረግ ጀምሯል በማለትም አክለዋል። በቅርቡ በነቀምት እና በባህር ዳር በተደረጉት የድጋፍ ሰልፎች ላይ ከተናገሩት በተቃራኒ በአብዛኛው የአማራ እና የኦሮሚያ ክልሎች በጦርነት የተጎዱ አካባቢዎች እየተስፋፉ እንጂ እየቀነሱ አይደሉም ያሉት ጃዋር መሀመድ፤ መከላከያ ሠራዊት በአንዳንድ አካባቢዎች ጥሩ ውጤት ያስመዘገበ ቢሆንም፣ “ስለ ታጣቂዎች የጅምላ መክዳት በተመለከተ የቅርብ ጊዜ ዘገባዎች በጣም የተጋነኑ እና አንዳንዶቹ ፍጹም የፈጠራ ወሬዎች ናቸው” በማለት ጽፈዋል። አብዛኛዎቹ ዞኖች እና ወረዳዎች በመንገድ አለመገናኘታቸው ማሳያው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአየር ጉዞው በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር እንደሆነ የጠቀሱት ፖለቲከኛው ጃዋር፤ ገበሬዎች ማዳበሪያ መቀበልም ሆነ ሰብል መትከል አይችሉም፣ በሰላማዊ ዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለው አፈና እና ሕግ-ወጥ ግድያ ህይወትን በገጠሩ ሕዝብ ላይ መቋቋም የማይቻል አድርጎታል ብለዋል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ኢትዮ - ቴሌኮም በታችኛው እርከን ሰራተኞች የደሞዝ ማሻሻያ እንዲያደርግ ጥያቄ ቀርቦበታል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት ሰራተኞቹን ባወያዩበት ወቀትም ሰራተኞቹ ለተቋሙ ያላቸውን የኔነት ስሜት ጥሩ የሚባል ቢሆንም በታችኛው እርከን የሚገኙ ሰራተኞች የደሞወዝ ማሻሻያ ጉዳይ ቅሬታ እንዳላቸው ተናግረዋል። ተቋሙ በታችኛው እርከን ለሚገኙ ሰራተኞቹ የደሞዝ ማሻሻያ እንዲያደርግና ከዚህ ቀደም የወጣውን የደሞዝ የማሻሻያ መመርያ እንደገና እንዲፈትሸው ጥያቄ ቀርቦበታል ተብሏል። ኢትዮ ቴሌኮም ታችኛው እርከን ለሚገኙ ሰራተኞቹ የሚከፍለው ደመወዝ ከሌሎች ተቋማት አንፃር ጥሩ የሚባል ቢሆንም ካለው የኑሮ ውድነትና የመኖሪያ ቤት ችግር አንፃር በቂ የሚባል አለመሆኑን የቋሚ ኮሚቴ አባላት ጠይቀዋል ነው የተባለው። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
“ከ274 ሺህ በላይ የትግራይ ሠራዊት አባላት ትጥቅ ይፈታሉ” ብሔራዊ የተሐድሶ ኮሚሽን የትግራይ ኃይል አባላትን ትጥቅ ለማስፈታት፣ ለማሰናበትና ከማህበረሰቡ ጋር ዳግም እንዲቀላቀሉ የሚያስችል የቅድመ ትግበራ ውይይት በመቀለ ተካሂዷል። በዚህ ሳምንት መጀመርያ ላይ በተካሄደው ምክክር ላይ የፌደራል መንግሥት ተወካዮች፣ የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት አመራሮች እና የአፍሪካ ኅብረት የስምምነት ክትትል፣ አረጋጋጭ እና አስከባሪ ኮሚቴ አባላት መገኘታቸውን የብሔራዊ ተሐድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ተመስገን ጥላሁን በኤክስ ገጻቸው አስታውቀዋል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንቶች እንዲሁም የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በዚህ ምክክር ላይ የትግራይ ተዋጊዎችን በመበተን እና ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ወደ ኅብረተሰቡ የማዋሃድ ፕሮግራም፣ ፕሮጀክቶች መንደፍ እንዲሁም የመጀመሪያው የትግበራ እቅድ ላይ ውይይት እንደሚደረግ ተጠቅሶ ነበር። ጦርነቱ መቋጨቱን ተከትሎ ጥያቄ እያስነሳ ያለው ትጥቅ የመፍታት ጉዳይ እና የተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎች፣ በጀት እና ሌሎችንም ጉዳዮች አስመልክቶ ቢቢሲ ከብሔራዊ የተሐድሶ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ተስፋዓለም ይሕደጎ ጋር ቆይታ አድርጓል። ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ:- https://www.bbc.com/amharic/articles/c6pypp0jp8wo https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1
Показати все...
የራያ አካባቢዎች መሠረታዊ አገልግሎቶች እንደተቋረጡ ነዋሪዎች ገለፁ! የፕሪቶርያው የሰላም ስምምነትም ኾነ የፌደራሉ መንግሥት “አከራካሪ” በሚላቸው፣ የማንነት እና የወሰን ጥያቄ ከሚነሣባቸው አካባቢዎች አንዱ በኾነው የራያ አካባቢ፣ መሠረታዊ አገልግሎቶች መቋረጣቸውን፣ የአላማጣ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የአላማጣ ከተማ ሆስፒታል፣ ላለፈው አንድ ወር ገደማ አገልግሎት መስጠት በማቋረጡ በሕክምና አገልግሎት ዕጦት የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉን፣ የከተማዋ ከንቲባ አቶ ኀይሉ አበራ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል፡፡ ሕይወታቸውን ካጡት ውስጥ፣ “ስምንቱ ጨቅላ ሕፃናት ሦስቱ ደግሞ እናቶች ናቸው፤” ብለዋል፡፡ ከንቲባው፣ የማንነት እና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ በሚነሣባቸው በአላማጣ ከተማ፣ በራያ አላማጣ፣ ራያ ባላ እና ኮረም አካባቢዎች በሚገኙ 123 ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚማሩ ከ42 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ለማቋረጥ መገደዳቸውን አስረድተዋል፡፡ ከተማሪዎቹ መካከል፣ ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተናን የሚወስዱ ከ900 በላይ ተማሪዎችን ግን፣ የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ፥ የትምህርት፣ የምግብ እና የማደሪያ አገልግሎቶችን ለመስጠት፣ ከዛሬ ጀምሮ ተማሪዎቹን መቀበል መጀመሩን ዩኒቨርሲቲው አመልክቷል፡፡ በሌላ በኩል ባለፈው ሚያዚያ 8/2016 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ የሰጡት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ሌተና ጄኔራል ታደሰ ወረደ በአማራ ክልል በተዋቀሩት የራያ አላማጣ ታጣቂዎችና በተፈናቀሉ የትግራይ ሚኒሻዎች መካከል የተቀሰቀሰው የአካባቢ ግጭት ተስፋፍቶ አላማጣ ጫፍ መድረሱን መግለጻቸው ይታወሳል፡፡ https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1
Показати все...
ቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና ፐርፐዝ ብላክ አለመግባባታቸውን በስምምነት ፈቱ     ቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና ፐርፐዝ ብላክ በፍርድ ቤት መር አስማሚ በኩል አለመግባባታቸውን በስምምነት ፈተዋል።   የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሁለቱ ወገኖች መካከል የተፈፀመውን ስምምነት አፅድቆ ክሱን በመዝጋት እግዱም እንዲነሳ አዟል፡፡   በስምምነቱ መሰረት ቢጂአይ-ኢትዮጵያ የተከፈለውን የቀብድ ክፍያ ለፐርፐዝ ብላክ የመለሰ ሲሆን ፐርፐዝ ብላክ በፍርድ ቤት የጀመረው ክስም ተቋረጦ እግዱ ተነስቷል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1
Показати все...
ፍትህ ሚንስቴር፣ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ማስተግበሪያ ፍኖተ-ካርታ እየተዘጋጀ መኾኑን ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ፍኖተ ካርታውን ማዘጋጀት ያስፈለገው፣ ሚንስትሮች ምክር ቤት ባጸደቀው የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ሰነድ ላይ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን በመፈጸም ረገድ የትግበራ ምዕራፉ መቼ እና እንዴት ተጀምሮ እንደሚያበቃና በሽግግር ፖሊሲው ትግበራ ሂደት የባለድርሻ አካላት ሚና ምን እንደሚኾን ለመወሰን እንደሆነ ሚንስቴሩ ገልጧል።  ፍኖተ ካርታውን እያዘጋጀ ያለው ቡድን፣ ከፍትሕ ሚንስቴር፣ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን እና ከሲቪል ማኅበረሰብ ብሔራዊ አደረጃጀቶች የተውጣጡ ከፍተኛ ባለሙያዎችን ያካተተ እንደኾነ ተገልጧል። ፍኖተ ካርታው በሦስት ሳምንት ውስጥ ተጠናቆ ተግባራዊ መኾን ይጀምራል ተብሏል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1
Показати все...
በሕወሃት አመራር ውስጥ የርስበርስ መገዳደል ሊሰፍንና ይህም በትግራይ ሕዝብ ላይ አደጋ ሊደቅን ይችላል በማለት ዶይቸቨለ የዜና ማሠራጫ ጣቢያ ባለፈው ዕሁድ "ሐሰተኛ" እና "አሳሳች" መረጃ አሠራጭቷል ሲል ሕወሃት ዛሬ ባወጣው መግለጫ ከሷል። ሕወሃት፣ የጣቢያው ዘገባ በክልሉ ሽብር እና ጥርጣሬ እንዲነግስ የሚያደርግ እና ምናልባትም ያልታወቀ ስውር ሴራ መኖሩን የሚያሳይ ሊኾን ይችላል ብሏል። ሕወሃት፣ የጣቢያው አስተዳደር በዘገባው ላይ ምርመራ በማድረግ ለዘገባው ተጠያቂ በኾኑ ግለሰቦች ላይ አስፈላጊውን ርምጃ እንዲወስድና ይቅርታ እንዲጠይቅም ጠይቋል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1
Показати все...