cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

ቅንጭብጭብ ወሬወች

Aznagni ena astemari yehonu message or melikit ....photo..keld ...gitim..sle Fikir yetetsafu metsstsifoch...wegoch ....

Більше
Країна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
Рекламні дописи
129
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

(1)#❤️💋#እናት ለምን ትሙት ትሂድ አጎንብሳ ታበላ የለም ወይ በጨለማ ዳብሳ💋❤# (2)#😘😘😘#ሮዝ አበባ ላይ አሞኝ ተኝቻለው በሌላ አይደለም በፍቅር ብቻ ነው😘😘😘 (3)#😡😡#ባዳ እና ቁንጫ በልቶ ሩጫ😡😡 (4)#😔😔#ቀን ሲከፋ ያሳደግከው ውሻ ይነክስሃል😊😊፡፡ (5)#ብትውልም መልካም ውለታ ስለሰው ብትንገላታ👍👍 ከልለህማንአለእደጅህ ኪስህነው የቅርብ እደጅህ👍👍 (6)#ጓደኛ ማለት ጊዜ ጠብቆ የሚከዳ ሳይሆን እንደ ማየት የተሳነው ሰው ሸመል የሚመራ ነው፡፡👬👈👈🤝🤝👬 (7)# 😍😍#የታገሰ ማን ከ ማን አነስ😒😒፡፡ (8)#👊#ወደ ከፍታ ስትወጣ ለስዎች ጥሩ ሁን ምክንያቱም ከከፍታ ስትወርድ ታገኝችዋለህ 💪🤜🤛👊 (9)#🤔☺🔑#እራስክን አትገድብ ብዙ ስዎች እራሳችውን በሚያስቡት ሀሳብ ልክ ብቻ ይገደባሎ ነገር ግን አስታውስ ባምንክው ልክ ታገኝለህ 🌺🌸( Gech ) 🌸🌺
Показати все...
✅በአሜሪካ ዋይት ሀውስ አቅራብያ የተሰማ ተኩስን ተከትሎ በህንጻው ውስጥ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጡ የነበሩት ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለደህንነታቸው ሲባል መግለጫ ከሚሰጡበት ክፍል ለቀው እንዲወጡ ተደረገ ፡፡ሲኤን ኤን እንደሚለው ፕሬዘዳንቱ ተኩሱ ከቆመ በኋላ ወደ ጋዜጣዊ መግለጫቸው ተመልሰው የፀጥታ ሰራተኞቻቸው እሳቸውን በማግለል የወሰዱትን እርምጃ በጣም ውጤታማ ስራ ሲሉ አመስግነዋቸዋል፡፡ ✅የጸጥታ ባለስልጣናት በሰጡት መግለጫ ተኩሱ የተሰማው አንድ የደህንነት ሰራተኛ በሌላ ሽጉጥ ታጥቂያለሁ ብሎ ባስፈራራውና ለመተኮስ በሚመስል ሁኔታ እጁን ሲያንቀሰቅስ የደህንነት ሰራተኛው በግለሰቡ ላይ በመተኮሱ ነው።ሆኖም ሆዱን በጥይት የተመታው ግለሰብ በመጨረሻው ምንም አይነት መሳርያ እንዳልያዘ መረጋገጡን የቴሌቪዥን ጣብያው ዘግቧል፡፡ @mezinagnaw
Показати все...
ብርዱም ተነሳበት - ያው ዝናቡ መጣ ' ትውስ አለኝ ፍቅርሽ - አንቺን አለኝ አምጣ ' እርሷ በንዴት: ' የሄን ሁላ ጊዜ አንዴም - ትዝ ያላልኩህ ! ክረምቱ ሲገባ አሁን - የታወስኩህ ' ዘርተህ ያበቀልከኝ - በቆሎ መሰልኩህ !!
Показати все...
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ 👉👉 #ኪያዬ_አይደለሽም 👈👈 ትዝ ይልሻል #ውዴ ያኔ... ከ 3 ወራት በፊት እኔና አንቺ ሆነን በፍቅርም ከንፈን፤ ህይወትን እረስተን፤ ሀዘንን አባረን፤ እየተደሰትን.... ከሰፊው ሰማይ ላይ በፍቅር ስንበር፤ ከፊት ማለፍ ስንችል፤ ከዃላ አየቀረን፤ እየተጎተትን፤ ደስተኞች ነበርን.... አዎ ውዷ #ህይወቴ አውቃለሁ ታውቂያለሽ፤ ይህን አትረሽውም፤ ልብ ለልብ ገጥመን፤ የየቅል ህይወት ትተን፣ እኔ ባንቺ ልብ፣ አንቺ በኔ ልብ ስንኖር ብዙ አስበን ነበር..... °°°°°°°°°°° #ህይወቴ..... አሁን ግን ከፍቶኛል.... ልቤም ሀዘን ሞልቶት የምር ደብሮኛል.... ከሳቅም ከደስታም ሀዘን ይቀናኛል.... ውብ ናቸው ባልሻቸው ሁለቱም አይኖቼ፣ እንባ ተንንቆኛል... መኖርም ስጀምር... ከባዶ አስነስቸሽ፤ ከ ዜሮ አስጀምረሽ፤ ያዳንሽኝን ያህል፣ ደግመሽ ገለሽኛል... አናም ውዴ.... እሱም ሲል #ኪያዬ፤ እኔም #ህይወቴ አልኩኝ... ባነባበት መጠን፤ እኔም አነባሁኝ.... በእሱ ተስፍ መቁረጥ፤ እራሴን ከተትኩኝ..... ሀዘኑ ሲጎዳው፤ እኔም ተጎዳሁኝ.... ተመለሺ ሲላት እኔ አልተመኘሁም... ደስታሽ ደስታዬ ነው የኔ ባትሆኝም..... °°°°°°°°° #ኪያዬ ሲላት ግን .....እኔ አላልኩሽም.... .....ምክንያቱም..... አንቺ ለኔ... #ህይወቴ ነሽ እንጂ፤ #ኪያዬ አጀለሽም። ✍ተፃፈ በ @Mak_bale #ካነብብሽው_ላንቺ _እንደሆነ_ታቂዋለሽ። 13.6.2012 @yeneta
Показати все...
የጣልያን ጠቅላይ ሚንስትር ጁሴፔ ኮንቴ ውሳኔ ! ጁሴፔ ኮንቴ የጣልያን ሴርያ ክለቦች ግንቦት 10 ጀምሮ ልምምድ መስራት መጀመር እንደሚችሉ አስታውቀዋል። ከዚህ በተጨማሪም ሌሎች ወደ አገልግሎት መስጠት ዳግም የሚገቡበትን ቀን ይፋ አድርገዋል ፦ • ሚያዝያ 26 - የቤተሰብ ጉብኝት፣ ፓርኮች እንደገና ይከፈታሉ፡፡ • ግንቦት 24 - የውበት መጠበቂያ ቤቶች ፣ ካፌ እዲሁም ምግብ ቤቶች ክፍት ይሆናሉ። • መስከረም - ትምህርት ቤቶች እንደገና ይጀመራሉ። MORE : @TIKVAHETHSPORT (ቲክቫህ ስፖርት) @tikvahethsport @tikvahethiopia
Показати все...
#ሰበር_ዜና #እስራኤል_ኮሮናን_100 %_ማዳን_የሚችል_መድሐኒት_አገኘች። Pluristem Therapeutics Inc., a biotech company እንደገለፀው ከሆነ የCovid - 19 በሽታን 100% ማዳን የሚችል ፍቱን መድሐኒት ማግኘታቸውን ዛሬ ይፋ አድርገዋል። በአሜሪካን ሀገር በጣም ከፍተኛ ደረጃ ላይ ባሉ 7 ታማሚዎች ላይ ውጤታማነቱንም አርመስክሯል። መድሐኒቱ የተሞከረባቸው ሰባቱም...... የመተንፈስ ችግር ያለባቸው ፣ multi system organ failure, including heart and kidney failure የነበረባቸው ታማሚዎች እና በዚህም ምክንያት በከፍተኛ ደረጃ የመሞት አደጋ ላይ የነበሩ ናቸው ተብለዋል። ፕሉሪስተም ቴራፑቲክ በተሰኘው የምርምር ተቋም የተሰራው መድሃኒት እንደ ስኳር የደም ግፊት አስም የልብ ህመም ሌሎች በሽታዎች የሚሰቃዩ ሰባት ታማሚዎች ላይ ተሞክሮ ኮሮናን በስኬታማነት ፈውሶታል። እንደ ምርምር ቡድኑ ሃላፊ ዶክተር ያኪ ያናይ ገለፃ በሴል ፕሮቲን ውስጥ በሁለት ተልእኮዎች ነው መድሃኒቱ የተዘጋጀው በሴል ውስጥ በሽታን የመከላከል ብቃትን የማሳደግ ና በተለይም ከሴሉ ውስጥም የኮሮና ቫይረስን በሚያስውገድ ዘዴ ህመምተኞች ከኮቪድ 19 ፈጥነው እንዲያገግሙ ሆኖ ነው መድሃኒቱ የተሰራው። በእስራኤል ሃይፋ ከተማ የሚገኘው የምርምሩ ተቋም እንዳስታወቀው መድሃኒቱ በህመምተኞቹ ሴል ክፍል ተውስዶ በሽታን በሚቋቋም አካል ቅንጣት እንዲያድግ ሆኖ ነው የተሰራው። ይህም በሽታን የሚከላከል የፕሮቲን ሴሎች አብቅሎ ሞትን የሚያስከትለውን የኮቪድ 19 ቫይረስ በመርታት ፍውስ እንደሚያስገኝ አረጋግጠናል ነው ያሉት ተመራማሪዎቹ የምርምር ተቋሙ ሃላፊዎች ሙከራው ስኬታማንቱን ተከትሎ ከፈቃድ ሰጪ አካል ይሁንታን እንዳገኘ በፍጥነት በጅምላ ማምረት እንደሚጀምሩ ገልፀዋል። ምንጭ :- thedailyvendor.com https://thedailyvendor.com/breaking-isr @wollouniversity12 @wollouniversity12
Показати все...
BREAKING: Israel Finds Possible 100% Cure For COVID19

The Israeli COVID19 drug reportedly with a 100% success rate even among severely ill patients is being tested in the United States for the first time.

ያማል! እና እንደነገርኩሽ ዩንቨርስቲ ገብቶ “A”ን እንደመጠበቅ እነ “D” “FX”ን አይቶ እንደመሳቀቅ ባልታሰበ ፍላት ተጭሮ እንደመውደቅ ቴንሽን በበዛበት በዩንቨርስቲ አለም ከዚ የበለጠ ምንም ህመም የለም ጥናቱ ያማል ፈተናው ያማል አሳይመንቱ ያማል የማይጎል የ “C” ጎርፍ የ “F” ማዕበሉ ለማይሞላ ግሬድ ቁጭ ብሎ ማደሩ የ “D” መደርደሩ ምን ብዬ ልንገርሽ ያማል ይሄ ሁሉ እና እንደነገርኩሽ... የምናለመው "A" ተጠንቶ ካልመጣ የምንጓጓለት “B” ተጠንቶ ካልመጣ ግሬድ ተበላሸ “C” እና “D” ሲመጣ ሁሉ ተቀይሮ ይተካል በሲቃ ምን ብዬ ልንገርሽ ይሄም ያማል በቃ ባፍንጫው ሚያወራ የህንድ አስተማሪ slide ያደከመው ምስኪኑ ተማሪ ፈተና አስተሽኖት እግሩን ውሀ ዘፍዝፎ እንቅልፍ አባራሪ ቁጭ ብሎ አዳሪ ኀላም ፌንት ሰሪ ደሞኮ... አለኮ እንደ ወገብ ቅማል የሚጠምድ ሌክቸረር ሳይሰጥ የሚጠይቅ ከውቀት ነፃ መምር ምን ብዬ ልንገርሽ ይሄን ሁሉ ህመም ሀንዳውት ሸምዳጁ ሰቃዩ ኮራጁ ውጣና ውረዱ ልፋቱ ድካሙ የሚጫር ተማሪ መጫሩ ለማይቀር ግቢ ውስጥ መክረሙ እልፍ አእላፍ ተማሪ ፕሮጀክት ላይሰራ ሊደሩን ማጀቡ ደግሞ ለሷ ግጥም “እናቷን” ፕሮጀክት ምን ብዬ ልንገርሽ ይሄም ያማል በውነት እና እንደነገርኩሽ ጉንጭ 'ማትሞላ ሳንቡሳ በ 3 ብር የሸጠ የ lounge አሳላፊ ወደኔ አፈጠጠ ዘይት የነካውን መንታ እጁን አጣምሮ ውሃ ልቅዳ ይላል ፌቴ ተገትሮ ቦንቦሊኖ ልዘዝ ወይስ ዶናት ልዘዝ ለምን ዳቦ አላዝም ግን ደግሞ ቢቀርስ ብሬን ከምጨረስ ሻይ ብቻ ጠጥቼ ችከላ ብሄድስ እንዴ ! ሲጠርስ! እና እንደነገርኩሽ ጠዋት ሩዝ ሲሆን ምሳ ደግሞ ዜርፎር ሰልፉን አይጣልብሽ ያለውን ግርግር እንዲያ ተጋፍቼ ገብቼ ብበላም ጣጠኛው ክላሴ መርፈዱ አይቀርም ምን ብዬ ልንገርሽ ይሄን ሁሉ ህመም እና እንደነገርኩሽ ከዚ ሁሉ ህመም በዛ ካለ ስቃይ ደስ እንዲልሽ አርጎ ሳቅሽን የሚያሳይ የዶርሙ ላይፍ ነው መኖሩ በአብሮነት ምክንያት የሚሆነው ጥርስሽ እንዲከፈት እና እንደነገርኩሽ የያዝኩት ፕሮጀክት ታይትሉ ተይዟል ዋይፋይ ገባ ወጣ ሜምበር ቀረት መጣ ፕሮጀክት የለችም እናቷን ስላልኳት ደግሜ ሰድቤ ሺህ አመት እንዳይገርማት እናቷን !!! ... እናቷን ፕሮጀክት ተይ አታስለፍልፊኝ ይሄም ያማል በውነት ግን... እኔ አንቺን ስወድሽ ድግሪዬ ስወድሽ ይህን ሁሉ ችዬ ነው የምጠብቅሽ አምስት አመት ሙሉ የምፋለምልሽ ቢሆንም ግን ያማል፡፡
Показати все...
ሚዛን አልባው ሚዛን ፧ ፧ ፧ ፧ በመኖር ስንክሳር በፈተና ማዕበል ሁሉን በድል አልፎ የጀገነ ልቤ ዓላማው አንቺ ነሽ መሆንሽ ድንቅ አብቃይ የስምረት ክበቤ፡፡ ያ'ርነት ሰንደቄ ፍቅርሽ ነው መንገዴ የሕያውነት ግቤ፡፡ ዓለም ግን አታላይ ደም ግባታም መሳይ አኖራለሁ ብሎ ሕይወታዊ ፍቅርን በቅጽበት ነው ገዳይ፡፡ መሆኔን ሊሰፍር በሕይወት አባይ ሚዛን ነገን ናፋቂ አ'ርገህ ያስቀመጥከኝ ጊዜ በተስፋ ገንዘህ በፍቅር ከፍነህ ለቃሌ ማደሬን ቆጥረህ ከመዘዜ በዘመን ሕልም አስረህ በቅፅበት ልትቀጥፈኝ በምንተ'ዳ ግብርህ ስለምን መያዜ - !? እካሰስሀለሁ - !! እፋረድሀለሁ - !! አቋምህ መሰሪ ግብርህ ነው ግፈኛ ለምን ጤዛ አረከኝ የፍቅር መናኙን ታላቁን ጀብደኛ - !? ተስፋዬን ሳነቡጥ ቀኔን ሳጎነቁል ለምን ታከስማለህ ልክ እንደሸረኛ - !? ሕያው ፍቅር አቅፎኝ ለመኖር ስጠራ ለምን አደረከኝ የሞት መንገደኛ - !? ይኸውልሽ ፍቅሬ..... አድምጪኝ መኖሬ..... ሊያወሩት የሚከብድ ሊያምኑ ሊቀበሉት እንኳንስ በራስ ላይ በሌላው ላይ ቢደርስ ፍርጃ ወርዶብኝ ነው ስራይ ተንዶብኝ በመዐት ታጥሬ በጭንቅ የምታመስ፡፡ አይምሰልሽ ፍቅሬ.... ኪዳኔ መኖሬ...... እንኳንስ ልለወጥ ወረት ሊጎበኘኝ አይኔን ካንቺ ልነቅል በመሰልቸት ልነግስ ግዙፉ ጽንፍ አልባው ከ...እስከ...የሌለው በላዬ ላይ ሊወድቅ ሰማይ ቢደረመስ ምድር ብትናወጥ ሩኋን ብትስት አንቺን ታምኜ ነው የልቤ የሚደርስ፡፡ ላቀልጥህ ነው ያለ ገሞራው ቢያጓፍጥ ባንቺ ፀንቼ ነው የልቤ የሚደርስ፡፡ ማኅተቤ እኮ ነሽ የፍቅር ገዳሜ የምቀደስብሽ የእምነት እትብቴ ካ'ለም ተቆርጬ ካንቺ ተሳስሬ በውስጥሽ የምኖር ነሽ እኮ ባዕቴ፡፡ አንተ ግን መሰሪው አንተ ግን ግፈኛው አድምጠኝ ልንገርህ.... ቃሌን ላፍስስልህ.... የሆነውን ሁሉ እውነቱን ልንገርህ!!! የሐሳዊ መሲሕ ቅጥፈት ሰበካህን የነቃብህ ሰማይ በንዴት ራደ መሰሪ ግብርህን ደባህን ለማስቆም ስለፍትህ ቀንቶ ስለእውነት ማለደ፡፡ ምልጃውን ብትንቅ በንዴት አምጦ ጦርነት ሊገጥምህ መብረቁን ወለደ፡፡ መስሚያ ጆሮ ካለህ ይሄንን ብሎሀል ስለፍቅር ቆሞ ይሄን ተናግሮሀል፡፡ " ሰርግና ሞት አይነት አጉል ግራ ተረት አንድነት ማስታቀፍ አይገባም ለ'ሱ፡፡ ሰርቆ የቀረበው መሞቱ የራቀው ሕያው ዘላቂ ነው አፍቃሪ መንፈሱ፡፡ ለሱ አይሰራም ስልህ የእንሰሴ ትርክት < ጅብ ወለደች > እጣ ፀሐዩም ዝናቡም እንዴትም ቢሰላ አንድነት አይመጣ፡፡ ሕይወትን አርግዞ በፍፁም አይሆንም ሞት ሊወልድ የሚያምጥ የእባብን እንቁላል ለእርግብ ማስታቀፍ ምን የሚሰኝ ፈሊጥ - !? እንዴት ቢሆን ነው ለግጥ -!? እንዴት ያለ ልኬት የትኛው ሚዛንህ መኖሩን ሰፈረ - !? እንዴት ተመትሮ ቀኑን ከውድቅቱ ባ'ንዶነት አሰረ - !? " ይሄንን ብሎሀል ሰማይ ተናግሮሀል መስሚያህን ብትደፍን ልብህ ቢደነድን ላይለቅህ ቃል ገብቷል፡፡ ይሰማሃል ጊዜ አንተ ሚዛን አልባ አባይ ነው ስፍርህ ቃልህ ነው ገለባ፡፡ ምድር ሊጋተርህ በምርኮ ሊያግዝህ ባርነት ሊያወርድህ ባ'ንተ ላይ ዘመተ ፍቅርን ስትቀጥፍ ዝም ብሎ ላያይህ መንቀጥቀጡን ታጥቆ ሊታገልህ ዛተ፡፡ ሀገር አቃለለህ አክ እንትፍ ብሎ ከልቡ አወጣህ መኖርህን ካደ ስብከትክን ላይሰማ ብትመንን ላያምንህ ካንተ የገባውን ሰማኒያ ቀደደ፡፡ ግብርህ ግፍ አርቃቂ ጭቃኔ ታጣቃ የመሪ ሴራ ሆኖ ተገለጠ በቃል በገዘፈ ፀንቶ በከነፈ በምስኪን ፍቅር ላይ ተንኮልህ ፈጠጠ አበባ ነኝ እያልክ መላከ ሞት ገጽህ መቃብር ፈንቅሎ ፊቴ ተገሰጠ፡፡ እካሰስሀለሁ - !! እዋቀስሀለሁ - !! ስራህ የመሰሪ ግብርህ ነው ግፈኛ ለምን ጤዛ አ'ረከኝ ለምን ረጋፊ - !? ሕያው ፍቅር አቅፎኝ የሞት መንገደኛ - !? " እውነት አለኝ " ብለህ መከላከያህን በፀጋ እንድቀበል ላድምጥ አሰማኛ፡፡ እኮ በል ላድምጥህ.... ሐቅህን ልመንህ......!! በፍቅሩ ቃል - ኪዳን ሰምሮ የጣፈጠን ሊኖር የቆረጠን ያፍቃሪን ተስፈኛ ማኖሩ ሲቻልህ በገድል አንቆጥቁጠህ ለምን ትቀጥፋለህ ልክ እንደሸረኛ -!? አየሽልኝ አይደል የጊዜን አሻጥር በፊቱ እየሳቀ ሲቀጥፈኝ በእጅ አዙር - !? የቀን ፍካቴ ላይ የቀን ለምለሜ ላይ አየሽልኝ አይደል ሲተክል አሜኬላ፡፡ መኖሬን ቀርጥፎ ሙሽርነቴ ላይ ማብቃቴን ደግሶ እርም እንኳ ላይበላ፡፡ ምንድን ሚዛንህ አንተንስ ገምቶ ማነው የሚሰፍርህ - !? በፍቅር ቀኔ ላይ በኪዳን ስጸና ፀሐዬ ሳትጠልቅ ዝናቤን የምትለቅ እኮ ምን ልትሰኝ ማን ተባልኩ ልትል ሰርጌን ከሞቴ ጋር ቀላቅለህ የምትስቅ፡፡ አየሽ አይደል ፍቅሬ.... ኪዳኔ መኖሬ..... ከመኖር ሚዛን ላይ ቅፅበት እያሰረ ነገን የሚያስናፍቅ የጊዜ አባይ ሚዛን በቃል የታሰረን እስከዘላለሙ በፍቅር የጣፈጠን ጤዛ አርጎ ሲያመክን እሱን ማን ይስፈረው ማን ይዳኘው እሱን -
Показати все...