𝑩𝒆𝒌𝒊𝒓𝒔𝒕𝒐𝒔 𝒌𝒂𝒔𝒔𝒂
እኔን ማገኜት ከፈለጉ @Bekrstos_kassa ይጻፉልኝ፡፡ ወይም 0914463334 ይደውሉ ♥ © አዘጋጅ 𝐁𝐞𝐤𝐢𝐫𝐬𝐭𝐨𝐬 𝐊𝐚𝐬𝐬𝐚
Більше564
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
+830 днів
- Підписники
- Перегляди допису
- ER - коефіцієнт залучення
Триває завантаження даних...
Приріст підписників
Триває завантаження даних...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
❤#በክረምቱ ምን_አስበዋል??
መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮዎችን በተመረጡ መምህራን
ለተከታታይ ለ21 ቀን ለአንድ ሰዓት ብቻ በሚቆይ መርሃ ግብር በኮምቦልቻ ደብረ ምኅረት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ተዘጋጅቶለወታል ይምጡ ጥያቄዎት ይመለስለዎታል ብዙ ይማሩበታል።
Фото недоступнеДивитись в Telegram
^_
🌹🌹#የእኔን_ትቼ_አንተን_ተቀብያለሁ🌹🌹
.
መድኃኔ ዓለም አባቴ ሆይ ጸሎት አስተምረኝ እስኪ?..ይገርማል!! ጥሩ ኑሮ ሳይሆን ጥሩ ሞት በሚናፈቅበት ዘመን በሕይወት መኖሬ ገራሚ ነው። ካንተ ካልሆነ ይህ ከወዴት ይገኛል?
ሟች ነኝ ብዬ በሰጠህኝ እድሜ ስደነቅ "ብትሞትም እንኳ አንተ ዘለዓለማዊ ነህ" ትለኛለህ። ይህችን ምድር ስለሰጠህኝ ስገረም "የማወርስህ አገር ከምታየው ሰማይ ይሰፋል"አልከኝ።
፧
አቤት ሆይ ከዓለም ፊት ማጥቆር በላይ ያንተ ፈገግታ ለእኔ ግሩም ነው ። አናውቀውም ተብሎ ከመካድ በላይ ከዘላለም በፊት ባንተ መታሰቤ ለእኔ ልዩ ነው ። ጆሮ አትስጡት ተብሎ ከሚዘመተው በላይ ጸሎቴን መስማትህ ዕፁብ ነው ። እንዳይነሣ እርገጡት ከሚባለው በላይ የተዘረጋልኝ እጅህ ለእኔ ትንሣኤ ነው ። እኔማ ሌት የማስበው ፣ ቀን የማመላልሰው መኖሬን ነው እንደ ኖርሁ አውቃለሁ እንዴት እንደ ኖርሁ ግን ምሥጢሩ አንተ ጋ ነው ። ሳላየው ያጎረሰኝ እጅህ ጥጋቤ ነው። በማላይህ ዘመን ሁሉ ታየኝ ነበር ። እስካይህ ብትጠብቅ ኖሮ እስካሁን በጨለማ ነበርሁ። የሰው ፍቅር እንጂ የሰው ወረት የለህምና መድኃኔ ዓለም አባቴ እኲት ስቡሕ እልሃለሁ።
❤ 1
"#እባክህን_ከእሳቱ_ላይ_አትውረድ"
አንድ ወንድም አባ ጴሜንን "ምከረኝ" ብሎ ጠየቀው። አባ ጴሜንም "ድስት በእሳት ላይ እያለ ምንም አይነት ተባይ ሊቀርበውና ሊያበላሸው አይችልም። ከእሳት ወጥቶ ሲቀዘቅዝ ግን ነፍሳት ሁሉ ለመግባትና ለማበላሸት ይቻላቸዋል። ክርስቲያንም ከመንፈሳዊ ተግባር ካልራቀ ጠላት የድቀት ምክንያት አያገኝበትም" አለው።
ወዳጄ ሆይ ሕይወት ቀዝቅዛብሃለችን? ከእሳቱ ወደ መሬት ወርደህ በርደሃልን? የሕያውነትህ ሙቀት እሳት በማጣት ተንዘፍዝፏልን? ድስት የተባለ ሰውነትህ ክረምት የሚያህል ጉድን ተሸክሟልን? ዙሪያ ገባህ ፀሐይ እንደማትወጣበት ምእራብ ጨለማን የሚጠራ ሆኗልን? ማንነትህ እሳት እንዳጣ ምግብ ጥቃቅን ነፍሳት በተባሉ ኃጢአቶች (ቁጣ፣ ቸልተኛነት፣ ስስት፣ አልታዘዝ ባይነት፣ ጭንቀት፣ ሁሉን የመናቅ ስሜት፣ ተስፋ መቁረጥ፣ ...) ተወርሮ፣ መዓዛ ቅድስና ተለይቶት እጅ እጅ ብሏልን? ሞቅ የሚያደርገው አጥቶ በዓለማዊነት ሻግቷልን? የተባዮች መጫወቻ፣ የተውሳኮች መቀለጃ ሆኗልን? እንግዲያውስ በቶሎ ወደ እሳቱ ውጣ፡፡
ወዳጄ ሆይ ሃይማኖት በተባለችና ከሰማይ በወረደች ልዩ እሳት (ሉቃ.12፥49) ላይ ተቀምጠህ የድስትነትህን ሙቀት መልስ፡፡ እምነት፣ ተስፋና ፍቅር (1ቆሮ.13፥13) በተባሉ ሦስት ጉልቻዎች ላይ በምቾት ተጥደህ የሕይወትህን የኃጢአት ብርድ አስወግድ፡፡ ንስሐ በተባለች ነበልባል ውበትነት የክረምትህን ጽልመት በምስራቃዊ በጋነት ድል ንሳ፡፡ በሥጋ ወደሙ ፍምነት ድስት የተባለ ሰውነትህን በከዊነ እሳትነት ቀድስ፡፡ እባክህን በቶሎ ወደ እሳቱ ውጣ፡፡
ሃይማኖት የተባለ እሳትን ተባይ አይቀርበውም፡፡ እምነት ተስፋና ፍቅር የተሰኙ ጉልቻዎችን ተውሳኮች ሽቅብ አይወጡአቸውም፡፡ የነበልባለ ንስሐን ብርሃንና ሙቀት ነፍሳተ ጽልመት መቋቋም አይችሉም፡፡ ስለዚህ በእሳቱ ላይ እስካለህ ድረስ (በመንፈሳዊ ተግባራት እስከጠነከርክ ድረስ) አንተ ሁሌም ከተባይና ከነፍሳት ብልሽት (ከአጋንንት) የራቅክ ነህ፡፡
ወዳጄ እባክህን ከእሳቱ ላይ አትውረድ፡፡ እሳቱ በደንብ ይነድ ዘንድ ጾም፣ ጸሎት፣ ስግደት የተባሉ እንጨቶችንና ምጽዋት የተባለ ጋዝን መጨመርህን እንዳትዘነጋ፡፡ እንዲህ ከሆነ ዘንዳ ድስትነት ሁሌም የሞቀ ይሆናል፡፡ እጅ እጅ ከማለት፣ ከመሻገትና የተባይ መጫወቻ ከመሆን ትድናለህ፡፡
ወዳጄ ሆይ እባክህን ከእሳቱ ላይ አይትውረድ፡፡
በኃጢአት "እጅ እጅ '' ከማለትና በበደል ከመሻገት እግዚአብሔር ይሠውረን! አሜን!
https://t.me/Bekirstos_Kassa
𝑩𝒆𝒌𝒊𝒓𝒔𝒕𝒐𝒔 𝒌𝒂𝒔𝒔𝒂
እኔን ማገኜት ከፈለጉ @Bekrstos_kassa ይጻፉልኝ፡፡ ወይም 0914463334 ይደውሉ ♥ © አዘጋጅ 𝐁𝐞𝐤𝐢𝐫𝐬𝐭𝐨𝐬 𝐊𝐚𝐬𝐬𝐚
Оберіть інший тариф
На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.