ቫቲካን "ግ*ብ*ረ ሰ*ዶ*ማዊነትን" የሚቃወሙትን ሊቀ ጳጳስ አወገዘች
++++
(ቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ)
የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያ፤ ፖፕ ፍራንሲስ ግ*ብ*ረ ሰ*ዶ#ም ላይ ባላቸው አቋም የሚቃወሟቸውን፤ ከፍተኛ የቫቲካን ባለሥልጣን ሊቀ ጳጳስ አወገዘች።
ካርሎ ማሪያ ቪጋኖ የተባሉት የ82 ዓመት አረጋዊ ሊቀ ጳጳስ የተወገዙት "በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ክፍፍል በመፍጠራቸው" እንዲሁም " የፖፕ ፍራንሲስን ሥልጣን ባለመቀበላቸው እና በመቃወማቸው ("the “crime of schism” and “denial of the legitimacy of Pope Francis") መሆኑ ተዘግቧል።
ካርሎ ማሪያ ቪጋኖ በቫቲካን ውስጥ አለ ያሉትን ሙስና በዝርዝር በማሳወቅ እንዲሁም የሮም ጳጳሳትና ካርዲናሎች በሕጻናትና ልጆች ላይ ሲፈጽሙ የኖሩት አስጠያፊ ወንጀል እንዲድበሰበስና እንዲቀር በማድረግ በኩል ፓፓውን ጨምሮ የቫቲካን ባለሥልጣኖች እጃቸው አለበት ብለው በግልጽ ደብዳቤ በማጋለጥ ይታወቃሉ።
የሮም ካቶሊክ በተለይም "መሻሻል አድርጌአለሁ" ካለችበት "ቫቲካን 2" በመባል ከሚጠራው ከ1960ዎቹ ወዲህ ብዙ ነገር እንደተበላሽ ካርሎ ማሪያ ቪጋኖ ይናገራሉ። በላቲን ቋንቋ መቀደስን ከመከልከል ጀምሮ የተፈጸሙ ጥፋቶች ቫቲካንን ከመንገዷ አስወጥቷታል ሲሉ ይከስሳሉ።
ፖፕ ፍራንሲስ ይባስ ብለው በቅርቡ ባሳለፉት ውሳኔ የካቶሊክ ቄሶች "ተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ መባረክ" እንደሚችሉ መግለጻቸው ነገሩን የበለጠ አክርሮታል። ካርሎ ማሪያ ቪጋኖ ፓፓውን በግልጽ "የሰይጣን መልእክተኛ" በማለት ገልጸዋቸዋል።
እናም ይህንን ሁሉ ያጣራው የሥነ ሥርዓት ኮሚቴ ካርሎ ማሪያ ቪጋኖ እንዲወገዙ ያደረገ ሲሆን "በንስሐ የሚመለሱ ከሆነ ለማየት" ለጊዜው ያላቸውን ማንኛውንም ጥቅማ ጥቅም (defrocking ይሉታል) አልቀማቸውም። በውግዘቱ መሠረት "Viganò cannot officially accept Catholic sacraments including Communion, ordain priests or officiate Mass" ማለትም "ከካቶሊክ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን መሳተፍ አይችሉም (ለምሳሌ መቁረብ)፤ ቅስናም ሆነ ዲቁና መሾም አይችሉም፣ መቀደስም አይችሉም"።
++++
ማጠቃለያ፦
ከዚህ የምንወስደው ዋና ሐሳብ ምንድነው?
** ግ*ብ*ረ ሰ*ዶ*ምን መቃወም እንኳን በዓለማዊ ሥፍራ፣ በቤተ እምነቶችም ውስጥ ዋጋ የሚያስከፍልበት ዘመን ላይ እንገኛለን።
** ይህንን ኃጢአት በሕዝባችን ላይ አንጭንም፣ ሕዝባችንን ለዚህ አሳልፈን አንሰጥም ያሉ መሠረታቸው ኦርቶዶክስ የሆኑ ሀገራት ላይ ብዙ መከራ እየደረሰ መሆኑን መመልከት እንችላለን።
** በሀገራችንም ይህ ነገር በተለያዩ NGOዎች አማካይነት፣ በመብትና በሊበራሊዝም ስም፣ በተለይ ለወጣቱ በስፋት እየተሰጠ የሚገኝ ነገር ነው።
** ቅዱስ ሲኖዶስ በግንቦቱ የርክበ ካህናት ጉባዔው ይህንን አጀንዳ አድርጎ መወያየቱ በሀገራችን የነገሩአሳሳቢነት ከፍ ማለቱን ያሳያል።
** በአሜሪካ እና በአውሮፓ ሕጻናት ልጆቻችን በግድ ስለዚህ ነገር እንዲማሩ በመገደድ ላይ ናቸው።
+++++
** ጆሮ ያለው መስማቱን ይስማ!!!!!