uk
Feedback
🧡❤️መልካም ልቦች💞 ✍️

🧡❤️መልካም ልቦች💞 ✍️

Відкрити в Telegram

🌷 🥀♡♡ ማፍቀር ስትጀምር ከእምነት ጀምር ♡♡🌷 🙏WELLCOM TO 🧡❤️መልካም ልቦች💞 ✍️ ☆በዚህ ቻናል ውስጥ ደስ የሚሉ ☞ የ ፍቅር ቃላቶች፣ ☞ግጥሞች፣ ☞የፍቅር ታሪኮች ያገኛሉ ! t.me/Melkam_liboch1 ● ቻናላችንን SHARE ያድርጉ 🙏

Показати більше
2 109
Підписники
+224 гОдини
+47 днів
+1830 день
Архів дописів
​​​​❣"ጤዛዉ ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🍂ክፍል-➎- አምስት ❥............🍃💐💐🍃..............❥ .... ብዙ የፍቅር አይነቶች ቢኖሩም የሀቢብ አይነት ፍቅር ግን መጀመሪያዉኑም ፍቅር ሊያስብለዉ የሚችል አልነበረም፡፡ ሀምዛ በሀቢብ ንግግር ወደ መናደዱ እየሄደ ነዉ፡፡ ሀምዛ   ሀቢብና ፎዚን ሊያስማማ፤ በሁለት ባለትዳሮች መካከል የነበረን ጥላቻ አስወግዶ እርቅ ለማስፈን ነበር አካሔዱ፡፡ ነገር ግን የሀቢብ ንግግር ወደ ድርድር የሚያስገባ ሳይሆን መቃቃርን የሚፈጥር እንደ ስድቡ 'ርካሽ ቃላትን የሚመርጥ 'ርካሽነቱን የሚያንፀባርቅ ባህሪ አወጣ፡፡ ..."ጓደኛዬ (አለዉ ሀምዛ... ለዘብ ባለ ንግግር) ... እየዉልህ ሀቢብ በርግጥ አንተ ከፎዚ በፊት ብዙ ሴቶችን ታዉቃለህ፤ ከብዙ ሴቶችም ጋር ነበርክ፡፡ እነዚያ ጋር የነበርከዉ ብዙ አመታት ግን ፎዚ ጋር እንዳለህ የትዳር ዘመን የተባረከ ሳይሆን የረከሰ ጊዜ ነበር፡፡ ፎዚ ጋር አዲስ ህይወት ከጀመርክ ሰነባበትክ የመጀመሪያ ሰሞን ደስተኛ ነበርክ፡፡ አሁን ምን ተፈጥሮ ነዉ የተቀየርከዉ ሀቢብ...!?" ብሎ ጠየቀዉ፡፡ ሀምዛ በሚያወራበት ጊዜ ግን የሀቢብ ሀሳቡ በሙሉ በጥላቻ የመረዘዉ ልቡን ተጠቅሞ ጥላቻን እየሰነቀ ነበር፡፡ ....."ሀቢብ!!? ሄይ... ወደ የት ነጎድክ?" አለዉ ከተጓዘበት አለም እየመለሰዉ፡፡ ....."ሀምዛ እየሰማሃኝ ነዉ፡፡ አንተ ፎዚን ልትወዳት ትችላለህ እኔ ግን... እጠላታለሁ?" ሀምዛ የሀቢብ ነገር አዝማሚያ የገባዉ ይመስላል፡፡ ሀቢብ ወሬዉን ቀጠል አደረገና፡፡ ..."ለመሆኑ ከፎዚ ጋር ከመቼ ጀምሮ ነዉ መገናኘት የጀመራችሁት?" ..." ያዉም እኔ ባለቤቷ ሳላዉቅ?? ... እ??" ብሎ ዉስጡ ያለዉን ስሜት ቀስ እያለ ያወጣዉ ጀመር፡፡ "ሀቢብ.." አለዉ ሀምዛ በተምስጦ አይኑን እየተመለከተ ..."የኔና ያንተ ጓደኝነት ዛሬ አልተጀመረም፡፡ ፎዚያን ከማግባትህ በፊት ብዙ ችግሮችንና ፈተናዎችን አሳልፈናል፡፡ አያሌ የደስታ ቀኖችን አብረን ቦርቀናል፡፡ እኔም እነዚያን መልካም ጊዜዎች በማስታወስ የተለመደዉን የጓደኝነቴን ከጎንህ ልሆን ስለፈለኩኝ፣ ትዳርህ የሰመረና በባለቤትህ ደስተኛ እንድትሆን እንጂ ሌላን ነገር አስቤ አልነበረም፡፡" ብሎ መለሰለት በተረጋጋ መንፈስ፡፡ ሀቢብ ግን ለትዳሩ መስመር፣ ለህይወቱ መቃናት የሚጥርለትን ጓደኛዉን ዛቻም ጭምር እየተናገረዉ ነዉ፡፡ ..."ሰማሃኝ ሀምዛ... ምንም እሰብ ምን ከዚያች ሴት ሴት ጋር ያለህ ግንኙነት ጤነኛ አይደለም፡፡" አለዉ፡፡ መደዋወላቸዉንና ግንኙነታቸዉን እንዲያቋርጥ በማስጠንቀቅ፡፡ ..."እሺ ይቅርታ ጓደኛዬ...." ብሎ ከሀቢብ ጋር የያዘዉ ሙግት መፍትሄ እንደሌለዉና እንደማይበገርለት አወቀ፡፡ . . . ..... ፎዚ የቤቱ ሾል አድክሟት  ምንም ሳትተጣጠብ በስራ ልብሷ ቤቷ ቁጭ የማትመለስበት በሚመስል ያለፈ ትዝታዋ ላይ ተተክላ በሀሳብ ባህር ሰምጣለች፡፡ የትዝታን ቅኔ እያዜመች፤ እጆቸቿን አገጯ ላይ እንዳስደገፈች አይኖቿ ላይርገበገቡ ምለዉ የልጅነት ምኟቷን፤ የኮረዳነት ደስታዋን ማስታወስ ይዛለች፡፡ አሁን የተማረረችበትን ህይወት በትዝታ እንኳ ትደሰትበት እንጂ...፡፡ በዚህ መካከል ሀቢብ ከጓደኛዉ ሀምዛ ጋር የነበራቸዉን እሰጥ አገባ ጨርሰዉ ባለመስማማት ተለያይተዉ ወደ ቤቱ መጣ፡፡ ቤቱ እንደደረሰ በሩን ሳያንኳኳ ከፍቶ ገባ፡፡ ፎዚያ ከበሩ ፊት ለፊት ሶፋዉ ላይ ተቀምጣ ሀቢብ በሩን ከፍቶ ሲገባ አላስተዋለችዉም፡፡ ደትዝታን ባህር እየቀዘፈች ነበርና አዮታዉ ሳታየዉ ቀረች፡፡ አይኖቿ ሀቢብን በር ከፍቶ ሲገባ ቢያዩትም ልቧ ከትዝታዋ ጋር ነበርና ሳታስተዉለዉ ቀረች፡፡ 'ልብ ካላዬ አይን አያይም' አይደል ተረቱስ፡፡ ሀቢብ የበሩን እጄታ ይዞ መልሶ ከዘጋ በኃላ እየተንጎራደደ ወደ ፎዚያ ተጠጋ፡፡ እሷ ግን አሁንም አላየችዉም፡፡ ወደ እሷ የሚጠጋዉ ሰዉ ይሁን ሌላ ነገር አላስተዋለችዉም፡፡ ወደ እሷ ተጠግቶ ከተቀመጠችበት ሶፋ ፊት ለፊቷ ካለዉ ሶፋ ተቀምጦ ..."ፎዚ አላት" እሷ ግን አልሰማችዉም፡፡ አዉቃ ዝም እንዳላለችዉና በሀሳብ  እንደተዋጠች በአቀማመጧና ከሁኔታዋ አስተዉላሏል፡፡ እጁን በፊቷ ላይ እየወዘወዘ "ሄይይ ኧረ ፎዚ..." ሲላት ፎዚያ ከእንቅልፏ እንደሚነቃ አይነት ሰዉ ብትት ብላ ..."  እ ሀቢቢ መጥተሃል እንዴ? ልብስ ሳጥብኮ ቆይቼ ድክም ብሎኝ ነዉ፡፡" እያለች ክስም ብሎ የነበረ ፊቷን በፈገግታ አደመቀችዉ፡፡ ሀቢብም ለጠጥ ብሎ ሶፋዉን እንደ መደገፍ እያለ ..."እ ... ነዉ?" ብሎ ወሬዉን አሳጠረዉ፡፡ ..."አዎ! ሁቢ ደግሞ ሶፊ ጋር ደዉዬ ስናወራ ቆዬን" ብላ ስትነግረዉ .."ለምን እሷ ጋር ደወልሽ?" ብሎ ጮኸባት፡፡ (ሶፊያ የሀቢብ እህት፤ የፎዚያ ደግሞ የግቢ ጓደኛዋ ናት!)፡፡ በዚህ ጊዜ ፎዚያ ደንገጥ ብላ ደህና ሆኖ የነበረዉን ለምን አሁን እንዲህ ብዬ ለምን አስከፋሁት ብላ ለልሡ አሰበች፡፡ 'ግን ሶፊ ጋር እንድደዉል ለምን አልፈለገም፡፡' ብላም ራሷን ጠየቀች እንደገና መለሾ ብላ 'አይይ እንደፈለገ!' አለች፡፡ ..."ሀቢቢ የስራ ልብሴን ሳልቀይር እንኳ መጣህ... ቆይ ልብስ ቀይሬ ልምጣ" ብላ ከተቀመጠችበት ስተትነሳ ..."ተቀመጭ..." አላት፡፡ ደንገጥ ብላ ..."እ..." አለችዉ፡፡ ..."ተቀመጭ" ብሎ ቃሉን ደገመዉ፡፡ ..."እ...እ እሺ " ብላ ተቀመጠች፡፡ ፊቱ ሳይፈታ እንደተኮሳተረ ቆጣ ብሎ... ..."እንድናወራ የምፈልገዉ ጉዳይ አለ" አላት፡፡ ╔═══❖•🌺🌺•❖═══╗       áŠ­ááˆ 6 ከ like በኋላ     á‹­  ቀ  ጥ  ላ  ል https://t.me/Melkam_liboch1

​​​​❣"ጤዛዉ ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🌿ክፍል አራት (➍)🌿 ጢርርር ... ጢርርርር..." ጥሪዉ (ደዋዩ) ማን እንደሆነ ለማየት ስልኩን ከሱሪዉ ኪስ አወጣና አየ፡፡ "Hamza" ይላል፡፡ ስልኩን ሳያነሳዉ ድምፁን ቀነሰና ጥሪዉን ድምፅ አልባ አደረገዉ፡፡ ንዴቱ ዉስጡን እያላወሰ ነበርና አይኑን ማጉረጥረጡን ቀጠለ፡፡... ..."ማን ነዉ የደወለዉ?" አላት፡፡ እጆቹን ጨብጦ ለቡጢ እያዘጋጃቸዉ፤ ሁኔታዉ ከሚስቱ ፊት ሳይሆን ከደመኛዉ ሊበቀለዉ ከሚፈልገዉ ሰዉ ፊት የቆመ ይመስላል፡፡ ፎዚያ ፈራችዉ፡፡ በዚህ ንዴቱ መምታት ከጀመራት እንደማያቆም ታዉቋት ትርበተበት ገባች፡፡ ወደ'ሡ ጠጋ እያላት ጥያቄዉን ደገመዉ፡፡ ..."ማን ነዉ የደወለዉ?... እ...?..." ፡፡ ምን ብላ ትመልስ?፡፡ ተደዉሎላት ሳይሆን ደዉላ ነዉ፡፡ 'ሀምዛ ነዉ ብለዉስ?.. ከ'ሹ ጋር ይጠረጥረኝ ይሆን?... የሚዋደዱ ጓደኛሞች በ'ኔ ምክንያት ቢጣሉስ?" እያለች ዉስጧን በስጋት ሞላችዉ፡፡ በዚሁ መካከል ሀምዛ ቅድም ደዉሎ ስላልተነሳለት በድጋሚ ለሀቢብ ደወለ ... "ጢርርርር... ጢርርርር...." የፎዚን ንዴት ስልኩ ላይ ሊወጣዉ ይመስል እጆቹን በሃይል ወደ ኪሱ ልኮ ስልኩን አወጣና  አረንጓዴዉን ተጭኖ..." ሄሎ ..." አለ፡፡ ..."ሄሎ ... ሃቢብ ብደዉልልህኮ አታነሳም" የሀምዛ ድምፅ ነበር፡፡ ከመበሳጨቱ የተነሳ ያሁኑ ደዋይ ማን እንደሆነ አላወቀዉም ነበር፡፡ ..."እ... አንተ ነህ እንዴ ሃምዛ..." ..."ስልክ ቁጥሬ ቢጠፋህ መቼም ድምፄ አይጠፋህም!" እሱ ልሹ ሃምዛ መሆኑን እያረጋገጠለት ነበር፡፡ ..."እ...ለማንሳት አልተመቸኝም ነበር" አለዉ፡፡ ..."ከፎዚ ጋር በምን ተጋጭታችሁ ነዉ?" ..."ማን ነገረህ?" ብሎ በቤቱ ዉስጥ አንገቱን አዟዙሮ ተመለከተ፡፡ 'ይሄ ሰዉዬ ተደብቆ እያየኝ ነዉ እንዴ?' ብሎ አሰበ፡፡  áˆ˜áŒĽáŽ የሚሰራ ሰዉ እንኳን ሌላ ሰዉ ራሱንም ይጠራጠራል፡፡ ስራዉ እንደ ቂል አደረገዉ፡፡ ..."ፎዚ አሁን ደዉላልኝ ነበር፡፡"  áˆľáˆáŠŠáŠ• ከጆሮዉ ሾር 'ራቅ እያደረገ ወደ ኃላ እንደማፈግፈግ ብሎ ፎዚን በቆመችበት ትቷት ወደ መኝታ ክፍሉ ተመለሰ፡፡ ..."እና... ምን አባቷ ወደ አንተ አስደወላት..." አለዉ፡፡ የተጠራጠረ ይመስላል፡፡ 'ግንኙነት አላቸዉ ማለት ነዉ' ሲል አሰበ፡፡ 'በዚህ አይነትማ እስከዛሬ የምነግረዉን ለሡ ይነግራት ነበር ማለት ነዉ!' ... 'ቆይ ግን... ምንድን ነዉ ግንኙነታቸዉ?'፡፡ ሀምዛ ማሜን እየመከረዉ ነዉ፡፡ 'አትጣሉ...' እያለ የጓደኝነቱን ይነግረዋል፡፡ ሀቢብ ግን አልሰማዉም፡፡ እንደዉም ይባስ ብሎ ሀምዛን ከፎዚ ጋር መጠርጠር ይዟል፡፡ ካፉ አላወጣዉም እንጂ 'እሰራለሃላችኃለሁ' እያለ ከንፈሩን በቁጭት ይነክሳል፡፡ ..."እሺ በቃ አንጣላም ... ስንገናኝ እናወራለን!" ብሎት ስልኩ ተዘጋ፡፡ ሀቢብ ፎዚን ጠልቷታል እንዳይባል ይቀናባታል፤ ይወዳታል እንዳይባል ደግሞ ያሰቃያታል፡፡ ነገረ ስራዉ ሁሉ 'እሱ እንዲህ ነዉ!' ብሎ ለመወሰን ይከብዳል፡፡ .... ፎዚያ እራሷን ማስጨነቁን ተያያዘችዉ ..'ቆይ ሀቢብ ሊጠላኝ የቻለበት ምክንያት ምን ይሆን?' ብላ እርግጠኛ ሁና መመለሾ በማትችለዉ ጥያቄ ራሷን ታፋጣለች፡፡ 'ያ የበፊቱ ፍቅርስ የት ገባ?' ...'ሶፊ ሾለ ሀቢብ ጥሩነት እንጂ አንድም ቀን መጥፎነቱን አዉርታኝ አታዉቅም ነበር፡፡ ፍቅር መስጠት እንደሚችል እንጂ ልቡ በጥላቻ የጠቆረ መሆኑን አልነገረችኝም ነበር፡፡' ነበር... ነበር ... ነበር... እያለች እራሷን ወደ ኃላ እየጎተተች ሀቢብን የተዋወቀችበትን የምርቃን ጊዜዋን አማረረች፡፡ ያን በደስታ የተፍነከነከችበትን ቀን ረገመችዉ፡፡ 'ቆይ ግን ምን አጉድየበት ተቀየረ?'.... ጥያቄ በጥያቄ ላይ ብቻ መልሱን አታዉቀዉም፡፡ ብታዉቀዉ ግን ደስ ይላታል፡፡ ምክንያቱም ራሷን በራሷ ያፋጠጠችበትን ጥያቄ መልስ ከተመለሰላት ትዳሯ ይሰምራል፤ ፍቅሯ ያብባል ስለዚህ ለልሡ ለህይወቷ ስትል መሆን ያለባትን ሁና፤ መክፈል ያለባትን መስዋእትነት ከፍላ ደስታዋ እንደገና መለምለም አለበት፡፡ . ... ሀቢብና ሀምዛ ሁሌም ከሚገናኙበት ዘቢብ ካፌ ተገናኝተዉ እየተጨዋወቱ ነዉ፡፡ ሀቢብ ዉስጡ ልቡ በጥላቻ ከመጥቆሩም በላይ ከርፍቷል፡፡ የገዛ ጓደኛዉን ሀምዛን በፊት በሚወዳት ዛሬ ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ከሚጠላት ሚስቱ ጋር ጠርጥሮታል፡፡ በጨዋታቸዉ መካከል እየተሳሳቁ ቢያወሩም የሃቢብ ሳቅ የማስመሰል ግልፈጣ፤ የሀምዛ ግን ከልቡ የሚመጣ ነበር፡፡ ሀምዛ ቀስ እያለ ወደ ቁምነገሩ እየተንደረደረ ነዉ፡፡ ..."ታዉቃለህ ግን ሀቢብ?" ..."ምኑን ነዉ የማዉቀዉ?" አለዉ፡፡ ግንባሩን አጨማዶ፡፡ ሀምዛም ቀጥታ ሾለ ፀቡ አንስቶ ይበልጥ ከሚያበሳጨዉ ምናልባት ያንን ጣፋጭ የፍቅር ጊዜዉን አስታዉሸዉ ልቡ ቢለዝብ ብሎ አሰበ፡፡ ..."ያንን የፍቅር ጊዜህን፡፡ በፍቅር ክንፍ ብለህ ከፎዚ ዉጭ ማሰብም ሆነ ማለም ያቆምክበት..." እያለ ሾለ መልካም የፍቅር ጊዜዉ ሊያስታዉሰዉ ሲሞክር ሀቢብ የሃምዛን ወሬ አቋረጠና... ..."እ... አዎ ትዝ አለኝ!" ብሎ ወሬዉን ከመቀጠሉ በፊት ተንፈስ ሲል ሀምዛ ወደ በፊት አቋሙ ሊመለስልኝ ነዉ በማለት ልቡን ደስታ ተሰምቶት ጥርሶቹ ታዩ፡፡ ፈገግ አለ፡፡ ሀቢብም ያዘዉን ማኪያቱ ፉት ብሎ አፉን በማኪያቶዉ ቃና ካጣጣመ በኃላ ወሬዉን ቀጠለ... ..."እርካሽ መሆኗን ባዉቅ ኑሮ በፍቅር ቅልጥ ባላልኩላት ነበር፡፡" ብሎ ፈግጎ የነበረዉን የሀምዛን ፊት ወዲያዉ አከሰመዉ ╔═══❖•🌺🌺•❖═══╗        áŠ­ááˆ 5 ከlike👍 በኋላ       ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል https://t.me/Melkam_liboch1

​​​​​​❣ጤዛዉ ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝   💐ክፍል ሶስት 💐   ....ፎዚ 'አሁን ደግሞ ምን አጠፋሁ?' ብላ የሀቢብ ሁኔታ አስጨነቃት፡፡ ከእለት ወደ እለት ለሡ ያለዉ ጥላቻ እየጨመረ መሄዱ ሃሳብ ገባት፡፡ እንዲህ አምራና ተዉባ ስጠብቀዉ 'የኔ ቆንጆ ዛሬ ደግሞ ይበልጥ አምሮብሻል' እንዲላት ነበር የፈለገችዉ፡፡ እሱ ግን ማሞገስ፤ ዉበት ማድነቅ የሚባለዉ ሃሳብ ሊመጣለት ቀርቶ እሷን መሸሽና እንደ ቆሻሻ ይርቃታል፤ ይፀየፋታል፡፡ ለዚህ ነገር መፍትሄ ማበጀት እንዳለባት አምና የሀቢብን የልብ ጓደኛ ሀምዛን ማማከር እንዳለባት ወሰነች፡፡ ምክንያቱም ሀቢብን ወደ ቀድሞዉ ፍቅሩ መመለሾ ካልቻለች ትዳራቸዉ ገደል ሾር እንደበቀለ ዛፍ በጊዜ ቆይታ ብዛት ተመንጉሎ እንደሚወድቅ ታዉቋታል፡፡ በፀብ የጠነከረ ትዳር፤ በንትርክ የተገነባ ፍቅር፤ በመቃቃር የተዋቀረ መዋደድ እንደሌለ ታዉቃለችና፡ . ... ሀምዛ የሀቢብ የልብ ጓደኛዉ ነዉ፡፡ ሁለቱ ጓደኛሞች (ሀቢብና ሀምዛ) መካከል ሚስጥር የሚባል ነገር የለም፡፡ እናም የሀቢብን የባህሪ መቀየር ሀምዛ ሊያዉቀዉ ይችላል በሚል ስልኳን አነሳችና የሃምዛን ቁጥር ጽፋ ደወለች፡፡ ስልኩ እየጠራ ነዉ፡፡ ሀምዛ ስልኩን አነሳና የፎዚ ጥሪ እንደሆነ በቁጥሩ ስላወቀ... ..." ሄሎ ፎዚ..." አላት፡፡ ..."አሰላሙዓለይኩም ሀምዛ... እንዴት ነህ?" ድምፅዋ ለቅሶዋን አቋርጣ የደወለች ሀዘንተኛ አስመስሏታል፡፡ ..."ወአለይኩም ሰላም ፎዚ ...ምን ሁነሻል?" ብሎ ጠየቃት፡፡ ልትደብቅዉ ያልቻለችዉ የዉስጥ ሀዘን እንዳለባት ያስታዉቅባታል፡፡ ፎዚም እየሆነች ያለችዉንና የሀቢብን የባህሪ መቀየር ለመንገር ስለደወለች ልትደብቀዉ ወይም በዝምታ ልታልፈዉ አልፈለገችም፡፡ ለሃምዛ ከመንገሯ በፊት ግን ዉስጧ ያለዉን ስሜቷን ትንፋሿ ቀድመዉ ነገሩት፡፡ "እህህህህ..." አለች፡፡ ሳታስበዉ ነበር በረጅሙ የተነፈሰችዉ፡፡ ..."ምነዉ ፎዚ?... ከሀቢብ ጋር ተጣላችሁ እንዴ?" ብሎ ከምትቀዝፈዉ የሀሳብ ባህር ዉስጥ አናጠባት፡፡ ..."ሀምዛ... (ብላ ጠራችዉና ለማዳመጥ ዝግጁ እንደሆነ ስታዉቅ ተንፈስ ብላ ንግግሯን ቀጠለች... ) ... ከሀቢብ ጋር እንደምንጣላ ታዉቃለህ እንዴ?" ብላ ጠየቀችዉ፡፡ ሀምዛ ያላሰበዉን ጥያቄ ስትጠይቀዉ ደንገጥ አለና... ..." ፎዚ ... ሀቢብ ጓደኛዬ እንደሆነ ታዉቂ የለ? ሁሌም ቤቱ ዉስጥ ስለተፈጠረዉ ነገር አይደብቀኝም" አላት፡፡ ..." ለምን ተገናኝተን አናወራም?" ብላ የትዳሯን አሳሳቢነትና አስጊ ሁኔታ ላይ እንዳለ ልትነግረዉ ፈለገች፡፡ በዚሁ ቅፅበት ግን ሀቢብ ሌላዉን ሁሉ የስልክ ንግግር ሳይሰማ "ለምን ተገናኝተን አናወራም?" የምትለዋን ቃል ሰይጣን ለጆሮዉ አቀበለዉ፡፡ ..."ምን? ... ከማን ጋር ነዉ የምትገናኘዉ?" ብሎ ጋደም ካለበት አልጋ ዘሎ ተነሳና ፎዚያ ወዳለችበት ክፍል ተጣደፈ፡፡ ልክ እሷ ጋር እንደደረሰ ከሀምዛ ጋር የሚገናኙበትን ቦታና ሰአት ተነጋግረዉ ስልኩን እየዘጋችዉ ነበር፡፡ እሷ ጋር እንደደረሰ አይኖቹ ሊወጡ ምንም አልቀራቸዉም፡፡ አፈጠጠባት፡፡ ፎዚ ፈራችዉ፡፡ ምን ትበለዉ? ምታወራዉ አጣች፡፡ ፊቷ የቆመዉ የምትወደዉና ዛሬ ቢቀየርም ድሮ የሚወዳት ባልሽ አልመስልሽ አላት፡፡ እሷን ለመደብደብ፤ ህይወቷን ለማበሳቆል፤ ትዳሯን ለማተራመስ፤ ኑሮዋን ለማዘባረቅ የተላከ 'ሰይጣን' ተመሰለባት፡፡ ሀቢብም ንዴቱ ምንም ሊያነጋግረዉ አልቻለም፡፡ አይኖቹ የሆነ ኢንች ያክል ቦታቸዉን ለቀዉ ወደ ፊት ወጣ ያሉ ይመስላሉ፡፡ ጉንጮቹ ተለጠጡ፤ ግባሩ ላይ የተጋደሙት መስመሮች የዘጠና አመት አዛዉንት አስመሰሉት፡፡ ኩስትርትር ብሏል፡፡ ሊመታትም ይቃጠዋል፡፡ በዚህ መሃል ጓደኛዉ ሀምዛ ደወለለት ... "ጢርርር ጢርርር..... ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 4  áЍ100like👍 በኋላ   ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል https://t.me/Melkam_liboch1

​​​​​​❣" ጤዛው ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🍄ክፍል ሁለት (➋)🍄 ....... የሃቢብ ስድብ በየቀኑ ቢብስም ፎዚ ግን ቁብ ሳሰጠዉ እሱን ከማፍቀር አላስቆማትም ነበር፡፡ እየሰደባት ትወደዋለች፡፡ ከምንም በላይ የማትረሳዉ ነገር ቢኖር... አንድ ቀን ከስራ መመለሻዋ ሰአት ደርሶ ወደ ቤት እየሄደች ስልኳ ከቦርሳዋ ዉስጥ ሆኖ ይጠራ ነበር፡፡ ፎዚ አልሰማችዉም፡፡ በምትሄድበት መንገድ ዳር የነበረዉ ጫጫታና ሁካታ የስልኩን ድምፅ ሊያወጣዉ ስላልቻለ ፎዚ ስልኩን አንስታ ጥሪዉን ሳታስተናግድ ቀረች፡፡ ቤቷ እንደደረሰች ሃገር አማን - ቤቴ ሰላም ብላ የቤቷን የበር ቁልፍ ከፖርሳዋ አዉጥታ ስትሞክር እንዳጋጣሚ ሆኖ በሩ ክፍት ነበር፡፡ ሀቢብ ቀድሞ እንደገባ ስለተረዳች ሀሳቧን ሁሉ በሩ ላይ ጥላ ባሏን በአንዲስ መንፈስ ለመገናኘት በሙሉ ፈገግታና በሚያስቀና ደስታ እየተፍነከነከች የበሩን እጄታ ይዛ ከፈት ስታደርገዉ ያላሰበችዉ ነገር ገጠማት፡፡ ... ጣቶቹ ከብረት የጠነከሩ የሚመስሉ ሸካራ መዳፍ የፎዚ ፊት ላይ አረፈ "ጯ........." አይኗ እስኪሸፈን፤ የጉንጯ ቆዳ እስኪገፈፍ በጥፊ መታት፡፡ በድጋሜ 'ጯ...........'፡፡ ሀቢብ ነበር፡፡ "ለምንድን ነዉ ስልክ ያላነሳሽዉ?" በሚል ጥያቄ አንባረቀባት፡፡ ፎዚ አይኖቿን በግድ ከገለጠቻቸዉ በኃላ በፍርክርክ መዳፎች ጥፊ የቆሰለዉን ጉንጯን በእጆቿ እያሻሸች፤ ለማልቀስ እየዳዳት አይኖቿ በመቅፅብት እምባ አዝለዉ በለሆሳስ ድምፅ ... " ደዉለህ ነበር እንዴ?" አለችዉ፡፡ ሁሌም በመጥፎ ይጠረጥራት ኑሯልና... "አሃ... አንቺ ከማንም ወንድ ጋር እየዘለልሽ አዉቀሽ ያላነሳሽዉን ልትዋሺ ነዉ??" ብሎ ደም ማንባት በቀራቸዉን አይኖቹ አፈጠጠባት፡፡ አይኖቹ ቀልተዉ ነበር አይገልፃቸዉም፡፡ ደም የለበሱ፤ በርበሬ የጎረሱ መስለዋል፡፡ ሞባይሏን ለማዉጣት እጇን ወደ ፖርሳዋ እየሰደደች "ወላሂ አልዋሸሁህም" አለችዉ፡፡ "ዝምም በይ .. ቀጣፊ!" ብሎ ጥፊዉን ሊደግመዉ ቃጣዉ፡፡ . ... ፎዚያ በሃቢብ ከቦክስ ያላነሰ ጥፊ ጉንጯ ላይ ጠባሳ የቀረ ይመስል ይሄን ክስተት አረሳችዉም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ፍቅሩ በልጦ፤ መዉደዷ ገጦ ይበልጥ ነበርና ሁሉንም ይሁን ብላ በተቀበለችበት፤ ፀቡንም ነገሩንም ወደ ፍቅር ለዉጣ ትዳሯን አቆይታለች፡፡ . ...የሀቢብን መጥፎ ጥርጣሬ ለማስወገድ ስትል የድሮዉ ፍቅሩን ቢመልሰዉ ብላ ከምትሰራበት መስሪያ ቤት የመልቀቂያ ደብዳቤ እንኳ ሳታስገባ ለቀቀች፡፡ ምክንያቷ ደግሞ በተደጋጋሚ ከመስሪያ ቤት ወንዶች ጋር ትቀብጫለሽ 'እኔን ቀይረሽኛል' እያለ መዉጫ መግቢያ ሲያሳጣት፤ በቤቷ ዉስጥ ሰላም ሲነሳት 'ወጥቼ እንድሰራ ካልፈለክና ካላስደሰተህ ቤቴ እዉላለሁ' ብላዉ ባሏን ለመንከባከብ ለሀቢብ ካላት ሙሃባ የተነሳ ስራዋን እርግፍ አድርጋ ትታ ቤት ዉላለች፡፡ . ....... ይሄን ዱላና ተዳጋጋሚ የሆነዉ ስድቡ (ቀጣፊ...ዉሸታም...) ሳይከብዳት ዛሬ የተነፈሳት "እርካሽ" ያላት 'ርካሽ' ቃል ፎዚን እያነፋረቀ ያስለቅሳታል፡፡ 'እኔ ነኝ?... እኮ እኔ?... እኔ ነኝ እርካሿ?" እያለች ታላዝናለች፡፡ የኔ ዉድ የሚለዉ ጥሪዉ ባንዴ ተወግዶ፤ የፍቅር ቃላቶች እንደ ስደተኛ ርቆ ተሰዶ ቤታቸዉ የፀብ አዉድማ ሁኗል፡፡ ሰሞኑን ያመጣዉ አዲስ ፀባይ ደግሞ ፎዚን እየተፈታተናትና ትዳር እንዲያንገሻግሻት ሊያደርጋት ምነንም አልቀሯትም፡፡ ለሹ ብላ ሾል እንዳቆመች፤ በፀብ የጠለሸዉን ትዳር ወደ ፍቅር ለመቀየር እየተጋች ባለበት ወቅት......"እኔ ማመጣዉን ተቀምጦ መብላት አይከብድሽም?" ይላት ጀምሯል፡፡ ምንም አትመልስለትም ይልቁንስ በሱ መጥፎ ንግግርና ፀያፍ ተግባሩ ብትማረርም ሀቢብን መንከባከቧ ከእለት ወደ እለት ጨምሯል፡፡ ከስራ መመለሻዉ ሰአት ሲደርስ በሚያማምሩ ልብሶች ተሽቀርቅራ፤ እሱን በሚያማልሉ ነገሮች ተዉባ፤ እሱዉ በመረጠዉ ሽቶ ጠረኗን አዉዳ ትጠብቀዋለች፡፡ ..."... ሀቢቢ እንኳን ደህና መጣህልኝ!" ብላ እቅፏ ዉስጥ ልታስገባዉ እጇን ስትዘረጋ፤ የዘረጋችዉን እጇቿን በእጆቹ ገፍትሮና አመናቅሮ ... ..."አንቺማ በደህና እንድመለስ አትፈልጊም ነበር... ያዉ ተመለስኩ" ብሎ ነገሩን ይጀምረዋል፡፡ አሁንም ግን... ነገሩን ወደ ነገር ቀይራ ቤቱን በፀብ ቦንብ ማጋይት ስለማትፈልግ በሙሉ ፈገግታ ፈግጋ ወደ'ሹ ጠጋ እያለች... ..." ሀቢቢ ንፍቅ ብለኸኛል!" ትለዋለች፡፡እንደምታፈቅረዉ ያዉቃል፡፡ ነገር ግን እሱ ጸቡን ስለሚፈልገዉ የሷ የፍቅር ቃል አይረታዉም፡፡ "ሀቢቢ...፤ የኔ ማር...፤ የኔ ፍቅር...፤ ዉዴ..." እያለች የምትጠራዉ ነገር አይዋጥለትም፡፡ አጠገቡ ከተቀመጠች በኃላ ፀጉሩን እያሻሸች "ምን ሁነህብኝ ነዉ ዉዴ?" አለችዉ፡፡ እጆቿን ከፀጉሩ ላይ እያነሳ "ለምን ትነኪኛለሽ?" ብሎ አይኑን ጎለጎለባት፡፡ ፎዚ ይብስ እንዳይናደድ ብላ ዝም አለችዉ፡፡ ብቻ በስስት እያየችዉ አይኖቿን አይኖቹ ላይ ታንከባልላቸዋል፡፡ ግንባሩ ተጨማዶ ተኮሳትሮና ተቆጥቶ ከተቀመጠበት ምንጥቅ ብሎ ተመናጭቆ ተነሳና ወደ መኝታ ክፍሉ ገባ፡፡ በአስተያየቷ ተናዷል፡፡ የፍቅሯ ሃያልነት አፉን ዘጋዉ እንጂ በስስት የምታዬዉን ሚስቱን "ምን ታፈጫለሽ?" ማለትም አስቦ ነበር ። ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 3 ከ150 like በኋላ ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1

​​​​​​❣" ጤዛው ፍቅሬ"❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝 🍄ክፍል ሁለት (➋)🍄 ....... የሃቢብ ስድብ በየቀኑ ቢብስም ፎዚ ግን ቁብ ሳሰጠዉ እሱን ከማፍቀር አላስቆማትም ነበር፡፡ እየሰደባት ትወደዋለች፡፡ ከምንም በላይ የማትረሳዉ ነገር ቢኖር... አንድ ቀን ከስራ መመለሻዋ ሰአት ደርሶ ወደ ቤት እየሄደች ስልኳ ከቦርሳዋ ዉስጥ ሆኖ ይጠራ ነበር፡፡ ፎዚ አልሰማችዉም፡፡ በምትሄድበት መንገድ ዳር የነበረዉ ጫጫታና ሁካታ የስልኩን ድምፅ ሊያወጣዉ ስላልቻለ ፎዚ ስልኩን አንስታ ጥሪዉን ሳታስተናግድ ቀረች፡፡ ቤቷ እንደደረሰች ሃገር አማን - ቤቴ ሰላም ብላ የቤቷን የበር ቁልፍ ከፖርሳዋ አዉጥታ ስትሞክር እንዳጋጣሚ ሆኖ በሩ ክፍት ነበር፡፡ ሀቢብ ቀድሞ እንደገባ ስለተረዳች ሀሳቧን ሁሉ በሩ ላይ ጥላ ባሏን በአንዲስ መንፈስ ለመገናኘት በሙሉ ፈገግታና በሚያስቀና ደስታ እየተፍነከነከች የበሩን እጄታ ይዛ ከፈት ስታደርገዉ ያላሰበችዉ ነገር ገጠማት፡፡ ... ጣቶቹ ከብረት የጠነከሩ የሚመስሉ ሸካራ መዳፍ የፎዚ ፊት ላይ አረፈ "ጯ........." አይኗ እስኪሸፈን፤ የጉንጯ ቆዳ እስኪገፈፍ በጥፊ መታት፡፡ በድጋሜ 'ጯ...........'፡፡ ሀቢብ ነበር፡፡ "ለምንድን ነዉ ስልክ ያላነሳሽዉ?" በሚል ጥያቄ አንባረቀባት፡፡ ፎዚ አይኖቿን በግድ ከገለጠቻቸዉ በኃላ በፍርክርክ መዳፎች ጥፊ የቆሰለዉን ጉንጯን በእጆቿ እያሻሸች፤ ለማልቀስ እየዳዳት አይኖቿ በመቅፅብት እምባ አዝለዉ በለሆሳስ ድምፅ ... " ደዉለህ ነበር እንዴ?" አለችዉ፡፡ ሁሌም በመጥፎ ይጠረጥራት ኑሯልና... "አሃ... አንቺ ከማንም ወንድ ጋር እየዘለልሽ አዉቀሽ ያላነሳሽዉን ልትዋሺ ነዉ??" ብሎ ደም ማንባት በቀራቸዉን አይኖቹ አፈጠጠባት፡፡ አይኖቹ ቀልተዉ ነበር አይገልፃቸዉም፡፡ ደም የለበሱ፤ በርበሬ የጎረሱ መስለዋል፡፡ ሞባይሏን ለማዉጣት እጇን ወደ ፖርሳዋ እየሰደደች "ወላሂ አልዋሸሁህም" አለችዉ፡፡ "ዝምም በይ .. ቀጣፊ!" ብሎ ጥፊዉን ሊደግመዉ ቃጣዉ፡፡ . ... ፎዚያ በሃቢብ ከቦክስ ያላነሰ ጥፊ ጉንጯ ላይ ጠባሳ የቀረ ይመስል ይሄን ክስተት አረሳችዉም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ፍቅሩ በልጦ፤ መዉደዷ ገጦ ይበልጥ ነበርና ሁሉንም ይሁን ብላ በተቀበለችበት፤ ፀቡንም ነገሩንም ወደ ፍቅር ለዉጣ ትዳሯን አቆይታለች፡፡ . ...የሀቢብን መጥፎ ጥርጣሬ ለማስወገድ ስትል የድሮዉ ፍቅሩን ቢመልሰዉ ብላ ከምትሰራበት መስሪያ ቤት የመልቀቂያ ደብዳቤ እንኳ ሳታስገባ ለቀቀች፡፡ ምክንያቷ ደግሞ በተደጋጋሚ ከመስሪያ ቤት ወንዶች ጋር ትቀብጫለሽ 'እኔን ቀይረሽኛል' እያለ መዉጫ መግቢያ ሲያሳጣት፤ በቤቷ ዉስጥ ሰላም ሲነሳት 'ወጥቼ እንድሰራ ካልፈለክና ካላስደሰተህ ቤቴ እዉላለሁ' ብላዉ ባሏን ለመንከባከብ ለሀቢብ ካላት ሙሃባ የተነሳ ስራዋን እርግፍ አድርጋ ትታ ቤት ዉላለች፡፡ . ....... ይሄን ዱላና ተዳጋጋሚ የሆነዉ ስድቡ (ቀጣፊ...ዉሸታም...) ሳይከብዳት ዛሬ የተነፈሳት "እርካሽ" ያላት 'ርካሽ' ቃል ፎዚን እያነፋረቀ ያስለቅሳታል፡፡ 'እኔ ነኝ?... እኮ እኔ?... እኔ ነኝ እርካሿ?" እያለች ታላዝናለች፡፡ የኔ ዉድ የሚለዉ ጥሪዉ ባንዴ ተወግዶ፤ የፍቅር ቃላቶች እንደ ስደተኛ ርቆ ተሰዶ ቤታቸዉ የፀብ አዉድማ ሁኗል፡፡ ሰሞኑን ያመጣዉ አዲስ ፀባይ ደግሞ ፎዚን እየተፈታተናትና ትዳር እንዲያንገሻግሻት ሊያደርጋት ምነንም አልቀሯትም፡፡ ለሹ ብላ ሾል እንዳቆመች፤ በፀብ የጠለሸዉን ትዳር ወደ ፍቅር ለመቀየር እየተጋች ባለበት ወቅት......"እኔ ማመጣዉን ተቀምጦ መብላት አይከብድሽም?" ይላት ጀምሯል፡፡ ምንም አትመልስለትም ይልቁንስ በሱ መጥፎ ንግግርና ፀያፍ ተግባሩ ብትማረርም ሀቢብን መንከባከቧ ከእለት ወደ እለት ጨምሯል፡፡ ከስራ መመለሻዉ ሰአት ሲደርስ በሚያማምሩ ልብሶች ተሽቀርቅራ፤ እሱን በሚያማልሉ ነገሮች ተዉባ፤ እሱዉ በመረጠዉ ሽቶ ጠረኗን አዉዳ ትጠብቀዋለች፡፡ ..."... ሀቢቢ እንኳን ደህና መጣህልኝ!" ብላ እቅፏ ዉስጥ ልታስገባዉ እጇን ስትዘረጋ፤ የዘረጋችዉን እጇቿን በእጆቹ ገፍትሮና አመናቅሮ ... ..."አንቺማ በደህና እንድመለስ አትፈልጊም ነበር... ያዉ ተመለስኩ" ብሎ ነገሩን ይጀምረዋል፡፡ አሁንም ግን... ነገሩን ወደ ነገር ቀይራ ቤቱን በፀብ ቦንብ ማጋይት ስለማትፈልግ በሙሉ ፈገግታ ፈግጋ ወደ'ሹ ጠጋ እያለች... ..." ሀቢቢ ንፍቅ ብለኸኛል!" ትለዋለች፡፡እንደምታፈቅረዉ ያዉቃል፡፡ ነገር ግን እሱ ጸቡን ስለሚፈልገዉ የሷ የፍቅር ቃል አይረታዉም፡፡ "ሀቢቢ...፤ የኔ ማር...፤ የኔ ፍቅር...፤ ዉዴ..." እያለች የምትጠራዉ ነገር አይዋጥለትም፡፡ አጠገቡ ከተቀመጠች በኃላ ፀጉሩን እያሻሸች "ምን ሁነህብኝ ነዉ ዉዴ?" አለችዉ፡፡ እጆቿን ከፀጉሩ ላይ እያነሳ "ለምን ትነኪኛለሽ?" ብሎ አይኑን ጎለጎለባት፡፡ ፎዚ ይብስ እንዳይናደድ ብላ ዝም አለችዉ፡፡ ብቻ በስስት እያየችዉ አይኖቿን አይኖቹ ላይ ታንከባልላቸዋል፡፡ ግንባሩ ተጨማዶ ተኮሳትሮና ተቆጥቶ ከተቀመጠበት ምንጥቅ ብሎ ተመናጭቆ ተነሳና ወደ መኝታ ክፍሉ ገባ፡፡ በአስተያየቷ ተናዷል፡፡ የፍቅሯ ሃያልነት አፉን ዘጋዉ እንጂ በስስት የምታዬዉን ሚስቱን "ምን ታፈጫለሽ?" ማለትም አስቦ ነበር ። ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 3 ከ150 like በኋላ ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1

​​​​​ ❣ጤዛዉ ፍቅሬ🌿❣ 💝በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል የቀረበ💝      💘💘ክፍል አንድ💘💘 ❥..........🍃💐💐🍃...... .....የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የአራቱም ካምፓስ ተማሪዎች የምርቃን ፕሮግራም ለመታደም ተማሪዎች ቤተሰቦቻቸዉን ይዘዉ ከታሪካዊዉ ቦታ ተገኝተዋል፡፡ ይህ ቦታ ብዙ ሰዎች ይቺን ሃገር ለመታደግና ለመጠበቅ  ተሰግስጎባት የነበረዉን መዥገር ለመንቀል ለትግል የወጡ ጀግኖች የተቀበሩበት ቦታ 'ሀወልቲ-ሰማእታት' ነዉ፡፡ ተማሪዉቹ ደስታ ዉጧቸዉ ይፍነከነካሉ፡፡ እዚህም እዚያም ከወላጆቻቸዉ ጋር ተቃቅፈዉ ፎቶ የሚነሱ ይስተዋላሉ፤ እቅፍ አበባዎችና ሌሎች ዉድ ዉድ  ስጦታዎች ከወላጅና ከወዳጆቻቸዉ ይነጉዳሉ፡፡ በደስታ ብዛት ጥርሳቸዉ መከደን ያቃታቸዉ ተማሪዎች በዝተዋል፡፡ ከእነዚህ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል ደግሞ ፎዚ አንደኛዋ ናት፡፡ ፌሽታ በፌሽታ ሆናለች፡፡ እንኳን ስቃ አኩርፋም እጅግ በጣም ዉብ ናት!፡፡ በዚያ ላይ ደስታዋ ሰዉነቷን፤ ፈገግታዋ ፊቷን አስዉቦት ከቤተሰቦቿ ጋር የሰማእታቱን ሀዉልት እየተጠጉ ፎቶ ይነሳሉ፡፡ ... ትንሽ እህቱን ለማስመረቅ ከአዲስ አበባ ተነስቶ የሰሜኗን ኮከብ መቀሌን የረገጣት ሀቢብ በእህቱ ጓደኛ ዉበት ፈዞ፤ ፍቅሯን አርግዞ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል፡፡ ፎዚ የሀቢብ እህት ጓደኛ በመሆኗ መቀሌ በቆየባቸዉ የአምስት ቀን እድሜ በደንብ ተግባብተዉና ስልክ ተለዋዉጠዉ ነዉ የተመለሰዉ፡፡ ትዉዉቃቸዉ በዚሁ ጀመረ.... ፡ ፡ ....... ሀቢብና ፎዚያ ከተጋቡ ሳምንታቶች ነጉደዉ ወራቶች ተቆጥረዋል፡፡ ፎዚን ከማግባቱ በፊት ለሁለት አመት ያክል ፍቅሩን በዉስጡ አምቆ ይዞት ለአንድ አመት ያክል ደግሞ የፍቅር ጥያቄ እያቀረበላት በመጨረሻም በጌታ ፍቃድ ተጋቡ፡፡ በጣም ይወዳታል፡፡ ሲወዳት ይወዳታል የሚለዉ ቃል ያንሰዋል፡፡ ሲያፈቅራት ያፈቅራታል የሚለዉ የፍቅር ትልቁ ቃል ሀቢብ ለፎዚያ ያለዉን ፍቅር አይገልፀዉም፡፡ ዘመኑን ሙሉ ከርሷ ጋር ሊኖር ምሎ፤ ዘላለም ላይለያት፤ በማንም ላይቀይራት ተገዝቶ ለምኗት አስለምኗት ብዙ መስዋእትነትን ከፍሎ ፎዚን የራሱ የግሉ ሊያደርጋት ችሏል፡፡ አግብቷታል፡፡  áˆ…á‹­á‹ˆá‰ˇáŠ• በህይወቱ አቆራኝቱ የሰዉነቱ አምሳል፤ የአካሉ ክፋይ አድርጓታል፡፡ . ....... ፎዚያ የልጅነት ህልሟ ለትዳር ስትደርስ ማግባት የምትፈልገዉ ወንድ በዲኑ የላቀ፤ በትምህርቱ የረቀቀ፤ ጥላቻን አድክሞ፤ ፍቅርን አጣጥሞ መስጠት የሚችል ሰዉ እንዲያገባት ትፈልግ ነበር፡፡  á‹¨áŠ áŠŤáˆ‰ ፍላጭ፤ የችግሩ ተጋፋጭ እንዲያደርጋት መሆን ምኞቷ ነበር፡፡ የፀባዬ ሸጋ፤ የቁመተ ሎጋ ወንዳ ወንድነትን ተላብሶ በሱና የደመቀ፤ በዒባዳ ለጌታዉ የወደቀ ሰዉ እንዲዘዉጃት- የዚያ ሰዉ ሚስት መሆን አቅዷ ነበር፡፡ . ....... ሁሌም ቢሆን አላህ የፈለገዉና የወሰነዉ ተግባር ላይ  ይዉላል እንጂ ሰዉ የፈለገዉን አያገባም፡፡ ሰዉ ያቀደዉን አይኖርም፡፡ ለህይወቱ ስኬት የቀየሰዉን መንገድ አይጓዝበትም፡፡ ሁሉም የአላህ ዉሳኔና የጌታ መሻት ናቸዉ፡፡ በዚህም ፎዚያ የልጅነትን ህልሟን በሚያኮላሽ መልኩ ስትመኘዉን የነበረ ነገር ሁሉ ሳይሳካላት በተቃራኒዉ የሆነዉን ሀቢብን አገባች፡፡ . ...... በርግጥ ሀቢብ የዲን እዉቀትም የለዉም፤ እንዲኖረዉም ጥረት አድርጎ አያዉቅም፡፡ ሶላት ሊሰግድ ቀርቶ የሶላት ጥሪ /አዛን/ ሲሰማ ያንገሸግሸዋል፡፡ ፎዚያ ይሄንን ሁሉ ተግባር ሳታገባዉ በፊት ቀድማ አዉቃ ነበር፡፡ ነገር ግን ... ፎዚን ለማግባትና ላለማጣት የራሱ ማድረግ ስለነበረበት፤ እንቡጥ ፅጌረዳ አይቶ ማለፍ ተስኖት ... 'የዲን እዉቀት የሌለኝ የቤተሰቦቼ አስተዳደግ ነዉ' እያለ ዋሻት፡፡ 'አንቺን የማገባ ከሆነ ግን ፀባዬ ይስተካከላል፤ ሶላት እጀምራለሁ፤ ቁርዓንም እቀራለሁ' ብሎ አሳምኗት የዋኀ ፎዚም ይሁን ብላ አምና ተቀብላዉ 'ባሌ ይስተካከላል፡፡ ቃል የገባልኝን ይፈፅማል' እያለች በባዶ የህልም ሩጫ ትሮጣለች፡፡ ....... በተጋቡ ከጥቂት ሳምንታት ቆይታ በኃላ ነገሩን ጀምሮት እያመሸ መግባት አዘወተረ፡፡ ከእሷ ጋር ላለማደር አልጋ እየለየ መተኛት ከጀመረ ሰነባበተ፡፡ የሚገባትን ክብርና እንክብካቤ ነፍጓት ሳያገባት በፊት ለፎዚ የነበረዉ ፍቅር በሚገርም ፍጥነት አሽቆልቁሎ በገባ በወጣ ቁጥር ባ'ፉ እያከላፈታት፤ አይኑና ፊቱ እየገለመጧት ኑሮን ከሃቢብ ጋር እየኖረች ነዉ፡፡ የሚገርመዉ ግን... ትወደዋለች፡፡ በጣም አፍቀረዋለች፡፡ ባሏን (ሀቢብ) በልቧ ዉስጥ እንደ ንጉስ አንግሳ፤ የፍቅር ካባን አልብሳ እየተንከባከበች ይዘዋለች፡፡ . .......ከእለታት ባንዱ ቀን ፎዚ መኝታ ቤቷ ዉስጥ አልጋዋ ላይ እጥፍጥፍ ብላ ተኝታ የተንተራሰችዉ ትራስ በእንባዋ ርሜ ታጥቦ እንደተጠመዘዘ ጨርቅ ረጥቧል፡፡  ... "እኔ ነኝ እርካሿ?" እያለች በመነፋረቅ አይኖቿን ቀይስር ያገመጠቻቸዉ እስኪመስል ድረስ ታነባለች፡፡ ታለቅሳለች፡፡ 'እርካሽ..." የሚለዉ የሀቢብ ስድብ በአይነ-ህሊናዋ እየተመላለሰ እንደ ገደል-ማሚት ያስተጋባባታል፡፡  "እርካሽ.... እኮ እኔ...እርካሽ....!" ❥..........🍃💐💐🍃............❥ ክፍል 2 ከ200like👍 በኋላ  ይ  ቀ  ጥ  ላ  ል‼️ https://t.me/Melkam_liboch1 ሼር🙏

ምርጥ ባህሪ🧡✅ --------- ★. ጥቂት አዉራ፡፡ ስታወራ ቀስ ብትል መልካም ነዉ ★. አንድ ቦታ ላይ ብዙ አትታይ፡፡ ስራህ ላይ አተኩር ተግባቢና የተረጋጋ ሰዉ ሁን ★. ማንም ትክክል ነህ እንዲልህ #አትጠብቅ፡፡ ማንም ደጋፊህ እንዲሆን አትጎትጉት ★. ስላለህ ነገር ደጋግመህ እየተናገርክ የመጎረር ስሜትን አስወግድ ★. ምርጥ #አዳማጭና መፍትሄ አምጪ ሁን ★. አደርገዋለሁ ያልከዉን ነገር አድርገዉ ★. በጣም ደስ ሲልህ ወይም በጣም ስታዝን ዉሳኔ #አትወስን! ★. የግል ጉዳይህን ላገኘኸዉ ሰዉ አትናገር ★. ሰዉ ስላንተ የፈለገዉን ቢያስብ ከማንነትህ ጋር አታገናኘዉ ★. ማንንም ለመጉዳት ብለህ ጉድጓድ ከመቆፈርም ይሁን ከማስቆፈር ራስህን አሽሽ ★. የጎዱህንና ‘ምንም የለዉም!’ ብለዉ የራቁህን ሰዎች ስኬታማ በመሆን አሳያቸዉ ★. ሃሳብህን ለማሳመን የሰዎችን ማንነት አትጉዳ፡፡ ትክክክል ብትሆን እንኳን ካመኑ ይመኑህ ካላመኑህ ጊዜዉ ያሳምናቸዋል መልካም ምሽት ምርጦቼ💛 https://t.me/Melkam_liboch1 ሼር አደራ

🥰 ልስምሽ ዞር ስል 💋                                      ልስምሽ ዞር ስል                  የሳትኩሽ አሳሳት🫣        አልረሳ ብሎኝ ፊቴ ላይ ታትሟል                ልክ እንደ ንቅሳት🤗          ድጋሜ አስበላኝ ይሄ ሞኝ ከንፈሬ   ይኸው ሳማት ስለው ይላል ነው አፍሬ🫣           ምኔ ነው ያስጠላሽ ፊቴ ነው አይኔ👁           ወይ ደግሞ ሊስምሽ ያሰበው                  ያ ሞኙ ከንፈሬ🥺   ምኔን ጠልተሽው ነው እንደዛ ሽል ያልሽኝ😒                   ያ ሞኙ ከንፈሬን💋           ልክ እንደ አበባ ያገረጣሽብኝ😢 ቆይ ምን አስበሽ ነው እንደዛ ሽል ያልሽኝ🤔 🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔 https://t.me/Melkam_liboch1

​​💖 ኤልዳና  đŸ’ž 💝ልብ አንጠልጣይ የ ፍቅር ታሪክ በመልካም ልቦች የቴሌግራም ቻናል ተዘጋጅቶ የቀረበ💝           ክፍል 3⃣4⃣ የመጨረሻው ክፍል ዝም ዝም ዝም ተባባልን ትንሽ ቆየና አንዳንዴ አንቺ ከለፋሽለት ዋጋ ከከፈልሽለት ፍቅር ይልቅ እጣ ፈንታሽ በልጦ ይገኛል እጣ ፈንታ ሚባለው ነገር ለካ እውነት ነው አይገርምሽም ያን ያህል ቀን ካንቺጋ ስናድር አላረገዝሽም መከላከያም አልተጠቀምሽም አንድ ቀን ከቃልጋ አደርኩ ለዛውም በስተት እሷ ግን አረገዘች በዛ አሰረችኝ እናቴን መሾመር ባታስዢልኝ ባታግዣትና አሪፍ ሁኔታ ላይ ሆና ባጠብቀኝ ኖሮ እራሴን ሳላስተዳድር ለሷም ሸክም እሆንባት ነበር አሁን ግን ቢያንስ ለልጄ መኖር አያቅተኝምአለ። አንቸ ባበጀሽው ባስተካከልሽው መንገድ ላይ እኔ ከሚስቴና ከልጄጋ ልጓዝበት ነው። አንዳንድ ስተቶች አንዴ ከሆኑ ቡሀላ መስተካከያ የላቸውም ከረፈደ እረፈደ ነው። አብሮ የኖረን ሰው መሸኘት ባንድ ቀን ያውም ባንድ ጀንበር ማጣትን የሚያህል ለሰው ልጅ ምን አለ የሚከብድ ነገር የሚለውን ዘፈን አዳመጥሽው ታቂያለሽ ብሎ ተነስቶ ጥሎኝ ሄደ። . . . . ዛሬ ከሶስት አመት ቡሀላ መኪናዬ ውስጥ ቁጭ ብዬ ባሌን (ዴቭን)እየጠበኩ እዩና ቃል ከግራና ከቀኝ ልጃቸውን ይዘው ከሱፐርማርኬት ሲወጡ አየኋቸውና የመጀመሪያ ፍቅር ጠባሳ ነው  ልተውህ ልርሳህ ብትይው አይረሳም  ልብሽ ላይ ተጣብቆ ይቀራል ያለኝንና  ለሶስት አመታት ከልቤ ያደረኩትን ፍልሚያ ከእውነት መሆኑን  አስታውሼ ብቻዬን  ፈገግ አልኩ ።።። ተ ፈ ፀ መ (ኤልዳና በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ  ልብ አንጠልጣይ ታሪክ ነው። አንዳንዴ ትክክለኛ ህይወታችን የአማረኛ ፊልም ይመስል ሁሌም የተዋበ መጨረሻ የለውም አንዳንዴ ከህይወትጋ እንድንታገል  ሚያስገዱድን ብዙ ሁኔታዎች አሉ ። ከአቅም በላይ ማፍቀር ብቻውን አብሮ ለመኖር በቂ አይደለም ) አብራችሁን ስለነበራች ከልብ እናመሰግናለን በቀጣይ በሌላ ቆንጆ ታሪክ እስከምንገናኝ መልካም ጊዜ❤️ አንብበው ሲጨርሱ Like ማድረግ አይርሱ። https://t.me/Melkam_liboch1

አቀዋለሁ ግን የመጨረሻ አንድ ውሳኔ ማስተላለፍ ስላለብኝ ነው እዚህ አንቺና ዴቭን የጠራኋችሁ አለኝ። በቃ ነፍሴ ባፌ ልትወጣ ደረሰች አባቴ የእስከዛሬው ጥፋቱ አልበቃ ብሎ ጭራሽ ነፍሰ ገዳይ ሆነ የምሰማው የማየው ግራ ገባኝ አባቴ ከዛ በላይ ማውራት ስላልቻለ የዴቭ አባት ቀበል አረገና በቃ አሁን የሚሰጥሽ ወረቀት ላይ ፈርሙ አንቺና ዴቭ ከዛሬ ጀምሮ ባልና ሚስት ትሆናላችሁ አባትሽ ያለውን ነገር በሙሉ በዴቭ ስም አድርጎታል አንቺ እሱን ስታገቢው በሙሉ የጋራ ይሆናል ማለት ነው አለኝ። እኔ በፎፁም አልፈርምም አልኩኝ። አባቴ በጥፊ ሞቅ አደረገኝና ፈጠን ብለሽ ፈርሚ አሁኑኑ ያዘዝኩሽን አድርጊ ገና እድሜ ልኬን ልበሰብስ እንደሆነ እየነገርኩሽ ማን ስለሆንሽ ነው ማትፈርምው አንቺስ ተይው እናትሽና እህትሽ አያሳዝኑሽም እኔ አምስት ሳንቲም ሳላስቀር በሱ ስም አድርጌዋለሁ ምትታዘዙት ላይ በሙሉ ፈርሙ ከዛ እኔ እጄን አሰጣለሁ አለኝ። እጄ እየተንቀጠቀጠ የሰጡኝ ወረቀት ላይ እንዳለ ፈረምኩኝ አባቴ በእንባ ታጅቦ ከተሰናበተኝ ቡሀላ ወደ ውጭ ወጣና ተከትሎኝ ለመጣው ፖሊስ እጁን ሊሰጥ ሲል ሲቭል ፖሊሶች ባንዴ ፍስስ አሉ። አባቴም በፍርድ ቤት የሁለት ሰው ህይወት በማጥፋት ወንጀል የእድሜ ልክ እስራት ተፈረደበት። እኔና ዴቭም ባልና ሚስት ሆንን በተቻለኝ መጠን ሀላፊነትን ለመውሰድና ለማስተዳደር እንድችል እያንዳንዷን ነገር ያለማምደኝ ጀመር ከየተወለድኩበትንና ያደኩበትን ቤት ለእናቴ በስሟ አዞርንላት። ለታናሽ እህቴም መደበቅ ስለማንችል የእናቷን መሞት አረዳናት እናቴ ከጎኗ ሆና ከእናትም በላይ ተንከባከበቻት። እዩ ለመመረቅ ሶስት ወር ሲቀረው ከመሬት ተነስቶ አኮረፈኝ በቃ ዘጋኝ በምንም አይነት ስልክ ደውዬ ላገኘው አልቻልኩም ቢቸግረኝ እናቱገ ሄጄ የሆነውን ነገር እንድትጠይቅልኝ ለመንኳት በሷ ስልክ ደውለን አነሳውና የኔን ድምፅ ሲሰማ ይዘጋዋል ። እኔ ግን ተስፋ ሳልቆርጥ የምርቃቱን ድግስ ከእናቱ እኩል ደገስኩለት እዛው እያደርኩ እየዋልኩ ስራውን ሰራራን ምርቃቱ ቀን ደረሰ እናቱና ዴቭ ወደግንደር ሄደው  ስለነበር እኔ የቤቱን ነገር ጨራርሼ ጠበኳቸው እሱ ግን ምንም ሳያፍር ቤት ሲመጣ ቃልን እጇን ይዟት ገባ ምን እየተካሄደ እንዳለ እንዳለ ግራ ገባኝ እኔ እየሮጥኩ ወደ ጓዳ ገባሁና ለዴቭ ምን እየተፈጠረ እንዳለ ጠየኩት እሱ ዝም አለኝ ። ከሰው መሀል አንዴ ላውራህ ብዬ እጁን ይዥ ወሰድኪትና እዩ ምን እየተካሄደ ነው ጤነኛ አደለህም እንዴ ቃል እዚህ ምን ትሰራለች አልኩት አታሰቢ ቤተሰቦቿም እየመጡ ነው ብሎ ገፍትሮኝ ወጣ ምርቃቱ ተካሄደ ከምሳ ፕሮግራር ቡሀላ እዩ ቆም አለና ሁላችሁንም  አመሰግናለሁ ዛሬ እንግዲ ለምወዳት ልጅ ቀለበት ማሰር እፈልጋለሁ ቃል ነይ ወደመድረክ ብሎ እጁን ዘረጋላት ቀለበቱን አደረገላትና ብድግ ብሎ እንግዲህ በቅርቡም የልጅ አባት ልታደርገኝ ነው ይሄንን ክብር ስለሰጠሽኝ አመሰግንሻለሁ ብሎ ንግግር አደረገ  እናቱን አመስግኖ ንግግሩን ቋጨው ....... ክፍል ሰላሳ አራት #የመጨረሻው ክፍል ከ 200 like👍 á‰ áŠ‹áˆ‹ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ # Like👍 #Share #Add ማድረግ አይርሱ።       â€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œ      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን https://t.me/Melkam_liboch1

💖 ኤልዳና💞   ‍ ​ 💝ልብ አንጠልጣይ የ ፍቅር ታሪክ በመልካም ልቦች የ ቴሌግራም ቻናል ተዘጋጅቶ የቀረበ💝           ክፍል 3⃣3⃣ አባቴ እናቴን ሳይፈታት እኔም እህት እያለችኝ አንድ ቀን እንኳን ሳላያት እዩም የግቢ ትምህርቱን ለማጠናቀቅ 6 ወር እኔም እንደዛው ወራቶች ቀርተውት ዴቭም ካወኩት ቀን አንስቶ አንድ ቀን ፀባዩ ሳይቀየር እናቴም ውስጧ ያለው ንዴት እየበዛ ሲሄድ በግልፅ ፊቷ ላይ መታየት ጀምሮ የእዩም እናት ገበያዋን አጧጡፋ ሱቋን አስፋፍታ ለልጇ ምርቃት ድግሷን እንዴት በሰፊው እንደምትደግስ ከምርቃቱ ቡሀላ ስለሰርጋችን ብቻ እንድናስብ  እየተመካከርን ጊዜያቶች ተቆጠሩ። ሰኞ ክላስ ስላልነበረኝ ቤት ተኝቼ ከእዩጋ በvedio call እያወራን ፂም ማውጣት መጀመሩን አስመልክቶ ሙድ እየያዝኩበት ጠዋት የበላው ምግብ እንዳልተስማማው እየነገረኝ ድንገት ቃል መጣችና vedio ውስጥ ገባች ከጎኑ ቁጭ ስትል የሆነ ሴጣን ካጠገቡ የተቀመጠ ያህል ጋደም ካልኩበት ብድግ አልኩና በቃ ቻው ጊዜያችሁን አልሻም አልኩት እዩ እየተበሳጨ ያምሻል እንዴ ኤልዱ ቃልኮ ስለኔና ስላንቺ አውቃለች እንደውም ማታ ስላንቺ አንስተን ምን ያህል እንደማፈቅርሽ እየነገርኳት ነበር እንደውም የምርቃቴ ቀን ፕሮሚስ ላስርልሽ እንዳሰብኩ ስነግራት በምን መልኩ እንደምናደርገው እያወራን ነበር አንቺ ግን ለሰርፕራይዝ እንኳን አትሆኚም ይኸው አስለፈለፍሽኝ አለኝ። ባንዴ ፊቴ ሁላ በራ አፌን አፍኜ እየሳኩ እሺ በቃ አልሰማሁም አሉ እኔ ስለቀለበት ምንም ማቀው ነገር የለም እሺ በቃ የዛን ቀን እንደማያቅ ሰው እደነግጣለሁ አልኩት እሱ ግን ንዴቱ ስላልበረደለት ኤልዱ ግን ይሄን ቅናትሽን አቁሚ ቅናት ቤት ያፈርሳል ትለኝ ነበር እናቴ ነግሬሻለሁ ብሎ አስጠነቀቀኝና ወሬያችንን አፈቅርሻለሁ አፈቅርሀለሁ ተባባልን ተቋጨ እንዴት ደስ ብሎኝ እንደነበር ፈጣሪ ያውቃል ቀለበቱን ያደረገልኝ ያህል እጄን እያየሁ ፍንድቅድቅ አልኩና ለእናቴ ሄጄ ነገርኳት ያድርግልሽ ልጄ ይገባሻል አለችኝ ደስ እያላት። በነጋታው ዴቭ መጣና ክላስ አደረሰኝ ስወጣ እንድደውልለት ነግሮኝ ተመልሶ ሄደ ። እኔም ስጨርስ ደወልኩለትና እስኪመጣ ካፌ ቁጭ አልኩኝ አንድ የክላሴ ልጅ መጥቶ ካጠገቤ ቁጭ አለ እኔም ሰላምታ አቀረብኩለትና ዝም ብዬ ተቀመጥኩ እየተቅለሰለሰ የሆነ ነገር ላወራሽ ነበር ማለቴ እእእ በቃ ድምፁ ሁላ ተቆራረጠ እኔ ምን ሊያወራኝ ነው ብዬ እያሰብኩ ችግር የለም ሳትፈራ አውራኝ ምን ሆነህ ነው አልኩት። ያው ብዙ ጊዜ ልነግርሽ ብዬ እየፈራሁ ነው ዛሬ ግን ጓደኞቼ አስገድደውኝ ነው ማለት እኔ ካየሁሽ ቀን ጀምሮ አፍቅሬሻለሁ አብረን ብንሆን ደስ ይለኛል አለ። ለምን እንደሆነ አላቅም ሳቄ መጣ እሱ ፊት ላለመዋረደና ላለመሸማቀቅ አስቤ ዋጥ አደረኩትና እኔ ከሀይስኩል ጀምሮ የምወደው ፍቅረኛ አለኝ አሁን ስመረቅ ቀለበት ላስር ነው ይቅርታ እሺ ብዬ ተነስቼ ወጣሁ ደግነቱ ዴቭም ደርሶ ስለነበር ብዙ አልቆምኩም መኪና ውስጥ ከገባሁ ቡሀላ ግን ሳቄን ለቀቀኩት ልጁ ያለኝን ከነ አባባሉ እያስመሰልኩ ነገርኩትና ከዴቭጋ እየተሳሳቅን ቤት ደረስን ። ሌላ ጊዜ ከውጭ ሚመለሰው ዴቭ ተከትሎኝ ቤት ድረስ ገባና ቁጭ አለ እናቴን ልጥራት ቆይ ብዬ ወደክፍሏ ወጣሁ ከሆነች ልጅጋ ተቃቅፋ ተኝታለች እንዴ እማ ማናት ያቀፍሻት ልጅ ካፌ ሳልጨርሰው ዝም እንድል በእጇ ምልክት ሰጠችኝና ቀስ ብላ ተነስታ መጥታ ወደታች ወረድን ምንድነው እማ ማናት አልኳት ቡሀላ ነግርሻለሁ አባትሽ ደውሎልሽ ነበር እንዴ አለችኝ አረ አልደወለልኝም ምነው እማ አልኳት ዴቭ ላንተስ ደውሎልህ ነበር ? አዎ ቅድም ደውሎ ቤት እስክመጣ ጠብቀኝ እንዳትሄድ ብሎኝ ነበር ምነው ችግር አለ እንዴ አላት። አላቅም ግን የሆነ ሰላም ያልሆነ ነገር አለ አለችና እናቴ ቁጭ አለች። እኔ ስለልጅቷ ማንነት አስሬ ስጠይቃት ኤልዱ ደሞ ድርቅ ካልሽ መመለም የለሽም እህትሽ ናት አለችኝ ።ማለት ?? በቃ እህትሽ ናት ኤልዱ አንቺም አታስጨንቂኝ ልቤ ባፌ ልትወጣ ነው አለችና ተመልሳ ወደክፍሏ ወጣች እኔ ምን ልትሰራ መጣች ብዬ ድርቅ ብዬ ቀረሁ። ለምን እንደሆነ ባላውቅም ተናደድኩባት ልክ አባቴን የቀማች ያህል ብቻ ምን ልትሰራ እሷ እዚህ መጣች ግራ ገባኝ። ነገሮች ልክ አደሉም ምንድነው የተፈጠረው አባትሽ በፅሁፍ መልእክት እየላከልኝ ነው አለኝ ዴቭ ። እኔ ምን አቃለሁ አብሬህ አልነበርኩ እንዴ አልኩት እንዲሁ እንደተጨነቅንና ውዝግብ እንዳልን ከምሽቱ ሁለት ሰአት ሆነ እስከዛ ሰአት ድረስ እናቴ ከክፍሏ አልወጣችም። ማታ ሁለት ሰአት ላይ በራችን በጣም በሀይል ተደበደበ እኔ በድንጋጤ ዴቭን ጥብቅ አድርጌ ያዝኩት እናቴ በምን ቅፅበት ከላይ እንደመጣች ሳላውቅ መጣችና ኤልዳና አፍጥኝው አፍጥኝው እላይ ውጭና እህትሽጋ ሁኚ አለችኝ ወደላይ ወጥቼ ሚሆነውን መከታተል ጀመርኩ እህቴ ስሟ ሜሎና ነው ሳያት ትራስ እቅፍ አድርጋ ቁጭ በላ እያየችኝ ነው በጣም ቆንጆ ናት አይኗ ቡኒ ነው ሳያት አሳሳችኝ ላቅፋት ፈልጌ ቀድንጋጤ ውስጥ ስለነበርኩ ማቀፍ አልቻልኩም ወዲያው ፖሊሶች ያለንበትን ክፍል ከፍተው ገቡና እያንዳንዱን ነገር መፈተሽ ጀመሩ ። እናቴ ሁለታችንንም አቅፋን አይዟችሁ ተረጋጉ እሺ ብላ አይናችንን ጨፈነችን ቤቱ ትርምስሥምሱ ወጣ ምን እየፈለጉ እንደሆነ ማናችንም አልገባንም ነበር። ቡሀላ ላይ እናቴ ወደታች ወረደችና ተመልሳ መጣች ፊቷ ቅይይር ብሎ ሰውነቷን መቆጣጠር አቅቷት ሳያት ልቤ መምታት ጀመረ ቀስ ብዬ ወደሷ ተጠጋሁና ምን እንደተፈጠረ ጠየኳት በሹክሹክታ አባትሽ ትልቅ ወንጀል ፈፅሟል ልጄ አሁን እህትሽን አጫውቻት ዴቭ አደራ ዛሬ ከኛጋ እደር ከዚህ ክፍል እንዳትወጣ አለችውና ሌሊቱን ሙሉ አንዳችንም እንቅልፍ ሳይወስደን በጭንቀት ተወጥረን ነጋልን ጠዋት ወደውጪ ስመለከት ፖሊሶች በር ላይ ቆመዋል ። ትንሽ ቆይቶ ተነሽ ኤልዳና ለባብሺ እኛ ቤት እንድንሄድ አባትሽ አዞናል አለኘና ተያይዘን ወጣን ፖሊሶቹ ወዴት እነሰደሆነ ጠየቁን ነገርናቸው አንዱ ፖሊስ ከኋላችን በመኪና ይከታተለን ጀመር እኔና ዴቭ እነሱጋ ስንደርስ አባቱ ሳሎን ቁጭ ብሎ አገኘነው ኑ ተከተሉኝ ብሎ ወደላይ ይዞን ወጣ በር ይሁን ግድግዳ አይለይም ግን ሲነካው ግድግዳው እንደበር ተከፍቶ አባቴ ውስጥ ቁጭ ብሎ አገኘሁት ሚስጥራዊ ክፍላቸው መሆኑንም ተረዳሁ። አባቴን እንዳገኘሁት አቀፍኩትና አባ ምንድነው የተፈጠረው ምን ሆነህ ነው እንደዚህ የገረጣኸው አይንህ ምን ሆኖ ነው ያበጠው ምን ወንጀል ነው የሰራኸው ብዬ በጥያቄ አጣደፍኩት። እሱ ነይ ልጄ ተረጋጊና አጠገቤ ቁጭ በይ ብሎ አስቀመጠኝና እየውልሽ እኔ ካሁን ቡሀላ አብሬሽ የለሁም እኔ እንደሞትኩ ቁጠሪው ሀላፊነቱን ባንቺ ላይ ጥያለሁ ከእንግዲህ ልጅነት የለም ህይወትሽ ውስጥ ቆፍጣና ውሳኔ ያላት ጠንካራ ሴት ሁኝልኝ አለኝ የስንብት ንግግር በሚመስል መልኩ እኔ እየተርበተበትኩ አባ ንገረኝ ለምንድነው እንደዚህ ምትለው አልኩት??? ​​ልጄ እኔ ነፍሰ ገዳይ ሆኛለሁ  እህትሽን ከትምህርት ቤት የማመጣት እኔ ነበርኩ አጋጣሚ ሆኖ ትናትና አስተማሪዎች ድንገተኛ ስብሰባ ስለሚያደርጉ ናና ውሰዳት ብለው 6.30 ላይ ደውለውልኝ ወደትምህርት ቤት ሄድኩና ልጄን ይዤ ወደቤት ተመለስኩ ሾመለሾ ግን እታች ማንም ስላልነበር  ሚስቴን ልጠራት ወደመኝታ ቤቴ ወጣሁ  ከሌላ ወንድጋ እርቃኗን ተቃቅፋ ተኝታ ሳያት ሁለቱንም በሽጉጥ እዛው ደፍቻቸው ልጄን ይዤ ከዛ አካባቢ ጠፋሁና ቤት ይዣት መጣሁ የእናትሽ ግፍ ዋጋዬን ሰጠኝ እኔ ማምለጥ አልችልም

​​አባባሏ ልክ ነው አባቴን ከማውራት ውጭ አማራጭ የለኝመ። አባቴጋ ደውዬ ቤት መምጣት ከቻለ ጠየኩት እሺ እመጣለሁ አለኝ ግን ሳይመጣ አደረና በነጋታው 8 ሰአት አካባቢ መጣ ። ከቤት ይዘኸኝ ውጣ እዚህ ማውራት አልፍልግም ብዬው ይዞኝ ወጣና ዝም ያለ ቦታ ወሰደኝ ገና ማውራት ሳልጀምር እንባ ቀደመኝ። እኔ አሁን ላይ እንደትናቱ ህፃን አደለሁም ብዙ ነገሮችን አስታውላለሁ ሌላ ጊዜ ቢሆን አደለም ደውዬልህ ላግኝህ ብዬህ ይቅርና ስታወራኝ ሁላ ድምፄ ከተቀየረ ከመቼው ቤት እንደመጣህ ሳላውቅ ትመጣ ነበር አሁን ግን ሌላ ልጅ አገኘህ እናቴን በሌላ ሚስት እኔን በሌላ ልጅ ተካህን ባንዴ ቤተሰብህን የከዳኸው ባንዴ ነው የተቀየርክብን አልኩት። እንደሱ አደለም ልጄ ተሳስተሻል እኔ በፍፁም ባንቺ ላይ መቀየር አልችልም ለኔ ጥንካሬዬ ብርታቴ ነሽ አንቺን ካገኘሁ ወዲህ አንድም ቀን ከፍቶኝ አያውቅም ገና ሳያሽ ነው ደስ የሚለኝ ግን በቃ ያደረኩት ነገር እንደሀፍረት ሆኖ ስለተሰማኝ አይንሽን ሳየው ሁላ እየከበደኝ እያፈርኩኝ ነው አለኝ። እሺ እንደሱ ከሆነ ቢያንስ ተፀፅተሀል ማለት ነው ስለዚህ በቃ አንድ ነገር ብቻ ላስቸግርህ እናቴን ፍታልኝ በፈጠረህ በቃ የሚገባንን ስጠንና እናቴን ፍታት አባ አታሳዝንህም ይሄንን መልክ ይዛ ይሄን የመሰለ ሰውነት ይሄን የመሰለ ፀባይ እያላት አንድ ቀን እንደሰው ካፈቀረችው ሰው አጠገብ ከእንቅልፏ ሳትነቃ እድሜዋን ስትጨርስ እእ አንተ ከሚስትህጋ ተቃቅፈህ ስትተኛ እሷ ትራሷን አቅፋ ባሏ ከሌላ ሴት እቅፍ ውስጥ እንደሆነ እያሰበች ስትቀመጥ ምን ያህል ልቧ እንደሚሰበር ግን አስበኸዋል አልኩት። ትኩር ብሎ ተመለከተኝና  ልጄ እንደዚህ መናገር ከቻልሽ በስለሽልኛል ማለት ነው። ልክ ነሽ እናትሽና እኔ መፋታት አለብን ግን ስንፋታ ቢያንስ እሷ ከድርጅቱ የሆነ ድርሻ ልሰጣት ይገባል ያንን ለማድረግ ደሞ እናትሽ አትችልም ታቂያለሽ አንድም ቀን ከሰዎችጋ የቢዝነስ ሾል ሰርታ አታቅም የውጭውን አለም ሳታቀው ምንም አይነት ነገር መስጠት አልችልም አንዱ ተነስቶ ይጥላታል ስለዚህ ቢያንስ አንቺ እስክትመረቂ ድረስ መጠበቅ አለብን አንቺ ስትደርሺ አንችን ተክቼ ከሷጋ እፋታለሁ አይ ምንም አልፈልግም ባዶ እጄን ወጥቼ እራቆታለሁ ካለች ግን መብቷ ነው ዛሬውኑ እፈታታለሁ አለኝ ንግግሩ ደሜን ስለፈላው የውጭውን አለም እንዳታውቅ ያደረካትኮ አንተ ነህ ሚስትህ አድርገህ አግብተህ ሰራተኛ አድርገህ ያስቀረሀት አንተ እራስህ ነህ እድሜዋን ነው ቀረጣጥፈህ የበላኸው አሁን ወደቤቴ መሄድ እፈልጋለሁ ብዬ ተነስቼ ወጣሁ በር ላይ ከደርስኩ ቡሀላ የት ብዬ እንደምሄድ እራሱ ግራ ገባኝ ውጭ እንደቆምኩ ዴቭጋ ደወልኩለት ዴቭ ካለበት ቦታ እዛ እስኪደርስ ድረስ አባቴ ከተቀመጠበት ሳይነሳ ከላይ ሆኖ እየተመለከተኝ ነበር ሁኔታው ግራ አጋባኝ በሆነ በሚወደን ቀሚሳሳልን ስፍስፍ በሚልልን ሰው መጠላት ግን በጣም ሚያስጠላ ነገር ነው አልጋ ሳነጥፍ የተጎዳሁ መስሎት ሚቆጣኝ አባቴ ዛሬ ካጠገቡ ተነስቼ የሆቴል በር ላይ ያን ያህል ሰአት ስገተር እያየ ዝም ሲለኝ ውስጤ የሆነ ባዶነት ተሰማኝ በቃ ክፍት አለኝ ። ዴቭ መጥቶ ከቆመ ቡሀላ ከመቼው አጠገባችን እንደደረሰ ሳላውቅ መጥቶ አጠገባችን ቆመና ብልህ መሆንሽን ያወኩት ዴቭን ለህይወት አጋር አድርገሽ ስትመርጪ ነው በራስሽ ወደቤት ለመመለሾ ብታስቢ ኖሮ ባንቺ ተስፋ እቆርጥ ነበር ግን ስትወድቂ ሚያነሳሽ ስትንገዳገጂ ሚደግፍሽን ሁነኛ ሰው ጠንቅቀሽ አውቀሽዋል በሉ ሂዱ ብሎ ወደመኪናው ገባ እኔም የዴቭ መኪና ውስጥ ገብቼ እዩጋ ደወልኩና ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩበት አንተ ከሄድክ ቡሀላ ትንሹም ትልቁም ነገር እያስከፋኝ ነው ትንሽ እንኳን ለኔ ስሜት ካለህ ምናለ እዚህ መተህ እኔ እየከፈልኩልህ ብትማር ምናለ ለፍቅራችን ትንሽ መስዋትነትን ብትከፍል አልኩት እሱ ነገሩን ቀለል አድርጎ እኔን ይክፋኝ አይዞሽ የኔ ፍቅር ትንሽ ጊዜኮ ነው የቀረን ምን አቆራረጠኝ እእ ደሞ ክረምትን እየመጣሁ አደል እንዴአሁንኮ እንደጨረስኩ ቁጠሪው ትንሽ ጊዜ ብሎ አፅናናኝና ስልኩ ተዘጋ ክፍል ሰላሳ ሶስት ከ160like👍  በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ #Like 👍 #share #Add ማድረግ አይርሱ።       â€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œ      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን! https://t.me/Melkam_liboch1

​​አባባሏ ልክ ነው አባቴን ከማውራት ውጭ አማራጭ የለኝመ። አባቴጋ ደውዬ ቤት መምጣት ከቻለ ጠየኩት እሺ እመጣለሁ አለኝ ግን ሳይመጣ አደረና በነጋታው 8 ሰአት አካባቢ መጣ ። ከቤት ይዘኸኝ ውጣ እዚህ ማውራት አልፍልግም ብዬው ይዞኝ ወጣና ዝም ያለ ቦታ ወሰደኝ ገና ማውራት ሳልጀምር እንባ ቀደመኝ። እኔ አሁን ላይ እንደትናቱ ህፃን አደለሁም ብዙ ነገሮችን አስታውላለሁ ሌላ ጊዜ ቢሆን አደለም ደውዬልህ ላግኝህ ብዬህ ይቅርና ስታወራኝ ሁላ ድምፄ ከተቀየረ ከመቼው ቤት እንደመጣህ ሳላውቅ ትመጣ ነበር አሁን ግን ሌላ ልጅ አገኘህ እናቴን በሌላ ሚስት እኔን በሌላ ልጅ ተካህን ባንዴ ቤተሰብህን የከዳኸው ባንዴ ነው የተቀየርክብን አልኩት። እንደሱ አደለም ልጄ ተሳስተሻል እኔ በፍፁም ባንቺ ላይ መቀየር አልችልም ለኔ ጥንካሬዬ ብርታቴ ነሽ አንቺን ካገኘሁ ወዲህ አንድም ቀን ከፍቶኝ አያውቅም ገና ሳያሽ ነው ደስ የሚለኝ ግን በቃ ያደረኩት ነገር እንደሀፍረት ሆኖ ስለተሰማኝ አይንሽን ሳየው ሁላ እየከበደኝ እያፈርኩኝ ነው አለኝ። እሺ እንደሱ ከሆነ ቢያንስ ተፀፅተሀል ማለት ነው ስለዚህ በቃ አንድ ነገር ብቻ ላስቸግርህ እናቴን ፍታልኝ በፈጠረህ በቃ የሚገባንን ስጠንና እናቴን ፍታት አባ አታሳዝንህም ይሄንን መልክ ይዛ ይሄን የመሰለ ሰውነት ይሄን የመሰለ ፀባይ እያላት አንድ ቀን እንደሰው ካፈቀረችው ሰው አጠገብ ከእንቅልፏ ሳትነቃ እድሜዋን ስትጨርስ እእ አንተ ከሚስትህጋ ተቃቅፈህ ስትተኛ እሷ ትራሷን አቅፋ ባሏ ከሌላ ሴት እቅፍ ውስጥ እንደሆነ እያሰበች ስትቀመጥ ምን ያህል ልቧ እንደሚሰበር ግን አስበኸዋል አልኩት። ትኩር ብሎ ተመለከተኝና  ልጄ እንደዚህ መናገር ከቻልሽ በስለሽልኛል ማለት ነው። ልክ ነሽ እናትሽና እኔ መፋታት አለብን ግን ስንፋታ ቢያንስ እሷ ከድርጅቱ የሆነ ድርሻ ልሰጣት ይገባል ያንን ለማድረግ ደሞ እናትሽ አትችልም ታቂያለሽ አንድም ቀን ከሰዎችጋ የቢዝነስ ሾል ሰርታ አታቅም የውጭውን አለም ሳታቀው ምንም አይነት ነገር መስጠት አልችልም አንዱ ተነስቶ ይጥላታል ስለዚህ ቢያንስ አንቺ እስክትመረቂ ድረስ መጠበቅ አለብን አንቺ ስትደርሺ አንችን ተክቼ ከሷጋ እፋታለሁ አይ ምንም አልፈልግም ባዶ እጄን ወጥቼ እራቆታለሁ ካለች ግን መብቷ ነው ዛሬውኑ እፈታታለሁ አለኝ ንግግሩ ደሜን ስለፈላው የውጭውን አለም እንዳታውቅ ያደረካትኮ አንተ ነህ ሚስትህ አድርገህ አግብተህ ሰራተኛ አድርገህ ያስቀረሀት አንተ እራስህ ነህ እድሜዋን ነው ቀረጣጥፈህ የበላኸው አሁን ወደቤቴ መሄድ እፈልጋለሁ ብዬ ተነስቼ ወጣሁ በር ላይ ከደርስኩ ቡሀላ የት ብዬ እንደምሄድ እራሱ ግራ ገባኝ ውጭ እንደቆምኩ ዴቭጋ ደወልኩለት ዴቭ ካለበት ቦታ እዛ እስኪደርስ ድረስ አባቴ ከተቀመጠበት ሳይነሳ ከላይ ሆኖ እየተመለከተኝ ነበር ሁኔታው ግራ አጋባኝ በሆነ በሚወደን ቀሚሳሳልን ስፍስፍ በሚልልን ሰው መጠላት ግን በጣም ሚያስጠላ ነገር ነው አልጋ ሳነጥፍ የተጎዳሁ መስሎት ሚቆጣኝ አባቴ ዛሬ ካጠገቡ ተነስቼ የሆቴል በር ላይ ያን ያህል ሰአት ስገተር እያየ ዝም ሲለኝ ውስጤ የሆነ ባዶነት ተሰማኝ በቃ ክፍት አለኝ ። ዴቭ መጥቶ ከቆመ ቡሀላ ከመቼው አጠገባችን እንደደረሰ ሳላውቅ መጥቶ አጠገባችን ቆመና ብልህ መሆንሽን ያወኩት ዴቭን ለህይወት አጋር አድርገሽ ስትመርጪ ነው በራስሽ ወደቤት ለመመለሾ ብታስቢ ኖሮ ባንቺ ተስፋ እቆርጥ ነበር ግን ስትወድቂ ሚያነሳሽ ስትንገዳገጂ ሚደግፍሽን ሁነኛ ሰው ጠንቅቀሽ አውቀሽዋል በሉ ሂዱ ብሎ ወደመኪናው ገባ እኔም የዴቭ መኪና ውስጥ ገብቼ እዩጋ ደወልኩና ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩበት አንተ ከሄድክ ቡሀላ ትንሹም ትልቁም ነገር እያስከፋኝ ነው ትንሽ እንኳን ለኔ ስሜት ካለህ ምናለ እዚህ መተህ እኔ እየከፈልኩልህ ብትማር ምናለ ለፍቅራችን ትንሽ መስዋትነትን ብትከፍል አልኩት እሱ ነገሩን ቀለል አድርጎ እኔን ይክፋኝ አይዞሽ የኔ ፍቅር ትንሽ ጊዜኮ ነው የቀረን ምን አቆራረጠኝ እእ ደሞ ክረምትን እየመጣሁ አደል እንዴአሁንኮ እንደጨረስኩ ቁጠሪው ትንሽ ጊዜ ብሎ አፅናናኝና ስልኩ ተዘጋ ክፍል ሰላሳ ሶስት ከ160like👍  በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ #Like 👍 #share #Add ማድረግ አይርሱ።       â€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œ      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን! https://t.me/Melkam_liboch1

💖 ኤልዳና 💞  ‍ ​ 💝ልብ አንጠልጣይ የ ፍቅር ታሪክ በመልካም ልቦች የ ቴሌግራም ቻናል ተዘጋጅቶ የቀረበ💝           ክፍል  3⃣2⃣ ሳንገናኝ አንድ ሳምንት ቆየን በቃ የመጨረሻ የመከፋት ስሜት ውስጥ ገብቼ ነበር። ከሳምንት ቡሀላ ዴቭ መጥቶ ይዞኝ ወጣና ከእዩጋ አገናኘኝ ችግራችሁን ተነጋግራችሁ ፍቱ እያንዳንዷ ክፍተት ፍቅራችሁን ታደበዝዛለች አለኝ። እኔ ካፌ ክፉ ቃል ማውጣት ስላልፈለኩ ዝም አልኩኝ እዩ ማውራት ጀመረ። ቆይ የምር እኔን በቃል ጠርጥረሽኝ ነው አንቺን በሷ ምተካሽ መስሎሽ ነው አለኝ። ዝምም አልኩት: ኤልዱ እኔ ካስፈለገ በምወዳት እናቴ እምልልሻለሁ አንቺን በማንም አልተካሽም አንቺ ህይወቴ ውስጥ ያለሽው ትልቋ መሰሬቴ ነሽ ለኔ ብቻ ሳይሆን ለናቴም ደስታ ነሽ ግን በቃ ቃልን ግዴታ ማውራት ስለነበረብኝ ነው ያወራኋት ብሎ ስልኩን ከፍቶ ፎቶ አሳየኝ ቃል እራሷን ለማጥፋት ሙከራ አድርጋ እንደነበር የሚያሳይ ፎቶ አሳየኝና እኔ አላወራሽም ብያት ፊት ነስቻት ነበር እሷ ግን እራሷን ልታጠፋ ሞከረች ድጋሜ ማላወራት ምርቃት ምዘጋት ከሆነ እራሷን እንደምታጠፋ እያለቀሰች ስትለምነኝ እኔም ሀገሩን ስለማታቀው ከቤተሰብ መነጠል ብቸኝነት ስለሚፈጥርባት ነገሮች ሲደራረቡ ሆድ ከሚብሳት ብዬ ነው የቀረብኳት አንቺ እንደምታስቢው በሌላ ነገር አደለም ደሞ በጣም ታማሚ ሆናለች እዛ ከሄድን ቡሀላ በየጊዜው ነው እራሷን ምትስተው  ስለምታሳዝነኝ ነው አለኝ። እኔ ውስጤን በምንም ቃላት ማስተካከል አልቻልኩም ክፍት እንዳለኝ ስለነበር በድጋሜ ዝምታን መረጥኩ እሱ የሆነውን ያልሆነውን ወሬ እየፈጠረ ሊያስቀኝ ሊያዝናናኝ ሲሞክር አልቻልኩም ያ በከፋኝ ሰአት ከጎንደር አዲስ አበባ ለኔ ብሎ መምጣቱን አሰብኩና ታረኩት። አብረን እናምሽ በቃ ዴቭ ቤት እንሂድና እዛ እንደር እስክሄድ አብረን እንሁን አለኝ እሺ ብዬ ተያይዘን ከዴቭጋ ሶስታችንም ሄድን ዴቭ አድርሶን ሊሄድ ሲል እዩ አብሮን እንዲያድር ሌሊቱን ሙሉ ስንፍታታ ማደር እንደምችል ነገረውና ወደ ውስጥ ገባን ዴቭ ወጥቶ መጠጥ ይዞ መጣ መሬት ላይ ክብ ሰርተን ከተቀመጥን ቡሀላ ጨዋታ እየተጫወትን አንዴ ሚስጥር መናገር አንዴ መታዘዝ (ተነስቶ መጨፍር: መዝፈን: ) ብቻ እንዲሁ ሆዳችን እስኪቆስል ስንስቅ አመሸን ዴቭ ተነሳና ሶፋ ላይ ተኛ እኔና እዩ ቁጭ ብለን አሰብከው ግን ወደፊት እኔና አንተ የራሳችን ቤት ኖሮን አብረን ውለን አብረን አድረን በቃ ሳንለያይ ሁሌ እየተያየን በፍቅር ብዙ አመት ስንኖር አልኩት እዩ ፈገግ ብሎ አቅፎ እየሳመኝ ትንሽ ግዜ ብቻ ነው የቀረን ታገሽ አለኝ። ሁለታችንም እንቅልፋችን ስላልመጣ መተኛት አልቻልንም ዴብን መበጥበጥ ጀመርን ትራስ እየወረወርን አላስተኛ አልነው ፊቱን አዙሮ ተኝቶ እረፉ ሊለን ሲዞር አይኑ ቀልቷል ደንግጬ ትኩር ብዬ ሳየው አታይም እንዴ እንቅልፌ በጣም ስለመጣኮ አይኔ ሁላ ቀለ አለ ነገሩ ባይዋጥልኝም ዝም አልኩ። ጠዋት አብረን ቁርስ በላንና እዩ እናትጋ ሄድን ተአምራዊ ሴት ማለት እሷ ናት በቃ በየቀኑ ታስገርመኛለች ዴቭን ደሞ እንዴት እንደምተወደው: ሱቋ ስንሄድ ለመጣው ሰው ሁላ ፊቷ ፍክት እንዳለ ነው እጇ ስስት አያቅም ትጎጃለሽኮ ለምን እንደዚህ ትመዝኛለሽ ስትባል ከብዛት አገኘዋለሁ ትላለች። በቅርቡ የከተማዋ ባለሀብት አንቺ ነሽ እያልኳት ተጨዋወትንና እኔና ዴቭ እናቴጋ ሄድን እዩ እናቱን እያገዛት እዛው ቀረ። ሌላ ሳምንታቶች ተቆጠሩ እኔና እናቱ እዩ  ከመሄዱ በፊት ተለቅ ያለ ቆንጆ ቤት ተከራይተን ሰርፕራይዝ ለማድረግ አሰብንና እዛው ከስራ ቦታዋ ጀርባ ባለ አንድ መኝታ ቤት አገኘንና ያጠራቀመችውን ገንዘብ እንዳለ እቃ ላይ አዋለችው እኔም ያቅሜን አገዝኳት ቀኑን ሙሉ እዩ ሱቅ ውስጥ ሲሸጥ ዋለ እኛ ደሞ ቤት ስንቀይር ዋልን ማታ ላይ አስተካክለን ለመጨረስ ስላልቻልን እዩን ከሱቅ ቀጥታ ይዤው ዴቭ ወደተከራየው ቤት ሄድኩና እዛው አደርን ጠዋት እሱን ሱቅ አድርሰን እኔ ወደ አዲሱ ቤት አመራሁ እናቱ ቀድማኝ ደርሳ እያዘገጃጀች ነበር አጋዦች ጠርተን ቤቱን አሰማመርነው መኝታ ቤቱንም ሳሎኑንም ፏፏ አደረግንና ቤቱን ቄጤማ ጎዝጉዘን ቡና አቀራርበን  ስንጨርስ እዩን ከሱቅ ይዤው ለመምጣት ሄድኩኝ ማታ ሁለት ሰአት ላይ ሱቃችንን ዘግተን አንድ ምኔድበት ቦታ አለን ብዬ ይዠው ሄድኩ። እናቱን ውስጥ ቁጭ ብላ ሲያያት ግራ ገብቶት ወደ ውስጥ ገባ  ሲገባ የራሱ ሽልማቶችና ፎቶዎቹ ውስጥ ተሰቃቅለው ሲያያቸው ግራ ገብቶት ነበር ነገሩን ስንነግረው በደስታ አለቀሰ እንባውን ማቆም እስኪያቅተው ድረስ እያቀፈን ደስታውን ገለፀለን ቡና ጠጥተን እስቅንጨርስ ማመን አቅቶት አስሬ ግን ከምራችሁ ነዋ እያለ ሲጠይቀን ነበር። ቡናው ሲያልቅ ዛሬ የቤት መመረቂያ ሁላችንም እዚሁ ነው ምናድረው ተባለ እዩ እጄን ያዘኝና አየር ወስደን እንምጣ ብሎ በዛ በማታ ይዞኝ ወደ ውጭ ወጣ ጥብቅ አድርጎ አቅፎኝ ስለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ የወደፊት ህልሜን በሙሉ ቀድመሽ እያሳየሽኝ ነው አንቺ ለኔ በረከቴ ነሽ ህይወቴ ውስጥ ከገባሽ ቀን አንስቶ በየቀኑ ጥሩ ነገሮች ወደኔ ይመጣሉ ከምስጋና በላይ ላንቺ ምንም ላደርግልሽ አልችልም የእናቴ ምርቃት ነው አንቺን የሰጠኝ ብሎ አለቀሰ አብረው እያለቀስኩ እንባውን ጠረኩለት ትንሽ እስክንረጋጋ ሁለታችንም ጨረቃዋ ላይ አፍጥጠን ውጭ ቁጭ አልንና ተመልሰን ገባን። ነገሮች አሪፍ እየሄዱ ነው አሁን ጥሩ ላይ ነኝ ብዬ ሳስብ የእዩ መሄጃ ቀን ደረሰና ተመልሶ ወደግቢ ሄደ። በዛን ሰአት ላይ ከእናቴጋ ቁጭ ብዬ አወራሁ ለምን ካባቴጋ አትፋችም ከዚህ በላይ ምን እስከሚመጣብሽ ነው ምትጠብቂው ሴት ልጅ ለውሳኔ ከዘገየች ዋጋ ትከፍላለች አልኳት። እናቴ ፈገግ ብላ አየችኝና ልጄ እየበሰልሽ ነው ግን እኔ አባትሽን መፍታት አልችልም ለምን??! ምክንያቴን መናገር አልፈልግም ግን ልጄ አሁን ሳይሽ እያደግሽልኝ እየደረሽልኝ ጓደኛ እየሆንሽኝ ስለሆነ ካንቺ መደበቅ አልችልም እኔና አባትሽ ባለትዳሮች ሆነን ለብዙ አመታቶች ብንቆይም ይሄ ሁላ የምታይው ሀብት ላይ እኔ ምንም ድርሻ የለኝም እኔ አባትሽን ከፈታሁት ባዶ እጃችንን ነው ምንቀረው አለችኝ። እ እማ ምንድነው ምታወሪው ሚስቱኮ ነሽ ሙሉ መብት አለሽ እንጂ አልኳት። አይ የለኝም ከመጋባታችን በፊት በዚህ ተስማምቼ ነው የገባሁት  አለችኝ ። ቤተሰቦቼ በላዬ ላይ ፊልም ሲሰሊ መኖራቸው አስገረመኝ እውነት እናቴ ለገንዘብ ብላ እራሷን ሸጣ እየኖረች ነው ወይስ ለኔ መስዋት እየከፈለች ለነገሩኮ እኔ የመጣሁት ቡሀላ ከመጀመሪያው ምን አስባ ነው ያገባችው:: በቃ አንዴ መጥፎ ነገር ወደኛ መምጣት ከጀመረ ማቆሚያ የለውም ያለሁበት ሁኔታ አስገረመኝ ችግርን ስለማላቀው አካብጄው ነው ወይስ ነገሩ የምር ከብዶ አላቅም ብቻ ግን ሲከፋኝ መሸሸጊያዬ ወይ ዴቭ ነው አለበለዚያ የእዩ እናትጋ ሄዶ ቁጭ ማለት ከሁለቱ ውጭ አማራጭ የለኝም ። እንደለመድኩት ሄድኩና እንደከፋኝና የተፈጠረውን በሙሉ ነገርኳት አባትሽን አውሪው እናትሽን ነፃ አውጫት አለችኝ።

እሷም ስታየን እንባ እየቀደማት ፈጣሪ ለኔ ያደረጋችሁት በእጥፉ ምትደሰቱበትን ነገር ያሳካላችሉ ብላ መረቀችን ደንበኛ አያያዟ ይለያል ትንሽ ተቀምጠን ካወራናት ቡሀላ ተሰናብተናት ወደቤታችን ሄዴ ቤቴ በር ላይ ስደርስ ወደውስጥ ለመግባት ፈራሁ ቤቱ ሁላ አስጠላኝ ዴቭ መኪናውን በር ላይ አቆመና ወክ እያደረግን ወደ አስፋልት ተመለስን ዴቭ በመሀል እኔ ምልሽ ኤልዱ አለኝ ወዬ ዴቭ እንዴት ነው ግን የወደድነውን ሰው የኛ ብቻ ማድረግ ምንችለው አሁን አሁንኮ የተዋደደ ሰው አብሮ እንዳይኖር የተፃፈ ህግ ያለ እየመሰለኝ ነው አንዱ አንዱን ሲውድ እሱ ሌላ ይወዳል ብቻ ፍቅር ሰንሰለት እየሆነብኝ ነው አለኝ። አይ ዴቭ ከኔ በተሻለ ህይወትን አንተ ትረዳታለህ ብዬ አስባለሁ እኔማ ምኑን አውቄ ግን ፀሎት ትልቁ መፍትሄ ይመስለኛል አልኩት። እኔ ግን ፀሎት በራሱ መፍትሄ ነው ብዬ አላምንም!! እንዴት ??? ለምሳሌ እኔ አንቺን ባፈቅርሽ አንቺን እንዲሰጠኝ እለምነዋለሁ አንቺ ደሞ እዩን ስለምታፈቅሪው እዩን ስጠኝ ብለሽ ትለምኚዋለሽ ቃልም በተራዋ እዩን ስለምታፈቅረው የኔ አድርግልኝ ብላ ትማፀናለች ስለዚህ ለማንኛችን ቢሰጥ ነው ትክክል ሚሆነው አለኝ። ዝም አልኩት ። ወክ አድርገን ትንሽ እየደከመኝ ሲመጣ ወደቤቴ አስገብቶኝ እሱ ሄደ። እንደቀልድ የእዩ መምጫ ደረሰና በድጋሜ ወደአዲስ አበባ ተመለሰ ዴቭ ቃሉን ጠብቆ ቤት ተከራይቶ ነበር እዩም እንደመጣ ሻንጣውን እዛ አሳረፈና ወደናቱጋ ሄደ ሲያያት እጅግ ደስ አለው ቀድመሽኝ ሚሊየነር ልትሆኚ ነው ብሎ ቀለደባት። እረፍቱን ሁለታችንም አብረን ለማሳለፍ አቅደን ነበር ግን ገና በመጣ በሁለተኛው ቀን እናቱጋ ሱቅ ቁጭ ብለን አመሸንና ዴቭ መጥቶ ወደተከራየበት ቤት ሊያደርሰን እየሄድን እዩ ስልክ ተደወለለትና አነስቶ አወራ ወዲያው ቃል እንደሆነች አወኩኝ ። ስልኩን ሲዘጋው አንድ ቦታ ደርሼ ልምጣ አንቺ ከዴቭጋ ሆነሽ ጠብቂኝ አለ። የት ልትሄድ ነው ብዬ ጠየኩት ምንም ሳያፍር ቃልን ላገኛት ነው እሷ ናት የደወለችልኝ አለኝ። ካፌ ምንም ቃል ሳይወጣ ችግር የለውም ደርሰህ ና አልኩትና ከመኪናው ወረደ እሱ ዞር ሲልልኝ እንባዬን ለቀቀኩት ለዴቭ እየተንሰቀሰኩ አየሀ የሆነ ነገር ጀምሮ ነው ከሷጋ ለኔ ስሜት ምንም ሳይጨነቅ ጭራሽ ሊያገኛት ሄደ አሁን ወደቤት አድርሰኝ አልኩት አደረሰኝና ተከትሎኝ ወደቤት ገባ ። እኔ ወደክፍሌ ገብቼ ክፍሌን ቆለፍኩት ለእዩም አባቴ ቤት ስለሆነ ስልክ ማውራትም ከቤት መውጣትም እንደማልችል ነገርኩትና ስልኬን አጠፋሁት.... ክፍል ሰላሳ ሁለት ከ160like በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍 ማድረግ አይርሱ።       â€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œ      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን! https://t.me/Melkam_liboch1

💖ኤልዳና 💝ልብ አንጠልጣይ የ ፍቅር ታሪክ በመልካም ልቦች የ ቴሌግራም ቻናል ተዘጋጅቶ የቀረበ💝           ክፍል 3⃣1⃣ አሁን ማይገቡሽ ብዙ ነገሮች አሉ እኔና እናትሽ መፋታት አንችልም አሁን ከዚህ በላይ ማውራት አልችልም ብቻ ይቅር በይኝ ብሎ አቀፈኝ ከአንገት በላይ ሆኜ አቀፍኩትና ዝም አልኩት። ተነስቶ ከክፍሌ ወጣ የኔና የሱም ነገር ከአንገት በላይ እንደሆነ እናቴን ባየኋት ቁጥር ባሏ ከሌላ ሴትጋ እያደረ ሲመጣ የሚሰማትን ህመም እያሰብኩ እንደተሰቃየሁ ክረምት ገባና እዩ ወደአዲስ አበባ ለእረፍት መጣ ። 12 ከተፈተንኩ ቡሀላ ህይወቴ ውስጥ አንድ አመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ብዙ ውጥቅጥ አሳለፍኩ አብዛኛው የህይወቴ ክፍል መከፋት ሆነ ።። ቢሆንም ግን እዩ መጥቶ አጠገቤ ሲሆን ነገሮች ባንዴ የተስተካከሉ መሾመር የያዙ ያህል በጣም ደስ ይለኛል። እዩ ወደዚህ ከተመለሰ ቡሀላ ተደጋጋሚ ጊዜ አብረን ሆነን ቃል ስትደውልለት እና አጠገቤ ሲያወራት አስተውለዋለሁ እኔም ስሜቱን ላለመጋፋት ዝም አልኩት እሱም ነገሩን ቀለል አድርጎ ለማለፍ ይሞክራል። ክረምትን በሱ ተፅናንቼ አሪፍ ጊዜ አሳልፈን ካሁን ቡሀላ አባቴ በኔ ህይወት ውስጥ ስለማያገባው ልክ እንደተመረክ እንጋባለን ብዬው ተመልሶ ወደጎንደር በረረ። እዩ ወደጎንደር ከበረረ ቡሀላ ዴቭ አንድ ሀሳብ አቀረበልኝ ለምን ሰርፕራይዝ አናደርገውም ለእናቱ ለምን ሱቅ አንከራይላትም ጎበዝ ሴት ከሆነች በትንሽ ጊዜ ውስጥ እራሷን ትቀይራለች አለኝ:: በእዩ እናት በጣም ስለምተማመንባት እሺ አልኩትና እሷ ሳታቅ እነሱ ሰፈር ሱቅ ማፈላለግ ጀመርን በአምስት ሺ ብር የሰፈራቸው መግቢያ ላይ ሱቅ አገኘን እኔና ዴቭ ሟር አድርገን ኪራዩን ከፈልንላትና የሱቁን አትክልትና ፍራፍሬ በሙሉ እሱ ሸፍኖላት ሙሉ በሙሉ ካዘጋጀንላት ቡሀላ እሁድ ቀን ደውዬላት ሰፈር እየመጣሁ እንደሆነና ወጥታ አስፋልት እንድትቀበለኝ ነገርኳት እኔና ዴቭ ሱቅ ውስጥ ሆነን እየጠበቅናት ነበር እንደደረሰች ስትነግረኝ ሱቁጋ እንድትመጣ እየጠቆምኳት ደረሰች እኔ ውስጥ ስለነበርኩ እንደደረሰች ብድግ አልኩና ምን ልስጥሽ አልኳት ዴቭ ከኋላዬ ቁጭ ብሎ ለእዩ በvediocall ደውሎ የሚሆነውን በሙሉ እያሳየው ነበር። ስትደርስ ከት ብላ ሳቀችና አይ ያለው ማማሩ ደሞ እዚህ ሱቅ ከፈትሽ አለችኝ። ያው ምን ታደርጊዋለሽ ለመመረቂያ እንዲሆነኝ በይ የሆነ ነገር ግዥኝ ብዬ ድርቅ አልኩ ምንም ብር ሳልይዝ ነው የወጣሁት ታቂ የሌ ሰሞኑን ሾል ቀዝቅዞ ቤት እንደምውል ባይሆን ማታ እመለሳለሁ አለችኝ። ወደ ውስጥ እንድትገባ ከጋበዝኳት ቡሀላ ሱቁ ያንቺ ነው በትንሽ ጊዜ ውስጥ እንደምትቀየሪበት አቃለሁ አልኳት። መጀመሪያ ላይ ስላላመነችኝ እየሳቀች ዝም ብትለኝም ነገሩ እውነት መሆኑ ሲገባት ግን ስቅስቅ ብላ እያለቀሰች የምስጋናና የምርቃት መአት አወረደችብኝ ዴቭ ጥጉን ይዞ በፈገግታ ይመለከተናል። ሁለታችንም ተቃቅፈን ዴቭ ስልኩን ወደኛ አዙሮ እዩን አውሩት አለን አወራነው እሱም በደስታ እያነባ ስላደረግንለት ነገር በሙሉ እያመሰገነን ነበር እኔም የዴቭም እርዳታ እንደተጨመረበትና ሀሳቡ የኔ ብቻ እንዳልሆነ ነገርኳቸውና ስልኩ ተቋረጠ። ማታ ላይ እዩ ደውሎ ለረጅም ሰአት አወራኝ በህይወት ዘመኑ በሙሉ ሚመኘውን ነገር እንዳደረኩለት እና የልቡን ምሞላለት አይነት ሴት እንደሆንኩ ሲነግረኝ ከልቤ ደስታ ተሰማኝ ። እዚህ ምድር ላይ እንደአባቴ አይነት ከሀዲ ና እንደ እዩ አይነት ታማኝ ወንድ ነው የሞላው ብቻ ፈጣሪ መርቆ ይስጥ እንጂ ከባድ ብዬ አሰብኩ ብቻ ህይወት ቀጠለች አባቴም ከበፊቱ የበለጠ ቶሎ ቶሎ ቤት መምጣቱን ተያያዘው ዴቭም ቢሆን አንድ ቀን ፊቱን ሳያጠቁርብኝ: ስበሳጭበትም: ስናደድበትም: ስደሰትም :ስከፋም ሁሌም አብሮኝ ነው። በሌላ በኩል እዩ ሁሌ ማታ ማታ ስልክ እያወራን ቃል መጣች ቆይ እደውልልሻለሁ እያለ ይዘጋብኝ ጀመር ። ነገሩ ምንም አላምርሽ ሲለኝ ቃልጋ ደወልኩና እዩና እኔ ጓደኛሞች እንደሆንን ፍቅራችን ከስንተኛ ክፍል ጀምሮ እንደሆነ ሁሉንም እስከዛሬ ሚስጥር አድርገን የያዝነውን ነገር አፍረጥርጬ ነገርኳት እሷ ግን ከት ብላ ሳቀችና እንኳን እቺን ብዙም አቃለሁ ገና ዘጠና ክፍል እያለን እንዴት እንደምትተያዩ አይቻችሁ ነበር የዛኔ ነው እንደምትዋደዱ ያወኩት ግን ካንቺ ፍቅር የኔ ይበልጣል ካንቺ ፀሎትም የኔ ይሰማል ምናለች በይኝ እዩ የኔ ነው የመጀመሪያ ሚዜ አድርጌሽ ነው ምምሸረው አለችኝ። አነጋገሯ ደሜን ስላፈላው እሱኮ ደሀ ነው ላንቺ አይመጥንሽም ምን ያህል ሰው እንደምትንቂና እንደምትመርጪ አውቅሻለሁ አልኳት። ኮራ ብላ ድህነት ቆሻሻ ነው ታጥቦ ይጠራል ብላኝ ስልኩን ዘጋችው። ከሷጋ ካወራሁ ቡሀላ ማታ ላይ  ለዴቭ ደውዬ ቤተክርስቲያን እንሂድ ብዬ ጠየኩት መጥቶ ወሰደኝ ። ዝም ብዬ ለረጅም ሰአት ቁጭ ካልኩ ቡሀላ ፈጣሪ ሆይ አውቃለሁ አንተን አላደረክልኝም ብዬ መውቀስ አልችልም ግን ምናልባት እሷ ከኔ በላይ ፀልያ ይሆን ምናልባት የሷ ፀሎት ይሰማ ይሆን ምናልባት እሷም እሱን ስጠኝ ብላ አስጨንቃህ እኔም እሱን ስጠኝ ብዬ አስጨንቄህ ይሆን በቃ አንተ የፈቀድከውን አድርግልኝ ልቤን ከስብራት ጠብቅልኝ ነገሮች መስመራቸውን ቢስቱ እንኳን ምፅናናበትን ምችልበትን ልብ ስጠኝ ብዬ ፀለይኩ። ዞር ስል ዴቭ በሀሳብ ሂድት ብሎ መሬት መሬቱን እያያ ሳየው አሳዘነኝ ይሄ ልጅ ግን ምናልባት ከኔ ፍቅር የያዘው ከልቡ ይሆን እኔ ለእዩ ያለኝን ስሜት ያክል ለኔ ይኖረው ይሆን እንዴ አልኩኝ ለራሴ። ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ሄድኩና ከጎኑ ቁጭ አልኩ ምን ብለህ እየፀለይክ እንዲህ በሀሳብ የሄድከው አልኩት ምን ተብሎ እንደሚፀለይ ስለማላቅ ፀሎት አስተምረኝ እያልኩት ነበር አለኝ። ፈጣሪ የልባችንን መች አጣው የልቤን መሻት ፈፅምልኝ በለው አልኩት። ትኩር ብሎ ተመለከተኝና ለምሳሌ በልቤ አንቺ የኔ እንድትሆኚ ብፈልግና እሷን ስጠኝ ብዬ ፀልዬ አንቺና እዩኤል ስለምትዋደዱ መጨረሻ ላይ ከሱጋ ስትሆኚ ለምን ለኔ አልሰጠኸኝም ብዬ እንዳማርረው ነው አለኝ። እእ ልብህ ውስጥ ያለው ይሄ ብቻ ነው እንዴ ???? አይ አደለም አንቺ በልብሽ ምን እያሰብሽ ነው እስቲ ንገሪኝ አለ። እኔ ብዙ ነገር እያሰብኩ ነው ለምሳሌ እናቴ ካባቴጋ ተለያይታ ሌላ ሰው አፍቅራ እሱም አፍቅሯት በኖረች ብዬ እየተመኘሁ ነው በተጨማሪም እዩን ከሁሉም ሴቶች ለይቶ የኔ ባደረገውም ብዬም እየፀለይኩ ነው አልኩት። አይዞሽ በቅርቡ ለእረፍት ይመጣል አብራችሁ ትሆናላችሁ እሱ ከመምጣቱ በፊት ቤት ቸከራይቼ እወጣና ክረምትን ጨርሶ እስኪመለስ እኔ ቤት መሆን ትችላላችሁ አለኝ። ዴቭ ማለቴ ይቅርታ አድርግልኝና አንዳንዴ ደግነትህና አስተሳሰብህ በጣም ሲበዛብኝ የምርህን መሆኑ እራሱ ያጠራጥረኛል እንዴት ነው በዚህ ልክ ልብህ ንፁህ ሊሆን የቻለው አልኩትና ትከሻው ላይ ደገፍ አልኩ::መልሱን በዝምታ ገለፀልኝ። ወደቤት ከመመለሳችን በፊት እዩ እናትጋ ሄድንና ሱቋን አየንላት ። ​​አንዳንድ ሰዎች የመንገዱን ጫፍ የሚያሳያቸው ሰው ብቻ ነው ሚፈልጉት እንጂ አካሄዱን ጠንቅቀው ያቁበታል ከመቼው በዛ ልክ ሱቁን በእቃ እንደሞላችው ፈጣሪ ይወቀው ሱቁን ለሁለት ከፍላዋለች ባንድ በኩል ሙሉ የባልትና እቃዎችን ደርድራለች በታችኛው በኩል ደሞ በጣም ብዙ ሸቀጣሸቀጦችን አዘጋጅታ ውጪ ላይ አትክልትና ፍራፍሬውን ግጥም አድርጋ ሳያት በጣም ደስ አለኝ ።

ኤልዱዬ ብዙ ጊዜ እናቶቻችን ሲናገሩ ሴት ልጅ ሚወዳትን ነው ማግባት ያለባት ይላሉ እኔ ግን አልስማም ሴት ልጅ የምትወደውን ብቻ የሚወዳትን ብቻ  ሳይሆን የእውነት ምታፈቅረውን የእውነት ሚያፈቅራትን ነው ማግባት ያለባት ፍቅር ከአንድ ወገን ሲሆን ለሁለቱም ህመም ነው ሚሆነው ። ​​ለዛ ነው ሁሌም ከእዩጋ ያለሽን ግንኙነት ምደግፍልሽ የሁለታችሁም ስሜት ፊታችሁ ላይ ያስታውቃል አብራችሁ እንድትሆኑ ማድረግ ያለብንን በሙሉ እናደርጋለን ቢያንስ እሱም አንቺም ትምህርታችሁን እስክትጨርሱ ድረስ እኔና አባትሽ መለያየት የለብንም ልጄ እኔ ይሄን ያህል አመት አባትሽ ከሌላ ሴትጋ እየወጣ እንደሚያድርና እንደሚማግጥብኝ አቃለሁ አሁን ግን ነገሮች ገፍተው ልጅ እንዳለው ሳውቅ ትንሽ ተበሳጭቼ ነበር አሁን ግን ትቼዋለሁ። እኔና አንቺ ወደቤት እንመለሳለን ዞሮ ዞሮ አብሮን አይኖርም አደል። አንዳንዴ ችለሽ ምታሳልፊያቸው ነገሮች አሉ አለችኝ። እኔ ሞቼ እገኛለሁ እሱ ሳይሄድ እዛ ቤት አልገባም አልኩኝ ጠዋት እሱም ወደሚስቱ እንደሄደና እሱ ሲወጣላት እንደመጣች ነገረችኝ ። እሺ በቃ እንደዛ ከሆነ እመለሳለሁ ቤታችን ቁጭ ብለን እንነጋገራለን አልኳትና ተያይዘን ሁላችንም ወደቤት ሄድን ምግባችንን በላላን እኔም ሻወር ወስጄ ልብሴን ቀያየርኩ ማታ እዩ እናቱጋ ሄዶ እንደሚያድር ነግሮኝ ወደቤቱ ሄደ ። በነጋታው  ወደጎንደር መመለሾ እንዳለበትም ነግሮኝ በሚቀጥለው ቀን ተመለሰ። እሱ ከሄደ ቡሀላ መልሶ የብቸኝነት የመከፋት የባዶነት ልክ ምንም ቁም ነገር ላይ መዋል የማትችል ተራ ሴት የሆንኩ ያህል ተሰማኝ ከናቴጋ ስለአባቴ ማውራት ይበልጥ እየረበሸኝ ስለነበር ዝም አልኳት። ስልኬ ላይ ስልኩ እንዳይጠራ አድርጌዋለሁ በዛ በመከፋቴ ውስጥ ሁሌ ዞር ስል ከጀርባዬ ማላጣው ሰው ዴቭ ነበር ነገሩ ትንሽ እየከበደኝ ሲመጣ ሌላ ሾል መጀመር እንደሚችልና እኔ ላይ ጊዜውን ማጥፋት እንደሌለበት በዚህ እድሜው ፍቅረኛ መያዝ ከሷጋ መዝናናት ጊዜ ማሳለፍ ያለበት ሰአት እንደሆነ ነገርኩት። እሱ ግን በዚህ ሰአት ብቸኛ ደስ የሚለውና ሰላም ሚሰጠው ነገር ከኔ አጠገብ መሆን እንደሆነ ነገረኝ። አባቴ ቤት ሳይመጣ  ለሶስት ሳምንት ያህል ከቆየ ቡሀላ ድንገት ለማናችንም ሳይናገር መጣ እኔ ክፍሌን ቆልፌ ቁጭ አልኩ እናቴ መጥታ ለምና አስከፈተችኝና አብረው ወደክፍሌ ገቡ አባቴ ሊያወራኝ እንደሚፈልግና ተረጋግቼ ማዳመጥ እንዳለብኝ ነግራኝ ክፍሉን ዘግታው ወጣች። ለወትሮው እንደዛ ምፈራውና ማከብረው አባቴ ለአይኔ አስጠላኝ ካጠገቤ ሲቀመጥ ዝግንን አለኝ። አባቴ ተስተካክሎ እየተቀመጠ ወደኔ ፊቱን አዞረና ልጄ በእርግጥ አጥፍቻለሁ ከኔ ማጠብቂውን ነውር ፈፅሚያለሁ ግን አንዳንዴ በኔ ቦታ ሆነሽ ነገሮችን መመለከት አለብሽ ሰው ሆነሽ ስቶኖሪ ስሜት ሚባል ነገር አለ ማፍቀር መፈቀር ያምርሻል እኔ ከናትሽጋ ይሄን ያህል አመት ስኖር አፍቅሪያትም አፍቅራኝም አታውቅም ብቻ በዘፈቀደ ዝም ብለን ነው ምንኖረው አለኝ.. ለምን እናቴን አላፈቀርካትም ምን ያንሳታል ወይስ አንተን ብቻ ብላ ቤት ውስጥ ስለተቀመጠች ነው እእእ አንተስ ወንድ ነህ በፈለከው ሰአት ከፈለከው ሴት ሄደህ ብዙ ልጆችን መውለድ ትችላለህ እናቴ ግን ሴት ናት እድሜዋ ይሄዳል መውለድ ታቆማለች ገባህ የሷን እድሜ ቀረጣጥፈህ እየበላህ የራስህን ህይወት ታማሙቃለህ ካልወደድካት ካልወደደችህ እኮ መፋታት ሚባል ነገር አለ አልኩት። ፀሀፊ  ማኔ ክፍል ሰላሳ አንድ ከ150like👍  በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍 ማድረግ አይርሱ።       â€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œ      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን! https://t.me/Melkam_liboch1

ኤልዱዬ ብዙ ጊዜ እናቶቻችን ሲናገሩ ሴት ልጅ ሚወዳትን ነው ማግባት ያለባት ይላሉ እኔ ግን አልስማም ሴት ልጅ የምትወደውን ብቻ የሚወዳትን ብቻ  ሳይሆን የእውነት ምታፈቅረውን የእውነት ሚያፈቅራትን ነው ማግባት ያለባት ፍቅር ከአንድ ወገን ሲሆን ለሁለቱም ህመም ነው ሚሆነው ። ​​ለዛ ነው ሁሌም ከእዩጋ ያለሽን ግንኙነት ምደግፍልሽ የሁለታችሁም ስሜት ፊታችሁ ላይ ያስታውቃል አብራችሁ እንድትሆኑ ማድረግ ያለብንን በሙሉ እናደርጋለን ቢያንስ እሱም አንቺም ትምህርታችሁን እስክትጨርሱ ድረስ እኔና አባትሽ መለያየት የለብንም ልጄ እኔ ይሄን ያህል አመት አባትሽ ከሌላ ሴትጋ እየወጣ እንደሚያድርና እንደሚማግጥብኝ አቃለሁ አሁን ግን ነገሮች ገፍተው ልጅ እንዳለው ሳውቅ ትንሽ ተበሳጭቼ ነበር አሁን ግን ትቼዋለሁ። እኔና አንቺ ወደቤት እንመለሳለን ዞሮ ዞሮ አብሮን አይኖርም አደል። አንዳንዴ ችለሽ ምታሳልፊያቸው ነገሮች አሉ አለችኝ። እኔ ሞቼ እገኛለሁ እሱ ሳይሄድ እዛ ቤት አልገባም አልኩኝ ጠዋት እሱም ወደሚስቱ እንደሄደና እሱ ሲወጣላት እንደመጣች ነገረችኝ ። እሺ በቃ እንደዛ ከሆነ እመለሳለሁ ቤታችን ቁጭ ብለን እንነጋገራለን አልኳትና ተያይዘን ሁላችንም ወደቤት ሄድን ምግባችንን በላላን እኔም ሻወር ወስጄ ልብሴን ቀያየርኩ ማታ እዩ እናቱጋ ሄዶ እንደሚያድር ነግሮኝ ወደቤቱ ሄደ ። በነጋታው  ወደጎንደር መመለሾ እንዳለበትም ነግሮኝ በሚቀጥለው ቀን ተመለሰ። እሱ ከሄደ ቡሀላ መልሶ የብቸኝነት የመከፋት የባዶነት ልክ ምንም ቁም ነገር ላይ መዋል የማትችል ተራ ሴት የሆንኩ ያህል ተሰማኝ ከናቴጋ ስለአባቴ ማውራት ይበልጥ እየረበሸኝ ስለነበር ዝም አልኳት። ስልኬ ላይ ስልኩ እንዳይጠራ አድርጌዋለሁ በዛ በመከፋቴ ውስጥ ሁሌ ዞር ስል ከጀርባዬ ማላጣው ሰው ዴቭ ነበር ነገሩ ትንሽ እየከበደኝ ሲመጣ ሌላ ሾል መጀመር እንደሚችልና እኔ ላይ ጊዜውን ማጥፋት እንደሌለበት በዚህ እድሜው ፍቅረኛ መያዝ ከሷጋ መዝናናት ጊዜ ማሳለፍ ያለበት ሰአት እንደሆነ ነገርኩት። እሱ ግን በዚህ ሰአት ብቸኛ ደስ የሚለውና ሰላም ሚሰጠው ነገር ከኔ አጠገብ መሆን እንደሆነ ነገረኝ። አባቴ ቤት ሳይመጣ  ለሶስት ሳምንት ያህል ከቆየ ቡሀላ ድንገት ለማናችንም ሳይናገር መጣ እኔ ክፍሌን ቆልፌ ቁጭ አልኩ እናቴ መጥታ ለምና አስከፈተችኝና አብረው ወደክፍሌ ገቡ አባቴ ሊያወራኝ እንደሚፈልግና ተረጋግቼ ማዳመጥ እንዳለብኝ ነግራኝ ክፍሉን ዘግታው ወጣች። ለወትሮው እንደዛ ምፈራውና ማከብረው አባቴ ለአይኔ አስጠላኝ ካጠገቤ ሲቀመጥ ዝግንን አለኝ። አባቴ ተስተካክሎ እየተቀመጠ ወደኔ ፊቱን አዞረና ልጄ በእርግጥ አጥፍቻለሁ ከኔ ማጠብቂውን ነውር ፈፅሚያለሁ ግን አንዳንዴ በኔ ቦታ ሆነሽ ነገሮችን መመለከት አለብሽ ሰው ሆነሽ ስቶኖሪ ስሜት ሚባል ነገር አለ ማፍቀር መፈቀር ያምርሻል እኔ ከናትሽጋ ይሄን ያህል አመት ስኖር አፍቅሪያትም አፍቅራኝም አታውቅም ብቻ በዘፈቀደ ዝም ብለን ነው ምንኖረው አለኝ.. ለምን እናቴን አላፈቀርካትም ምን ያንሳታል ወይስ አንተን ብቻ ብላ ቤት ውስጥ ስለተቀመጠች ነው እእእ አንተስ ወንድ ነህ በፈለከው ሰአት ከፈለከው ሴት ሄደህ ብዙ ልጆችን መውለድ ትችላለህ እናቴ ግን ሴት ናት እድሜዋ ይሄዳል መውለድ ታቆማለች ገባህ የሷን እድሜ ቀረጣጥፈህ እየበላህ የራስህን ህይወት ታማሙቃለህ ካልወደድካት ካልወደደችህ እኮ መፋታት ሚባል ነገር አለ አልኩት። ፀሀፊ  ማኔ ክፍል ሰላሳ አንድ ከ150like👍  በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍 ማድረግ አይርሱ።       â€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œâ€Œ      ይ 🀄️ላ🀄️ሉን! https://t.me/Melkam_liboch1

💖 ኤልዳና 💞  ‍ ​ 💝ልብ አንጠልጣይ የ ፍቅር ታሪክ በመልካም ልቦች የ ቴሌግራም ቻናል ተዘጋጅቶ የቀረበ💝           ክፍል 30   ሌሊቱን ሙሉ አንዴ ስናለቅስ አንዴ ስንፈዝ እንዲሁ እንቅልፍ ባይናችን ሳይዞር ነጋልን። ዴቭ በሌሊት መጣ የሚቀየር ልብስ አምጥቼላችኋለሁ ታጠቡና ቀይሩ ኤልዱ አባትሽ በጣም እየጨቀጨቀኝ ነበር ካወቀ ስለሚገለኝ አልነገርኩትም አለኝ። አመሰግናለሁ ዴቭ እንዳትነግረው እሺ አልኩት። ቀኑን ሙሉ እዩ ሳይደውልልኝ ምን ሆነሽ ነው እንኳን ሳይለኝ ቀረ ሁኔታው ቢያስገርመኝም ዝምታን መርጬ ዝም አልኩት። ማታ ላይ እናቴ እኔ ሳላይት ከክፍሉ ወጥታ ሄደች ደውላልኝ ወደቤት እንደተመለሰችና ካባቴጋ ምታወራው ትልቅ ጉዳይ እንዳለ ነገረችኝ ። ሁኔታ በጣም አበሳጨኝ ጭራሽ የት አረፋችሁ የት ወደቃችሁ ሳይለን መጥቶ ይቅርታ ሳይጠይቀን እራሷ ወደቤት መሄዷ አናዶኝ ማልቀስ ጀመርኩ ። ትንሽ ቆይቶ ዴቭ ደወለልኝና እየመጣ እንደሆነ ነገረኝ እሺ አልኩት እንባዬን ጠራርጌ ፀጉሬን አስተካክዬ ወደአልጋዬ ተመልሼ ቁጭ አልኩ ድንገት ነገሮች በዚህ ልክ ሲደበላለቁ ማየት በጣም ነው ሚያስጠላው ። ባንዴ የቤተሰብ ችግር በሙሉ የተሸከመች ትልቅ ሴትዮ የሆንኩ ያህል ተሰማኝ ውስጤ ያለውን ስሜት በምን እንደማጠፋው ጨነቀኝ ብቻዬን እየተብሰለሰልኩ በር ተንኳኳ ዴቭ መጣ ብዬ በሩን ከፈትኩት ከፊት ለፊቴ እያሱ እየተፍለቀለቀ ቆሟል አይኔ ነው ጭንቅላቴ ወይ በሀሳቤ እያሰብኩ ይሁን አላቅም ብቻ ፍዝዝ ብዬ ካየሁት ቡሀላ እዩ ብዬ ጮኬ ተጠመጠምኩበት የምር መተህ ነው አዎ በዚህ ሰአት አብሬሽ ካልሆንኩ መቼ ነው አብሬሽ ምሆነው አለኝ ወደውስጥ እየገባ። አልጋ ላይ ቁጭ ብለን ተቃቅፈን እዬዬ ማለት ጀመርኩ ሳየው የውስጤ መከፋት ባዶነት በሙሉ ትዝ አለኝ የምወደው ሰው ትከሻ ላይ ደገፍ ስል የውስጤን ቁስል በእንባ አጠብኩት። አይን አይኔን እያየኝ እንደዚህ ስታለቅሺ ሳይሽ ልፍስፍ ወንድ የሆንኩ ያህል ነው ሚሰማኝ የማፈቅራትን ልጅ መጠበቅ እንዳልቻልኩ እንድታለቅሺ ምክንያትሽ የሆንኩ ሁላ ይመስለኛል አለ እሱም እያለቀሰ ነው ሲያወራ የነበረው። ያንተ ጥፋትኮ አደለም ግን በቃ ሳይህ ህመሜን መደበቅ አልቻልኩም የማወራው ጓደኛ እንኳን እንደሌለኝ ታውቅ የለ ..... እሺ በቃ አውሪኝ የተፈጠረውን በደንብ አስረጂኝ እኔ እሰማሻለሁ ጓደኛሽም ሚስጥረኛሽም መሆን እችላለሁ አደል ንገሪኝ ጀምሪ .... ምድር ላይ ከተፈጠሩ ጀግና ወንዶች 10 ጥቀሽ ብባል ከአንድ እስከ አስር አባቴን ነበር ምጠቅሰው አምነዋለሁ እወደዋለሁ የሱ ልጅ ስለሆንኩኝ እኮራለሁ ይሄንን ህይወት የሰጠኝኮ ብቻውን ለፍቶ ነው እያልኩ ጠዋት ማታ እብከነከናለሁ እስከማቀው ድረስ እናቴን ያከብራታል ይወዳታል ካፉ ክፉ ቃል ሲወጣ ሰምቼ አላቅም ሁሌ እንደተከባበሩ ነው ተጣልተው የታረቁበትን ቀን ሁላ አላስታውስም እሱ ግን ምንም ሳያፍር በናቴ ላይ ሌላ ሴት ደረበ ጭራሽ አግብቷት ይሄን ያህል አመት fild እያለ ከሷጋ ነው ሚኖረው እሱ አልበቃ ብሎት ልጅም አለው እኔ እህት ወይ ወንድም አለኝ ማለት ነው በዚህ ሰአት የናቴን ስሜት የናቴን ስብራት ይሄ ነው ብዬ መናገር አልችልም የሷ ቁስል ደሞ እኔን እየተሰማኝ ነው አልኩትና ከዛ በላይ ማውራት ስላልቻልኩ ደረቱ ላይ ተለጥፌ ተንሰቀሰኩ እሱም አብሮኝ አለቀሰና በይ ተነሽ ልብስሽን ቀይሪና እንውጣ አለኝ ያምሀል እንዴ ምኔን ነው ምቀይረው ቤት ያለሁ መሰለህ እንዴ ይሄንንም ዴቭ ነው ጠዋት ያመጣልኝ አልኩት እሺ በቃ ፀጉርሽን ላስተካክልልሽ ብሎ ፀጉሬን አሲያዘልኝና ይዞኝ ወጣ። እጄን ይዞ ወደቤተክርስቲያን ወሰደኝ በይ ተንበረኪኪና ሚሰማሽን እንዲሆንልሽ ምትፈልጊውን በሙሉ ፀልይ አለኝ። በሰአቱ እንዲሆንልኝ ምፈልገው ምን እንደሆነ ግራ ገባኝ ብቻ እናቴን አጠንክርልኝ ልቧን አጀግንልኝ ብቻ አልኩት። ከቤተክርስቲያን አንስቶ እስከሆቴላችን እረጅም ወክ አደረግን በቃ አሁን ለፈጣሪ ነግረሸዋል እሱ እንዲያስተካክልልሽ ተይውና ፈታ በይ ብሎ በሆነው ባልሆነው እያሳቀኝ ያን ያህል መንገድ በእግሬ እንደሄድኩ እንኳን ሳይታወቀኝ ነበር የደረስኩት እዩ ወደዚህ ሊመጣ የቻለው እኔና እሱ ከቆጠብነው ገንዘብ ላይ አንስቶ ባስቸኳይ እንደመጣና እናቴና ዴቭ የት እንዳለሁ እንደነገሩት ነገረኝ። እስካሁን እናቱን እንዳላያትም ጭምር ነገ በጠዋት አብረን ሄደን ሰርፕራይዝ እንደምናደርጋት ተስማማን። ወደ ውስጥ ከገባን ቡሀላ ሌላ ጊዜ በሀሳብ ተውጠሽ ጭንቅላትሽ እረፍት ካጣ እረጅምም ወክ አድርጊ ሰውነትሽ ሲዝል ስለሚደክምሽ ጥንቅላትሽም አብሮ እረፍት ያገኛል አለኝ ቁጭ ብለን ለእናቴ ደወልኩላት አታነሳም ደጋግሜ ስደውል አነሳችውና አወራችኝ ተረጋግታ እየሳቀች ደና እንደሆነች ስትነግረኝ ቢያንስ እናቴ ከምር ደና ባትሆን እንኳን ማስመሰል መቻሏ ትልቅ ነገር እንደሆነ አሰብኩና ልቤ አረፍ አለ። ከእዩጋ ቆንጆ ምሽት አሳለፍን በጠዋት ተነስተን እናቱጋ ሄድን ስታየው እረጅም አመት እንደተለያየ ሰው አቅፋው አለቅም አለች። ድንጋጤም ጭምር ስለተሰማት ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ለምን መጣህ እንዴት መጣህ አለችው። ሁሉንም ነገራትና አረጋጋት ፈተና ቢያመልጥህስ ውጤትህ ዝቅ ቢልስ ብላ ተቆጣችው በዛ መሀል ከምንም በላይ የእዩ ትምህርት ለሡ ምን ያህል ዋጋ እንዳለው ተረዳሁ። አውርተናት ወደ ማረፊያችን ስንመለስ ዴቭና እናቴ ውስጥ ቁጭ ብለዋል። ሳያት በጣም ደንግጬ ሄጄ አቀፍኳት ብቻችንን እናውራ ወንዶቹ ውጭ ሁኑልን አለቻቸውና እዩና ዴቭ ወደ ውጪ ወጡ። ደህንነቷን ጠየኳት አዎ ደና ነኝ ልጄ ከኔ በላይ አንቺ እንደተጨናነቅሽ ስለገባኝ ላውራሽ ነው አሁን የመጣሁት በዛ ላይ አባትሽ በጣም ተናዶብናል ከቤት ወጥተን በማደራችን አለችኝ። ንዴቴን መቆጣጠር አቅቶኝ ጭራሽ አሁንም እሱ ነው ሚናደደው እንደመፀፀት አልኳት። ምን መሰለሽ ልጄ አንቺ ገና ስለሆንሽ ብዙ ነገሮች አይገቡሽም እኔና አባትሽ ከተጋባን ቀን ጀምሮ የምር ተዋደን ተፋቅረን አናቅም የተጋባነው አፍቅሬው ወድጄው አደለም በሰአቱ እሱ በቂ ሀብት ነበረው እና እንደኔ አይነት ቆንጆ ሴት ማግባት ይፈልግ ነበር እኔ ደሞ ሀብታም ማግባት ስለምፈልግ እሱም እኔም ጥቅም አስተሳስሮን ተጋባን አንድም ቀን ትዳራችን እንደሰው ትዳር ሆኖ አያቅም ሁሌም ቢሆን ፍቅር እንደሆንን እናስመስላለን እንጂ ፍቅር ሆነን አናቅም ። እኔና አባትሽ በቂ ከሚባለው በላይ ሀብት አለን ግን እንደምታይው ልቻችን አንቺ ብቻ ነሽ በፍቅር ምንኖር ሰዎች ብንሆን ግን ይሄኔ ልጅ በልጅ ሆነን ልጆቻችንን ባሳደግን ነበር። ኤልዱ መቼስ ላንቺ አልነግርሽም አደል ምንም ሳያንስብን እኔ የራሴ መኪና እንኳን የለኝም መኪናው ቀርቶ መንጃ ፍቃድ እንኳን የለኝም ጓደኛ ዘመድ vacation መውጣት ልጄን ይዤ ወጥቼ የናትና ልጅ ወግ ማሳለፍ ወጥቼ ያማረኝን ያየሁትን ገዝቼ አላቅም ላለፉት አመታት እኔ የቤት እመቤት ሳልሆነ የቤት ውስጥ እስረኛ ነኝ ልክ ብር ከፍሎ ገዝቶ እንዳስቀመጠውእቃ ማለት ነኝ።

ክፍል ሰላሳ ከ150 like👍 በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like 👍 ማድረግ አይርሱ። https://t.me/Melkam_liboch1