cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Getse gedamat

Більше
Ефіопія571Мова не вказанаОсвіта3 773
Рекламні дописи
39 443
Підписники
-12024 години
-1 2387 днів
-3 81030 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Фото недоступнеДивитись в Telegram
♦️ለዘላለም ማረፊያዬ ትሆን ዘንድ መርጫታለሁ ብሎ እግዚአብሔር በነቢያት እንደተናገረ የእግዚአብሔር ማረፊያ ለመሆን በመንፈስ ቅዱስ አስቀድሞ የተዘጋጀች የድንግል ማርያም ሠላሳ ሦስት በዓላት መካከል ሰኔ ፳፩ ቀን የሚከበረው አንዱ ነው ። 👉በዚህ ቀን በቂሣርያ በአማናዊት ቤተ መቅደስ በድንግል ማርያም ስም በሦስት ድንጋዮች ብቻ ቤተ መቅደስ ተሰርቶ በእራሱ በክርስቶስ ተባርኮ የሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያው ቤተ መቅደስ አገልግሎት የጀመረበት ታላቅ በዓል ነው ። እንኳን አደረሳችሁ ። የእናታችን የእመቤታችን የድንግል ማርያም ፍቅሯን በልቡናችን ጣዕሟን በአንደበታችን ያሳድርብን አማላጅነቷ ቃል ኪዳንዋ ይጠብቀን አሜን ።
Показати все...
16👍 4
Показати все...

ጣና ከመከራው ውኃ የተረፈ፣ ከኤዶም ገነት የተጨለፈ፣ የቃል ኪዳኗን መርከብ ያንሳፈፈ፣ ፍጥረቱንም ሁሉ ያተረፈ ሐይቅ ነው፡፡ በልብ አምሳያ የተሠራ፣ ከልብ የመነጨ ሃይማኖት፣ እምነት፣ ታሪክ፣ ትውፊት፣ አርቆ አሳቢነትና ደግነትን አቅፎ ይዟል፡፡ ••• ጣና ምንጩ ከኤዶም ገነት ሚወርደው ግዮን በላዩ ላይ ይሄዳል። ••• ጣና በኢትዮጵያ ትልቁ ሐይቅ ነው።አጠቃላይ ስፋቱ 695,885 ሔክታር ነው። ከሰሜን እስከ ደቡብ ያለው የሐይቁ ርዝመት 85 ኪሎ ሜትር ሲቃረብ ከምሥራቅ ወደ ምዕራብ ያለው ስፋቱም 66 ኪሎ ሜትር ተገምቷል፡፡ ••• ጣና  በፈረንሳይ መዲና ፓሪስ ከሰኔ 1 ቀን እስከ ሰኔ 5 ቀን 2007 ዓ.ም. ጉባኤውን ያካሄደውና የብዝኃ ሕይወት ጉዳይን የሚመረምረው ዓለም አቀፉ ምክር ቤት ጣና ሐይቅን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣የሳይንስና የባህል ድርጅት ዩኒስኮ በያዘው ብዝኃ ህይወት ክምችት በቅርስነት መዝግቦታል። ••• ጣና ሐይቅ በጥንታዊ ቋንቋ (ግእዝ) አገላለጽ ‹‹ጻና ሐይቅ›› ይባላል፡፡ድንግል ማርያም በገዳሙ የነበራትን ቆይታ አጠናቃ ስትመለስ “ፀአና በደመና” በደመና ጫናት የተባለው በጊዜ ብዛት ለአሁኑ የሐይቁ መጠሪያ ስም “ጣና” መሠረት ሆኖታል ነው የሚባለው። ••• ጣና ምድር ጥፋት ውኃ በጠፋች ጊዜ ዘር እንዲያተርፍ ቃል ኪዳን የተሰጠው የኖኅ መርከብ ማየ አይኅ መጉደል ሲጀምር በ7ኛ ወር ከወሩም በ27ኛው ቀን  በአናቱ ላይ ያረፈበት ታላቅ ሐይቅ ነው። የኖኅ መርከብ ያረፈበትም አራራት ተራራ በጣና ራስጌ (ዘጌ)  የይጋንዳ ተክለሃይማኖት ቤተ ከርስቲያን  ላይ ይገኛል። ••• በክርስቶስ ልደት ገደማ ስለግብጽ ብዙ ምርምር ያደረገው ስትራቦ ዓባይ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኝ ትልቅ ሐይቅ እንደሚነሳ ያውቅ ነበር ይባላል፡፡ የሐይቁን ስምም ስትራቦ “ሴቦ” ብሎታል፡፡ የሁለተኛው ዘመን የግብጽ መልክዓ ምድር ተመራማሪ ገላውዲዮስ ፕቶሎሚ ደግሞ “ኮሎ” ይለዋል፡፡ የአቴናው ድራማ ጸሐፊ አስክለስ “መዳብ የተቀባው ሐይቅ የኢትዮጵያ ጌጥ” ብሎታል፡፡ ባለቅኔው ሆሜርም “ከሌሎች የተለየና ጥርት ያለ የውኃ ባለቤት ነው” ብሎ ጠርቶታል፡፡ ••• ከ3000 ዓመት በፊት የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ የኾነችው ታቦተ ጽዮን ቀዳማዊ ምኒሊክ  ከ318 ሌዋውያን እና ከ12 ነገደ እስራኤል ጋር ይዞ ወደ ኢትዮጵያ በመጣ ጊዜ ያረፈችው ጣና ቂርቆስ ገዳም ላይ ነው።ዛሬም ጣና ቂርቆስ 4 ሺህ 518 ዓ.ዓ ጀምሮ መሰዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ፣አራት ማዕዘን ቅርጽ ያለው ከአናቱ ላይ እንደ ሙቀጫ የተቦረቦረው ድንጋይና የኦሪት  የብረት መስዋዕት ማቃጠያ በሥፍራው ይገኛሉ።ከታቦተ ጽዮን ጋር የመጣው ሊቀ ካህናቱ አዛርያስ ጣና ቂርቆስ ገዳም ላይ  ነው የተቀበረው። ••• ከ3000 ዓመት በፊት የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ የኾነችው ታቦተ ጽዮን ባረፈችበት ጣና ቂርቆስ ገዳም በአንደኛው መክዘ ሄሮድስ ጌታን ሊገድል በፈለገ ጊዜ ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር 3 ወር ከ10 ቀናት የተቀመጠችበት ቦታ ነው። ••• ጣና በአጠቃላይ በውስጡ ከ37 በላይ ደሴቶች ሲኖሩት 27 ገዳማትን አቅፎ ይዟል።ገዳማቶች በ14ኛ ምእት ዓመት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ባመነኮሷቸው ‹‹ሰባቱ ከዋክብት›› ተብለው በሚጠሩት ቅዱሳን አባቶች የተመሠረቱ ናቸው።ከገዳማቶች መካከል፦ •••ደብረ ማርያም •••ክብራን ገብርኤል •••ዑራ ኪዳነምህረት •••መሀል ዘጌ ጊዮርጊስ •••አቡነ በትረ ማርያም •••አዝዋ ማርያም •••ዳጋ ኢስጢፋኖስ •••ይጋንዳ ተለሃይማኖት •••ናርጋ ስላሴ •••ደብረ ሲና ማርያም •••ማንድባ መድኃኒዓለም •••ጣና ቂርቆስ •••ክርስቶስ ሳምራ ገዳም •••ራማ መድሕኒ ዓለም •••ኮታ ማርያም…እና ሌሎችም ገዳማቶች ይገኙበታል። ••• ሰባቱ ከዋክብት የሚባሉት አኩስም አቅራቢያ የሚገኘው የደብረ በንኮል ገዳም መሥራች አቡነ መድኅነ እግዚእ ደቀ መዛሙርት ናቸው።እነርሱም፦ 1.አቡነ ታዴዎስ~ደብረ ማርያም መሥራች 2.አቡነ ዘዮሐንስ~የክብራን እና የእንጦስ ገዳም መሥራች 3. አቡነ በትረማርያም~የዘጌ ጊዮርጊስ መሥራች 4. አቡነ  ኂሩተ አምላክ~የዳጋ እስጢፋኖስ መሥራች  5.አቡነ ኢሳይ~የመንዳባ መድኃኔዓለም መሥራች 6.አቡነ ዘካርያስ~ደብረ ገሊላ መሥራች 7.አቡነ  ፍቁረዮሐንስ~ጣና ቂርቆስ መሥራች ናቸው። ••• ጣና ቂርቆስ ታቦተ ጽዮን ለ800 ዓመታት ያረፈችበት፣ ሊቀ ካህናቱ አዛርያስ የተቀበረበት፣ቅድስት ድንግል ማርያም  ከልጇ ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር 3 ወር ከ10 ቀናት የተቀመጠችበት ገዳም ነው።ቅዱስ ያሬድ ምልክት የሌለውን ድጓ የጻፈባትና መጽሐፉና መስቀሉ የሚገኝበት ገዳም ነው። https://www.youtube.com/@Getsegedamat
Показати все...
Getse-Gedamat ገጸ-ገዳማት

በዚህ ቻናል ገጸ-ገዳማትን የምንመለከትበት ቦታ ነው። ሼር ላይክ ሰብስክራይብ በማድረግ አገልግሎታችንን እንድትደግፉን በትህትና እንጠይቃለን!

👍 4 4
ሼር በማድረግ ለሌሎችም እናድርስ! https://t.me/adugna_123 https://t.me/adugna_123 https://t.me/getsegedamat ዝግጅታችን ለወደፊት በዩቲዩብም ይኖረናል። ሰብስክራይብ በማድረግ ጠብቁን። https://www.youtube.com/@Getsegedamat
Показати все...
እስኪ ይህን ታላቅ ቦታ ላስቃኛችሁ!
Показати все...
👍 4
#አቡነ ገሪማ ታላቁ ገዳም🔺#zemedkunbekele @Getsegedamat https://youtube.com/watch?v=PYJ16XCJG8M&si=Ko3qwljg8SrGLpzp
Показати все...

5👍 2
አቡነ ገሪማ ከተሰአቱ ቅዱሳን አንዱ ሲሆኑ የትውልድ ሀገራቸው ሮም ነው።የአባታቸው ስም አስግንያኖስ ሲሆን የእናታቸው ደሞ ሰፍነግይ ይባላል።ወላጆቻቸው መካን ሆነው ልጅ ሳይወልዱ ብዙ ግዜ ሲኖሩ ልጅ እንዲሰጣቸው ወደ ፈጣሪያቸው አብዝተው ይፀልዩ ነበር። እግዚአብሄርም ፀሎታቸውን ሰምቶ ልጅ ሰጣቸውና ስሙን ይስሐቅ አሉት።እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ወደ ትምህርት ቤት አስግቡትና እየተማረ አድጎ ከማእረገ ድቁና ደርሶ ይቀድስ ጀመር። አባቱም አገረ ገዥ ስለነበር እሱ በሞተ ግዜ የአባቱን ግዛት ተረክቦ ለሰባት ዓመታት እንደገዛ አባ ጴንጤሌዎን ደብዳቤ ስለ ላከለት ሳይውል ሳያድር እለቱን ግዛቱን እርግፍ አድርጎ ትቶ በሌሊት መንኖ ወደ አባ ጴንጤሊዎን ሄደ።አባ ጴንጤሊዎንም በደስታ ተቀብሎ ስርአተ ምንኩስናን በሚገባ አስጠንቶ አመነኮሰው። ከዚያም ከትሰአቱ ቅዱሳን አንዱ ሆኖ ወደ ኢትዮጲያ መጣ። የአባ ገሪማ ሀገረ ስብከታቸው መደራ ነበር።መደራ የምትገኝው በትግራይ ሀገረ ስብከት በክእልተ አውላእሎ ወረዳ ነው።አባ ይስሐቅ በፆም በፀሎት ተወስነው አጋንንትን ከሰው እያወጡ ድውይ እየፈወሱ ለ27 ዓመታት በገዳሙ ተቀምጠዋል። አባ ገሪማ የሚታወቁበት አንድ ትሪክ አላቸው።ክእለታት አንድ ቀን አኃው ለተልእኮ እንደወጡ ከመንገድ ምሳ ለመብላት ዐረፍ ብለው ድርሻ ድርሻቸውን ተካፍለው ሲበሉ አባ ይስሐቅ ቅዳሴ እንዳለ አውቀው ድርሻቸውን የበሉ መስለው አስቀመጡ።ለአኃው ግን የበሉ መስሏቸው ነበር።ከተላኩበት ቦታ ሲደርሱም መስዋእት ተሰርቶ አንድ ቀዳሽ ጎሎባቸው ሲጨነቁ አገኙ።አባ ይስሐቅም ገብትው ቀደሱ።ጓደኞቹ በልቶ ቀደሰ እያሉ ተገርመው ነበር። ይህንን ወሬ ለአባ ጴንጤሌዎን ሲመለሱ ነገሯቸው።አባ ጴነጤሌዎንም አባ ይስሐቅን አስጠርተው ሲመጡ ብዙ ሰዎች እብረዋቸው ነበሩና ልጄን የምጠይቀው ነገር አለኝና ውጡልኝ አሏቸው። በዚህ ግዜ አባ ይስሐቅ ምን ሰዎች ብቻ እንጨቶችም ድንጋዮችም ይወገዱ እንጂ ብለው በተናገሩ ግዜ ድንጋዮችና እንጨቶች 5 ምዕራፍ ሸሹ።አባ ጴንጤልዎንም ይህንን ተአምር ባዩ ግዜ "ገረምከኒ ኦ ወልድየ ይስሐቅ" እሏቸው።ከዚያ ወዲህ አባ ገሪማ ተብለው ተጠሩ።አባ ገሪማ ለ27 ዓመት በአርኡተ ምንኩስና ተጠምደው ፈጣሪያቸውን ከአገለገሉ በኃላ ሰኔ 17 ቀን እንደ ሄኖክ ተሰውረዋል። ከአባታችን እረድኤት በረከት ያሳትፈን ሀገራችንን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንንም ከምንሰማው ከምናየው ከማንሰማው ከማናየው ክፉ ነገር ይጠብቅልን።የፃድቁ አማላጅነት አይለየን አሜን አሜን አሜን ምንጭ ፦የቤተክርስቲያን መረጃዎች ካስ ዘሚካኤል 05/01/2009 ዓ/ም
Показати все...
👍 6 3
04:01
Відео недоступнеДивитись в Telegram
አቡነ ገሪማ ታላቁ ገዳም!
Показати все...
32.34 MB
4
      የጩጊ ማርያም አንድነት ገዳም ሰሜን ጎንደር ሀገረስብከት በወገራ ወረዳ ከሚገኙ ገዳማት አንዱ ነው፡፡ገዳሙ ከጎንደር ከተማ 25 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ኮሶዬ ከተማ ሲደርሱ ሶስት ሰአት የእግር መንገድ እንደተጓዙ የሚገኝ ገዳም ነው፡፡ የጩጊ ማርያም ገዳም በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተመሰረተ ጥንታዊ ገዳም ሲሆን የመሰረቱትም አባ ምእመነ ድንግል የተባሉ ጻድቅ ናቸው፡፡ገዳሙም ጻድቁ የጸለዩበት እና ከጌታችን ከመድሃኒታች ከኢየሱስ ክርስቶስ ቃልኪዳን የተቀበሉበት ቅዱስ ቦታ ነው፡፡ የአባ ምእመነ ድንግል ታሪክ አባ ምእመነ ድንግል የተወለዱት በወገራ አውራጃ ሲሆን ገና በህፃንነታቸው በእናት በአባታቸው ቤት እያሉ ጀምሮ መንፈሳዊ ትሩፋቶችን በመስራት በታላቅ ተጋድሎ ኖረዋል፡፡ አባታችን ምእመነ ድንግል የምንኩስና ልብስና የእግዚአብሔር ጸጋ በመፈለግ አዳጋት ማርያም ወደ ምትባል ገዳም በመሄድ ብዙ ተጋድለዋል፡፡ ከዚያም ወደ ዋልድባ ገዳም በመሄድ ብዙ ተጋድለዋል፤ጽናታችውን ያዩ የዋልድባ ገዳም መነኮሳት አባትና መምህር እንዲሆኗቸው ቢጠይቋቸው እራሳቸውን ዝቅ በማድረግ “እኔ መምህርና አባት ልሆን አይገባኝም ” በማለት እንቢ ቢሉም መነኮሳቱ አበምኔት አድርገው ሾመዋቸዋል፡፡ አባታችንም በተሾሙበት በዚህ ገዳም በከፍተኛ ተጋድሎና በእግዚአብሔር ጸጋ ብዙ መንፈሳዊ መነኮሳትንና መምህራንን በትምህርታቸው አፍርተዋል፡፡ ከዚህ በኋላ በጊዚው በዐፄ ሱስንዮስ ዘመነ መንግስት በሃይማኖት ምክንያት በርካታ ቅዱሳን መነኮሳት ሰማዕትነትን እየተቀበሉ ስለነበረ እሳቸውም ስለ ትክክለኛይቱ ሃይማኖት መስክረው ሰማዕትነትን ሊቀበሉ ሲመጡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል “ጊዜህ ገና ነው፤የተዋሕዶ ሃይማኖት መመለሷን ሳታይ ሰማዕትነትን አትቀበልም” ብሏቸው አሁን በስማቸው በሚጠራው ተራራ ዋሻ ፈልፍለው እንዲጸልዩና እንዲያስተምሩ እስከመቼም ቢሆን በረድኤት እንደማይለያቸው አስረድቷቸው ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ዋሻው ውስጥ እያሉ የኢትዮጰያን ቤተክርስቲያንና ሃይማኖት ለማጥፋት ያቀደ አረመኔ ካቶሊክ ፈረንጅ መጥቶ፤“ክርስቶስን አንድ አካል ሁለት ባሕርይ” ብላችሁ እመኑ እያለና ሕዝቡን እየጨፈጨፈ በሚያስቸግርበት ጊዜ በመቃወም “ክርስቲያን ሁሉ በአበው ሃይማኖት ጽኑ፣እግዚአብሔር በአካል ሦስት በመለኮት፣በአገዛዝ፣በሥልጣን፣ … አንድ ነው እንጂ ከዚህ ውጭ አይደለም፤ በሃይማኖታችሁ ጽኑ” እያሉ ቀን ከሠራዊቱ ጋር እንደሠራዊት እያስተማሩ፣ ያመኑትን እያጠመቁ፣ ቀድሰው ሥጋወደሙን እያቀበሉ፣ በትግሃ ሌሊት በጸሎትና በስግደት የክርስቶስን መከራ በማሰብ ፊታቸውን እየጸፋ በከፍተኛ ተጋድሎ የሃይማኖትን መንገድ በፋናቸው አሳይተዋል (ኤፌ. 4÷5-6)፡፡ አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት ከሁሉ በላይ የሚሆን በሁሉም የሚሠራ በሁሉም የሚኖር አንድ አምላክ እያሉም አስተምረዋል፡፡ በዚያን ዘመን ዐፄ ሱስንዮስ ነግሠው በነበሩበት ወቅት ከፖርቹጋል ጋር ግንኙነት ነበራቸው፡፡ ይህንንም ግንኙነታቸውን ለማዳበርና ለማጠናከር የፖርቹጋል ሴት እንዲያጩ ተገደዱ፤ ዐፄ ሱስንዮስ በዚህ ምክንያት ሃይማኖታቸውን ለውጠው ሲኖሩ በገዳማት የሚኖሩ መነኮሳትና በኢትዮጰያ አድባራትና አብያተ ክርስቲያናት የሚኖሩ ሊቃውንተ ቤተ ክርስትያን ስለተቃወሟቸው መነኮሳት ካሉበት ከበኣታቸው ሊቃውንትን ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት እና አድባራት እያደኑ ያስፈጇቸው እንደነበር ታሪክ ያስረዳናል፡፡ ለምሳሌ ከቅዱሳት አንስት እነ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን የመሳሰሉ ቅዱሳን በዚያን ጊዜ ነው የተሠውት፡፡ በዚህን ጊዜ ጻድቁ አባ ምእመነ ድንግል ከ40 ልጆቻቸውና ደቀመዛሙርቶቻቸው ጋር ጩጊ ቅድስት ማርያም ገዳምን ጥግ ከለላ አድርገው መኖር ጀመሩ፡፡ በዚህም ቦታ ዋሻ ፈልፍለው በጸሎትና በተጋድሎ በሚኖሩበት ወቅት የነገሩትን የማይረሳ የለመኑትን የማይነሳ ምስጋና የባህርይ ገንዘቡ የሆነ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ በታላቅ ቦታ እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ዘጠና ዘጠኙን ነገደ መላእክትን፣ ነቢያትን፣ ሐዋርያትን፣ ሰማዕታትን እና ቅዱሳን አበውን፣ አስከትሎ “ወዳጄ የአባቴ ወዳጅ የመንፈስ ቅዱስ ወዳጅ ሰላም ላንተ ይሁን” አላቸው፡፡ ጻዲቁ ይህን የመሰለ ብርሃንና ልዩ ንውጽውጽታ በማየት ተደንቀው አምላካቸውን እጅ ነስተው (ሰግደው) ለእመቤታችን ለቅድስት ማርያም ሰግደውና እጅ ነስተው ድንቅ ነገር በማየታቸው በሚደሰቱበት ጊዜ ጌታችን በእጅ አንሥቶ አቅፎ ስሟቸው የሚከተለውን ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ “በዚህ ቦታ አንተ በተጋደልክበት ማኀበር መሥርቶ የሚኖረውንና የሚማፀነውን ሁሉ አኗኗኑ እንደ ሰማይ መላእክት ይሆንለታል፡፡ ወደዚህ ቦታ ሥጋዬንና ደሜን አምኖ የተቀበለውን ከቅዱሳን መላእክት ጋር በአባቴ ክብር በመምጣበት ጊዜ ፍጹም ገሃነመ እሳትን አላሳየውም፡፡ ምንም ኃጥያት ቢሠራ አምላከ ምዕመነ ድንግል ይምረኛል ብሎ በፍጹም እምነት የመጣውን ወደ ተወለድኩባት ቤተልሔም፣ ወደ አደኩባት ናዝሬት፣ ወደ አስተማርኩባት ደብረዘይት፣ ወደተጠመኩባት ዮርዳኖስ እና ወደተሰቀልኩበት ቀራንዮ እንደሄደ እቆጥርለታለሁ” በማለት ይህን አማናዊ ቃል ኪዳን ከሰጣቸው በኋላ ካሉበት ከበኣታቸው በስተቀኝ በኩል የኪዳነ ምሕረትን ጸበል በስተግራ የዮርዳኖስ ጸበል አፍልቆላቸዋል፡፡(ገላ.3÷15-18) ታላቁ ጻድቅ አቡነ ምእመነ ድንግል ይህን ቃልኪዳን በተቀበሉበት በዚህ ቅዱስ ሥፍራቸው ተጋደሎአቸውን በበለጠ ሲጋደሉ “ፈዋሴ ድውያን” ተብለዋል፡፡ ይኽውም ዐፄ ሱስንዮስ ሃይማኖታቸውን ወደ ካቶሊክ ለውጠው እንዲሁም “የሃገሪቷ ሃይማኖት እንዲለወጥ” በማለታቸው ምክንያት 140 ሺህ ቅዱሳን አባቶች ይህን ተቃውመው መስቀል እንደጨበጡ ስለሃይማኖታቸው በሰማዕትነት ሲጋደሉ ንጉሡ በቅዱሳኑ ላይ ባደረሱት ጭቃኔ የተሞላበት ጥፋት ምላሳቸው ተጎልጉሎ ነበር፡፡ በዚሁ ጊዜም በጣም ደግና ብልህ የነበሩት ልጃቸው ዐፄ ፋሲል ስለ አባታቸው መዳን በጣም ተጨንቀው መፍትሔ ለማግኘት የሚነግራቸው ብቁ ሰው ሲያፈላልጉ አንድ የበቁ አባት ከሞት የተረፉ፣ ከጥላ ያረፉ፣ በዕድሜ የገፉ፣ ግዝቱን ለመፍታት የማይችሉ ፣ አንድም ወለቴ የተባለችው አገልጋያቸውና የአቡነ ምእመነ ድንግል ክብር እንዲገለጽ የተረዱ ታላቅ ባሕታዊ ተገኙና “ከዚያው ከቤትህ ከሴት ሠራተኛ አገልጋዮችህ ውስጥ አንዲት የበቃች አለችና እርሷ መፍትሄውን ትነግርሃለች” ብለው አመላከቷቸው፡፡ ይህችውም ወለቴ የተባለች ስትሆን ከብቃቷ የተነሳ በክንፍ እንደ መላእክት እየበረረች ስትሄድ ያያት ሁሉ “አሞርዬ” ይሏታል፡፡ እሷም እስከ ዛሬ ድረስ በሕቡዕ ተሰውራ ትኖራለች፡፡ የመጸለያ በኣቷ እና ገዳሟ ባሕርዳር ዙርያ አዴት አካባቢ አዳማ ጊዮርጊስ አጠገብ ነው፡፡ ዐፄ ፋሲልም በየበሩ ወታደሮችን አሰልፈው ሲያስጠብቁ ይህችው አገልጋይ በጸሎት አድራ ስትመለስ አግኝታው ይዘው አቀረቧት፤ በዚህ ጊዜ በብዙ ማግባባት ቢጠይቋት ምንም እንደማታውቅ ተራ ኃጢያተኛ እንደሆነች ገለጠችላቸው፡፡ ሆኖም በብዙ ልመና ሲማጸኗት “ድንግል መነኩሴ ቢገኝ አባታቸውን እንደሚፈውስላቸውና ዐፄ ፋሲልም እንደሚነግሡ” ነገረቻቸው፡፡
Показати все...

👍 7 2👏 1
ዐፄ ፋሲልም “ድንግል መነኩሴ ፈልጎ ላመጣልኝ እሸልማለሁ” ብለው አወጁ፡፡ አቡነ ምእመነ ድንግል ባሉበት አካባቢ የሚኖሩ ይጉይታና ባጅር የሚባሉ ባላባቶች ውሾቻቸውን አስቀድመው ሲያፈላልጉ ጻድቁም እንደሚፈለጉ ስለሚያውቁ አርድቶቻቸውን “ሰው ሲመጣ በበሩ እየተመለከታችሁ እንድትነግሩኝ” ብለው ዳዊታቸውን እየደገሙ ሳሉ ረዳታቸው ውሻ አዩና “አባ ውሻ መጣ” አሏቸው፡፡ አባም “እ! ብለው ውሻ መጣ ሰው መጣ፤ ሰው መጣ ነገር መጣ ” ብለው ወደ ባሕር ገቡ፡፡ በገቡም ጊዜ እዚህ ነበር የማይባል ድንጋይ ከውኃው ወደ ላይ ገፍቶ (አንሥቶ) አወጣቸው፡፡ ይህ ድንጋይም በአሁኑ ሰዓት በዚያው ይታያል፡፡ ባላባቶችም “አባ ከዐፄ ፋሲል ተልከን ነው፡፡ ‘የአባቴን ምላስ ግዝቱን ፈቶ የሚመልስ መነኩሴ ካገኘሁ ተዋሕዶ ሃይማኖትን እመልሳለሁ’ ብለው ቃል ስለገቡ ነውና ማስረጃ የንጉሡ ማኅተም ይኸው” ብለው ባሳይዋቸው ጊዜ በደስታ አብረዋቸው በመሄድ ከእነ አባ ዓምደ ሥላሴ ጋር በመጸለይ አዋጅ አስነግረው “ፋሲል ይንገሥ፣ ካቶሊክ ይፍለስ፣ ተዋሕዶ ይመለስ፣ የዐፄ ሱስንዮስ ምላስ ይመለስ፣ እግዚአብሔር ይፍታህ” ሲሉ ተጎልጉሎ የነበረው ምላሳቸው ተመለሰ በዚያን ጊዜ ዐፄ ሱስንዮስ “ብቆይ ዓመት ብበላ ገአት/ገንፎ/” ብለው በመናገር ምላሳችው፤ እንደ ቀድሞው ሆነላቸው፡፡ ዐፄ ሱስንዮስም ለንሰሓ ሞት በቅተው፣ መንግሥታቸውን ለልጃቸውን አውርሰው በክብር አርፈው በታላቁ ገዳም ዳጋ እስጢፋኖስ አፅማቸው ከብዙ ነገሥታት አፅም ጋር ይገኛል፡፡ በዚያን ጊዜ ያች ደገኛ አገልጋይ ጎንደር የዐፄ ግንብ እንደሚሠራ ለዐፄ ፋሲል ትንቢት ተናግራለች፡፡ይህ ቦታ ብዙ ዘመናትን ያስቆጠረና ዛሬም ድረስ ድንቅ ተአምራት እየገለፀበት ይገኛል፡፡ ከነዚህም ውስጥ ለግንዛቤ ያህል የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡ ፩) ንጉሡ ዐፄ ፋሲልም የጻድቁን ቦታ ሳይረሱ መንግሥታቸው ከጸናላቸው በኋላ ለገዳሙ ርስት ጉልት ሊሰጡ በተጓዙ ጊዜ ከአፋፍ ቆመው “የት ነው የጻድቁ በዓት?” ሲሉ “ይህ ወይራና ጽድ የበዛበት በፊታችን የምናየው ነው” ሲሏቸው “ይህ ጭው ያለው ዱር ነው?” ሲሉ “አዎ” አሏቸው፡፡ በዚህ የተነሳ የቦታው ስያሜ “ጩጊ” ለመባል በቃ፡፡ የጻድቁ በኣት መጸለያ ዋሻም በስማቸው “ምእመነ ድንግል” እንደተባለ አለ፡፡ ጻድቁም በሕይወት እንደነ ሄኖክ፣ ኤልያስ፣ ቅዱስ ያሬድ እና አባ ዮሃኒ በህቡእ አሉ፡፡ ፪) የጻድቁ መጸለያ ቦታ በተፈጥሮው የተሸነቆረ መስኮት አለው፡፡ በዚህ ቦታ ላይ መኻን የሆኑ ሁሉ በመስኮቱ ወጥተው ሲመለሱ ማየ ዮርዳኖሱን ጠጥተው ሲሳሉ ልጅ ለማግኘት ይበቃሉ፡፡ ይህን ቃል ኪዳን የሚያውቁ ጳጉሜን በሙሉ በማየ ዮርዳኖሱ በመጠመቅ ትልቅ ሐብተ ፈውስ ያገኛሉ፡፡ ፫) የዮርዳኖሱን ጸበል የጠጣ ሲሞት ሥጋው አይፈርስም፣ አይበሰብስም፡፡ እንኳን በአርአያ ሥላሴ የተፈጠረው ሰው እንስሳቱ እንኳን አካላቸው ሳይፈርስ ይቆያል፡፡ ለማስረጃ ያህል እንኳን 16 የሚሆኑ ፍየሎች አካላቸው ሳይፈርስ 400 ዘመን ያስቆጠሩ አሉ፡፡ ፬) በ1968 ዓ.ም. አንድ ዛፍ ከወንዝ ዳር ወድቆ አንድ ገበሬ ለማገዶ ሲፈልጠው እስከነ ምሳሩ ተነሥቶ ቆሞ በሥሩም ሰባት ጸበል ፈልቶ ብዙ ህሙማንን ፈውሰዋል፡፡ ፭) ሰኔ 21 ቀን 1988 ዓ.ም. አንድ ዛፍ በእርሻ መካከል ስለወደቀ ለማስወገድ ከሥሩ በእሳት ቢያቃጥሉት ሥሩን ትቶ ከጫፍ እየነደደ ከወደቀበት ተነሥቶ ቆሟል፡፡ ፮) በቦታውም ላይ የብዙ ቅዱሳን አፅም ይገኛል፡፡
Показати все...
👍 32🙏 10 4👏 2😍 2
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.