cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

የእንጦጦ መ/ስ/ቅ/ሥላሴ ቤ/ክ. ዉሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ዋና ገጽ

ይህ የእንጦጦ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ዉለደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ዋናው ገፅ ነው በዚህ የሰንበት ት/ቤት ዋና ገፅ ላይ በሰንበት ቤት ስም የሚለቀቁ ትምህርቶች፣ መዝሙሮች፣ ኪነ ጥበባዊ ፅሁፍፎች እና የሰንበት ት/ቤቱ መልእክቶች የሚተላለፍበት ነው። ስለሆነም ወደ ዋናው ገፅ እንድትቀላቀሉ ይሁን የሰ/ት/ቤቱ ሥራ አመራር ጽ/ቤት

Більше
Країна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
Рекламні дописи
206
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

የወንድማችን የአባይነህ እንዳለ አባት ሰላረፉ ፤ነገበ18/9/201 3ዓ/ምከ6-7 ሰዓት የቀብር ሥነ-ሥርዓት በመንበረ ንግስት ቁሰቋም ቤተክርሰቲያን ይፈፀማል ።
Показати все...
የማፅናኛ ፕሮግራም ነገ18/9/201312፡00 ይደረጋል።#አድራሻ አምሃ ደስታ ት/ቤት ጀርባ ገበያው ጋ።
Показати все...
የእንጦጦ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን፤ የዉለደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ☦☦ የሀዘን መግለጫ፤ ☦☦ የቀድሞ የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆኑት የወንድሞቻችን የሻረው ተፈሪ እና የእስክንድር ተፈሪ አባት ከዚህ ዓለም በእረፍተ ሥጋ በመለየታቸው በወንድሞቻችን እና በቤተሰቦቻቸው ላይ በደረሰባቸው ሀዘን የሰንበት ት/ቤታችን ሥራ አመራር እና መላው የሰ/ት/ቤታችን አባላት ጥልቅ ሀዘን የተሰማን መሆኑን እየገለጽን ለሞተው አባታችን ቸሩ አምላካችን ቅድስት ሥላሴ እረፍተ ቅዱሳንን እንዲያድልልን። እንዲሁም፤ ለሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል ለሆኑት ለወንድሞቻችን እና ለመላው ቤተሰቦቻቸው ሁሉ ቸሩ አባታችን ቅድስት ሥላሴ መፅናናትን እንዲሰጥልን እንመኛለን። 🙏 የሰ/ት/ቤቱ ሥራ አመራር ጽ/ቤት 🙏 http://t.me/WuludeBirhane7
Показати все...
የእንጦጦ መ/ስ/ቅ/ሥላሴ ቤ/ክ. ዉሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ዋና ገጽ

ይህ የእንጦጦ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ዉለደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ዋናው ገፅ ነው በዚህ የሰንበት ት/ቤት ዋና ገፅ ላይ በሰንበት ቤት ስም የሚለቀቁ ትምህርቶች፣ መዝሙሮች፣ ኪነ ጥበባዊ ፅሁፍፎች እና የሰንበት ት/ቤቱ መልእክቶች የሚተላለፍበት ነው። ስለሆነም ወደ ዋናው ገፅ እንድትቀላቀሉ ይሁን የሰ/ት/ቤቱ ሥራ አመራር ጽ/ቤት

የወንድማችን የሻረው ተፈሪ አባት አርፈዋል ፤የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ17/9/2013 በ8:00በሥላሴ ቤተክርሰቲያን ይፈፀማል ።
Показати все...
💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐 የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥራ አመራር በሀገረ ስብከቱ ከሚገኙ ከ200 በላይ ከሚደርሱ ሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር አባላት ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አደረገ!!! 💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐 ግንቦት 15/2013 ዓ.ም በሀገረ ስብከቱ ከሚገኙ 200 በላይ ሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር አባላት ጋር በተደረገው ግማሽ ቀን የፈጀ ውይይት በሁለት ወቅታዊ አጀንዳዎች ዙሪያ በጥልቀት ፥ በሰፊው ፥ ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ ... ውይይት የተደረገ ሲሆን ፦ #በእጀንዳ_አንድ ላይ የጃንሆይ (ጃን) ሜዳን እና የመስቀል አደባባይን ጉዳይ የተመለከተ ጥልቅ ውይይት የተደረገ ሲሆን የጃንሆይ (ጃን) ሜዳን ጉዳይ ሀገረ ስብከቱ ከሚመለከታቸው ጋር አበክሮ በመወያየት ጉዳዩ የመጨረሻ መፍትሔ እንዲያገኝ እንዲያደርግ ። ቅዱስ ሲኖዶስም አቋም እንዲይዝበት እንዲጠየቅ ። እንዲሁም በዚሁ እጀንዳ ላይ ወቅታዊው በሀገረ ስብከቱ ምዕመናን በእጅጉ ያሳዘነው የተፈጸመውን ስህተት እና መዋቅራዊ ጥሰት በተመለከተ ጉባዔው የእርምት የመፍትሄ ሐሳቦች አቅጣጫ ያስቀመጠ ሲሆን በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ሀገረ ስብከቱ አስቸኳይ የእርምት ምላሽ እንዲሰጥበት ተጠይቋል:: ይህ የማይፈፀም ከሆነ ግን ጉዳዩን ለቅዱስ ሲኖዶስ በማቅረብ መፍትሔ እንዲወስድበት በቤተ ክርስቲያን ልጅነት መንፈስ አቅጣጫ ተይዟል፡፡ #በእጃንዳ_ሁለት ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ን በተመለከተ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ላይ ውይይት ተደርጎል:: ለውይይት በር የከፈተውን ሐሳብ ወደ ጎን ትተን በምንም መልኩ የቤተክርስቲያኒቷን ቀኖናዊ ሥርዓት ለመናድ እየተወራ ያለውን በእንደራሴ ጉዳይ የሚናፈሰውን መረጃ በፍፁም አንቀበልም ፤ ቤተክርስቲያኒቷን እና አባቶችን እንደቀደመው ጊዜ ለመከፋፈል የሚሠራውን ሂደት እንቃወማለን ፤ መንፈስ ቅዱስ እና ቅዱስ ሲኖዶስ የመረጣቸውን ቅዱስ ፓትርያርክ ማንም ከመንበራቸው እንዲነካብን አንፈቅድም ፤ ቅዱሳን አባቶቻችንን ሳይገባ ሰድቦ ለሰዳቢ የሚያጋልጣቸውን ሁሉ በእጅጉ እናወግዛለን ፤ ሰሞኑን በተለያዩ ሚዲያዎች የቅዱስ አባታችንን የክብር ስም በንቀት በማሳጠር እና ባልተገባ መልኩ ለማቅለል እየተሠራ ያለውን ሂደት በፍጹም አንቀበልም ይህን ያደረጉ ሁሉ ክብርት ቤተክርስቲያኒቷን ፥ ቅዱስ አባታችንን እና ምዕመኑን ሁሉ በይፋ ይቅርታ ሊጠይቁ ይገባል ፤ ብፁዓን አባቶቻችንም እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነው የቤተክርስቲያንን ክብር እና መብት ፥ ... ለማስጠበቅ ከምንጊዜውም በላይ በቁርጠኝነት በአንድነት እንዲሰሩ በልጅነት መንፈስ የውይይቱ ተሳታፊዎች ጠይቀዋል... በዚህም የመጨረሻ የመፍትሔ ሐሳብ በማስቀመጥ ፤ በቀጣይም አጥቢያ ድረስ የሚደርስ ሰፊ እንቅስቃሴ ለማድረግ ስምምነት ላይ ተደርሷል :: ማስታወሻ 👉 በውይይቱ ላይ የተወሰኑ ውሳኔዎችን የአንድነቱ ሥራ አመራር በተዋረድ ለቅዱስ ሲኖዶስ ፤ ለሀገረ ስብከቱ ፤ ለምዕመናን እንዲሁም ለሚመለከታቸው ሁሉ በደብዳቤ እና በመግለጫ በቀጣይ የሚያደርስ ይሆናል :: ግንቦት 15/2013 ዓ.ም የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት 💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐🥀💐
Показати все...
+ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ አለ + አንድ ሰው እኔ ክርስቲያን ነኝ ሲል በአንድ ቃል ዜግነቱንና ቤተሰቡን ሥራውን ጠቅልሎ ተናገረ ማለት ነው:: የሚያምን ሰው ከሰማያዊት ኢየሩሳሌም በቀር ምድራዊ ከተማ የለውም" 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 "እግዚአብሔር የሚጠይቅህ ጥቂት ነው የሚሠጥህ ግን ብዙ ነው 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 "የዚህ ዓለም ኑሮ እንደ እንቅልፍ ነው:: በዚህ ሕይወት የሚሆኑት ሁሉ ሕልም ናቸው:: በሕልምህ ባለጸጋ ብትሆን ምን ጥቅም አለው? በእንቅልፍ ልብ ሆኖ በቅዠት የሚናገር ሰው ስለ ንግግሩ አይፈረድበትም:: እኛ ግን በዚህ የእንቅልፍ ዘመን የምንናገረው ሁሉ የዘላለም ሕይወትን ሊያሳጣን ይችላል" 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 "በድህነት እና በረሃብ የሚሰቃዩ ሰዎች እንደ ሠለስቱ ደቂቅ ናቸው:: ከድህነት የበለጠ ምን እሳት አለ? ከረሃብስ የሚበልጥ ምን ነበልባል አለ? ሦስቱ ወጣቶች እሳት ውስጥ ሆነው እንደዘመሩ በመከራ ውስጥ ሆኖ ፈጣሪን የሚያመሰግን ሰው የመከራው እሳት ውኃ ይሆንለታል:: ለድሆች ምጽዋትን የሚሠጥ ሰው ደግሞ ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት የታደገውን የእግዚአብሔር መልአክን ይመስለዋል" 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በትንንሽ ነገሮች ማመስገንን ከለመድህ ትንንሽ ነገሮች ብዙ ስለሆኑ ሕይወትህ ምስጋና ይሆናል" 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በኀዘን ጊዜ የማያጉረመርሙ ከንፈሮች ከቅዱሳን ሰማዕታት እኩል ናቸው 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ሕይወታችን ለሌሎች የሚያበራ ቢሆን ኖሮ ስብከት ባላስፈለገ ነበር:: በምግባራችን መመስከር የምንችል ብንሆን ኖሮ ቃላት ባላስፈለጉ ነበር:: እውነተኛ ክርስቲያኖች ብንሆን ኖሮ አረማውያን ባልበዙ ነበር ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
Показати все...
+++ ከካም መንገድ ተመለሱ +++ * ዛሬ ቤተክርስቲያናችንን እጅግ በጣም እየጎዳት ያለው ከውጪው የጥቃት እንቅስቃሴ ይልቅ የውስጡ ውስብስብ እንቅስቃሴ ነው። በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ብዙዎች ቤተክርስቲያንን ክፉኛ እየጎዷት ነው። በአደባባይ ዕርቃኗን እየገለጡ በአሕዛብ ፊት መዘባበቻ ከማድረግ በዘለለ በምእመናን መካከል ጥርጥርና መለያየት እንዲፈጠር እያደረጉ ነው። * እርግጥ ነው በቤታችን እጅግ በርካታ ችግሮች አሉ። ቢሆንም ችግሮቹ የውስጣችን እንጂ የአደባባይ አይደሉም። ስለዚህ በቤታችን እንጂ በአደባባይ የምንከራከርባቸው፥ የምንተቻችባቸው፥ የምንሰዳደብባቸው፥ የምንጎሻሸምባቸው ወይም የእውቀታችንን ልክ የምናሳይባቸው ወይም የጽሁፍ ችሎታችንን የምናስመሰክርባቸውም አይደሉም። * ማንም አዋቂ ነኝ ካለ ለምን በአደባባይ የወንጌሉን የምሥራች በመስበክ የቤተክርስቲያንን የአገልግሎት ግዳጅ አያግዝም? ወይም ምእመናን በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲበረቱና ወደ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን እንዲቀርቡ አያንጽም? * ሌላው ደግሞ በእውቀትና በመንፈሳዊነት መካከል የሰማይና የምድር ያህል ልዩነት መኖሩንም መገንዘብ ያስፈልጋል። አዋቂ ሆነህ መንፈሳዊነቱ ላይኖርህ ወይም መንፈሳዊነቱ ተትረፍርፎ እውቀት ላይኖርህ ይችላል። “ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም፤ ትንቢት ቢሆን ግን ይሻራል፤ ልሳኖች ቢሆኑ ይቀራሉ፤ እውቀትም ቢሆን ይሻራል።”(1ኛ ቆሮ.13፥8) * እንደዚሁ ሙያና መንፈሳዊነትም መለየት አለበት። ማንኛውም የሙያ ደረጃና ምስክርነት ካላጣመሩትና ካልኖሩበት በቀር ከመንፈሳዊነት ጋር ተዛምዶ ላይኖራቸው ይችላል። ሰው ሙያው በሥነ መለኮት ዘርፍ ቢሆንም እንኳ ባለሙያ እንጂ መንፈሳዊ ላይሆን ይችላል። ስለ እግዚአብሔር ሊያውቅ እግዚአብሔርን ግን ላያውቅ፤ ስለ ሃይማኖት ሊያውቅ ሃይማኖቱን ግን በሕይወት ላያውቅና ላይኖርበት ላይጠቀምበትም ይችላል። * በፌስ ቡክና በዩቲዩብ ሚድያዎች የምንዘረግፋቸው የቤተክርስቲያን የውስጥ ጉዳዮች የሚያንጸው ማንን ነው? መእመናንን ነው እንዳንል ምን ያህሉ ኦርቶዶክሳዊ ነው ፌስ ቡክና ዩቲዩብ የሚጠቀመውና የሚከታተለው? ለመሆኑ እየተደረገ ያለው ስብከት ነው? ማንቃት ነው? መካሰስ ነው? መፈራረጅ ነው? ተቆርቋሪነት ነው? ወይስ ዝናንና ክብርን ማሳደግ ነው? ወይስ የቲፎዞ(ተከታይ) ብዛት ፉክክር ነው። * የቤተክርስቲያንን የውስጥ ጉዳይና ችግር አደባባይ ላይ ማስጣት ዕውቀትም፥ ተቆርቋሪነትም፥ አገልግሎትም ሊሆን አይችልም ከውጭ ኃይሎች ይልቅ ቤተክርስትያንን በራስ እጅ ማፍረስ እንጂ። በካም መንገድ መጓዝ እንጂ። * እኔ እላለሁ፣ ማናችንም ከቤተክርስቲያን አንበልጥምና አካሄዳችን እንዲህ ከሆነ፥ መንገዳችን የካም ከሆነ ዕውቀታችንም፥ ተቆርቋሪነታችንም፥ አገልግሎታችንም ይቅርባት። በርግጠኝነት ነው የምነግራችሁ በዚህ አንዳች አይጎድልባትም፤ እንዲያውም እፎይ ትላለች። የካም የግብሩ መጨረሻ በፃድቅ አባቱ መረገም እንደሆነ ቅድስት ቤተክርስቲያን እንዳትረግማችሁ ጥንቃቄ አድርጉ። * አክቲቪስቶችም ብትሆኑ፥ ምንም ታላቅ ብትባሉ፥ ምንም ሚሊየን ተከታይ ቢኖራችሁ፥ በጀመራችሁበት መንገድ እንደ ሀሳባችሁ ሂዱ እንጂ የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ አማኝ ብትሆኑም እንኳን በአደባባይ ከምትራቀቁበት የቤተክርስቲያን የውስጥ ጉዳይ ታቀቡ አይደለም ውጡ!!! ይበልጡኑ ደግሞ በናንተ አያምርም። ፖለቲካና ማኅበራዊ ጉዳይ የአደባባይ ነው፤ የቤተክርስቲያን ጉዳይ ግን የአማኞቿ የውስጥ ጉዳይ ብቻ ነው። * በማኅበራዊ ሚድያ የአድማጭ ተመልካች መድረክ ከፍታችሁ ለቤተክርስቲያን የማይናቅ አስተዋፅዖ እያበረከታችሁ ያላችሁ አገልጋዮችም በዚህ ረገድ ድካማችሁን የሚያመክንና ዓላማችሁን የሚፃረር ድርጊት ውስጥ እንዳትወድቁ ብርቱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ በእግዚአብሄር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ። መርሐ ግብር ስታዘጋጁ ከቤተክርስቲያን ጥቅም አኳያ በርዕሰ ጉዳዩ የሚገኘውን ትርፍና ኪሳራ አስቀድማችሁ አስሉ። መርሐ ግብራችሁ ለሁሉም ክፍት ስለሆነ ኦርቶዶክሳውያኑን ብቻ አድሬስ የምታደርጉ መስሏችሁ እንዳትዘናጉ። ስለዚህ በርዕሰ ጉዳይ መረጣ ላይ የውስጥ ችግራችን አጀንዳ ሆኖ አደባባይ እንዳይወጣ ብርቱ ጥንቃቄ አድርጉ። * እንደኔ እንደኔ የቤት ውስጥ መድረክ እንዲዘጋጅና ተቆርቋሪ ነኝ፥ የቤተክርስቲያንን ችግር የሚፈታ የመፍትሄ ሀሳብ አለኝ፥ በዕውቀቴ ማገዝ እችላለሁ የሚል ኦርቶዶክሳዊ ሁሉ ከማኅበራዊ ሚድያ ወርዶ ወደ እልፍኙ ተሰብስቦ እንዲከራከርና በዚህ የጭንቅ ጊዜ በእውነተኛ ልጅነት ቤተክርስቲያንን ከመከራዋ እንዲታደጋት ምክር፥ ቅስቀሳና ግፊት ብታደርጉ ባለውለታ ትሆናላችሁ። * ስለዚህ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ወይም ባለማስተዋል ቤተክርስቲያንን የማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ሰቅላችሁ መከራዋን የምታበዙባት አባቶች ወንድሞችና እህቶች እባካችሁ ከካም መንገድ ተመለሱ፣ ከእርግማንም ራቁ። (ዘፍ.9፥20-27) * ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን። እንደ ቸርነቱ፥ እንደ ይቅርታውና እንደምኅረቱ እንጂ እንደ ኃጢአታችንና እንደ በደላችን አያድርግብን።
Показати все...
ዓለም ዘዉ.ብ: እንኳን ለታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ††† ††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ††† ††† ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ††† ††† ቅዱስ ያሬድ:- ከእግዚአብሔር ያገኘነው አባታችን : ክብራችን : ሞገሳችን ነውና በምን እንመስለዋለን? *አንደበቱ ጣፋጭ (ጥዑም):: *ልቡናው የቅድስና ማሕደር:: *ሕሊናው የምሥጢራት ሠረገላ ነው:: *እስከ አርያም ተነጥቆ የማይፈጸም ምሥጢርን የተመገበ ማን እንደርሱ! ሊቀ ሊቃውንት እዝራ ሐዲስ እንደሚሉት:- "ቅዱስ ያሬድ ለኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከራስ ጸጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ : ሙሉ አካሏ ነው::" ††† የሊቁ ዜና ሕይወት በጥቂቱ ††† ††† ቅዱስ ያሬድ የተወለደው በ505 ዓ/ም አክሱም አካባቢ ሲሆን እናቱ ክርስቲና (ታኡክልያ) አባቱ ደግሞ ይስሐቅ (አብድዩ) ይባላሉ:: ሊቁ በሕጻንነቱ ምሥጢር (ትምሕርት) አልገባው ብሎ ይቸገር ነበር:: ትምሕርት እንቢ ያለው ሰነፍ ስለ ነበር አይደለም:: በጥበበ እግዚአብሔር እንጂ:: ምን ትምሕርት ባይገባው ጾምና ጸሎትን ያዘወትር ነበር:: ልቡናው ደግሞ በእመቤታችንና በልጇ ፍቅር የታሠረ ነበር:: አንድ ቀን ግን መምሕሩ የነገሩት ቀለም አልያዝሕ አለው:: ሲፈትኑትም ባለመመለሱ ተገረፈ:: ዱላው በጣም ስለ ተሰማው ቅዱሱ ከመምሕሩ ኮብልሎ ማይ ኪራሕ አካባቢ ሲደርስ ደክሞት አርፎ እግዚአብሔር ትጋትንና ተስፋ አለመቁረጥን ከትል አስተማረው:: ትሏ ስድስት ጊዜ ወድቃ በሰባተኛው ፍሬዋን ስትበላት ተመልክቷልና:: ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ መምሕሩ ተመልሶ : ይቅርታ ጠይቆ ትምሕርት ጀመረ:: ሊቁም ትጋትንና ጸሎትን ከሰጊድ ጋር አበዛ:: እግዚአብሔር ደግሞ በድንግል እናቱ አማካኝነት የምሥጢር ጽዋን አጠጣው:: ካህኑ ያሬድ እንዲያ አልገባህ ያለው ምስጢር ተገልጦለት በጥቂት ጊዜ ብሉይ ከሐዲስ ወሰነ:: በምሥጢር ባሕርም ይዋኝ ጀመር:: ያን ጊዜ ሰማያዊ ዜማ አልተገለጠም ነበርና በጸሎት ላይ ሳለ ተደሞ መጣበት:: ሦስት መላእክት በሦስት ወፎች አምሳል መጥተው አነጋገሩት:: ድንገትም ነጥቀው ወደ ሰማያት : ወደ ልዑላኑ መላእክት ዘንድ አደረሱት:: ሊቁ በሰማያት ልዩ ምሥጢር : ልዩ ምስጋናና ልዩ ዜማን አዳመጠ:: ይሕንን ምስጋና ብዙ ቅዱሳን ቢሰሙትም ቅዱስ ያሬድ ግን ይዞት እንዲወርድ ተፈቀደለት:: ሊቁ ወደ ምድር ተመልሶ በታላቅ ተመስጦ አክሱም ጽዮን ውስጥ በሃሌታ አመሰገነ:: ሕዝቡና ንጉሡም ከጣዕሙ የተነሳ አደነቁ:: ቅዱስ ያሬድ ለተወሰነ ጊዜ በአክሱምና ደብረ ዳሞ ሲያገለግል ቆይቶ : ከመሬት ክንድ ከስንዝር ከፍ ብሎ ለእመቤታችን አንቀጸ ብርሃንን ደርሶላት ከሃገሩ ወጣ:: ††† ቅዱስ ያሬድ በቀሪ የሕይወቱ ዘመናት:- 1. አምስት ያሕል መጻሕፍትን ጽፏል:: 2. በጣና ቂርቆስ : በዙር አባና በሌሎችም ቦታዎች ወንበር ዘርግቶ ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርቷል:: 3.በሰሜን ተራሮች አካባቢ በትጋሃ መላእክትና በተባሕትዎ ኑሯል:: ††† በ576 (571) ዓ/ም በተወለደ በ71 ዓመቱ በዚህች ቀን ተሰውሯል:: ††† አባቶቻችን:- *ጥዑመ ልሳን *ንሕብ *ሊቀ ሊቃውንት *የሱራፌል አምሳያ *የቤተ ክርስቲያን እንዚራ *ካህነ ስብሐት *መዘምር ዘበድርሳን *ማኅሌታይ *ልዑለ ስብከት እያሉ ይጠሩታል:: ††† የቅዱሱ ጸሎትና በረከት ሃገራችንን ከክፉው ሁሉ ይጠብቅልን:: ✝ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✝
Показати все...
የሰንበት ትምህርት ቤቱ ገቢ አሰባሰብ ኮሚቴ ያዋቀረው የዕጣ ኮሚቴ የሕንጻውን የውስጥ በሮች ለማሰራት የገበያ ዋጋውን አጣርቶ ባለሙያዎች አነጋግሮ የተምቦላ ትኬት ተቀብለው በተለያዩ ምክንያቶች ገንዘብ ገቢ ያላደረጉ አባላት ሥም ዝርዝር 1. መምህር ታምሩ ይሽጥላ 1,250 2. ኪዳኔ ኃይሌ 250 3. ፌበን ፍሳሀ 250 4. ሙሉእመቤት ፍቃዱ 250 5. ዩሐንስ ወርቁ 250 6. ደርዛ ገረሱ 250 7. ታሪኩ ቶቾኖ 625 8. በሱፍቃድ በቀለ 250 9. ዳዊት ተስፋዬ 250 10. ወንዲፍራው 250 11. አልማዝ ታዬ 250 12. አማኑኤል ሙልጌታ 250 13. ረድኤት ደርበው 1,250 5,625 የገቢ ሁኔታ በጠቅላላ እጣው ተሸጦ የተገኘው ገቢ 110,414.00 ለተምቦላ ትኬት በአቶ ተሸመ ንጉሴ የተሸፈነ …… 5,500.00 ድምር 115914 ከአባላት ይሰበሰባል ተብሎ የሚጠበቅ ……………... 5,625.00 በአጠቃላይ ከአባላት ይሰበሰባል ከሚባለው ጋር 121,539.00 የወጪ ሪፖርት ለዕጣው የሚያስፈልጉ ማቴርያሎች ወጪ 25,414.00 ለዕጣ ትኬት ማሳተሚያ 5,500.00 ድምር 30,914.00 በአባላት ዕጅ ያለ ዕዳ 5,625.00 ከወጪ ቀሪ በኮሚቴው እጅ የሚገኝ 85000
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.