⏰⏰⏰⏰ ⏰ ⏰⏰⏰⏰
⏰ #ዝግጅት ⏰
⏰ #ለመምመለሻ_ዕለት ⏰
⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰
بسم الله الرحمٰن الرحيم
الحمد لِله رب العالمين والصلاة والسلام على سيدنا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين.
ውድ የቻናላችን ተከታታዮች ሰላሙ ሏሂ ዐለይኩም ወ ረሕመቱሁ ወ በረካቱሁ
አሕባቢ እንዴት ናችሁ?
_______________/////____________________
#ክፍል_8
و عن سفيان الثوريّ: "كلّ معصية عن شهوة فإنه يرجىٰ غفرانها، و كلّ معصية عن الكبر فإنّه لا يرجىٰ غفرانها؛ لأنّ معصية إبليس كان أصلها من الكبر بينما زلّة آدم كان أصلها من الشهوة "
ታላቅ ዓሊምና ሰለፍ ከሆኑት ከሱፍያነ ሰውሪይ በተወራው:-
" #ማንኛውም_ከሸህዋህ_ወይም_ከስሜት_የመነጨች_ወንጀል_መሀርታዋ_ይከጀላል። #ማንኛውም_ከኩራት_የመነጨች_ወንጀል_መሀርታዋ_አይከጀልም። ምክንያቱም #የኢብሊስ_ወንጀል_መሰረቱ_ኩራት_ነበር። #የነቢዩ_ሏህ_አደም_ስህተት_ከሸህዋ_ወይም_ከስሜት_የመነጨ_ነበር።
_____________________________________
#ኩራት የአሏህ እንጅ የማንም አይደለም። የሰው ልጅ ሊኮራ አይገባውም። ኩራት ከባድ ወንጀል ነው። ከኩራት የመነጨ ወኝጀልም ምህረትን የማግኘቱ ዕድል በጣም ጠባብ ነው። ኢብሊስ ለዕነቱ ሏሂ ዐለይህ ኩራቱ ነው ለዚህ ውርደት ያበቃው መጨረሻውም የጀሃነም ነው።
ከሸህዋ የመነጨ ወንጀል ግን ምህረትን የማግኘት ዕድሉ ሰፊ ነው። ነቢዩ ሏህ አደም ያቺን ክብርንና ውርደትን የማታስከትል የሆነችን ሰህተት የፈፀሙት በኩራት ሳይሆን በሸህዋ ምክንያት ነበር። ተውበት በማድረጋቸውም አሏህ መሀርታን ለግሷቸዋል።
የሰው ልጅ በተለይ እኛ ነፍስያችን ደካማ ስትሆን ስሜታችን ሸይጧንም ተጨምሮ የተለያዩ ወንጀሎችን እንድንሰራ ሊገፋፉን ይችላሉ። ሆኖም ግን በማንኛውም ሁኔታ ላይ ኩራት የሚባለውን ነገር ካላስወገድንና ተውበት ካላደረግን ወንጀላችን የከፋ ይሆናል። መሀርታንም ሳናገኝ ልንሞት እንችላለን። አሏህ ይጠብቀን።
‼️‼️‼️
#ኩራት ማለት አዳዲስ ልብሶችንና ጫማዎችን መልበስ አለያም መዋብ ሳይሆን 👉 ሌላን ሰው (ደሃ ስለሆነ አለያም በዕድሜ ያነሰ ስለሆነ) አሳንሶ ማየትና ሐቅን አለመቀበል ነው።
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
አሏህ ከኩራት ጠብቆ ከመልካሞች ጋር ያድርገን አሕባቢ!
አሚን!
________________\\\\\\_________________
صلُّ على الحبيب!💝
________________________________________
#ክፍል_9 ቀጣይ ሳምንት ጠብቁን!
ተቀላቀሉን
👇👇👇
@HabeshiyyuAbderiy