cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Amharic Bible Study Head 📚

" የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ፤ በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ፤ በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ በጸጋው በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤" (ቆላ 3: 16) ✔ Group @AmharicBS ✔ Channel @AmharicBSH Comment @Dave_b_cj or @AmharicBS_bot

Більше
Країна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
Рекламні дописи
3 770
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

🌻 አዲስ አመት እንዴት ነው? 🌻
Показати все...
👍
👎
⚠️ መሰማት አለበት ትልቅ ማስጠንቀቂያ ⚠️ ይሄ መልክት ከግሩፓች አባል ከሆነች @Wawa_Wawi የተላከ መልዕክት ነው። @Wawa_Wawi በጣም ነው የምናመሰግነው ተባረኪልን። እነኚ ሰዎች Inbox የሚያደርጉላቹ ከሆነ እባካችሁን እኔን @SML_LMYH አናግሩኝ ወይም እንዲያናግሩኝ አድርጉ። @AmharicBSH ¤
Показати все...
🆃🅷🅴 🅻🅰🆂🆃 🅿🅰🆁🆃 🔥🔥"የሚያየኝን ፊት ለፊት አየሁት "(የራሽያ ወጣት ኮሚኒስት)😱🔥 ክፍል :13 ✍.......ኮሚኒስቶች ሀገር እያለን እንደ ሌለን ፣ዜግነት እያለን እንደ ሁለተኛ ዜጋ ቢቆጥሩንም ለእኛስ ሀገር አለች በእጅ ያልተሰራች ግንበኞች የምድር ጠቢባን ያላዩዋት ከአመታት ከዘመናት ከአባቶቻችን ከነአብረሀም ያቆም ይስሀቅ በፊት የተሰራች። በበጉ ደም የተጠራች ቅድስት ሀገር አለችን።ከሞት ወዲያ ለኛ መጠለያ ሆና አልፈን ከአምላካችን እና ከጌታችን ጋር እንደ ገና መኖር የምንጀምርበት ሀገር አለችን። ከባእድ ከዚህ ጊዜያዊ ድንኳን መጠለያ አልፈን በልኡል ዙርያ ከበን እፎይ የምልበት በክርስቶስ ላመኑ ወደ በጉ እራት የሚታደሙበት ሀገር አለችን፣#መንግስተ ሰማይ። መጠለያችን ርስታችን ቀንና ለሊት ሳያቋርጥ የመልአክት ዝማሬ ሽብሸባ የምንሰማበት እኛም እንደ መለአክት ሆነን በዙፋኑ ፊት የምንሆንበት።ግርፋት ስቃይ መከራ መራርነት ምቀኝነት ሰው በሰው ወገን በወገኑ የማይጨካከንበት ሀገር ርስት አለን። በምስክርነታቸው አለምን ድል የነሱ በበጉ ደም ልብሳቸውን አጥበው ያነፁ የሚያዜሙ ቅዱሳን ወገን አለን ሊያውም ሰማያዊ ወገን። ትምህርት እና እውቀት እያለን እንደ መሀይም ምንም እንደማናውቅ ቢቆጥሩንም እኛስ ለአለም ሞኝነት የመሰላት ግን በብዙ ጥበብ እና ድካም ሳይሆን አመታት ሳንቆጥር ዝቅ ብለን በዙፋኑ ስር ተንበክከን ታላቁን ጌታ የጥበብ መጀመሪያውን አውቀናል። በማመን መዳንን ከነሱ ሰውሮ ለኛ ገልፆአልና። ዛሬ ውበት እያለን ስለ እምነት የምንከፍለው ስቃይ መከራ ፣ጭንቀት ፊታችንን ቢያበልዘውም ከሰው መልክ ወጥተን ብንጎሳቆልም በሰማይ የለው አባታችን ከፊቱ በሚወጣው ብረሀን ፀዳል የውበትና የእውነት ጨረር ለነብሳችን ሲፈነጥቅ ልዩ ሰዎች እንሆናለን።ያለማቋረጥ ቁፋሮ አታካች ስራ ቅዝቃዜ እና ብርዱ ቢገለንም ጌታን ስናስብ የአሁኑ መከራችንን እንረሳለን። አንድ ጊዜ ያለወትሮአችን በዚያ ቅዝቃዜ እና ብርዱን መግለፅ በሚያስቸግረው ለሊት ጠሩን። የተለመደውን ስቃይ ከተቀበልን በኋላ ወደ አንድ ሜዳ ወሰዱን። ጨለማ ነው ቦታው ሜዳ መስሎን ስንራመድ ይዞን ወደ ታች ሁለት ሜትር ያህል ገባ። ከታላቅ ድንጋጤ የተነሳ የሞትን ያህል ሆነን ወደቅን። ከስሩ ቅጠል የሚመስል የተቆራረጠ ነገር ተቀብሎ አሰመጠን። እንደምንም ብለን ስንነሳ ያ ቅጠል ስስ እሾህ መሳይ ነገር ሰውነታችንን ወጋግቶ ከመቅፅበት ፊታችንን ና እጅ እግራችንን በአንድ ጊዜ አሳብጦ ያሳክከን ጀመር።(እንደኛ ሀገር ሳማ መሆኑ ነው) ኡኡኡኡኡኡ አልን። በመሬት ተንከባለልን። ያው ቅጠሉ ተመልሶ ይወጋናል።ከትንሽ ደቂቃዎች በኋላ እየጎተቱ አወጡን በዚያን ጊዜ የማልረሳው ሁላችንም በሹክሹክታ ""አይዞህ አይዞሽ ጌታ ይመጣል ""እየተባባልን ስንፅናና ያሳለፍነው ለሊት አይረሳኝም።ያበጠው አይናችን አፍንጫችን እስከማይለይ አድበልብሎናል።ማን ማን መሆኑ እስከማይለይ ድረስ ይህን በመሰለ ስቃይ ውስጥ እያለን ወታደሮቹ ትተውን ሔዱ። ያን ግዜ በዛ ጭለማ ስፍራ ያየነው መለአክ እስከአሁን ያስደንቀናል። ቁመቱ ረዘም ያለ ልብሱ በታላቅ ብረሀን ነፀብራቅ የተከበበ የሚመስል አሁን ከፀጉር ቤት ተሰርታ የወጣች ዘይት የበዛበት ፀጉር ሆኖ እስከአንገቱ ጫፉ በጥንቃቄ የተጠቀለለ የወርቅ ዘንግ ሚመስል የያዘ ታላቅ የብረሀን ነፀብራቅ የተሞላ ፊቱ ርህራሄ የሚነበብበት ትኩር ብለው የማይንቀሳቀሱ አይኖች ሽፋሽፍቶቹም ችፍግ ብለው የበቀሉ ሲሆን ያጠለቀው ጫማ ወርቅ የሚመስል ባለ ልዩ ውበትና ድምቀት ያለው አንድ መለአክ ከፊት ለፊታችን በመሬትና በአየር መካከል ቆሞ አየን። ይህን ስናይ ሁላችንም ካለንበት ስፍራ ጩኸን ወደ ኋላ ወደቅን። እሱ ግን እጁን ዘርግቶ ንፁህ በሆነ የመስኮብ ቋንቋ እንደ ባለስልጣን መስሎ ""እናንተ #የልዑል አምላክ ታማኝ ባርያዎች ሰላም ለናንተ ይሁን""አለን። ማን ደፍሮ ይመልስለት። ያ ከደቂቃዎች በፊት ድካም ግርፋት ያቆሰለው ሰውነታችን በዚያ በሰማነው ቃል ተበረታታና ምንም እንዳልተፈፀመብን ሆነን ብድግ ብድግ አልን።ቢሆንም ወደኋላችን እያፈገፈግን መሔድ ጀመርንና ካለንበት ሆነን ወደ ምድር ወድቀን ሰገድንለት። እርሱ ግን በታላቅ ድምፅ ቁጣ በሚመስል ""እንዳታደርጉት ተጠንቀቁ ""አለን።ይቀጥላል......... 🔥🔥ይቀጥላል የቀሩትን ገፅ ለማግኘት join ይበሉ🔥🔥 🔥🔥 @AmharicBSH 🔥🔥 🔥🔥join👆👆👆👆🔥🔥
Показати все...
🔥🔥"የሚያየኝን ፊት ለፊት አየሁት "(የራሺያ ወጣት ኮሚኒስት) 😱🔥 ክፍል :12 ✍......በነዚህ ጨካኞች ሰወች ትእዛዝ እሳት አቀጣጥለህ ካነደድከው በኋላ እራስህ ግባ ብሎ ሲያዙ የሚሰማችሁን ስሜት ልትመዝኑ ትችላላችሁ። ወይም አማኝ እናት ክርስቶስን አልክድም በማለቷ ምክንያት ህፃን ልጇን ፊት ለፊቷ እያየች ቢያርዱባት ወላጆች ምን ይሰማችኋል? በሷ ቦታ ሆናችሁ ለአንድ ጊዜ አስቡ።እንግዲያውስ ቅዱሳን ስለ እምነታቸው ሲሉ የተቀበሉትን አሰቃቂ መከራ እንደሚገባ ልገልፅላችሁ አልችልም።ኮሚኒስቶች መጥፎነታቸው ሰወችን ማሰቃየት ወይም መግደላቸው ብቻ አይደለም። በሀሰተኛ ወሬ የሰውን ህሊና ማቆሸሻቸው እንጂ።አላማቸው ክርስቲያኑን ወደ ክህደት መምራት ሲሆን በትምህርት ቤት ህፃናት እና ወጣቶችን እግዚአብሔርን እንዲጠሉ ያስተምሯቸዋል። እኔ በእስር ቤት ያሳለፍኩት አስራ ሶስት አመታት ወደ ኋላ ተመልሼ ሳስበው በጣም ያረኩኛል ፤ያስደስቱኛል፣በደስታዬ ካገኘሁት ሰላምና እረፍት ይልቅ በመከራ ጊዜ ያገኘሁት #ኢየሱሴን በስቃዬ ስቃዩን ፣በግርፋቴ ግርፋቱን ፣በደም መፍሰስ የመስቀል ደሙን ይበልጥ እንዳስበው አድርጎኛል።ግርፋት ከሌለ ከባድ ስራ ካላጋጠመን በቀር በቀላል ቁፋሮ ጊዜ ድካማችንን ሳናስብ የለ ማቋረጥ እንፀልያለን።#ጌታን ለስምንት ጊዜ ፊት ለፊት ነጭ ውብ ልብስ ለብሶ ባማረና በተዋበ መልኩ ተገልጦልኝ ያየሁ በመከራዬና በእስር ሰዐቴ ላይ ነበር።ከዚህ ሁሉ በላይ አንድ ቀን በደረሰብን ከባድ ቶርች ለሶስት እና ለአራት ቀን እራሳችንን ስተን አጠገባችን ያሉት ከአሁን አሁን ሞቱ ብለው ሲጠብቁ ሳሉ ጌታ #ኢየሱስ እንደ ሰው ተገልጦ አሁን ካላችሁ እና ከገጠማችሁ ይልቅ ትወዱኛላችሁን?ሲል ጠየቀን። ሁላችንም የሞተው ሰውነታችን ሒወት ዘርቶ ያን ሁሉ ሰአታት የተገረፈ ሳይሆን ልምጭት ያረፈበት ሳይመስል ተፈውሰን ሀይል ተሞልተን የተየሳንበት ቀን አይረሳንም።ብዙውን ጊዜ ከሰው አእምሮ ና ህሊና ማስተዋል በላይ በሆነ አሰቃቂ ግርፋት ና ልፋት መፈጠራችንን እስክንጠላ ከስቃይ ለማረፍ ብለን ጌታን ለመካድ እስክንገዳገድ ያደርጉናል። ፊታችን በደም ተለውሶ ስንደናበር ኢየሱስን ክዳችሁ በሌኒን እመኑ ይሉናል፣ያን ጊዜ ጌታ በልዩ #ውቀቱ ይገለጥልናል፤የመስቀል ፍቅሩ ፣ስቅላቱ ድቅን ሲልብን እንበረታለን።በዙርያችን ከነብያት እና ከሀዋርያቶች ያላነሰ መከራ የደረሰባቸው ወገኖች አሉ። ይሁን እንጂ ኮሚኒስቶችን የሚጠላ ልብ ግን የለንም። በደላቸው ምንም የከፋ ቢሆንም ይህ የቀራኒዮ ስቃይ ኮሚኒስቶችን ያቅፋል፤እነሱ የሚያደርሱብን ስቃይ ባይገባቸውም እኛ ግን የመስቀሉ ፍቅር የገባን ሰዎች እነርሱን ያለልክ እንወዳቸዋለን። ካሰቃዩን በኋላ ጌታ ይባርካቹ ስንላቸው አእምሮአቸው ይመታል።ኮሚኒስቶችን ሊለውጣተው የሚችለው የፍቅር ሀይል ብቻ ነው።ጥላቻ የሰውን አይን ያሳውራል።ሌላው አንዲት ሀገር እንድትለወጥ ከፈለግን ለመሪዎች መፀለይ አለብን።መሪ ሲለወጥ ለጌታ ነገር ልቡ ሲከፈት እነርሱን ወደ ጌታ ለማምጣት ህዝቡ አስቸጋሪ አይሆንም።ለዚህ ነው ጌታ የእባቡን እራስ እንድንቀጠቅጠው ያዘዘን።ራሱን ሲመታ ይሞታል እኛ ግን ሆዱን እና ጅራቱን እየረገጥን መልሶ እነኛኑ ነድፎ ይገለናልና።ሀይለኛውን ሳናስር ለመበዝበዝ ማሰብ ሞኝነት ነውና።ስለዚህ እኛ እንደደረስንበት መሪዎች በጌታ ቢየምኑ ህዝቡ ቀቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መሪውን የመከተል ግዴታ ወይም ፍላጎት ይኖረዋል።እኔ ምን አልባት ከነበረብኝ ስልጣንና ሀላፊነቴ የተነሳ ወደ ቀደመው ኑሮዬ ለመመለስ ከሁሉ ይልቅ የከፋ ስቃይ ተቀብያለው።የቀኝ ጡቴን በአሰቃቂ ሁኔታ አጥቻለሁ። የስጋ ጡቴን ለክርስቶስ ስል ባጣውም እውነተኛ ጡቴ ልቤ ግን በሰማይ አለ በጽዮን ይቆየኛል።እንደወንድሞቼ እና እህቶቼ ለውዴ #ለኢየሱስ በሰማዕትነት አልሞትኩም እንጂ ስቃይ እስኪ በቃኝ ጠግቤአለሁ። ይሁን እንጂ የዘላለም ሕይወት ሳያገኙ ለሚጠፉት ኮሚኒስቶች ለደቂቃዎች እንኳ ጠልቻቸው አላውቅም ፤ይህ ደግሞ የሁላችንም ጠባይ ነበር። በሳይቬርያ እያለን አንዳንድ ሴቶችን ይወስዱና ስጋዊ ፍላጎታቸውን በተደጋጋሚ ከተጠቀሙባቸው በኋላ እንደ ርካሽ ዋጋ ይወረውሯቸዋል ፣ይህ ብቻ አይደለም፣ማርገዛቸውን ሲያውቁ ከኮሚኒስት ቢሮ የሚደርስባቸውን ቅጣት ስለሚያውቁ ኃጥያታቸውን ለመሸፈን ወስደው በጥይት ይገድሏቸዋል፤ ቢሆንም ልንወዳቸው እንጂ ልንጠላቸው አልተፈቀደልንም። ስለ አባታችን እና ወንድማችን ሪቻርድ ውምብራንድ ከብዙ ስቃይና መከራ በኋላ ስለኛ ምን ትላለህ ብለው ኮሚኒስቶች ሲጠይቋቸው የሚፈሰው ደማቸውን እየጠራረጉ ፈገግ ብለው ለእናንተ ያለኝ ፍቅር በወጣትነት ዘመኔ ባለቤቴን ለማግባትና ለመውሰድ የነበረኝ ፍፁም ደስታ የተለየ ለሊት ያህል ነው ይሏቸው ነበር።ኮሚኒስቶች ይህ ነው በማንለው በመከራ ስቃይ ቀጥተውናል።በላያችን የተፈፀመው ግፍና ስቃይ የፈጠሩብንን ህመም እና ቁስል ለልጅ ልጅ ለዘለአለም ይቅር የሚያስብል ከልባችን ይሁን ከህሊናችን ሊጠፋ የሚችል አይደለም። ይሁን እንጂጰ""የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው "የተባለውን የፍቅሩንና የመስቀሉን ቃል ወዴት እንጣለው። ስለዚህ እነሱ ከአቅማችን በላይ በሆነ ሁኔታ ገርፈው ረግጠው ቀልደው አመናጭቀው በዚያ ወፍራምና ጠንካራ ጫማቸው ረግጠው እንደ እቃ ሲጫወቱብን ስቃይ የፈጠረው ጣር ጩኸት በሰለለው ጉሮሮአችን በቀረችልን ትንሿ ስትንፋሳችን አንደምንም አሰባስበን """እንወዳችኋለን💗💖💖ጌታ ይባርካችሁ """ስንለቸው ይደነግጣሉ። አንዳንዴም በመደነቅ ፈዘው ያዩናል🙁።ሌላ ጊዜ ደግሞ እንደዚህ የምትሉን ወዳችሁን ሳይሆን የናንተ ፓርቲ አባል እንድንሆን ነው ይሉናል።እነርሱ የፈለጉትን ይበሉ እንጂ እኛ ግን እንወዳቸዋለን። ይህ ነው በልባችን የሞላው ፤ ከዚህ በላይ ባያምኑን ግን እምነት እና ፍቅር ዳቦ ሆኖ አናጎርሳቸው፤ወይም ውሀ ወይም ቮድካ አይደል በብርጭቆ ቀድተን አናጠጣቸውም። እኛ ግን #የኢየሱስ ልብ አለን ጌታ ይመስገን።ይቀጥላል...... 🔥🔥ይቀጥላል የቀሩትን ገፅ ለማግኘት join ይበሉ🔥🔥 🔥🔥 @AmharicBSH 🔥🔥 🔥👆join 👆👆👆👆🔥🔥 🗒ክፍል:13 እና የመጨረሻውን በቅርቡ ይጠብቁ 🖊
Показати все...
🔥🔥"የሚያየኝን ፊት ለፊት አየሁት"(የራሽያ ወጣት ኮሚኒስት)😱🔥 ክፍል:11 ✍........"#ኢየሱስ የሚባለውን ተው""ይሉና እምቢ ይሆናል መልሳችን ፤የዛን ጊዜ በያዙት ሳንጃ እየሰማን ጡታችንን ይቆርጡናል። በዚህ ሳይጠግቡ ሲቀሩ ደግሞ መርፌ ይወጉንና በሰመመን ሆነን ስንተኛ ኦፕሬሽን አድርገው ቀኝ ወይም ግራ ሳንባችንን ይበሱታል፤ኩላሊታችንን ወይም የጨጓራ አንጀታችንን ይቆርጡና ይወጡታል፤ከዚያ በኋላ ወደ እስርቤታችን ይመልሱናል።መላው ሰውነታችን ቆስሏል፤ደም በደም ሆነናል፤ ከሰመመን ስንነሳ መላ አካላችንን ይደክመናል፤አልቅሰን ጮኸን ""ጌታ ሆይ በዚህ ሁሉ መከራ ያንተን የመስቀል ፍቅርህን እንድካፈል ስለወደድክልኝ አመሰግንሃለሁ።ደግሞም እወድሃለሁ ""ብለን ስንናገር አንዱ ሌላውን አንቆ ይስመዋል፤""ጎሽ በርቺ ጌታን ከዚህ በኋላ አንካደው ፤በዚህ ሞተን ፊቱን እንይ"እንባባላለን።ከዚያ በኋላ የተገረፍንበት ያበጠው ሰውነታችን ተሽሎን ሲተወን በሰውነታችን የተሰነጠቀው እንደነገሩ የተሰፋው ነገር እናያለን። ህመሙ እየቆየ ያሰቃየናል።በዚህ አልፈናል፤በሳይቬርያ አካሉ ያልጎደለ :አይኑ ያልፈሰሰ፣የጆሮ ታንቡር ያልተበጠሰ የጽዮን አርበኛ የለም።እነሱ ባሰቃዩን ቁጥር ወደ #ኢየሱስ ያስጠጉናል፤በተሰቃየን ቁጥር እየሱስን ያስናፍቁናል። አንዳንዴ ደግሞ በተለያዩ ወንጀል ሞት የተፈረደባቸው ሰዎች ወደ እኛ ገርፈው እፊታችን ይገድሏቸዋል፤""እናንተ ካልካዳቹ የሚቀጥለው ጥይት ለእናንተ ነው ""ይሉናል፤እኛን ለማስደንገጥ አስበው። ከዚህ ሁሉ በላይ ለኛ የሚከብደን ግን ይሔንኛው ነው።ከእኛ መሀል ያገቡ ወንዶችን እና ሴቶችን ለይተው ቤተሰቦቻችንን ይጠሩና ተመካከሩ ይሉናል፤ህፃናት ልጆቻችንን ከፊታችን በኤሌክትሪክ ይገርፉዋቸዋል፤በመጨረሻም እያየን ይገድሉዋቸዋል። በእኛ እምነት ምክንያት ምንም የማያውቁትን ህፃናት ይቀጥፋሉ።የእስረኞች ሚስቶች እያየን በፊታችን በስጋ ይገናኙዋቸዋል።እራቁታቸውን በማውጣት ለአንዲት ሴት የማይባል ንግግር በመናገር ይዘብቱባቸዋል፣ያዋርዱዋቸዋል። ኮሚኒስት ወታደሮች የእስረኞችን ባሎች ጠርተው ከሌላ ሴት ጋር ተኛ ይሉታል። የኤሌክትሪክ ገመድ ለኩሰው እያቃጠሉት ስቃይን ፈርቶ ሳይወድ ከማያውቃት ሴት ጋር "ሴክስ"ያደርጋል እስረኛ ሚስቱ እያየች።""እንዴት ነው ከዝችኛዋየድሮ ሚስትህ እና አሁን ከተኛህባት ሴት መካከል ያለውን የደስታ ልዩነት ግለፅልን ""ይሉታል። የኤሌክትሪክ ሀይል ሲለቁበት ሳይወድ የቀድሞዋን ሚስቱን(እስረኛዋን)ሙልጭ አድርጎ ይሰድባታል፤ያንቋሽሻታል።ያስነውራታል ይህ ሁሉ ለኛ ይገባናል። እነርሱ (የእስረኞቹ ባሎች)ግን ሚስጥሩን ስለማያውቁት ይሰቃያሉ። ከዚያ በኋላ ሳይወድ በሚናፍቃት ሚስቱ ፊት የደረገው አንሶ ያስነወራትን ሲያስብ በፀፀት በምሬት ታንቆ ይሞታል፤ህፃናት ወላጅ አልባ ይሆናሉ።በንጋታው የኮሚኒስት ልሳን በሆነው""የኘራቫዳ ""ጋዜጣቸው ላይ "ሚስቱ #በኢየሱስ በማመኗ የተናደደ አንድ ራሺያዊ እራሱን ሰቅሎ ተገኘ፤ህፃና ልጆቻቸው ያለ ወላጅ ቀሩ፤""ብሎ የሀሰት ወሬ በጋዜጣው ላይ ይወጣል።አንድ ጊዜ ደግሞ አንድ የሀያ አመት ወጣት ምን ብለው እንዳሳመኑት አናውቅም ብቻ እኛ ጋር አምጥተውት የገዛ አባቱን ገርፎ ይሔን አጉል እምነትህን ተው በማለት ክፉኛ ይገርፈው ጀመር።አባቱ ሲናገር ጌታን እድሜ እንዲጨምርልኝ ምለምነው ለመኖር ሳይሆን ልጁን #ኢየሱስን መስክሬለት አሁንም እንደምወደው ገልጬለት እንዳይ ብቻ ነው """አለን። በመስኮቪ የፓርላማ አባላት ጉባኤ ፀሀፊና የቦርድ ሰብሳቢ የነበረው የዛሬው የክርስቶስ እስረኛ ወንድማችን በዚህ የኮንስትራክሽን (እስር ቤት) ውስጥ ራሺያዎች ብቻ አይለንም የታሰርነው ከሩማንያ ፣ከቺስኮቫሊያ ፣ከሀንጋሪ አምስት የሚሆኑ ደግሞ ከቬትናም ነበሩ።በጠቅላላ ከ 20-25 ሺህ እስረኛ በሳይቬርያ ውስጥ ነበርን።በዚህ ሁሉ የሚሆነው ስቃይ አላማው ከኢየሱስ ለመለየት ነው።ሲያቅታቸው ደግሞ ለቤተሰባችሁ ለልጆቻችሁ ስትሉ አትተውም ይሉናል፤ዘመድ ቤተሰብ ከኢየሱስ በኋላ ነው ስንላቸው ይናደዳሉ።ይገርፉንና ድቦች ወዳሉበት ስፍራ ወስደው ድቦቹን አስቆጥተው እንዲቦጫጭቁን ያደርጋሉ። የሚደርስብን መከራ ሁሉ መልካም አይደለም፤የመከራው አላማ ግን ለመልካሙ እየሱስ መሆኑን ስለምንረዳ ሀዘን ስቃያችንን ያስታግሰዋል። ደግሞም በሰማይ ያለውን ሀገራችንን ያስናፍቀናል፤በዚያ ስቃይ ፣ግርፋት ፣ኮሚኒዝም ፣ ጨካኝ ድቦች የሉም።#ኢየሱስ ከአባቱ ጋር ቅዱሳን መላእክት በዙሪያው ከበውት እኛም የዛሬው የምድር ጎስቋሎች ያን ጊዜ የሰማይ ሀገር ባለርስት ወራሾች የዘለአለም ዘመናት ባላገር ሰዎች እንሆናለን። 🤦‍♀ወደ ኋላ ልመልሳችሁና ያ መፅሐፍ ቅዱስ ያመጣልን ወንድም ከእኛ ጋር ለስምንት አመት ያህል ከተሰቃየና ለጌታ ዋጋ ከከፈለ በኋላ እስከ ዛሬ ድረስ በማናውቀው ምክንያት ይህን ወንድማችንን ከመካከላችን ወስደው እያየነው በሳንጃ ወግተው ገደሉት። አሰቃቂ ቀን ነበር😖😫።እሱ ሲሞት ነብሱ አልወጣ ብላ ስታስጨንቀው እነሱ እላዩ ላይ ይሸኑበት ያላግጡበት ነበር።እሱ ሲሞት ለመጨረሻ ጊዜ ሊናገር የፈለገው ነገር ያለ ይመስላል፤ሁለት ጊዜ አይኖቹን ከፈት ዘጋ በማድረግ ጣቶቹን እያንቀሳቀሰ ሊናገር የፈለገውን ሳይናገር ወደ ግራ ጎኑ ዘንበል ብሎ ነብሱን ሰጠ።አንዳንድ ጊዜ የኮሚኒስት ሰዎች ጭካኔ ለመግለፅየ ያስቸግራል😞🤭። ይቀጥላል............ 🔥🔥ይቀጥላል የቀሩትን ገፅ ለማግኘት join ይበሉ።🔥🔥 🔥🔥 @AmharicBSH 🔥🔥 🔥🔥join 👆👆👆👆🔥🔥 🗒ክፍል:12በቅርቡ ይጠብቁ 🖊
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
#Zelalemawi #Coming_soon
Показати все...
🔥🔥"የሚያየኝን ፊት ለፊት አየሁት"(የራሺያ ወጣት ኮሚኒስት) 😱🔥 ክፍል:10 ✍.........ምን አይነት ሰወች ናችሁ።የምታመልኩትን የምታውቁ ለቆማችሁለት አላማ የማትበገሩ ፅኑአን ሀያላን ናችሁ።የእናንተ ወዳጅ እና ወገን መሆኔን ሳስብ ደስተኛ ያደርገኛል አለን።የያዝነውን መፅሃፍ ቅዱስ ኮሚኒስት ወታደሮች እንዳያገኙብን በብዙ ጥንቃቄ እንጠብቀው ጀመር። ምክንያቱም ቢያገኙት የሚያደርሱብንን መከራ ስለምናቀው ነው።መፅሃፍ ቅዱሱን የምንደብቅበት ቦታ ስለሌለን ፣በረዶውን ቆፍረን ነበር ምናስቀምጠው ፤ከከባድ ስራ ስንመለስ ግን በረዶው መፅሃፍ ቅዱሳችንን አበስብሶት ለመግለጥ እንቸገር ነበር፣በዚህ ሁሉ ግራ ግብት ይለናል። የሳይቬርያን በረሀ ማንም አይወደውም ፣ከቅዝቃዜው ሌላ ከሰው ተለይተህ ከድቦች እና ከባህር እንሰሳት በስተቀር የሚታይ ነገር የለም። ስለዚህ ማንም ወታደር በፍቃዱ ወደዚህ ስፍራ የሚመጣ የለም።ከዚህ የተነሳ በዚህ ላለነው ክርስቲያኖች በሳይቬርያ እስር ቤት የሚፈፀመውን ግፍና መከራ ለመታደግ ሲባል ወንድ ክርስቲያኖች ወታደር ሆነው ይቀጠራሉ። የውትድርና ስልጠና ከወሰዱ በኃላ በፈቃደኝነት ወደ ሳይቬሪያ ሔጄ አንድ አመት ላገልግል በማለት ያመለክታሉ። ያን ጊዜ የወታደር ክፍሉ በመደነቅ አስፈላጊውን ነገር ያሟሉላቸውና ይልኳቸዋል።አንዳንዴ ደግሞ ለምን ሳይቬሪያ መሄዱን መረጥክ?፤ሲላቸው የሀገሬን ታሪካዊ ቦታ ለማየት ነው በማለት ይናገራሉ። እነርሱ ግን በኛ የሚደርሰውን ግፍ ስለሚያውቁ እኛን ለመርዳት አስበው ነው፤በዚያን ጊዜ ለመሄድ ሲያስቡ ለኛ የሚሆን መድሀኒት ትንንሽ ልብሶች እና ለእህቶች የሚጠቅም ነገር ይዘው ይመጣሉ። ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ይሄን ለእናንተ የምንመሰክርላችሁን ታሪክ እና ስውር ደብዳቤዎች ያመላልሱልናል።በዚያ ሳይቬሪያ የሚደረገውን ግፍ ያስታወቅነው በዚህ መንገድ ነበር። ደግሞ ወደ ሳይቬርያ የሚላክ👮‍♂ወታደር አንድ አመት ቢያገለግል እንደ ሁለት አመት ይቆጠርለታል። ብርዱና ቅዝቃዜው እንደ አንድ አስተዋፅኦ ይቆጠርላቸዋል።ደመዙም እጥፍ ይሆናል፤በዚህ ጊዜ የሚከፈለው ደሞዝ በእስር እና በግርፋት ላሉት ለወንጌል ማስፋፊያ እናውለዋለን። በሳይቬርያ እስር ቤቶች ክርስቲያኖችን ለመግረፍ የተመደቡ ወታደሮች ታሪክ እና ማንነት ልንገራችሁ። በመስኮቪች ከተማ በከፍተኛ ወንጀል የሚታሰሩ ወይም ኮሚኒስት እንቅስቃሴ አራምደዋል የተባሉ መንግስትን ለመገልበጥ አሲረዋል የተባሉ በአጠቃላይ ከበድ ያለ ወንጀል የፈፀሙ ሰወች ወይም ሰው በመግደል ካልሆነ ደግሞ("መርድረርስ")የጭከና ወንጀል የፈፀሙ ሰወች አስረው ብዙ ካሰቃዪአቸው በኋላ እንዲህ ይሏቸዋል። ""አንተ የፈፀምከው በደል ቀላል አይደለም፤አንተ ብቻ ሳትሆን ያስጨርሳል፤እነሱም ካንተ ወንጀል ጋር ተባብረው እንደሆን ማን ያውቃልዐ፤ ስለዚህ ሁላችሁንም እፈጃችኋለን ይሏቸዋል። ያን ግዜ እስረኛው ሲማፀናቸው እሺ እንግዲየውስ አንተ ከዚህ ነፃ መሆን ካለብህ እኛ የምናዝህን ስራ በመስራት አገርህን ትክሳለህ በማለት ይነግሩታል። እስረኞቹ እኛን እና ቤተሰባችንን አትግደሉን እንጂ ወደምትፈልጉበት ቦታ እንሔዳለን ፤እዘዙን እንታዘዛለን ይሏቸዋል። ከስቃይ ለመዳን ሲሉ።ከዚያ በኋላ ወደ አንድ ወንጀለኞች አሉ ወደ ተባለው እስር ቤት ይወስዱትና '"ይህ ወንጀለኛ ከበድ ያለ ጥፋት ሰርቷል።እኛ ስንመረምረው ሚስጥሩንና ወንጀሉን አልገልፅ ብሎ አስቸግሮናል፤እስኪ አንተ በፈለከው መንገድ ገርፈህ ቶሮች አድርገህ አሳምነህ የልቡን ለማወቅ ሞክር ፤ከዚያ በኋላ ነፃ ትወጣለህ። """""ይሉታል።ልብ አድርጉ ይህ ሰው በሰራው ወንጀል በፖሊሶች ሲሰቃይ የከረመ ነው፤ስለዚህ እራሱን ነፃ ለማውጣት ሲል እሱ ትላንት ያለፈበትን መከራ ይረሳና እስረኛውን እጥፍ ያሰቃያል።ይህም ደግሞ እነረሱን የሚያስደስት ስለሚመስለው ነው።ያንጊዜ ይመጡና አየህ አንተ በሰራኸው ምርመራ ስራ አገርህን ሞስኮቪ ልትወድቅና ሊደርስባት ከነበረው ታላቅ ሽንፈት ታደካት፤ይህ አስተዋፅኦህ ደግሞ ይመዘገብልሀል፤ተብሎ ከሰማይ መና ያወረደ ያህል ያመሰግኑታል። በዚህ አይነት ሁኔታ ካሳመኑት በኋላ ወደ ምርመራ ቤሮ ተጠርቶ በመጀመርያ ከሁለት እስከ አምስት ቮድካ ተጋብዞ ቤተሰቦቹ ወደ እስር ቤት እንዲመጡና እንዲያገኛቸው ይፈቀድለታል። ይሁን እንጂ ከቤተሰቡ ጋር የሚነጋገራትን እያንዳንዷን ቃል በራድዮ እና በቴሌቪዥን ይከታተሉታል። ከዚህም ሌላ ""ከጥቂት ቀናት በኋላ ትፈታለህ ""ተብሎ የውሸት ተስፋ ይነገረዋል፤በዚህ ተደስቶ ሲስቅ ደስታውን ሲገልፅ ሲያዩት አሁን ተፈተህ ስትወጣ ስራ ፍለጋ ከምትንከራተት ለምን ከኛ ጋር ተቀጥረህ መርማሪ ሆነህ አትሰራም ይሉታል።ደመወዝና ልብስ ሲያሳዩት ወገኖቹን ለማሰቃየት ሳያቅማማ እሺ ይላል።በራሽያ ያለው የስራ አጥነቱን ያውቀዋልና አያመነታም። ይግባችሁ ልብ በሉ እነዚህ ሰወች ለመንግሥት ስራ አስፈላጊ ሆነው ሳይሆን በሳይቬርያ ለታሰርነው የክርስቶስ አማኞች በብርቱ ስቃይ ለማስካድ ከጌታ አላማና በሰማይ ከተዘጋጀልን የማያልፍ በሚመስል ስቃይ ለማስቀረት ነው።#ለዚህ ይጠቀሙባቸዋል። ስለዚህ እነዚህ ሰዎች ከፍተኛ ወንጀል ሰርተው ከሞት ላዳኗቸው አለቆቻቸው ለማስደሰት የእኛን ስቃይ ከስቃይ አይቆጥሩትም። በዚህ አይነት አሰቃቂ ቶርች ሰልጥነው ከመጡ ሰዎች ከሚያደርሱብን ሰቆቃ ጥቂቱን እንግለፅላችሁ።ይቀጥላል.......... 🔥🔥ይቀጥላል የቀሩትን ገፅ ለማግኘት join ይበሉ።🔥🔥 🔥🔥 @AmharicBSH 🔥🔥 🔥🔥join👆👆👆👆🔥🔥 🗒ክፍል :11በቀርቡ ይጠብቁ🖊 🔑share 💯💯💯💯💯💯
Показати все...
🔥🔥"የሚያየኝን ፊት ለፊት አየሁት"(የራሽያ ወጣት ኮሚኒስት) 😱🔥 ክፍል :9 ✍️...........እስዋ ስትወድቅ አጠገቡ የነበረው ሌላ ወታደር በያዘው መሳሪያ ግንባሩን በጣጠሰው፣ደሙ በዛ ነጭ በረዶ ላይ ሲፈስ ታዋቂ አርቲስት የሳለው ውብ አበባ አስመስለው። ቀጠለና መሳርያውን ወደ ኮሚኒስቶች በመመለስ ሌላስ በነዚህ እስረኞች ላይ ተኩሶ ሊገድል የሚደፍር ሰው ካለ ይንገረኝ በማለት አነጣጠረባቸው።መልስ ሲያጣ ከመኪነው በመውረድ መሳርያውን ወደ ሰማይ ያንጣጣው ጀመር።ጓደኞቹ አንድ ላይ "ፓዳዥዴ ቲሆንቺኩ "(ተረጋጋ ቀስ በል)ማንኛችንም ብንሆን አንገድላቸውም፥አንተ እንዳልክ እናደርጋለን፤መሳርያህን ጣለው በማለት ይጭዋጭዋሁ ጀመር። እሱ ግን በእጁ የያዘውን ጥይት እስኪያልቅ ድረስ እንደእብድ ሆኖ ይተኩስ ነበር። በመጨረሻ እንደሰከረ ሰው ይንገዳገድ ስለነበር ከአሁን አሁን ሁላችንን ፈጀን ጨረሰን ብለን ሰጋን።ከድቦች ጥርስ ያዳነን አምላክ ከሰው ጥይት ሊያድነን እንደሚችል ተጠራጠርነው። በመጨረሻም ያ ሰው ወደ እኛ ዘወር ብሎ በመጠጋት ""ማሩኝ ይቅር በሉኝ የእንጀራ ጉዳይ ሆኖብኝ ነው። አሁን ግን እኔ እንደእናንተ ውብ እናት እህት እና ከልቤ የማትጠፋ እጮኛ አለችኝ። ቤተሰቦቼ እንደእናንተ በሰማይ በዚህ በሚታየው ጋላክሲ ሰማያዊ ጠፈር ባሻገር #አገር አለ ምድር አለ ብለው የሚያምኑ ናቸው።እኔ ወደዚ ከተማ ወደማይታየው በአየር ላይ ሀገር አለ ወደምትሉት ሰው እና የፓርቲያችሁ መሪ ወይም ንጉስ አስተዋውቁኝ እና ማህበርተኛ ልሁን፣አባል ለመሆን እፈልጋለሁ ፣የሚከፈል ነገር ካለ አዋጣለው። ከአንድ ፓርቲ ወደ ሌላ ፓርቲ መቀየር አዲስ ሀሳብ (አይዶሎጂ)ታገኛለህ የማለው አባባል ለመቀበል ተገድጃለሁ። ከዚህ ቀደም ቤተሰቦቼ ስለዚህ ጉዳይ ሲተርኩልኝ በጣም ትንሽ ህፃን ሆኜ እሰማ ነበር። ያ አፈ ታሪክ ከደመናት ከጠፈር ባሻገር አገር አለ ያሉትን አፈታሪክ በገሀድ አይቼዋለሁ።ከሀይለኛ ድቦች ጥርስ ንጥቂያ ያዳናችሁ መሪያችሁን እከተላለሁ፤እኔም የእናንተ ማህበርተኛ የፓርቲያችሁ አባል መሆን ወስኛለሁ """ብሎ እየተንቀጠቀጠ እና እያለቀሰ የለበሰውን ጃኬት አውልቆ ለአንዳችን ሰጠን።ሸሚዙን አውልቆ ለሌላዋ ሰጣት።ካኔቴራ እና ሱሪውን አውልቆ አከፋፍሎ ጨረሰ።በጥይት የተመታችዋን እህታችንን እያቀፈ የፈሰሰው ደሟን እየጠረገ ለጓደኞቹ ይማፀን ጀመር ካላችሁ የልብስ መአት አንድ አውጡና ስጧቸው። ባዶ ሰውነት እራቁት ገላ ማየት ህሊናችሁ አይወቅሳችሁም።እህት የላችሁም ወይም አፍቃሪ የላችሁም ፣ይህ ሁሉ ባይሆን ቢያንስ እናት የሌለው ሰው የለም። እዘኑላቸው ለአመታት አሰቃየናቸው፤ዛሬ ግን እንራራላቸው ይል ጀመር።እኛም በሚሆነው እየተገረምን በመሀከላችን አስገብተን ከከበብነው በኋላ ስለ እርሱ መፀለይ ጀመርን። ጌታ ስለእርሱ ባደረገው በጎነት እያመሰገንን ሳለን ሌሎች ኮሚኒስቶች ጌታ ከድቦች ሲያድነን ያላዩ ወታደሮች በሁለት ትላልቅ መኪና መጥተው ምንድነው? እንዴት ነው? ሳይሉ እያዳፉ እየረገጡ እየገረፉ በጥፊ በካልቾ እየወለወሉን ጭነው ወደ እስር ቤታችን ወሰዱን። ማጎርያ ቤታችን ስንደርስ በእጃችን በእግራችን በፀጉራችን ባገኙት አካላችን እየጎተቱ አወረዱን።ያ በጎነት ያደረገልን ወንድም ማንነቱ ሳይለዩ አብሮኖና ባዶ ያለ ልብስ ሲያዩ እየቀጠቀጡ አስገቡት።በዚህ መሀል የሰጠንን ልብስ ሰጥተነው እራሱን እንዲልጥ ብንለምነውም ከእናንተ አልለይም ብሎ እምቢ አለ።ጌታን መርክረንለት የጌታን ፍቅር ገለፅንለት እና በብዙ እምባ ጌታን ተቀበለ። ይህ በድንገት ባገኘነው ቅዱስ ሰው በብዙ ነገር ይረዳን ጀመር። ይህ በእንዲህ እያለ ለሊት ወታደሮች መጥተው ምን እንደሰሙ አናውቅም ብቻ ወንድማችን የሰጠንን ልብስ ነጥቀው ወሰዱብን። ጌታ ለዚህ ወንድም ሰርቶ የማይደክም ጉልበት ሰጠሰቶት ስለነበር ሁላችንንም በቁፋሮ በከባድ ስራ ያግዘን ነበር።አንድ ጊዜ ከዚ ቀደም ያገኘናት የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅስ አንስተን ስናነብ አይቶ ጠየቀን። የመፅሐፍ ቅዱስ ቃል መሆኑን ስንነግረው ብድግ ብሎ በዛ ለሊት ወጣና ሔደ።ሁላችንም ተደናገጥን። ምክንያቱም አማኝ መስሎ ልባችንን ከሰለለን የምናደርገውን ካየ በኋላ ነግሮ መከራችንን እንዳያብስብን ተጠራጠርን። ከአንድ ሰዐት በኋላ በፍርሀት እና በድንጋጤ ሆነን ሳለን ያ ወንድም በብዙ ላብ ተጠምቆ እያለከለከ በእጁ አራት መፅሀፍ ቅዱስ ሙሉ ያልተቀደደ ይዞልን መጣ።ማመን አቃተን፤ ሁላችንም የጌታ ቃል የሆነውን በብዙ እምባ እና ናፍቆት የምንጠማውን እንደ እንጀራ የምንራበውን ያን ቅዱስ መፅሐፍ ስናይ ሁላችንም ተነስተን የመንጠቅ ያህል ተቀበልነው። ትኩስ እሬሳ የወጣበት ቤት እሰኪ ይመስል አለቀስን። ሁኔታችንን ያየ ያ ሰው ፊቱ ላይ መደናገጥን ጭንቀትን ተሞልቶ ምን ሆናችሁ? ይህን መፅሀፍ አትወዱትምን? ይህኮ እንድናቃጥለው ብለን የሰበሰብነው መፅሐፍ ነው፣ቦታውን ስለማውቀው እኮ ነው ያመጣሁላችሁ፤የማትፈልጉት ከሆነ ልመልሰው በማለት ድንጋጤ በሞላው ፊት ይጠይቀን ጀመር።መከራ መቀበላችን ስቃያችን ለክርስቶስ እና ለዚህ ታላቅ ቃል መሆኑን ስንነግረው ተደነቀ።ይቀጥላል....... 🔥🔥ይቀጥላል የቀሩትን ገፅ ለማግኘት join ይበሉ።🔥🔥 🔥🔥 @amharicbsh 🔥🔥 🔥🔥join👆👆👆👆🔥🔥
Показати все...
ጨው ውሀ ሊቀዳ ሔዶ በዛው ቀረ ምን ሆኖ? #ሟሙቶ 🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊🙊 ብዙ የሚያሟሟ ነገር በሞላበት ጊዜ ላይ ነው ያለነው። social media ያሟሟል የትምህርት ቤት ጓደኛ ያሟሟል የሰፈር ጓደኛ ያሟሟል የስራ ባልደረባ ያሟሟል የቲቪ ፕሮግራሞች ያሟሟሉ መጽሐፍት ያሟሟሉ ብዙ ብዙ ውሀ ሊቀዳ ሔዶ እንዳንሟሟው ጨው እንዳንሟሟ ራሳችንን ከውሀ ከሚያሟሟ ነገር እንጠብቅ "ቀዳሁ ብሎ #መቀዳት አለና።" አተረፍኩ ብሎ መክሰር አለ ክፉ ወደበዛበት ሀጢያት ወደ ነገሰበት ወደ ሚያሟሟው አንሂድ አንጠጋ አንቅረብ እንሽሸው ጨው አንዴ ከሟሟ በኋላ ጨዉን ለይቶ ማውጣት ከባድ ነው ብዙ ጊዜ እና አቅም energy ይፈልጋል:: 🌊🌊🌊🌊🌊🌊🌊🌊🌊🌊🌊🌊 ጨው ውሀ ውስጥ ለመሟሟት ጥቂት ደቂቃ ይፈጅበታል ከወሀው ለመለየት ግን በchemistry ቀመር boiling process ያስፈልጋል። 🔬🔬🔬🔬🔬🔬🔬🔬🔬🔬🔬🔬🔬🔬🔬🔬🧪🧪🧪🧪🧪🧪🧪🧪🧪🧪🧪🧪 boiling ደግሞ እሳት አለው መቃጠል አለው መንደድ አለው። በሀጢያት መንደር ከሟሟን እና ከተገኘን በኋላ ወደ ቀደመው መልካም ማንነታችን ለመመለስ ብዙ ጊዜ እና ብዙ እሳት እናልፋለን። የዘራውን ማጨድ ስላለብን ከዚህ ሁሉ በፊት ግን አስቀድመን ራሳችንን ከሚውጡን ነገሮች እንጠብቅ መጽሐፍ እንዲህ ይላልና ⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️ 1ኛ ጴጥሮስ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁰ ሕይወትን #ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች #ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል፤ ¹¹ ከክፉ #ፈቀቅ ይበል፥ መልካምንም ያድርግ፥ ሰላምን ይሻ ይከተለውም፤ ¹² የጌታ ዓይኖች ወደ #ጻድቃን ናቸውና፥ ጆሮዎቹም #ለጸሎታቸው ተከፍተዋል፥ የጌታ ፊት ግን ክፉ ነገርን በሚያደርጉ ላይ ነው። @AmharicBSH
Показати все...
የእሁድ ፕሮግራም በችግር ምክንያት ስላልነበረ በጣም ይቅርታ 🙏
Показати все...