cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

ETHIO12.COM

.ትኩስ መረጃ ethio12.com

Більше
Країна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
Рекламні дописи
953
Підписники
Немає даних24 години
-47 днів
-2030 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

የቅኔዋ ንግሥት ጂጂ 'አድዋ' የተሰኘውን ድንቅ ሥራዋን እንዴት እንደሠራችው.... #ጂጂ_እና_አድዋ (የጂጂ የቀድሞ ማኔጀርና ጓደኛዋ እንዲሁም ቤዝ ጊታሪስት ቶማሥ ጎበና Thomas Gobena (Tommy T) ጋር ካደረግኩት ቆይታ የቆነጠርኩት ነው።) ጋዜጠኛው፦ "ቶሚ፤ አድዋ ይገርመኛል። ሲሰራ ታስታውሳለህ??" ቶማሥ፦ "ታስታውሳለህ?? እንዲያውም ይገርመኛል፤ ልንገርህ። ፕሮፌሠር ሀይሌ ገሪማ አድዋ የተሠኘውን ፊልማቸውን በአሜሪካ እንደነገ ሊያስመርቁ እንደዛሬ የኔን ባንድ ተከራዩ። Instrument ብቻ ነበር ልንጫወት የታሰበው። ከዚያ ፕሮፌሠር ሀይሌ መጡና "እስቲ፤ የፊልሙን ምርቃት የሚከፍት ዘፋኝም ፈልግ። ብቻ ሴት ኢትዮጵያዊት ትሁን" አሉኝ። እሺ ብዬ ማንን እንደምጋብዝ እያሰብኩ ቤቴ ሄድኩና ከጓደኞቼ ጋር ልምምድ ጀመርን። ማታ 2 ሰዓት ተኩል ገደማ ጂጂ ሁለት ሺፍት ሥራዋን ጨርሳ ወደ ቤቷ ልትሄድ ስትል ጎራ አለች። "አንቺ፤ ፕሮፌሠር ሀይሌ ዘፋኝ ይፈልጋሉ። ለምን አንቺ አትሠሪም?!" አልኳት። "መጣሁ!" ብላ እየሮጠች ወጣች። 4 ሠዓት ሲል መጣች። "አዲስ ሙዚቃ ሠርቻለሁ። እናጥናው።" አለች። "አንቺ ልጅ አብደሻል እንዴ?! አይሆንም!" አልኳት። ጋዜጠኛው፦ ለምን???! ቶማሥ፦ እንዴ ፕሮፌሠር ሀይሌ እኮ ናቸው። በጣም ነው የምንፈራቸው። የማይሆን ሥራ ይዘን ገብተን አበላሽተን ቢገሉንስ?? ከዚያ "ዝምብለሽ "እማማ ኢትዮጵያ" የሚለውን ዝፈኝ እንጂ አይሆንም" አልኳት። ተስማማች። በማግስቱ ጠዋት መድረክ ላይ ወጥተን ልትዘፍን ስትል በምልክት "ፀጥ በሉ!" አለችን። በጣም ብዙ ህዝብ ነበር። ትላልቅ እንግዶች ከፊት ነበሩ። እኛ መጫወት አቆምን። "አድዋ"ን ያለ ሙዚቃ በድምጿ ብቻ መዝፈን ጀመረች። "የሠው ልጅ ክቡር..........." ስትል ክው አልኩ። ሰምተነው አናውቅም። በ 1 ሰዓት ተኩል የተደረሠ ዘፈን ነው። ከዚያ ከሀይሌ ጋር የተቀመጡ ነጭ ምሁራን እንባቸውን ያወርዱታል። ቋንቋው አይገባቸውም። ጂጂ ራሷ ደንግጣ እየዘፈነች ወደኔ ዞራ "ምንድነው?!" የሚል አስተያየት አየችኝ። በምልክት "ቀጥይ!" አልኳት። ስትጨርስ ቤቱ በእግሩ ቆመ። ፕሮፌሠር መጡና "እቺን ጉደኛ መተዋወቅ እፈልጋለሁ" ብለው ተዋወቋት። ያልመጣ ሠው አልነበረም። ከነሱ መሀል የ 7 ግራሚ አሸናፊዋና የ Bob Marley ልጅ ሚስት Lauren Hill ነበረች። እሷም ከትላልቅ የሙዚቃ ፕሮዲዩሰሮች ጋር አገናኘቻት። ከአመታት በኋላ አልበም ሆኖ ወጣ። ይሄ ነው ታሪኩ።"
Показати все...
Показати все...
በሼፍ ሳሙኤልሰን ማርኩስ ስም ሃያት ሪአገንሲ ሆቴል የሚከፍተው ሬስቶራንት ስልጠና አወዛገበ “የደንበኞችን ጾታ መጥራት አትችሉም”

ሼፍ ማርኩስ ሳሙኤልሰን ውድ የዓለማችን የምግብ አዘጋጅ ባለሙያና በዓለም ዙሪያ የበርካታ ታዋቂ ሬስቶራንቶች ባለቤት ነው። ቀደም ሲል እናቱ ሳይሞቱበት ካሳሁን ጽጌ ይባል የነበረው ድንቅ ሙያተኛ ከእህቱ ጋር በጉዲፈቻ ወደ ስዊዲን ወላጆቹ ዘንድ ካመራ በሁዋል የዓለማችን ድንቅ ሰው ሆኗል። ከመቂ አውራ ጎዳና ሰፈር …

Показати все...
ጊዜ እየጠበቀ የሚያገረሸው የአኙዋና ኑኤር ግጭትን ተከትሎ ሰዓት እላፊ ገደብ ተጣለ፣ እጃቸው ያለበት ባለስልጣናት እየተመረመሩ ነው

የአኙዋና ኑኤር ጎሳዎች ጊዜ እየጠበቀ የሚያገረሽ ግጭት ማንሳት ለማዳቸው ነው። የኑኤር አብላጫ ቁጥር ያለውና ከሱዳን እርስ በርስ ተፋላሚዎች ጋር ግንኙነት ያላቸው አመረሮችም ያሉበት በመሆኑ ብዙ ጊዜ የግጭቱ መነሻዎች እነሱ ናቸው። ከጋምቤላ የተሰማው ለበርካቶች ሞትና ንብረት ውድመት ምክንያት የሆነው አዲሱ ግጭት…

Показати все...

Показати все...
ለመሬትን ስጋት የሆነው አዲሱ ፕላኔት፤ ሙቀቱ 2,000 ዲግሪ ሴልሺየስ ይደርሳል

የአውሮፓ የህዋ ሳይንስ ድርጅት አዲስ ፕላኔት መገኘቱን በቅርቡ አስታውቋል። በአይነቱ ለየት ያለ ነው የተባለው ይህ  ፕላኔት ከፀሀይ ስርዓት / Solar system / ውጭ ሲሆን፤ እጅግ  ሞቃታማ እና አንፀባራቂ መሆኑም ተገልጿል።የዛሬው የሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ዝግጅት የአዲሱን ፕላኔት ባህሪያት እና  በምንኖርባ…

"ጄነራል አበባው ትክክለኛው ፋኖ በህጋዊ መስመር ተጨማሪ ሃይል እንደሆነ አመልከቱ፤ ያፈነገጠውም መስመር ይዟል አሉ – ETHIO12.COM" https://ethio12.com/2023/07/20/2309-285/
Показати все...
ጄነራል አበባው ትክክለኛው ፋኖ በህጋዊ መስመር ተጨማሪ ሃይል እንደሆነ አመልከቱ፤ ያፈነገጠውም መስመር ይዟል አሉ

ፋኖን አስመልክቶ የጦር ሀይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሠ በአብዛኛው ዓላማውን ተረድቶ ወደ ህጋዊ አግባብ መግባቱንና ይህም ሃይል ተጨማሪ ሃይል እንደሆነ ገለጹ። በማይሆን ስብከት አሻፈረኝ ያለውም ሃይል አስፈላጊው ስራ ተሰርቶ መስመር እንዲይዝ መደረጉን አስታወቁ። ቀደም ሲል ትክክለኛው …

"ሰበር ዜና – ኢሳያስ አፉወርቂ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይ ለሚተኩስ ማናቸውም ሃይል በራቸውን እንደዘጉ ማረጋገጫ ሰጡ – ETHIO12.COM" https://ethio12.com/2023/07/20/7230-3/
Показати все...
ሰበር ዜና – ኢሳያስ አፉወርቂ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይ ለሚተኩስ ማናቸውም ሃይል በራቸውን እንደዘጉ ማረጋገጫ ሰጡ

ኤርትራ ምድር ላይ ያሉ ኢመድበኛ ሃይሎች ጉዳይ ከዚህ ስምምነት በሁዋላ ያከትማል ተብሏል የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፉወርቂ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይ ቃታ ለሚስብም ሆነ ኢትዮጵያን ለሚያውክ ማናቸውም ሃይል ከለላም ሆነ ድጋፍ እንደማይሰጡ ሊታጠፍ በማይችል ደረጃ ማረጋገጫ መስጠታቸውን የኢትዮ12 የመረጃ…

Фото недоступнеДивитись в Telegram
Wasu Mohammed(ዋሱ መሀመድ): አልታገቱም ተብሏል። የእስራኤል ባለስልጣናት በኢትዮጵያ ታግቷል የተባለውን ግለሰብ ድርጊቱ ውሸት መሆኑን በማረጋገጡ ፍለጋውን አቋርጧል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ የተጓዘው የ79 አመቱ ግለሰብ የራሱን አፈና እንደሰራ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሁን ያምናል። የግለሰቡ ዘመዶች ባለፈው ሳምንት እንዳስታወቁት ታጣቂዎቹ በእጁ እና በእግሩ ታስሮ በታጠቀ ሰው ሲጠበቅ የሚያሳይ የተቀዳ መልእክት፣ ምስሎች እና አጭር ቪዲዮ ልከውላቸዋል። ታጋቾቹ እንዲፈቱ 2.5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር (45,000 ዶላር) እየጠየቁ ነበር። "እርዱኝ.  እኔ በጫካው መካከል ነኝ.  ከባድ ዝናብ እየዘነበ ነው።  እርዳኝ… ይህንን ችግር በጠላቶቼ ላይ አልመኝም ”ሲልም በቀረጻው ላይ ተናግሯል። የእስራኤል ባለስልጣናት ከኢንተርፖል ጋር በጉዳዩ ላይ እየሰሩ ነበር። ታገትኩ ያለው ሰው ከእስራኤል ቁጥሮች የሚመጡ የስልክ ጥሪዎችን መመለሱን ካወቁ በኋላ ባለስልጣናት ክሱን ማቋረጣቸው ተዘግቧል። ዘመዱ በግኝቱ ላይ ተከራክሮ አደባባይ አሁንም ምርኮኛ እንደሆነ አጥብቆ ተናገረ።
Показати все...
Показати все...
“የትግራይ አባቶች እናነትን የተቀየመው ቢበዛስ?” መርጦ አልቃሽነት

የትግራይ “የዕምነት አባቶች” አሁን ድረስ ኩርፊያ ላይ በመሆናቸው ሊያናግሯቸው የሄዱትን የዋናው ኦርቶዶክስ ጳጳስና አጋሮቻቸውን እንዳላገኙ ሰማን። ዕርቅ በጎ ነገር ነውና ትግራይ ድረስ ለይቅርታ መሄድ የመንፈሳዊው መንገድ መርህ ነውና ይበል ቢያሰኝም፣ ይህን ያህል የትግራይ አባቶችን ያስኮረፈው…

Показати все...
“የአማራ ህዝብ ማንነቱንም ፤ ነጻነቱንም ማስመለስ ችሏል” ኮሎኔል ደመቀ

ኮሎኔል ደመቀን ጠቅሶ የክልሉ ሚዲያ እንዳለው አማራ ማንነቱንም ፤ ነጻነቱንም ማስመለስ ችሏል። ያስመለሰው ነጻነትና ማንነቱ ደግሞ ቀደም ሲል በሃይል የተነጠቀውን ነው። ባህይል የተነጠቀውን ማንነቱን በሃይል ማስመለሱን ያመለከቱት ኮሎኔል ደመቀ ጉዳዩ ተፈጥሯዊ መብትን የማስመለስ ነው። ሰሞኑንን ጠቅላይ ሚኒስትር አ…

Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.