Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
Відкрити в Telegram
Показати більше
1 740
Підписники
-124 години
Немає даних7 днів
-630 день
Архів дописів
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ ለሚገኙ አጠቃላይ ሰራተኞች የኢንተርፕርነርሺፕ ስልጠና መድረክ አካሄደ::
ስልጠናው የአለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሺፕ ሳምንትን አስመልክቶ ከEntrepreneurship Development Institute(EDI) ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን በLeading the Shift: Systems Thinking for Transformative TVT እንዲሁም
በTVET Enterprise Development and Management Experiential በሚል ርዕስ ለኮሌጁ ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ተችሏል::
በመድረኩ ተገኝተው ለተሳታፊዎች መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው አዲሱ የዘርፉ እሳቤ የአቅምና የዝግጁነት ጥያቄን ይዞ የመጣ በመሆኑ በዘንድሮ በጀት ዓመት በሚኖረን ትግበራ ከዚህ በፊት ከለመድነው አካሄድ በተለየ አስተሳሰብ ተቋሙን ሊቀይሩ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ከፍ ብሎ ማሰብ ይጠበቅብናል ያሉ ሲሆን ሁላችንም የተሰጠንን ሀላፊነት በተገቢው መንገድ መወጣት ከቻልን እንደ ተቋም ለማሳካት ከያዝነው ግብ ለመድረስ ያስችለናልም ብለዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም በቀጣይ በአዲስ እይታ ኮሌጁን ወደፊት ሊያሻግሩ የሚችሉ ሀሳቦችን ይዘው የሚመጡ አካላትን ለመደገፍና እንደ ተቋም ኢንቨስት በማድረግ በጋራ ለመስራት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁነት መኖሩንም ገልፀዋል::
ኮሌጁ ከEntrepreneurship Development Institute(EDI) ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ስልጠና ከEDI በመጡ አሰልጣኞች ዶ/ር ያሲን መሀመድ እና አቶ ቴዎድሮስ አበበ አማካኝነት የተሰጠ ሲሆን በነበረው መድረክም የዘርፉን ለውጥ የመምራት አስተሳብን የመላበስ እንዲሁም የተቋሙን የኢንተርፕራይዝ ልማት አስተዳደርና የራስን ገቢ በዘላቂነት የማመንጨት ሂደት ውስጥ የሚገጥሙ ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ሰራተኛው ግንዛቤ እንዲጨብጥ ያስቻለ ውጤታማ ስልጠና መስጠት ተችሏል::
በቀጣይም ኮሌጁ ከEntrepreneurship Development Institute(EDI) ጋር Holistic Agreement በመፈራረም በየጊዜው መሰል ስልጠናዎች ለኮሌጁ ማህበረሰብ እንደሚሰጥም በመድረኩ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዲር 6/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የEASE ፕሮጀክት የ2017 ዓ.ም አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2018 ዓ.ም እቅድ ጨምሮ የኮሌጁ የ2018 ዓ.ም የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም ሪፖርት ለኮሌጁ አጠቃላይ ሰራተኞች ቀርቦ ውይይት ተካሄደ::
የእቅድ ሪፖርት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የስራና ክህሎት ም/ል ቢሮ ሀላፊና የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ሀላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በመልእክታቸውም ፕሮጀክቶች በባህሪያቸው ጊዜያዊ በመሆናቸው በፕሮጀክቱ የሚፈጠሩ ምቹ አጋጣሚዎችን በመጠቀም እንደ ተቋም ራስ ማብቃትና በመደበኛ ስራዎች ላይ በዘላቂነት አቅምን ማጎልበት ተገቢ ነው ያሉ ሲሆን የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም በEASE ፕሮጀክት የእስካሁን አተገባበር ጥሩ አፈፃፀም ያሳየ በመሆኑ ይህንንም እስከ ፕሮጀክቱ ፍፃሜ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል::
የEASE ፕሮጀክቱ የኮሌጁን መደበኛ ስራን በስፋት የመደገፍ ስራን እንደሚሰራ የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ አክለውም የEASE ፕሮጀክት የመደበኛ ስራውን ከመደገፍ በተጨማሪም በዋናነት ትኩረት አድርጎ የሚሰራው በፕሮጀክቱ ለማሳካት የተቀመጡ ቁልፍ ተግባራት ላይ ሲሆን የፕሮጀክቱ አፈፃፀም የሚለካውም በነዚህ ውጤቶች ላይ መሰረት አድርጎ መሆኑንም ገልፀዋል::
የEASE ፕሮጀክት የ2017 ዓ.ም አፈፃፀም ሪፖርትና የ2018 ዓ.ም ዋና እቅድ የፕሮጀክቱ አስተባባሪ በሆኑት ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት ለኮሌጁ ሰራተኞች የቀረበ ሲሆን በዚህም ባሳለፍነው ዓመት በEASE ፕሮጀክት ሊተገበሩ የታቀዱ እና ከስምንቱ Sub Component አኳያ የተከናወኑ ቁልፍ ተግባራት በዝርዝር የቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም በተያዘው በጀት ዓመት በፕሮጀክቱ አማካኝነት በኮሌጁ ሊከናወኑ በእቅድ የተያዙ ተግባራትን ለመድረኩ ተሳታፊዎች በሰፊው ገለፃ ማድረግ ተችሏል::
መድረኩ ቀጥሎም የኮሌጁ 2018 ዓ.ም የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም ሪፖርት ለአጠቃላይ ስራተኛው የቀረበ ሲሆን በዚህም የኮሌጁ የውጤት ተኮር ዋና ስራ ሂደትን ጨምሮ የቴክኖሎጂ ሽግግርና እንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዋና ስራ ሂደቶች የሩብ ዓመቱን አፈፃፀምና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን አያይዘው በቅደም ተከተል አቅርበዋል::
በመጨረሻም በመድረኩ በቀረቡት አጠቃላይ ሰነዶች ላይ ከሰራተኛው ሀሳብ አስተያየት ተሰጥቶባቸው ሰፊ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ለቀጣይ ትግበራዎችም ግብዓት የሚሆኑ ነጥቦች የተገኙበት መድረክም ሆኖ ተጠናቋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዳር 05/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
+2
የፅሁፍ ፈተና ጥሪ!!
ከዚህ ቀደም የኢትዮዽያ አየር መንገድ ባወጣው የስራ ማስታወቂያ የተወዳደራችሁ በሙሉ ለፅሁፍ ፈተና ያለፋችሁ ስም ዝርዝር ከዚህ በታች በተቀመጠው መሰረት ቅዳሜ ህዳር 6/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ላይ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እንድትገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን።
መረጃውን ሼር በማድረግ ይተባበሩ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ ለሚገኙ የፑል አመራር አባላት የኢንተርፕርነርሺፕ ስልጠና ሰጠ::
ስልጠናው የአለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሺፕ ሳምንትን አስመልክቶ የተዘጋጀ ሲሆን Strategic Alignment for Entrepreneurial TVET: Leading the Transformation በሚል ርዕስ ለኮሌጁ አመራር አባላቱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ተችሏል::
ስልጥናውን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ አገልግሎት ዋና ስራ ሂደት ሀላፊ አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆን በንግግራቸውም ስራ ፈጣሪ ተቋምን እውን ለማድረግ ስራ ፈጣሪነትን የተላበሰ አመራር መሆን ይገባል ያሉ ሲሆን አክለውም ኮሌጁ በስራ ፈጣሪነት ከTVET እስትራቴጂ አንፃር የተቀመጡ መስፈርቶችን ለሟሟላት የተለመዱ አሰራሮቻችን በመለወጥ ሂደቱ ውስጥ አመራሩ የግንባር ቀደምነት ሚና እንዲወጣ እንዲሁም ለውጡን በአግባቡ ለመምራት እንዲያስችል ይህ ስልጠና መዘጋጀቱንም ገልፀዋል::
ለኮሌጁ ፑል አመራር የተሰጠው ስልጠና ከEntrepreneurship Development Institute(EDI) በመጡ አሰልጣኝ አማካኝነት የተሰጠ ሲሆን በቀጣይም ለኮሌጁ አመራሮችና ሰራተኞች በየጊዜው ለሚሰጡ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ኮሌጁ ከኢንስቲትዩቱ ጋር በቅንጅት እንደሚሰራም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንትን በማስመልከት ከEntrepreneurship Development Institute(EDI)ጋር በመተባበር ለአዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎች የኢንተርፕርነርሽፕ ስልጠና ሰጠ::
ስልጠናው በዋናነት ሰልጣኝ ተማሪዎች የነገ ህይወታቸውን በተሻ ለመምራት እንዲሁም ከወዲሁ የስራ ፈጣሪነትን ባህሪ ከሚሰለጥኑት ስልጠና እኳያ አብረው እንዲያስኬዱ የሚያስችላቸው መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ አገልግሎት ዋና ስራ ሂደት ሀላፊ አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ እክለውም ሰልጣኞች በቀጣይ በኮሌጁ በሚቋቋመው የቢዝነስ ኢንኩቤሽን ሴንተር ስር ታቅፈው ውጤታማ ስልጠና እንዲሁም የቢዝነስ ልምዳቸውን የሚያጎለብቱበትን መንገድ በሰፊው ግብዛቤ የሚፈጥርላቸው የንግድ ስራ ክህሎት ስልጠና መድረክ እንደሆነም ገልፀዋል::
የኢንተርፕርነርሽፕ ስልጠናውን ከEntrepreneurship Development Institute(EDI) በመጡ አሰልጣኝ አማካኝነት የተሰጠ ሲሆን በቀጣይም መሰል ስልጠናዎች ለኮሌጁ ሰልጣኝ ተማሪዎች በየጊዜው እንደሚዘጋጅም ማወቅ ተችሏል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም የስልጠና ዘመን አዲስ ለተቀበላቸው ሰልጣኞች የህይወት ክህሎት(Life Skill) ስልጠና እየሰጠ ይገኛል::
የህይወት ክህሎት(Life skill )ስልጠናው ብቁ በሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን አማካኝነት ለቀጣይ 3ቀናት ለአዲስ ሰልጣኞች እየተሰጠ እንደሚቆይ የተገለፀ ሲሆን ይህ ስልጠናም ሰልጣኞች የቀጣይ ህይወታቸውን በእቅድ እዲመሩ እንዲሁም ራሳቸውን ፈልገው እንዲያገኙና ስልጠናቸውን በዓላማ እንዲሰልጥኑ የሚያስችላቸውን ክህሎት የሚያገኙበት ስልጠና እንደሆነም ተገልፇል::
ሰልጣኞቹ ይህን ስልጠና አጠናቀው ሲጨርሱ በኮሌጁ መደበኛ ስልጠናቸውን የሚጀምሩም ይሆናል::
ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ጥቅምት 26/2018 ዓ.ም
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
