uk
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Відкрити в Telegram

Показати більше
2 485
Підписники
Немає даних24 години
-157 днів
-5230 днів
Архів дописів
#CPJ #GobezeSisay ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች፤ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ በአፋጣኝ እንዲፈታ ጥሪ አቀረበ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይን በአፋጣኝ እንዲፈቱ ዓለም አቀፉ
#CPJ #GobezeSisay ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች፤ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ በአፋጣኝ እንዲፈታ ጥሪ አቀረበ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይን በአፋጣኝ እንዲፈቱ ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ሲፒጄ (CPJ) ጥሪ አቀረበ። መቀመጫውን በአሜሪካ ኒውዮርክ ያደረገው የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ትላንት አርብ ባወጣው መግለጫ “በአገር ውስጥና በውጪ ያሉ የፕሬስ አባላትን ማዋከብ እንዲያቆሙ” ለኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ጥሪ አስተላልፏል። “የአማራ ድምጽ” የተባለው በዩቲዩብ የሚተላለፍ የግል መገናኛ ብዙኃን መስራች እና አርታኢ የሆነው ጎበዜ፤ ሚያዝያ 28፤ 2015 በጅቡቲ በቁጥጥር ስር መዋሉን የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ይፋ እንዳደረጉ ሲፒጄ በመግለጫው ጠቅሷል። የጋዜጠኛው ጠበቃ አዲሱ አልማው፤ ጎበዜ ከጅቡቲ ለኢትዮጵያ መንግስት ተላልፎ መሰጠቱን እና በአዲስ አበባ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ በእስር ላይ እንደሚገኝ ለሲፒጄ ተናግረዋል። “የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይን ዝም ለማሰኘት እና ለመበቀል በድፍረት ድንበር ተሻግረዋል” ያሉት ከሰሃራ በረሃ በታች የሚገኙ የአፍሪካ አገራት የሲፒጄ ተወካይ ሙቶኪ ሙሞ፤ እስሩ “በስደት ደህንነት ፈልገው ከሀገራቸው በሄዱ ጋዜጠኞች ላይ ስጋት ይፈጥራል” ብለዋል። “ጎበዜ ያለመዘግየት ሊፈታ ይገባል” ያሉት የሲፒጄ ተወካይ የኢትዮጵያ እና የጅቡቲ ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር ስለዋለበት እና ተላልፎ ስለተሰጠበት ሁኔታ ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠይቀዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10925/ @EthiopiaInsiderNews

በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት ዋና ስራ አስፈጻሚ፤ በቢሯቸው በስራ ላይ ባሉበት በጥይት ተመትተው ተገደሉ በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት ዋና ስራ
በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት ዋና ስራ አስፈጻሚ፤ በቢሯቸው በስራ ላይ ባሉበት በጥይት ተመትተው ተገደሉ በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አለባቸው አሞኜ፤ ቢሯቸው ውስጥ በጥይት ተመትተው ህይወታቸው ማለፉን የወረዳው ኮሚዩኒኬሽን እና የዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታወቁ። ግድያውን ፈጽመዋል የተባሉት ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደዋሉም ተገልጿል። በዚህ ዓመት ጥቅምት ወር የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሆነው የተሾሙት አቶ አለባቸው፤ ግድያው የተፈጸመባቸው ዛሬ አርብ ግንቦት 4፤ 2015 ረፋድ ላይ መሆኑን የወረዳው የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ንዋይ ተሰማ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚው ካዛንቺስ በተለምዶ “ሀናን ዳቦ ጀርባ” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘው የወረዳው ጽህፈት ቤት ቢሯቸው ውስጥ ባሉበት ግድያ የተፈጸመባቸው፤ “ባለ ጉዳይ ሆኖ በገባ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አስተባባሪ” ግለሰብ መሆኑን የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊው ገልጸዋል። የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ባወጣው መግለጫ፤ አቶ አለባቸው “በቢሮአቸው ቁጭ ብለው የህዝብ አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት ከአንድ ተገልጋይ በደረሰባቸው ጥቃት” ህይወታቸው ማለፉን አረጋግጧል። ዋና ስራ አስፈጻሚው በጥይት የተመቱት “በግራ ልብ አካባቢ” መሆኑን የገለጹት የወረዳው የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ፤ ከጥቃቱ በኋላ በአቅራቢያው ወደሚገኘው ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ለህክምና ቢወሰዱም አምስት ሰዓት ገደማ አካባቢ መሞታቸውን ተናግረዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10912/ @EthiopiaInsiderNews

#DawitBegashaw #TewodrosAsfaw የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ በጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው ላይ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ፈቀደ በጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አ
#DawitBegashaw #TewodrosAsfaw የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ በጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው ላይ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ፈቀደ በጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው ላይ ለሁለተኛ ጊዜ 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት በፍርድ ቤት ተፈቀደ። የምርመራ ቀናቱን የፈቀደው ዛሬ አርብ ግንቦት 4፤ 2015 የዋለው፤ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው። የጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ የ“አራት ኪሎ ሚዲያ” የዩ ቲዩብ መገናኛ ብዙሃን መስራች ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና “ኢትዮ ሰላም” የተሰኘው የዩ ቲዩብ መገናኛ ብዙሃን መስራች ቴዎድሮስ አስፋውን ጉዳይ መመልከት የጀመረው ከሁለት ሳምንት በፊት ነው። ይኸው ችሎት ለዛሬ ቀጥሮ የነበረው፤ ፖሊስ ባለፈው ቀጠሮ በተፈቀዱለት 14 የምርመራ ቀናት ያከናወናቸውን ተግባራት ለማድመጥ ነበር። የፌደራል ፖሊስ በዛሬው ዕለት ለችሎቱ በጽሁፍ ባቀረበው ሁለት ገጽ ማመልከቻ፤ ያከናወናቸውን እና የሚቀሩትን ስራዎች ዘርዝሯል። ፖሊስ ባለፉት ቀናት ተሰሩ በሚል ከዘረዘራቸው ሰባት ተግባራት መካከል በቀዳሚነት የጠቀሰው፤ የምርመራ ቡድን በማቋቋም “በተለያዩ ቦታዎች ጉዳት የደረሰባቸውን [ግለሰቦች] የምስክርነት ቃል እንዲቀበል” መላኩን ነው። * ዝርዝር የችሎት ውሎ ዘገባውን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10921/ @EthiopiaInsiderNews

#AddisAbaba የአዲስ አበባ ከተማ መስሪያ ቤቶች አገልግሎት የሚሰጡበትን ጊዜ፤ ወደ 16 ሰዓት ለማራዘም የሚያስችል ጥናት እየተደረገ ነው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስሩ ያሉ መስሪያ ቤቶች
#AddisAbaba የአዲስ አበባ ከተማ መስሪያ ቤቶች አገልግሎት የሚሰጡበትን ጊዜ፤ ወደ 16 ሰዓት ለማራዘም የሚያስችል ጥናት እየተደረገ ነው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስሩ ያሉ መስሪያ ቤቶች አገልግሎት የሚሰጡበትን ጊዜ ከስምንት ወደ 16 ሰዓት ለማራዘም የሚያስችል ጥናት እያካሄደ መሆኑን አስታወቀ። ይህ ጥናት፤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ መስሪያ ቤቶችን የስራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡30 አስቀድሞ ለማስጀመር እና ከ11፡30 በኋላ እስከ ምሽት ለማስቀጠል ያቀደ ነው። ይህ ዕቅድ ይፋ የተደረገው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ፤ የከተማዋ መስሪያ ቤቶችን አገልግሎት አሰጣጥን አስመልክቶ ትላንት ሐሙስ ግንቦት 3፤ 2015 ከባለድርሻ አካላት ጋር ባደረገው ውይይት ላይ ነው። ይህ ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙት 47 መስሪያ ቤቶች የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች አፈጻጸም የመከታተል ኃላፊነት በአዋጅ የተሰጠው ነው። ቢሮው በትላንትናው ዕለት ከባለድርሻ አካላት ጋር ባደረገው ውይይት ላይ የአገልግሎት ቅልጥፍናን ለመጨመር ሊከተል ያሰባቸውን አሰራሮች አስተዋውቋል። አዲሶቹን አሰራሮች ለውይይቱ ተሳታፊዎች ያሳወቁት፤ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን ናቸው። ወ/ሮ ሂክማ በቀጣዩ በጀት ዓመት የአዲስ አበባ ከተማ መስሪያ ቤቶችን የስራ ሰዓት ከስምንት ወደ 16 ሰዓት ለማሳደግ “አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት” እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10906/ @EthiopiaInsiderNews

መንግስታዊ የልማት ድርጅቶች የሚያከናውኗቸው ግዥዎች፤ በፌደራል መንግስት የግዥ ስርዓት ስር እንዲከናወን የሚያደርግ የአዋጅ ረቂቅ ለፓርላማ ቀረበ የመንግስት የልማት ድርጅቶች በራሳቸው የግዥ አፈጻጸም
መንግስታዊ የልማት ድርጅቶች የሚያከናውኗቸው ግዥዎች፤ በፌደራል መንግስት የግዥ ስርዓት ስር እንዲከናወን የሚያደርግ የአዋጅ ረቂቅ ለፓርላማ ቀረበ የመንግስት የልማት ድርጅቶች በራሳቸው የግዥ አፈጻጸም መመሪያ ሲፈጽሟቸው የነበሩ ግዥዎች፤ በፌደራል መንግስት የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ስርዓት ስር እንዲሆን የሚያደርግ የአዋጅ ረቂቅ ለተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ። የአዋጁ ረቂቅ በመንግስት መስሪያ ቤቶች መካከል የሚፈጸመውን የቀጥታ ግዥም ያስቀራል። በግዥ እና በንብረት አስተዳደር ላይ ማሻሻያዎችን ያደረገው የአዋጅ ረቂቅ ለፓርላማ የቀረበው፤ ዛሬ ግንቦት 3፤ 2015 ዓ.ም በተካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ ላይ ነው። የአዋጅ ረቂቁን ማብራሪያ ለተወካዮች ምክር ቤት አባላት በንባብ ያሰሙት የመንግስት ተጠሪው አቶ ተስፋዬ በልጂጌ፤ “በአፈጻጸም ወቅት ካጋጠሙ ችግሮች በመነሳት” ነባሩን የፌደራል የመንግስት ግዥና የንብረት አስተዳደር አዋጅ ማሻሻል እንዳስፈለገ ተናግረዋል። አቶ ተስፋዬ በዚሁ ማብራሪያቸው፤ በ2001 ዓ.ም የወጣውን ነባሩን አዋጅ የሚያሻሽለው አዲሱ ህግ ያስተዋወቃቸውን አዳዲስ ነገሮች ለፓርላማ አባላቱ ጠቁመዋል። የመንግስት ተጠሪውን የጠቀሱት የመጀመሪያው ጉዳይ፤ የአዋጁ ተፈጻሚነት ወሰን የመንግስት የልማት ድርጅቶችን እንዲያካትት መደረጉን ነው። አዲሱ አዋጅ “የተወዳዳሪነት ሚናቸው ላይ ተጽዕኖ ሳያሳድር”፤ የልማት ድርጅቶች ላይ ተፈጻሚ እንደሚሆን ገልጸዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10900/ @EthiopiaInsiderNews

#ማስታወቂያ #Advertisement የመብቶችና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል ማዕከል (CARD) በተለያዩ አከራካሪ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሰናዳቸው ሰባት ዘጋቢ ፊልሞች ከዛሬ ሐሙስ፣ ግንቦት 3 ቀን 201
#ማስታወቂያ #Advertisement የመብቶችና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል ማዕከል (CARD) በተለያዩ አከራካሪ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሰናዳቸው ሰባት ዘጋቢ ፊልሞች ከዛሬ ሐሙስ፣ ግንቦት 3 ቀን 2015 ጀምሮ በአርትስ ቴሌቪዥን በየሳምንቱ ሐሙስ ከምሽቱ 1፡30 መታየት ይጀምራሉ። ካርድ “ከኢትዮጵያ ሰማይ ሥር” በሚል መሪየ ርዕስ አከራካሪ ጉዳዮች በውይይት ለማጥራት በማሰብ፣ ርዕሰ ጉዳዮቹን በይፋዊ የበይነመረብ ዜጎች ተሳትፎ በማስመረጥ፣ በባለሙያዎች ጥናት እና ተሳትፎ፣ እንዲሁም ከአገሪቱ ክልሎች በተውጣጡ በወጣቶች አስተያየት ሰጪነት ሰባት የ30 ደቂቃ ዘጋቢ ፊልሞችን አዘጋጅቶ ከዛሬ ጀምሮ በአርትስ ቴሌቪዥን ያስተላልፋል። የዘጋቢ ፊልሞቹ ዝግጅት፣ CARD ዴሞክራሲያዊ ባሕል ያበበባት ኢትዮጵያን ለማየት ራዕዩ አከራካሪ ጉዳዮች ላይ ዜጎች የሚወያዩበት እና መፍትሔ የሚፈልጉበት መድረክ መፍጠርን አንዱ ዓላማው ካደረገው የዜጎች ተሳትፎ መርሐ ግብሩ ሥር የተዘጋጀ ነው። የውይይት መድረኩ እና በውይይቱ ላይ የተነሱት ምክረ ሐሳቦች ኢትዮጵያ ለምታሰናዳው የአገራዊ ምክክር ጥሩ ግብዓት ይሆናል ብሎ CARD ያምናል።

በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚገኙ የግል ትምህርት ቤቶች፤ በቀጣዩ 2016 የትምህርት ዘመን በተማሪዎች ወርሃዊ ክፍያ ላይ ጭማሪ ለማድረግ የሚያስችላቸውን “ፕሮፖዛል” አዘጋጅተዋል። ወደ አንድ ሺህ ገ
በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚገኙ የግል ትምህርት ቤቶች፤ በቀጣዩ 2016 የትምህርት ዘመን በተማሪዎች ወርሃዊ ክፍያ ላይ ጭማሪ ለማድረግ የሚያስችላቸውን “ፕሮፖዛል” አዘጋጅተዋል። ወደ አንድ ሺህ ገደማ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች፤ በሚያደርጉት የክፍያ ጭማሪ ላይ ከተማሪ ወላጆች ጋር ውይይት ማካሄዳቸውም ተነግሯል። በእነዚህ ውይይቶች ላይ “ከስምምነት ላይ ተደርሶባቸዋል” የተባሉ የዋጋ ጭማሪ “ፕሮፖዛሎች”፤ ለአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት እና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ማቅረባቸውም ተገልጿል። “ፕሮፖዛሎቹ” ከ20 እስከ 100 በመቶ የሚደርሱ የዋጋ ጭማሪ የያዙ መሆናቸውን ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አስታውቋል። ባለስልጣኑ በትላትናው ዕለት ለትምህርት ቤቶቹ ባሰራጨው ደብዳቤ፤ ጭማሪውን በተመለከተ “ከወላጆች ጋር በቂ መግባባት ላይ ሳይደርሱ” ተግባራዊ ማድረግ እንደማይችሉ አስጠንቅቋል። በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ የግል ትምህርት ቤቶች “በምን ያህል መጠን ወርሃዊ ክፍያ ለመጨመር አቅደዋል?” የሚለውን ለመመልከት ከላይ የተያያዘውን መረጃ ይመልከቱ። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) ዝርዝር መረጃውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10883/ @EthiopiaInsiderNews

#US #MikeHammer የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ፤ ከኢትዮጵያ ዳያስፖራ ተወካዮች ጋር ሊወያዩ ነው የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመር በሎስ አንጀለስ ከሚገኙ የኢትዮ-አሜሪካ
#US #MikeHammer የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ፤ ከኢትዮጵያ ዳያስፖራ ተወካዮች ጋር ሊወያዩ ነው የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመር በሎስ አንጀለስ ከሚገኙ የኢትዮ-አሜሪካ ማህበረሰብ አባላት ጋር ሊወያዩ ነው። ልዩ ልዑኩ በሎስ አንጀለስ ቆይታቸው፤ የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የሶማሌ እና የትግራይ ማህብረሰብ ተወካዮችን እንደሚያነጋግሩ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ዛሬ ረቡዕ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ማይክ ሐመር ከዛሬ ጀምሮ ለዘጠኝ ቀናት በሎስ አንጀለስ ካሊፎርኒያ በሚያደርጉት ቆይታ፤ የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት እንዲያበቃ ያደረገውን የደቡብ አፍሪካ የግጭት ማቆም ስምምነትን ጨምሮ በኢትዮጵያ ስላሉ ወቅታዊ ጉዳዮች እንደሚወያዩ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ገልጿል። የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑኩ ከአሜሪካ ኢትዮጵያውያን ጋር በሎስ አንጀለስ ከተማ የሚያደርጉት ውይይት፤ “ሰላምን በማስፈን እና የሴቶችን አቅም በማጎልበት” የሚያተኩር ነው ተብሏል። “ዩናይትድ ውመን ኦፍ ዘ ሆርን” በተባለ የሲቪክ ድርጅት የተዘጋጀው ይህ ውይይት የሚካሄደው፤ 500 የሚጠጉ ሰዎችን ማስተናገድ በሚችለው በቦብ ሆፕ ፓትሪዮቲክ አዳራሽ ነው። አምባሳደር ሐመር በሎስ አንጀለስ ቆይታቸው፤ ከከተማይቱ ከንቲባ ካረን ባስ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ተገልጿል። ካረን ባስ ባለፈው ህዳር ወር ላይ የሎስ አንጀለስ የመጀመሪያዋነበር ሴት ከንቲባ ሆነው ከመመረጣቸው በፊት፤ በኮንግረስ አባልነታቸው ወቅት ኢትዮጵያን በተመለከተ በሚያራምዷቸው ጠንካራ አቋማቸው ይታወቁ የነበሩ ናቸው። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10892/ @EthiopiaInsiderNews

#AddisAbaba #Schools በአዲስ አበባ አንድ ሺህ ገደማ የግል ትምህርት ቤቶች፤ ከ20 እስከ 100 በመቶ የሚደርስ የክፍያ ጭማሪ ለማድረግ “ፕሮፖዛል” ማቅረባቸው ተነገረ በአዲስ አበባ ከተማ
#AddisAbaba #Schools በአዲስ አበባ አንድ ሺህ ገደማ የግል ትምህርት ቤቶች፤ ከ20 እስከ 100 በመቶ የሚደርስ የክፍያ ጭማሪ ለማድረግ “ፕሮፖዛል” ማቅረባቸው ተነገረ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚገኙ አንድ ሺህ ገደማ የግል ትምህርት ቤቶች፤ በተማሪዎች ወርሃዊ ክፍያ ላይ ከ20 እስከ 100 በመቶ የሚደርስ ጭማሪ ለማድረግ “ፕሮፖዛል” ማቅረባቸውን የከተማዋ የትምህርት እና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታወቀ። ትምህርት ቤቶቹ “ከወላጆች ጋር በቂ መግባባት ላይ ሳይደርሱ” ጭማሪውን መተግበር እንደማይችሉም አስጠንቅቋል። ባለስልጣኑ ይህን ማስጠንቀቂያ የሰጠው፤ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ የግል እና መንግስታዊ ላልሆኑ ትምህርት ቤቶች ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 2፤ 2015 በጻፈው ደብዳቤ ነው። የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ የትምህርት ተቋማት እውቅና የመስጠት እና አሰራራቸውን የመቆጣጠር ኃላፊነት በአዋጅ የተሰጠው ነው። በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙት 1,558 የግል ትምህርት ቤቶች ውስጥ፤ በቀጣዩ 2016 የትምህርት ዘመን ጭማሪ ለማድረግ የሚያስችላቸውን “ፕሮፖዛል” ያቀረቡት 1,257 መሆናቸውን የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ፍቅርተ አበራ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስረድተዋል። እነዚህ ተቋማት በዚሁ ፕሮፖዛላቸው ላይ፤ በምን ያህል መጠን ጭማሪ ለማድረግ እንዳቀዱ እና ይህንን የሚያደርጉበትን ምክንያት በዝርዝር ማስፈራቸውን ጠቅሰዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10883/ @EthiopiaInsiderNews

#GobezeSisay በጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ እና ሌሎች አምስት ተጠርጣሪዎች ላይ ፍርድ ቤት 14 የምርመራ ቀናት ፈቀደ በሽብር ወንጀል ተጠርጥሮ ትላንት ማክሰኞ ፍርድ ቤት በቀረበው ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ
#GobezeSisay በጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ እና ሌሎች አምስት ተጠርጣሪዎች ላይ ፍርድ ቤት 14 የምርመራ ቀናት ፈቀደ   በሽብር ወንጀል ተጠርጥሮ ትላንት ማክሰኞ ፍርድ ቤት በቀረበው ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ እና ሌሎች አምስት ግለሰቦች ላይ 14 የምርመራ ቀናት ለፖሊስ ተፈቀደ። የምርመራ ቀናቱን የፈቀደው ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 2፤ 2015 የዋለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው። ችሎቱ የምርመራ ቀናቱን የፈቀደው በተጠርጣሪዎች ጠበቆች በኩል የቀረበውን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ነው። ፍርድ ቤቱ ዋስትናውን ውድቅ ያደረገው፤ መርማሪ ፖሊስ ለችሎቱ ባስገባው የጊዜ ቀጠሮ ማመልከቻ “ተጠርጣሪዎቹ በመሩት እና ባስመሩት የሽብር ድርጊት በርካታ ንጹሃን ዜጎች እንዲሞቱ፣ በርካታ የህዝብ እና የመንግስት ንብረቶች እንዲወድሙ [ሆኗል]” የሚል መከራከሪያ በማቅረቡ ነው።  የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት በዛሬው ውሎው፤ ተፈጸመ በተባለው ወንጀል የሰው ህይወት ካለፈ የሚጣለው የቅጣት መጠን ከፍተኛ መሆኑን በማንሳት የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል። የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ከሶስት ዓመት በፊት የወጣው አዋጅ የተፈጸመው ተግባር “ሰውን መግደል” የሚጨምር ከሆነ፤ “ከአስራ አምስት ዓመት እስከ እድሜ ልክ በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይሞ በሞት” እንደሚያስቀጣ ያትታል።  ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10877/ @EthiopiaInsiderNews

#Tigray #Health በትግራይ ክልል ያሉ የጤና ተቋማት የአገልግሎት ሁኔታን የሚዳስስ ጥናት ሊካሄድ ነው በትግራይ ክልል የሚገኙ የጤና ተቋማት በአሁኑ ወቅት ያላቸውን ሀብት እና የሚሰጡትን የአገ
#Tigray #Health በትግራይ ክልል ያሉ የጤና ተቋማት የአገልግሎት ሁኔታን የሚዳስስ ጥናት ሊካሄድ ነው በትግራይ ክልል የሚገኙ የጤና ተቋማት በአሁኑ ወቅት ያላቸውን ሀብት እና የሚሰጡትን የአገልግሎት አይነት የሚዳስስ ጥናት ሊካሄድ ነው። የዓለም የጤና ድርጅት፣ የፌደራል የጤና ሚኒስቴር እና የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ በቅንጅት የሚያካሄዱት ይህ ጥናት፤ ተቋማቱ ያለባቸውን ችግር ለይቶ ትክክለኛውን ድጋፍ ለማድረግ የሚያግዝ ነው ተብሏል። ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ጥናት የሚደረግባቸው የትግራይ ክልል ጤና ተቋማት፤ የፌደራል መንግስት እና ህወሓት የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነትን ለማቆም በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ያደረጉትን ስምምነት ተከትሎ “በተወሰነ መልኩ” አገልግሎት መስጠት የጀመሩ መሆናቸውን የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ አስታውቋል። በክልሉ የሚገኙ የጤና ተቋማት “ታካሚዎች አገልግሎት እንዲያገኙ በሚል” ስራ ቢጀምሩም፤ ያላቸው ሀብት እና የጤና ባለሙያ ብዛትን በተመለከተ ግን የትግራይ ክልል ጤና ቢሮም ሆነ ሌሎች አጋር አካላት ዝርዝር መረጃ እንደሌላቸው የጥናቱ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ይብራህ አለማየሁ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በዚህም ምክንያት ወደ ትግራይ ክልል የሚመጡ የህክምና ቁሳቁሶች እና ሌሎች ድጋፎችን፤ በመረጃ ላይ ተመስርቶ በትክክል ለሚያስፈልጋቸው የጤና ተቋማት ማሰራጨት አለመቻሉን አስተባባሪው አስረድተዋል። ይህንን ችግር ለመቅረፍ፤ ከዓለም የጤና ድርጅት በተገኘ የሶስት ሚሊዮን ብር ገደማ የገንዘብ ድጋፍ የጤና ተቋማቱን ወቅታዊ ሁኔታ የሚዳስስ ጥናት ለማድረግ መወሰኑንም አክለዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10872/ @EthiopiaInsiderNews

#GobezeSisay በሽብር ወንጀል የተጠረጠረው ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረበ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለበት ጅቡቲ ወደ አዲስ አበባ ባለፈው ቅዳሜ ምሽት መግባቱ የተነገረው ጋዜጠኛ ጎበዜ
#GobezeSisay  በሽብር ወንጀል የተጠረጠረው ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረበ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለበት ጅቡቲ ወደ አዲስ አበባ ባለፈው ቅዳሜ ምሽት መግባቱ የተነገረው ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፤ ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 1፤ 2015 ፍርድ ቤት ቀረበ። ጎበዜ ከሌሎች አምስት ግለሰቦች ጋር ፍርድ ቤት የቀረበው፤ በሽብር ወንጀል ተጠርጥሮ መሆኑን የፌደራል ፖሊስ አስታውቋል። ፖሊስ ይህን የገለጸው የእነ ጎበዜን ጉዳይ ለመመልከት ዛሬ ተሰይሞ ለነበረው፤ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው። ጋዜጠኛ ጎበዜን ጨምሮ ስድስት ተጠርጣሪዎች የቀረቡበት የጊዜ ቀጠሮ መዝገብ የተከፈተው የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ መምህር በሆኑት በአቶ ሲሳይ አውግቸው ስም ነው። ስድስቱን ተጠርጣሪዎች ችሎት ፊት ያቀረባቸው የፌደራል ፖሊስ፤ ግለሰቦቹ “የሽብር ድርጊት ተግባር በመፈጸም በንጹሃን ህዝብ ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረሳቸው በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው” በእስር ላይ እንደሚገኙ ገልጿል። ፖሊስ ስድስቱን ተጠርጣሪዎች “ህገ መንግስቱን እና ህግ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመቀየር በመንቀሳቀስም” ወንጅሏቸዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10862/ @EthiopiaInsiderNews

#DanielBekele #EHRC #HumanRights የኢሰመኮን ተዓማኒነት እና አካታችነትን በተመለከተ ለቀረቡ ጥያቄዎች ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ምን ምላሽ ሰጡ? ⚫️ አቶ ከድር እንድሪስ የተባሉ የፓርላማ አባል “ ‘[ኮሚሽኑ] የሚያወጣቸው ዘገባዎች ምን ያህል ተዓማኒ ናቸው?’ የሚል ጥያቄ ይነሳል መብራራት አለበት” ብለዋል። “የተወሰነ የማህበረሰብ ክፍል ላይ ትኩረት አድርጎ ነው ብዙ ስራዎችን የሚሰራው በሚል ተቋሙ ላይ የሚነሳ ቅሬታ አለ” ሲሉም አክለዋል። ከደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን ገዢው ብልጽግና ፓርቲን ወክለው ፓርላማ የገቡት አቶ ከድር፤ ኢሰመኮ በዕቅድ የሚመራ ተቋም መሆኑ ላይም ጥያቄ አንስተዋል።    ⚫️ ኮሚሽኑ “ሚዲያን ይከተላል ይባላል” ያሉት አቶ ከድር፤ “እነዚያ ላይ ትኩረት አድርጎ እንጂ የራሱ ዕቅድ ኖሮት በራሱ ጊዜ የሚንቀሳቀስ ተቋም አይደለም” በሚል የሚነሳው ቅሬታ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ኢሰመኮ “የሚመለከተው አካል ባላረጋገጠው ጉዳይ ላይ ‘እከሌ ነው አጥፊው’ የሚል ፍረጃ ለመስጠት ይቸኩላል ይባላል። ማብራሪያ ቢሰጥበት” ሲሉም ተጨማሪ ጥያቄ አቅርበዋል። ⚫️ ሌላኛዋ የፓርላማ አባል ሙሉነሽ ላሞሬም በተመሳሳይ፤ የኮሚሽኑ “ገለልተኝነት ላይ ጥርጣሬ አለኝ” ሲሉ ተናግረዋል። ወይዘሮ ሙሉነሽ፤ “መግለጫዎች ሳይወጡ በፊት ከመንግስት ስራ አስፈጻሚ ጋር በደንብ መነጋገሩ ላይ ምንድን ነው ያለው?” የሚል ጥያቄም አንስተዋል።  ⚫️ ለእነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ዶ/ር ዳንኤል “ስለተዓማኒነታችን፣ ‘የተወሰነ ህብረተሰብ ክፍል አገልግላችኋል’ በሚል የተለያዩ አይነት ትችቶች እና አስተያየቶች እንደሚሰጡን እናውቃለን” ብለዋል። “የተሰጠ አስተያየት እና የተባለ ነገር በሙሉ ትክክል ነው ማለት አይደለም” ያሉት ዋና ኮሚሽነሩ፤ “ይህን ለህሊና ፍርድ ለእናንተ እተዋለሁ” ሲሉም ተደምጠዋል። ⚫️ ከፍረጃ ጋር በተያያዘ በተቋማቸው ላይ ለተነሳው ጥያቄ ዶ/ር ዳንኤል ሲመልሱ “ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ያለን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ተቋም፤ ሳያጣራ የሚፈርጅ አይደለም” ሲሉ ተናግረዋል። “ለማጣራት ከምንወስደው ጊዜ የተነሳ አንዳንድ ጊዜ ‘ለምን ቶሎ አልተናገራችሁም?’ የሚል ቅሬታ ነው የሚቀርብብን” ሲሉ ተቋማቸው ላይ የሚቀርበው ቅሬታ በፓርላማ አባሉ ከተነሳው ትችት በተቃራኒ መሆኑን ገልጸዋል። ⚫️ “ሚዲያ ይከተላሉ የሚለው አስተያየት ትክክል አይመስለኝም” ያሉት ዶ/ር ዳንኤል፤ “ነገር ግን የምንዘግባቸው የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች አብዛኛውን ጊዜ የሚዲያ ትኩረት የሚስቡ መሆናቸው አይካድም” ብለዋል። “አንድም ሪፖርታችን ላይ ‘ይሄ ድምዳሜያችሁ ስህተት ነው’ ተብሎ ክርክር ሊቀርብበት የቻለ የለም” ሲሉም ዋና ኮሚሽነሩ በተቋማቸው ላይ ለተነሳው ቅሬታ እና ትችት በአጽንኦት ምላሽ ሰጥተዋል።   ⚫️ ከመንግስት ስራ አስፈጻሚ አካል ጋር መነጋገርን በተመለከተ ለቀረበው ጥያቄም ዋና ኮሚሽነሩ ምላሻቸውን አስደምጠዋል። “እኛ ነጻ ብሔራዊ የሰብዓዊ  ተቋም ነን። ከመንግስት የስራ አስፈጻሚ ተጽዕኖ ወይም አቅጣጫ ነጻ ሆነን መስራት አለብን። ከመንግስት ጋር ለመስማማት ለመናበብ፣ አንድ አይነት አቋም ለመያዝ ብለን ግን አንሰራም” ብለዋል ዶ/ር ዳንኤል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) ዝርዝሩን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10853/ @EthiopiaInsiderNews

#EHRC #HumanRights በአማራ ክልል ያለው ወቅታዊ ሁኔታ ሳይባባስ፤ ፓርላማው የሰላማዊ መፍትሔ አስፈላጊነትን ለመንግስት “በአስቸኳይ እንዲያሳስብ” ኢሰመኮ ጠየቀ በአማራ ክልል እየተደረገ ባለ
#EHRC #HumanRights በአማራ ክልል ያለው ወቅታዊ ሁኔታ ሳይባባስ፤ ፓርላማው የሰላማዊ መፍትሔ አስፈላጊነትን ለመንግስት “በአስቸኳይ እንዲያሳስብ” ኢሰመኮ ጠየቀ በአማራ ክልል እየተደረገ ባለው “የጸጥታ እርምጃ” የተፈጠረው ጉዳት ሳይባባስ፤ ፓርላማው የሰላማዊ መፍትሔ አስፈላጊነትን ለመንግስት የስራ አስፈጻሚ አካል “በአስቸኳይ እንዲያሳስብ” የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጥያቄ አቀረበ። ብሔራዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም፤ በተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት “የተዓማኒነት እና የአካታችነት” ጥያቄም ተነስቶበታል። ጥያቄው የተነሳው ኢሰመኮ የ2015 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን፤ ለፓርላማው የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ነው። በኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ አማካኝነት የቀረበው ሪፖርት፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የነበሩ አዎንታዊ እርምጃዎች እና አሳሳቢ ሆነው የቀጠሉ ከሰብዓዊ መብት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን የዳሰሰ ነበር። በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለውን “ወታደራዊ እንቅስቃሴ” በአሳሳቢነት ያነሱት ዋና ኮሚሽነሩ፤ “ይህ ወታደራዊ እርምጃ የሰብዓዊ መብት አንድምታ ስላለው በቅርበት እየተከታተልነው ነው” ብለዋል። መንግስት በአማራ ክልል በማካሄድ ላይ ባለው “የጸጥታ እርምጃ” “በሲቪል ሰዎች ላይ የሞትም፣ የንብረት ውደመትም፣ የመፈናቀልም ጉዳት ደርሷል” ያሉት ዶ/ር ዳንኤል፤ “እስካሁን ባለው መረጃም በመነሳት ከሰብዓዊ መብት አንጻር በጣም የሚያሰጋ” መሆኑን ገልጸዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10853/ @EthiopiaInsiderNews

#MeraraGudina ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ስለ ሰሞኑ የሰላም ውይይት ምን አሉ? - ኦፌኮ የሰላም ድርድሩ ውጤታማነት ላይ ያለውን ተስፋ በተመለከተ ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ጥያቄ የቀረበላቸው የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፤ “ከአሁኑ አፍ ሞልቶ መናገር አይቻልም” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። ከስድስት ወራት በፊት በፌደራል መንግስት እና በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) መካከል በተደረገው ስምምነት በአደራዳሪነት ተሳታፊ የነበሩት አካላት ይታወቁ እንደነበር ያስታወሱት የፓርቲው ሊቀመንበር፤ “እዚህኛው ላይ በስሚ ስሚ ካልሆነ አይታወቁም” ሲሉ የሰላም ውይይቱ ዝርዝር መረጃ አሁንም ግልጽ አለመሆኑን አስረድተዋል።  - “ኢትዮጵያን ከመገዳደል ፖለቲካ እንድትሻገር የሚሞክሩ፣ የሚገፉ፣ የሚያደራድሩ፤ ጉልበትም፣ እውቀትም ያላቸው ይኑሩ አይኑሩ እርግጠኛ አይደለንም” ሲሉ በታንዛኒያው ድርድር ተሳታፊ ስለነበሩ ወገኖች ያላቸው መረጃ ውሱን መሆኑን ፕሮፌሰር መረራ ተናግረዋል። የኦፌኮ ሊቀመንበር አክለውም “ግፊት ማድረግ የሚችሉ አደራዳሪዎች፤ ከድርድሩም በኋላ ስምምነቱ ስራ ላይ መዋሉን መቆጣጠር የሚችሉ ኃይሎች ያስፈልጋሉ” ሲሉም የሰላም ውይይቱ ውጤታማ ከሆነ በኋላ ሊደረግ የሚገባውን ጠቁመዋል።  - ሁለቱም ወገኖች ወደ ድርድሩ ሲመጡ “የራሳቸው ስሌት” ይዘው እንደሆነ ያመለከቱት ፕሮፌሰር መረራ፤ በኢትዮጵያ መንግስት እና በ“ኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት” ተወካዮች በኩል ሊነሱ የሚችሉ የድርድር ነጥቦች ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ግምታቸውን አስቀምጠዋል። “ስልጣን ላይ ያለው መንግስት ታንዛኒያ የሄደው ‘እጃችሁን ስጡ፣ መሳሪያ አስቀምጡ፣ ምህረት እናደርጋለን፣ ከሶስት ዓመት በኋላ ደግሞ ምርጫ ይመጣል፣ ያን ጊዜ እድላችሁን ትሞክራላቸሁ’ [ብሎ] ለማባበል ይሆናል። እነዚያ ደግሞ ‘ጠመንጃ አስቀምጠን፣ ምን ዋስትና አለን? ማን ነው ዋስትና የሚሰጠን?’ የሚል ጭንቀት ያላቸው ይመስለናል” ሲሉ ስለ ድርድሩ ያላቸውን ግምገማ ለጋዜጠኞች አጋርተዋል።  - “እንደ ሰሜኑ ድርድር ’በሁለቱ ተደራዳሪዎች መተማመን እንዲፈጠር የሚያደርግ፣ ይሄንን የሚያጠብ ሶስተኛ ወገን ያስፈልጋል’ የሚባለው ለዚህ ነው። ፕሪቶሪያ እና ናይሮቢያ ላይ እነማን ተሳታፊ እንደነበሩ፣ አገናኝ እነደነበሩ፣ አስማሚ እንደነበሩ ይታወቃሉ። አሜሪካንን የሚህል ትልቅ ጭንቅላት ከኋላ አለ። ሶስተኛ ወገን የሚባለው [የኦሮሞ ነጻነት ጦር] ሲጠይቀው የነበረው ጉዳይ ነው” ሲሉ አብራርተዋል።  - ኦፌኮ በዛሬው መግለጫው እንዲዘረጋ የጠየቀው “የአስተዳደር ስርዓት” ምንነትን በተመለከተ ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ጥያቄ የቀረበላቸው ፕ/ር መረራ፤ ስርዓቱ “ሁሉንም የሚያሳትፍ” መሆን አለበት ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። “በተለይ የአሁኑ መንግስት የሽግግር መንግስት የሚለውን ለምን እንደሚጠላው አላውቅም፤ ይሸሻል። የሽግግር መንግስቱን እንተወውና ‘ሁሉን አሳታፊ መንግስት’፣ ‘ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ስርዓት’፣ ‘ብሔራዊ የአንድነት መንግስት’ በፈለጉት ስም ይጥሩት ግን ሁሉንም የሚያሳትፍ ስርዓት ያስፈልጋል” ሲሉ አስረድተዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10844/

ኦፌኮ የኦሮሞ ህዝብን በሚመለከቱ ፖለቲካ ጉዳዮች ላይ፤ “ቀሪ የኦሮሞ የፖለቲካ ኃይሎች ያሳተፈ ድርድር መደረግ” አለበት አለ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) በመንግስት እና በ“ኦሮሞ ነጻነት ሰራ
ኦፌኮ የኦሮሞ ህዝብን በሚመለከቱ ፖለቲካ ጉዳዮች ላይ፤ “ቀሪ የኦሮሞ የፖለቲካ ኃይሎች ያሳተፈ ድርድር መደረግ” አለበት አለ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) በመንግስት እና በ“ኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት” መካከል የሚደረገው የሰላም ድርድር ከተኩስ አቁም ስምምነት ባለፈ የኦሮሞ ህዝብን በሚመለከቱ ፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ቀሪ የኦሮሞ የፖለቲካ ኃይሎችን ማሳተፍ እንዳለበት አሳሰበ። ኦፌኮ እውነተኛ እና ቀጣይነት ላለው ዕርቅ እና መግባባት ሁሉንም የፖለቲካ አመራርና ድርጅቶች ያሳተፈ “የአስተዳደር ስርዓት” መዘርጋት እንዳለበትም በአጽንኦት ገልጿል። ተቃሚ ፓርቲው ይህን የገለጸው፤ የኦፌኮ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ለሁለት ቀናት ሲያካሄዱት የቆዩትን መደበኛ ስብሰባ ካጠናቀቁ በኋላ ዛሬ ቅዳሜ ሚያዝያ 28፤ 2015 በዋና ጽህፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የተካሄደው የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ የተጠናቀቀው፤ ሰባት የአቋም መግለጫዎችን በማውጣት መሆኑ ተገልጿል። ከሰባቱ የአቋም መግለጫዎች ሁለቱ ያተኮሩት መንግስት ከተለያዩ አማጺ ቡድኖች ጋር ሲያደርጋቸው በቆዩ የሰላም ድርድሮች ላይ ነው። የኦፌኮ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሱልጣን ቃሲም በንባብ ባሰሙት መግለጫ፤ “የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ እና ኦሮሚያን ጨምሮ በመላ ሀገሪቱ በአጠቃላይ እየሞከረ ያለውን እርቅ እና ድርድር” ፓርቲው “በመርህ ደረጃ” እንደሚደግፍ ያትታል፡፡ ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10844/ @EthiopiaInsiderNews

🎁❤️ ልብ የሚገዙ ስጦታዎችን ለሚወዱት ያበርክቱ..❤️🎁 📷Heart Shaped Wooden Engraving 👉Price =1100 👋👋Join us at👇👇 https://t.me/Gezeadver
🎁❤️ ልብ የሚገዙ ስጦታዎችን ለሚወዱት ያበርክቱ..❤️🎁 📷Heart Shaped Wooden Engraving 👉Price =1100 👋👋Join us at👇👇 https://t.me/Gezeadvert @ethiopiafoodengineering +251910159791

❤️‍🔥❤️‍🔥ልዩ ስጦታ ስጦታ ለ ሚወዱት ያበርክቱ❤️‍🔥❤️‍🔥 🎄Wooden Engraving 👉Price 1100birr 🛵Free Delivery in Addis Abeba 📞☎️0910159791
+1
❤️‍🔥❤️‍🔥ልዩ ስጦታ  ስጦታ ለ ሚወዱት ያበርክቱ❤️‍🔥❤️‍🔥 🎄Wooden Engraving 👉Price 1100birr 🛵Free Delivery in Addis Abeba 📞☎️0910159791 @Ethiopiafoodengineering

❤️🎁 በቆዳ ላይ የወዳጅ ዘመድ ፤ ፍቅረኛ ፤ ጓደኛ ፎቶ እንዲህ በሚያስደንቅ መልኩ ያሰሩ፡፡❤️🎁 👉Size 40*50=1,200 ብር 50*60=1,700 ብር 60*75=2,400 ብር 75*90=320
+2
❤️🎁 በቆዳ ላይ የወዳጅ ዘመድ ፤ ፍቅረኛ ፤ ጓደኛ ፎቶ እንዲህ በሚያስደንቅ መልኩ ያሰሩ፡፡❤️🎁 👉Size 40*50=1,200 ብር               50*60=1,700 ብር                 60*75=2,400 ብር                   75*90=3200 ብር 🛵Free Delivery Everywhere in Addis Ababa 🦋❤️Leather Engravings🦋❤️ 👉ለ ምርቃት 🎓🧑‍🎓 👉ለ ሰርግ 💍💐 👉 ለ ልደት 🎂 👉ለ ወዳጅዎ እና ለ ፍቅረኛዎ🎁💝 📞 +251910159791 @EthiopiaFoodengineering 🎁❤️ ልብ የሚገዙ ስጦታዎችን ለሚወዱት ያበርክቱ..

🌲🎄ልዩ የገና ስጦታ🌲🎄🎁❤️ 📷Photos Engraved on Mdf Wood A5=400Birr A4=550Birr A3=800Birr A2=1400Birr 🛵Free delivery everywhere
+1
🌲🎄ልዩ የገና ስጦታ🌲🎄🎁❤️ 📷Photos Engraved on Mdf Wood A5=400Birr A4=550Birr A3=800Birr A2=1400Birr 🛵Free delivery everywhere in Addis Ababa 📞☎️0910159791 @ethiopiafoodengineering @gezeadvert