uk
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Відкрити в Telegram

Показати більше
2 485
Підписники
Немає даних24 години
-157 днів
-5230 днів
Архів дописів
ኦፌኮ መንግስት የኃይል እርምጃዎቹን በአስቸኳይ እንዲያቆም ጠየቀ! (በተስፋለም ወልደየስ – ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) ተቃዋሚው የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ፓርቲ መንግስት የኃይል እርምጃዎቹን በ
ኦፌኮ መንግስት የኃይል እርምጃዎቹን በአስቸኳይ እንዲያቆም ጠየቀ! (በተስፋለም ወልደየስ – ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) ተቃዋሚው የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ፓርቲ መንግስት የኃይል እርምጃዎቹን በአስቸኳይ እንዲያቆም ጠየቀ። ሀገሪቱ ትረጋጋ ዘንድም መንግስት በእስር ላይ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትን እንዲፈታ አሳስቧል።  ፓርቲው ጥሪውን ያቀረበው “በኢትዮጵያ ውስጥ ለተከሰተው ወቅታዊ ችግር ፖለቲካዊ መፍትሄ ያሻል” በሚል ርዕስ ስር ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 16፤ 2012 ባወጣው መግለጫ ነው። “በሺህዎች የሚቆጠሩ የቄሮዎች ሕይወት ተገብሮበት የመጣው እና ተስፋ ሰጪ የተባለው ለውጥ አጣብቂኝ ውስጥ ከገባ ውሎ አድሯል” ያለው ኦፌኮ “ሞት፣ እስር፣ ድብደባ ተመልሶ መጥቶብናል” ሲል በመግለጫው አስፍሯል።  Readmore https://telegra.ph/Ethiopia-Insider-08-22 @ethiocheck

ከሀሰተኛ መረጃ እራሳችሁን ጠብቁ! (የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት) በአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ላይ በዛሬው እለት የተቃጣ የግድያ ሙከራ ከሸፈ በሚል በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች እ
ከሀሰተኛ መረጃ እራሳችሁን ጠብቁ! (የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት) በአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ላይ በዛሬው እለት የተቃጣ የግድያ ሙከራ ከሸፈ በሚል በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች እየተሰራጨ የሚገኝ መረጃ እንዳለ ተመልክተናል። ይሁንና በስም የተጠቀሱት ከፍተኛ አመራሮቻችን ማለትም አቶ ተመስገን ጥሩነህ ፤አቶ አገኘሁ ተሻገር እንዲሁም ኮሚሽነር አበረ አዳሙ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮቻችን ላይ ምንም አይነት የተቃጣ የግድያ ሙከራ የለም። አመራሮቹ ልክ እንደወትሮው ሁሉ ያለ ምንም ችግር በስራ ላይ የሚገኙ ሲሆን እንዲህ አይነት ህዝባችንን ለማደናገር የሚለቀቁ መረጃዎች የሚለቀቁበት አላማ እና ፍላጎት ከማን እንደሚመነጭ በመረዳት መረጃወቹን ከማሰራጨት በፊት አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ለማሳሰብ እንወዳለን። @ethiocheck

የወላይታ ዞን አመራሮች ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ተወሰነ! የደ/ብ/ብ/ህ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ማምሻውን በፌስቡክ ገጹ ባወጣው መግለጫ በወላይታ ዞን የፓርቲው አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ከፓርቲው
የወላይታ ዞን አመራሮች ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ተወሰነ! የደ/ብ/ብ/ህ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ማምሻውን በፌስቡክ ገጹ ባወጣው መግለጫ በወላይታ ዞን የፓርቲው አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ከፓርቲው እና ከመንግስት ስራ ኃላፊነታቸው ከትላንት በስቲያ ሐሙስ ነሐሴ 14፤ 2012 ጀምሮ እንዲነሱ መወሰኑን አስታውቋል። ለዞኑን አመራሮች መነሳት በምክንያትነት በመግለጫው የተጠቀሰው 'ከፓርቲዉ ዲስፒሊንና ከተሰጣቸዉ ህዝባዊና መንግስታዊ ኃላፊነት በተቃራኒ በመቆም የህዝቡን ጥያቄ ሽፋን በማድረግ ለዉጡን ለማደናቀፍ በግልፅና በህቡዕ ተደራጅቶ ከሚንቀሳቀሱ የዉስጥ እና የዉጪ ኃይሎች ጋር እየሰሩ እንዳሉ ተረጋግጧል' የሚል ነው። አክሎም 'በዚህም ለዉጡን በጉልበት ለመቀልበስ የተለያዩ ታክቲኮችን በመንደፍ፥ በክልል የመደራጀት ጥያቄ አመላለስ ለማወሳሰብ አቅደዉ በመፈፀም በዞኑ ያለመረጋጋትና የንጹሃን ዜጎች ህይወት እንዲቀጠፍ ምክንያት ሆነዋል' ሲል ይከሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በዎላይታ ውስጥ ሁሉም ወረዳዎች የሚገኙ አስተዳዳሪዎች ፣የከተማ ካንቲባዎች እንዲሁም የዞኑ ካብነዎች በነገው ዕለት በወቅታዊ ጉዳይ ስብሰባ ለማድረግ እንደተጠሩ #ወላይታታይምስ ዘግቧል። @ethiocheck

በአዲሱ ዓመት ሁሉም የኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ሥራ ይገባሉ ተብሏል! በግንባታ ላይ የሚገኙት አምስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች በአዲሱ ዓመት ወደ ሥራ እንደሚገቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታ
በአዲሱ ዓመት ሁሉም የኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ሥራ ይገባሉ ተብሏል! በግንባታ ላይ የሚገኙት አምስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች በአዲሱ ዓመት ወደ ሥራ እንደሚገቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታውቋል። በአገሪቱ ውስጥ 12 የኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚገኙ ሲሆን፣ ከእነዚህ መካከል ሰባቱ በሥራ ላይ የሚገኙ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የማርኬቲንግ እና ኮሙዩኒኬሽን ሓላፊ አቶ ደርቤ ደበሌ ተናግረዋል። ባለፉት አሥርት ዓመታት የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብታዊ እድገት በአማካይ 10 ነጥብ 8 በመቶ እድገት እንደነበረው እና ለዚህም በተለይ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ሥራ መጀመር አስተዋጽኦ እንዳላቸው #ኢዜአ ዘግቧል። @ethiocheck

በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ቁማር ከሚጫወት የፖለቲካ አካሄድ በመውጣት የኢትዮጵያን ደህንነታዊ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ማረጋገጥ እንደሚገባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አሳሰበ፡፡ ምክር ቤቱ በብሄራዊ መግባባት ዙሪያ ውይይት እያደረገ ነው፡፡ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን እየተካሄደ ባለው ውይይት መክፈቻ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሙሳ አደም፤ እንደ ሃገር በአንድነት ለመቆም መንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ህዝቡ የሚጠበቅባቸውን ሃገራዊ ሚና እንዲወጡ ጠይቀዋል፡፡ ፓርቲዎች መቀራረብና የሃሳብ መሸናነፍን ያስቀደመ የፖለቲካ ባህል በማዳበር ችግሮቻቸውን በጋራ የሚፈቱ መሆን እንደሚገባቸውም አንስተዋል፡፡ “ያለችን አንድ ሃገር ናት” ያሉት ሰብሳቢው፤ መንግሥት የዜጎችን ህይወትና ንብረት ከጥፋትና ውድመት የሚታደግ የህግ የበላይነትን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን የዜጎችን መንግሥትን በሃሳብና በሰላማዊ ሰልፍ የመቃወም መብትንም ማክበር አለበትም ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል ህዝቡ የእነዚህን የፖለቲካ ወገኖች አቋምና አቅም በሚገባ በመረዳት በሃገራዊ አንድነቱ ላይ አደጋ የሚደቅን ፖለቲካዊ ሴራ መፈፀሚያ ከመሆን መቆጠብ እንደሚገባውም አመልክተዋል፡፡ በችግሮች ጊዜም ቆም ብሎ በማሰብ በጥላቻ ፖለቲካ ትርክትና ግፊት ቋሚ ጎረቤቱንና ንብረቱን ከማውደም እንዲቆጠብ ጠይቀዋል ሰብሳቢው፡፡ “ይህ ሲሆን ብቻ ነው ብሄራዊ መግባባትን በኢትዮጵያ እውን ማድረግ የሚቻለውም” ብለዋል አቶ ሙሳ በንግግራቸው፡፡ ለአሳዳጅ ተሳዳጅ የፖለቲካ ፍፃሜ ለማበጀት እንደሚሰራ የገለፀው ምክር ቤቱ፤ ከሁሉ በፊት በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ቁማር ከሚጫወት የፖለቲካ ስርአት መውጣት እንደሚያስፈልግም በፅኑ አሳስቧል፡፡ ውይይቱን የመሩት ዶክተር አረጋዊ በርሄ፣ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ ሻምበል አማን ኡስማን እና አቶ የሺዋስ አሰፋ ሲሆኑ፤ ከኢትዮጵያ የምስረታ ዘመን እስከ ስርአቶች ዝርጋታ ታሪካዊ – ጥናታዊ የመነሻ ሃሳብ በፕሮፌሰር መረራ አማካይነት ቀርቦ በፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ውይይት እየተካሄደበት ነው፡፡ #via በሶዶ ለማ @ethiocheck

ንግድ ባንክ ለኮንዶሚኒየም ብድር ተበዳሪዎች የሰጠውት የእፎይታ ጊዜ አብቅቷል ብሏል! የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮቪድ - 19 ወረርሽኝን ተከትሎ ለኮንዶሚኒየም ብድር ተበዳሪዎች የሰጠውት የ3 ወር የእ
ንግድ ባንክ ለኮንዶሚኒየም ብድር ተበዳሪዎች የሰጠውት የእፎይታ ጊዜ አብቅቷል ብሏል! የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮቪድ - 19 ወረርሽኝን ተከትሎ ለኮንዶሚኒየም ብድር ተበዳሪዎች የሰጠውት የ3 ወር የእፎይታ ጊዜ (ከሚያዝያ 2012 እስከ ሰኔ 2012 ዓ.ም) ስላበቃ ደንበኞቹ ክፍያቸውን ከሀምሌ ወር 2012 ዓ.ም ጀምሮ እንዲከፍሉ ጥሪ አቅርቧል፡፡ የበለጠ መረጃም ውል ከተዋዋሉበት የብድር ማእከል ማግኘት ይችላሉ ብሏል፡፡ @ethiocheck

ገንዘብ ለማግኘት ሲባል ሰውን ማገት በተደጋጋሚ እየተስተዋለ የመጣ ወንጀል ሆኗል! ገንዘብ ለመቀበል ሲባል ሰዎችን ማገት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣ ወንጀል ሆኗል፡፡ በተለይ በአማራ ክልል በተለ
ገንዘብ ለማግኘት ሲባል ሰውን ማገት በተደጋጋሚ እየተስተዋለ የመጣ ወንጀል ሆኗል! ገንዘብ ለመቀበል ሲባል ሰዎችን ማገት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣ ወንጀል ሆኗል፡፡ በተለይ በአማራ ክልል በተለያዩ አከባቢዎች ይህ ወንጀል በተደጋጋሚ እየተፈጸመ ይገኛል፡፡ ከኢዜአ ባገኘነው መረጃ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ታች አርማጭሆ ወረዳ ካንፈንታ በተባለው ቀበሌ ሰው አግቶ 20ሺ ብር የተቀበለ ወንጀለኛ በ12 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተደርጓል፡፡ ከአማራ ክልል ፓሊስ ባገኘነው ሌላ መረጃም በባህርዳር ዙሪያ ወረዳ አዳሽ ርስተማርያም በተባለ ቀበሌ ከብት ሲጠብቅ የነበረ የ9 ዓመት ሕጻን ልጅ በማገት 50 ሺብር የተቀበለ ወንጀለኛ በ10 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጥቷል፡፡ @ethiocheck

የፖለቲካ ፓርቲዎች በብሔራዊ መግባባት ላይ ነገ ውይይት ያደርጋሉ! ( ኢትዮጵያ ኢንሳይደር - በተስፋለም ወልደየስ ) በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በብሔራዊ መግባባት ላይ ነገ ቅዳሜ ነሐ
የፖለቲካ ፓርቲዎች በብሔራዊ መግባባት ላይ ነገ ውይይት ያደርጋሉ! ( ኢትዮጵያ ኢንሳይደር - በተስፋለም ወልደየስ ) በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በብሔራዊ መግባባት ላይ ነገ ቅዳሜ ነሐሴ 16፤ 2012 ውይይት ሊያደርጉ ነው። በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ በሚካሄደው በዚህ ውይይት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ይገኛሉ ተብሏል።  በነገው ውይይት ሶስት የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጥናታዊ ጽሁፍ እንደሚያቀርቡ መርሃ ግብሩን ያሰናዳው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታውቋል። የምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሙሳ አደም ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት በነገው ውይይት ጥናታዊ ጽሁፍ የሚያቀርቡት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋ እና የኦሮሞ ኦቦ ነጻነት ግንባር ሊቀመንበር ሻምበል አማን ኦስማን ናቸው። Readmore https://telegra.ph/Ethiopia-Insider-08-21 @ethiocheck

#GERD - አሁን ላይ የሲቪል ሥራው 88 ነጥብ 8 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራው 46 ነጥብ 5 በመቶ ደርሷል፡፡ - የኮርቻ ግድብ ሥራ ደግሞ 99 በመቶ መከናወኑን ጠቁመው በዩኒት ዘጠኝ
#GERD - አሁን ላይ የሲቪል ሥራው 88 ነጥብ 8 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራው 46 ነጥብ 5 በመቶ ደርሷል፡፡ - የኮርቻ ግድብ ሥራ ደግሞ 99 በመቶ መከናወኑን ጠቁመው በዩኒት ዘጠኝና አሥር የተርባይን ተከላ እየተካሄደ ነው፡፡ - በ2013 በጀት ዓመት የበጋ ወቅት ግድቡን ወደ 595 ሜትር ለማድረስ ይሰራል ተብሏል፡፡ - በ2013 የ11 ተርባይኖች ገጠማ እንደሚጠናቀቅና በክረምቱ ወቅት ደግሞ ግድቡ 13 ነጥብ 4 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ እንደሚይዝም ይጠበቃል፡፡ - እስካሁን ባለው ሂደት ለግድቡ 121 ነጥብ 8 የብር መውጣቱን ጠቁመው ግድቡን ለማጠናቅቅም የሚፈጀው አጠቃላይ ወጭ 160 ቢሊየን ብር ይሆናል። @ethiocheck

ኢትዮ ቴሌኮም ለዚሁ ሥራ አዋጁ ሲዘጋጅ ጀምሮ በየጊዜው ከፍ ያለ ድጋፍ እያደረገ የቆየ ሲኾን፣ አሁንም እያደረገ እንደሆነ ሰምተናል። ከ'ሊበራላይዜሽን' በኋላ ኢትዮ ቴሌኮም ራሱ እንደ አንድ አገልግሎት ሰጪ ተቋም ቁጥጥር ይደረግበታል ብለዋል ዶ/ር እዮብ። በቅርቡም በጉዳዩ ላይ መንግሥት ከሕዝቡ ጋር እንደሚመክር ዶ/ር እዮብ ተናግረዋል። መንግሥት የጀመረውን የቴሌኮም ሪፎርም ሥራ እንደማያቆምና በብርቱ እንደሚጓዝበት ያስረዱት ሚንስትር ደኤታው፣ በዚህ ዙሪያ የተቀየረም ሆነ የሚቀየር ነገር የለም ብለዋል። በኢትዮጵያ ተግባራዊ የሚደረገው በከፊል የቴሌኮም ድርሻ ሽያጭን በተመለከተ፣ አዲስ ለሚገቡት ሁለቱ ኩባንያዎችና ለኢትዮ ቴሌኮም የቴሌ ማማ እየተከሉ ለማከራየት የናፈቁ የውጭ ኩባንያዎች ፈቃድ እንዲሰጣቸው እየጠየቁ ቢሆንም፣ ይህ ግን አልተፈቀደም ተብሏል። 2/2 @ethiocheck

ነሐሴ 15፣2012 ኢትዮ ቴሌኮምን በከፊል ወደ ግሉ ዘርፍ ለማዞር እና ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በዘርፉ ለመሰማራት የሻቱ የውጭ አቻ ኩባንያዎች ምዘና ተጠናቆ፣ ዘርፉን ለመምራት አማካሪ ድርጅት ተቀጠረ
ነሐሴ 15፣2012 ኢትዮ ቴሌኮምን በከፊል ወደ ግሉ ዘርፍ ለማዞር እና ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በዘርፉ ለመሰማራት የሻቱ የውጭ አቻ ኩባንያዎች ምዘና ተጠናቆ፣ ዘርፉን ለመምራት አማካሪ ድርጅት ተቀጠረ ተባለ። ወደ ኢትዮጵያ የቴሌኮምን አገልግሎት ለማቀላጠፍ ፈቃድ የሚሰጣቸው ኩባንያዎች የዋጋቸው ግምት ተሠርቶ መጠናቀቁን ሰምተናል። ባለፉት ጥቂት ቀናት የኢትዮጵያ መንግሥት በቴሌኮም ዘርፍ በሚያደርገው ሪፎርም ሂደት ዙርያ አወዛጋቢ ሪፖርቶች ተሰምተዋል። ሰሞኑን በተሰማው አወዛጋቢ ሪፖርቶች እና ዘርፉን በከፊል ለግሉ ክፍት በማድረግ ዙሪያ የመንግሥትን ቁርጥ ሐሳብ ለመስማት ሸገር የገንዘብ ሚኒስቴር ሚንስትር ደኤታ የሆኑት ዶ/ር እዮብ ተካልኝን ማብራርያ እንዲሰጡት ጠይቋል። ዶ/ር እዮብ ሰሞኑን በተሰራጩት አወዛጋቢ ሪፖርቶች የተፈጠሩ ውዥንብሮችን ለማጥራት የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለሥልጣን በቅርቡ መግለጫ ይሰጣል ብለውናል። ዶ/ር እዮብ በ'ፕራይቬታይዜሽን' እና 'ሊበራላይዜሽን' ዙሪያ ብዙ ጊዜ ብዥታ አለ ብለውናል። የኢትዮ ቴሌኮምን 40 በመቶ ድርሻ መሸጥ እና 2 አዳዲስ የውጭ የቴሌኮም አገልግሎት ሰጭ ተቋማትን ሐገር ቤት ማስገባት የተለያዩ ሥራዎች እንደመሆናቸው፣ ለያይቶ ማየት ያስፈልጋል ብለዋል። የቴሌኮም ሥራ እንዲሠሩ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የውጭ ኩባንያዎች የሚሰጣቸው ፈቃድ ብዙ ዋጋ ተሰጥቶታል ብለዋል። ቴሌኮምን በከፊል ወደግል ለማዞር ሥራዎች ተጠናቅቀው ተወዳድሮ ያሸነፈው አማካሪ ድርጅት ወደ ሥራ ይገባል ተብሏል። ኢትዮ ቴሌኮም ለዚህ ሪፎርም ከፍተኛ ሥራ እንዳከናወነ የፋይናንስ ሚኒስትር ደኤታው ተናግረዋል። 1/2 @ethiocheck

የኦሮሚያ ክልል መንግስት በኮሚዩኒኬሽን ቢሮው በኩል ትላንት ሐሙስ ምሽት ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን “በማህበራዊ ሚዲያ የሚነዙ የፕሮፓጋንዳ መልዕክቶችን እንደ መረጃ ምንጭ ተጠቅሟል” ሲል ወንጅሏል። ይህ አይነቱ አካሄድም “የተሳሳተና መታረም ያለበት ጉዳይ ነው” ሲል ክልሉ አቋሙን ግልጽ አድርጓል። “የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የጸጥታ አስከባሪ አካላት የህግ የበላይነትን የማስከበር እርምጃ የሚኮንን፣ ሚዛናዊ ያልሆነ እና ከእውነታ የራቀ፣ በወቀሳ የተሞላ መግለጫ ማውጣቱ ተገቢነት የሌለውና ካንድ ኃላፊነት ከሚሰማው ተቋም የሚጠበቅ አይደለም” ብሏል የኦሮሚያ ክልል መንግስት። ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ማገናኛ (ሊንክ) ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/1666/

በትግራይ ክልላዊ መንግስት ለሚካሄደው የክልል ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ጠዋት ተጀምሯል። የትግራይ ክልል የምርጫ ኮሚሽን ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ክልላዊ ምርጫው በጷግሜ 04/2012 ይከናወናል
በትግራይ ክልላዊ መንግስት ለሚካሄደው የክልል ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ጠዋት ተጀምሯል። የትግራይ ክልል የምርጫ ኮሚሽን ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ክልላዊ ምርጫው በጷግሜ 04/2012 ይከናወናል። @ethiocheck

ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ! የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እና የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋ
ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ! የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እና የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ በልጅጌ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል። ሃላፊዎቹ ዜሮ ኪሎ ሜትር የአድዋ ሙዚየምን እና የመስቀል አደባባይ ፕሮጀክቶችን የጎበኙ ሲሆን የፕሮጀክቶቹ አሁናዊ ሁኔታ እና የግንባታ ሂደት በተቋራጮቹ ገለፃ ተደርጎላቸዋል። በተለይም በመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት የተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት መሪዎች ጭምር ተገኝተው ከምክትል ከንቲባዋ ጋር የግንባታ ሂደቱን ተመልክተዋል። የግንባታ ሂደቱ መልካም በሚባል ሁኔታ ላይ ስለመሆኑ መመልከታቸውን የተናገሩት የሃይማኖት አባቶች ቀናቶች የቀሩትን ቀጣዩን አለም አቀፍ የመስቀል በዓል ማክበር በሚችል ሁኔታ እየተገነባ መሆኑ በባለሙያዎች እንደተገለፀላቸውም ተናግረዋል። @ethiocheck

ከዛሬው የአቶ ጀዋር የፍርድ ቤት ውሎ ፦ 1. ፍርድ ቤት ከዚህ ቀደም አቶ ጃዋር መሃመድ ከልጃቸው እና ከባለቤታቸው ጋር በቪዲዮ ኮንፈረስ እንዲገናኙ የሰጠው ትዛዝ መፈፀሙን አረጋግጧል። 2. የፌደራል
ከዛሬው የአቶ ጀዋር የፍርድ ቤት ውሎ ፦ 1. ፍርድ ቤት ከዚህ ቀደም አቶ ጃዋር መሃመድ ከልጃቸው እና ከባለቤታቸው ጋር በቪዲዮ ኮንፈረስ እንዲገናኙ የሰጠው ትዛዝ መፈፀሙን አረጋግጧል። 2. የፌደራል ፖሊስ አቶ ጃዋር መሀመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ ፣ አቶ ሃምዛ ቦረና እና ሸምሰዲን ጣሃ የኮቪድ-19 ምርመራ ተደርጎላቸው ከቫይረሱ ነፃ መሆናቸውን የሚያሳይ የህክምና ማስረጃ አቅርቧል፤ ችሎቱ ይህን ይፋ አድርጓል። ኢትዮጵያ ኢንሳይደር፣ @ethiocheck

አቶ ጃዋር መሐመድ "በማላውቀው ሐኪም መነካት አልፈልግም" በማለቱ በግል ሐኪም እንዲታከም ጥብቅ ትዕዛዝ ተሰጠ! አቶ ጃዋር መሐመድ ከአራት ቀን በፊት ነሐሴ 11 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደታመመ ለፍር
አቶ ጃዋር መሐመድ "በማላውቀው ሐኪም መነካት አልፈልግም" በማለቱ በግል ሐኪም እንዲታከም ጥብቅ ትዕዛዝ ተሰጠ! አቶ ጃዋር መሐመድ ከአራት ቀን በፊት ነሐሴ 11 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደታመመ ለፍርድ ቤት በማስረዳት የዓቃቤ ሕግ ምስክሮች ሳይሰሙ ለዛሬ ነሐሴ 14 ቀን 2012 ዓ.ም. በተቀጠረው መሠረት የዓቃቤ ሕግ ምስክሮች መሰማት ጀመሩ ። ምስክሮች ከመሰማታቸው በፊት ፍርድ ቤቱ ነሐሴ 11 ቀን 2012 ዓ.ም. የሰጣቸው ትዕዛዞች መፈጸም አለመፈጸማቸውን አረጋግጧል። በዚህም መሠረት አቶ ጃዋር መንግሥት ሳይሆን በመንግሥት ውስጥ ያሉ ሰዎች ሥጋት እንደሆኑበትና ለሕይወቱ ስለሚፈራ በግሉ ሐኪም ካልሆነ በስተቀር ሕይወቱን ቢስት እንኳን በመንግሥት ሐኪም መመርመር እንደማይፈልግ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል። በጣም መታመሙን፣ ምግብ ሲመገብ እንደሚያስመልሰውና አሁን ላይ ደግሞ እያስቀመጠው መሆኑን አስረድቷል። ዓቃቤ ሕግ በሰጠው አስተያየት ለአቶ ጃዋር ሕክምና እንዲያገኙ ተጠይቀው በግል ሐኪሜ ካልሆነ አልታከምም እንዳሉ ገልጿል። አቅርቦቱ እያለ አልፈልግም እያሉ ወደሌላ ሐኪም ቤት መውሰድ ሥልጣንን አላግባብ መጠቀም መሆኑን ጠቁሞ በሕግ ፊት ሁሉም ሰው እኩል ነው የሚለውን ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌም የሚጥስ መሆኑን አክሏል። ወደ ግል ሐኪም ሪፈር ሊደረጉ የሚችሉት ከመንግሥት ሕክምና በላይ የሆነ ሕክምና ሲያስፈልግ ብቻ መሆኑንም ተናግሯል።ፍርድ ቤቱ በሰጠው ብይን በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 21 ድንጋጌ መሠረት አቶ ጃዋር በግል ሐኪም እንዲታዪ ጥብቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል። @ethiocheck

የኢሰመኮ ጋዜጣዊ መግለጫ! ኦሮሚያ፡ የሞት እና አካል ጉዳት አደጋ በተቃውሞ ሰልፎች የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በኦሮሚያ ለተቃውሞ በተጠሩ ሰልፎች ምክንያት የሚከሰተው የሰዎች ህይወት መጥፋት
የኢሰመኮ ጋዜጣዊ መግለጫ! ኦሮሚያ፡ የሞት እና አካል ጉዳት አደጋ በተቃውሞ ሰልፎች የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በኦሮሚያ ለተቃውሞ በተጠሩ ሰልፎች ምክንያት የሚከሰተው የሰዎች ህይወት መጥፋት በእጅጉ እንደሚያሳስበው እየገለፀ የፀጥታ ሀይሎች ተመጣጣኝ ያልሆነ ሀይል ከመጠቀም እንዲቆጠቡ ጥሪውን ያቀርባል፡፡ በክልሉ የተለያዩ ቦታዎች በተለይም በአሳሳ፣ አሰቦት፣ አወዳይ፣ ባሌ ሮቤ፣ ጭሮ፣ ደንገጎ፣ ድሬ ጠያራ፣ ዶዶላ፣ ገለምሶ፣ ጊኒር፣ ሀሮማያ፣ ሂርና እና ሻሸመኔ የሞት ጉዳት መድረሱን ኮሚሽኑ ከተለያዩ ምንጮች መረጃ ደርሶታል፡፡ የሞት ጉዳቶቹ የደረሱት የኦሮሞ ተቃዋሚ ፓርቲ ፖለቲከኞች እንዲለቀቁ በተጠሩ የተቃውሞ ሰልፎች እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል፡፡ ‹‹የመንግስት አካላት የዜጎችን በሰላማዊ መልኩ ተቃውሞ የማሰማት መብት ማረጋገጥ እንዳለባቸው እና ሕግ የማስከበር ስራ ተመጣጣኝነት እንዲጠብቅ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው›› የኮሚሽኑ ከፍተኛ አማካሪ እና ቃል አቀባይ አቶ አሮን ማሾ ገልፀዋል፡፡ ‹‹የኦሮሚያ ክልል በዚህ አመት የተከሰቱ አሳዛኝ ግድያዎች ከፈጠሩት ሰቆቃ አሁንም ፈጽሞ አላገገመም፡፡ እነዚህ ከፍተኛ የመብት ጥሰት አዝማሚያዎች እንዲቀጥሉ ሊፈቀድላቸው አይገባም›› በማለት አክለው ገልጸዋል፡፡ እስካሁን በአንዳንድ ሚዲያዎች የወጡ ሪፖርቶች እና በማህበራዊ ሚዲያ የተለቀቁ መረጃዎች የሞቱ ሰዎችን ቁጥር በሚመለከት የተለያየ አሀዝ አስቀምጠዋል፡፡ ኢሰመኮ የደረሰውን ሞትና ጉዳት መጠን ለማረጋገጥ ከየአካባቢው ነዋሪዎች፣ ምስክሮች፣ ሆስፒታሎች እና የአስተዳደር አካላት መረጃ በማሰባሰብ ላይ ይገኛል፡፡ ኢሰመኮ የፌዴራል እና የክልል መንግስታት ጉዳዩን ለማጣራት በአፋጣኝ ምርመራ እንዲጀምሩ ጥሪውን ያቀርባል፡፡ @ethiocheck

ኢትዮጵያ የኮሮና ክትባትን በርካሽ እንደሚያገኙ ከሚጠበቁ 92 ሃገራት መካከል አንዷ ነች! ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2021 እንደሚደርሱ የሚጠበቁ የኮሮና ክትባቶችን በርካሽ ከሚያገኙ 92 ዝቅተኛ እና መካ
ኢትዮጵያ የኮሮና ክትባትን በርካሽ እንደሚያገኙ ከሚጠበቁ 92 ሃገራት መካከል አንዷ ነች! ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2021 እንደሚደርሱ የሚጠበቁ የኮሮና ክትባቶችን በርካሽ ከሚያገኙ 92 ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ሃገራት መካከል አንዷ እንደሆነች ዓለም አቀፉ የክትባቶች ትብብር (ጋቪ) መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ ጋቪ ከቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ደረጃቸውን የጠበቁ አንድ መቶ ሚሊዬን የቫይረሱን ክትባቶች በፍጥነት ለማምረት የሚያስለውን ስምምነት "ሴረም" ከተሰኘው የህንድ የክትባቶች አምራች ተቋም ጋር ስምምነት ፈጽሟል፡፡ ሴረም አስትራ ዜናካ እና ኖቫቫክስ በተባሉ የምርምር ተቋማት በመዘጋጀት ላይ ያሉ ክትባቶችን ነው የሚያመርተው፡፡ የጋቪ ቦርድ እውቅና የሰጣቸው 92ቱ ሃገራትም ኮቫክስ በተሰኘው የትብብሩ አዲስ የፋይናንስ ስርዓት በመታገዝ ክትባቶቹን ከሶስት ዶላር (መቶ አስር ብር ገደማ) ባልበለጠ ዋጋ የሚያገኙ ይሆናል፡፡ የስርዓቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የተመረጡ 92 ሃገራት ዝርዝርም ባሳለፍነው ሳምንት በጋቢ ቦርድ ጸድቋል፡፡ @ethiocheck

ኢትዮጵያ በኮሮና ተጠቂ ሰዎች ቁጥር ከምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ሆነች። ኢትዮጵያ በኮሮና ተጠቂ ሰዎች ቁጥር ከ14 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ቀዳሚ መሆኗን የአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማእከል መረ
ኢትዮጵያ በኮሮና ተጠቂ ሰዎች ቁጥር ከምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ሆነች። ኢትዮጵያ በኮሮና ተጠቂ ሰዎች ቁጥር ከ14 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ቀዳሚ መሆኗን የአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማእከል መረጃ አመልክቷል፡፡እንደማእከሉ መረጃ በሱዳን እስካሁን 805 ሰዎች በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው አልፏል፡፡በኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ኬንያና ሱዳን ከኢትዮጵያ ቀጥሎ 2ኛና 3ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ፡፡ @ethiocheck