uk
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Відкрити в Telegram

Показати більше
2 485
Підписники
Немає даних24 години
-157 днів
-5230 день
Архів дописів
ቪዲዮ፦ በመገባደድ ላይ ባለው የፈረንጆቹ 2023 ዓመት ብቻ 50 የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች “ላልተገባ እስር መዳረጋቸውን” የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል አስታወቀ። ከእነዚህ ውስጥ የተወ
ቪዲዮ፦ በመገባደድ ላይ ባለው የፈረንጆቹ 2023 ዓመት ብቻ 50 የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች “ላልተገባ እስር መዳረጋቸውን” የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል አስታወቀ። ከእነዚህ ውስጥ የተወሰኑት አሁንም በእስር ላይ የሚገኙ እንዳሉበት የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር አቶ ያሬድ ኃይለ ማርያም ተናግረዋል። አቶ ያሬድ ይህን ያሉት “በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶችን ለማስጠበቅ ያሉ ወቅታዊ ተግዳሮቶች እና የመፍትሔ አማራጮችን” በተመለከተ፤ ዛሬ እሁድ ህዳር 30፤ 2016 በተካሄደ የመድረክ ውይይት ላይ ነው። በአዲስ አበባው ካፒታል ሆቴል የተካሄደው ይህ የመድረክ ውይይት፤ በዛሬው ዕለት በዓለም አቀፍ ደረጃ ታስቦ የዋለውን የዓለም አቀፉን የሰብአዊ መብቶች ቀን ለማክበር የተዘጋጀ ነበር። በመድረክ ውይይቱ ላይ ጥናታዊ ጹሁፍ ካቀረቡ ባለሙያዎች አንዱ የሆኑት አቶ ያሬድ፤ የሚመሩት ድርጅት ላለፉት ሶስት ዓመታት በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ላይ የተፈጸሙ እስሮችን ዝርዝር መረጃ ማጠናቀሩን ተናግረዋል። “በ2023 ብቻ የተለቀቁትን ጨምሮ 50 የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ታስረዋል” ያሉት የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር፤ “በቅርብ ጊዜ ራሱ ወደ ስድስት የሚጠጉ ጋዜጠኞች ከእስር እና ከመጉላላት በኋላ፤ እንደገና በስልክም በምንም በሚደርስባቸው ዛቻ እና ማስፈራሪያ ምክንያት ሀገር ጥለው ተሰድደዋል” ሲሉ አክለዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) * የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ዋና ዳይሬክተር በዛሬው መርሃ ግብር ላይ ያቀረቡትን ገለጻ ይህን ሊንክ ተጭነው ይመልከቱ፦ https://youtu.be/eIrfQEDfMVs @EthiopiaInsiderNews

የመከላከያ ሚኒስትሩ በክልሎች በየደረጃው ያሉ አመራሮች “አካባቢያቸውን ከሽፍቶች ማጽዳት አልቻሉም” ሲሉ ወቀሱ ክልሎች በተለያየ ደረጃ ያሉ የመንግስት አመራሮች “አካባቢያቸውን ከሽፍቶች ማጽዳት ባለመ
የመከላከያ ሚኒስትሩ በክልሎች በየደረጃው ያሉ አመራሮች “አካባቢያቸውን ከሽፍቶች ማጽዳት አልቻሉም” ሲሉ ወቀሱ ክልሎች በተለያየ ደረጃ ያሉ የመንግስት አመራሮች “አካባቢያቸውን ከሽፍቶች ማጽዳት ባለመቻላቸው”፤ የመከላከያ ሰራዊት “የመንግስት መዋቅር ስራን ደርቦ እንዲሸፍን እየተገደደ ይገኛል” ሲሉ የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶ/ር አብርሃም በላይ ወቀሱ። ሚኒስትሩ “የሽፍታ እንቅስቃሴ” ሲሉ የጠሩት ድርጊት እና በተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋሉ እገታዎች የሚከሰቱት፤ በክልሎች ባሉ የአስተዳደር እና የጸጥታ አካላት “መሰራት ያለበት ስራ ባለመሰራቱ” መሆኑን ገልጸዋል። የመከላከያ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት፤ ከዘንድሮው የበጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹን የሶስት ወራት የመስሪያ ቤታቸውን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ለፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ ባቀረቡበት ወቅት ነው። ዶ/ር አብርሃም ለተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረቡት ሪፖርት ላይ፤ በሩብ ዓመቱ ያጋጠሙ “ችግሮች እና ፈተናዎች” በሚል ከዘረዘሯቸው ውስጥ አንዱ የመከላከያ ሰራዊት ስምሪት በየአካባቢው እንዲሰፋ መደረጉን ነው። “የመንግስት መዋቅር ላይ ያሉ አመራሮች ህዝባቸውን በማስተባበር አካባቢያቸውን ከሽፍቶች ማጽዳት ባለመቻላቸው፤ የሰራዊታችን ግዳጅ እንዲሰፋ እና የክልል መንግስት መዋቅር ስራን ደርቦ እንዲሸፍን እየተገደደ ይገኛል” ሲሉ የመከላከያ ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው አስፍረዋል። ዶ/ር አብርሃም ይህንኑ ጉዳይ ከቋሚ ኮሚቴው አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅትም በድጋሚ በአጽንኦት አንስተውታል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/12112/ @EthiopiaInsiderNews

ኢትዮጵያ ወደብ ለማግኘት በምታደርገው ግፊት ወደ ጎረቤቶቿ “ጥይት የመተኮስ ፍላጎት” እንደሌላት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ ኢትዮጵያ ወደብ ለማግኘት በምታደርገው ግፊት ወደ ሶማሊያ፣ ጅቡ
ኢትዮጵያ ወደብ ለማግኘት በምታደርገው ግፊት ወደ ጎረቤቶቿ “ጥይት የመተኮስ ፍላጎት” እንደሌላት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ ኢትዮጵያ ወደብ ለማግኘት በምታደርገው ግፊት ወደ ሶማሊያ፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ ወይም በሌሎች ጎረቤቶቿ ላይ “አንድ ጥይት የመተኮስ ፍላጎት” እንደሌላት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፓርላማ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ዛሬ ማክሰኞ ህዳር 4፤ 2016 በሰጡት ማብራሪያ “የማንንም ሉዓላዊነት የመንካት ፍላጎት የለንም፤ ማንንም የመውረር ፍላጎት የለንም” ሲሉ ተደምጠዋል። አብይ በዛሬው የፓርላማ ቆይታቸው ማጠቃለያ ላይ ባለፉት ሳምንታት በአፍሪካ ቀንድ ሀገራት መካከል ሌላ ጦርነት ሊቀሰቅስ ይችላል የሚል ስጋት ባጫረው የወደብ ጥያቄ ላይ ዘለግ ያለ ማብራሪያ አቅርበዋል። ወደብን በተመለከተ “ብዙ አይነት ንግግሮች፣ ትንበያዎች፣ ሴራዎች፣ ትንተናዎች ተደርገዋል” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ኢትዮጵያውያን፣ የኢትዮጵያ ጎረቤቶች እንዲሁም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ “ሊገነዘቡ ይገባል” ያሉትን የመንግስታቸውን “እውነተኛ ፍላጎት እና ችግር” ዘርዘር አድርገው አስረድተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ማብራሪያቸው “ኢትዮጵያ ወደብ ማግኘት አለባት” የሚል አቋማቸው በድጋሚ በጉልህ ተንጸባርቋል። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ያላት “የህዝብ ቁጥር እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት”፤ አብይ ለወደብ አስፈላጊነት ያቀረቧቸው ገፊ ምክንያቶች ናቸው። በሚቀጥሉት ሰባት ዓመታት የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር 150 ሚሊዮን እንደሚደርስ፤ ኢኮኖሚዋም እያደገ እንደሚሄድ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “ጣጣ እንዳያመጣ እና ልጆቻችንን እንዳያባላ አሁን መፍትሔ እናበጅለት” ሲሉ አሳስበዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/12103/

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ፤ ነገ ማክሰኞ ህዳር 4፤ 2016 በተወካዮች ምክር ቤት በመገኘት ከፓርላማ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ሊሰጡ ነው። ጥያቄዎቹ ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ፤ ነገ ማክሰኞ ህዳር 4፤ 2016 በተወካዮች ምክር ቤት በመገኘት ከፓርላማ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ሊሰጡ ነው። ጥያቄዎቹ ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የፌደራል መንግስትን ዓመታዊ ዕቅድ በተመለከተ፤ ከአንድ ወር በፊት ለተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ያቀረቡትን ዓመታዊ የመክፈቻ ንግግር ላይ የተንተተራሱ ናቸው ተብሏል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

ለምርጫ ቦርድ ሰብሳቢነት በዕጩነት የሚቀርቡ ሁለት ግለሰቦች ማንነት፤ እስከ ህዳር ወር ማብቂያ ባለው ጊዜ ይገለጻል ተባለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢን የሚተኩ ዕጩዎችን እንዲመለምል የተቋ
ለምርጫ ቦርድ ሰብሳቢነት በዕጩነት የሚቀርቡ ሁለት ግለሰቦች ማንነት፤ እስከ ህዳር ወር ማብቂያ ባለው ጊዜ ይገለጻል ተባለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢን የሚተኩ ዕጩዎችን እንዲመለምል የተቋቋመው ኮሚቴ፤ አጣርቶ የሚለያቸውን ሁለት ዕጩዎች የህዳር ወር ከመጠናቀቁ አስቀድሞ ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እንደሚያቀርብ አስታወቀ። ኮሚቴው ጥቆማዎችን ከመጪው ሰኞ ህዳር 3፤ 2016 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ አስር ቀናት እንደሚቀበል ገልጿል። የዕጩ መልማይ ኮሚቴው ይህን ያስታወቀው፤ የጥቆማ አቀራረብ ሂደቱን አስመልክቶ ዛሬ አርብ ጥቅምት 10፤ 2016 በሰጠው መግለጫ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በገዛ ፍቃዳቸው የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢነት ኃላፊነታቸውን በለቀቁት ብርቱካን ሚደቅሳ ምትክ ተተኪ ለመሾም ያስችላቸው ዘንድ መልማይ ኮሚቴ መሰየማቸውን ይፋ የተደረገው ከሶስት ቀናት በፊት ነበር። ኮሚቴው የውስጥ አሰራር መመሪያ እና የድርጊት የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ ወደ ስራ መግባቱን ሰብሳቢው ቀሲስ ታጋይ ታደለ በዛሬው መግለጫ ላይ ተናግረዋል። መግለጫውን በታደሙ ጋዜጠኞች ከቀረቡ ጥያቄዎች አንዱ፤ በኢትዮጵያ ካለው ነባራዊ ሁኔታ አንጻር ጥቆማ የሚቀርብበት የጊዜ ገደብ “አላጠረም ወይ?” የሚል ነበር። ቀሲስ ታጋይ ለዚህ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፤ “ከስራው አስፈላጊነት አንጻር፤ እንደውም እኛ ሰፊ ጊዜ ነው የሰጠነው” ብለዋል። “በብዙ ክልሎቻችን ምርጫው ተሟልቶ ያልተካሄደ መሆኑ ይታወቃል። በዚህ ምክንያት እየተጓተተ መሆኑን እንረዳለን። በዚህ የተነሳ ይሄ ኮሚቴም ባጠረ ጊዜ ስራውን ሰርቶ ማስረከብ እንዳለበት ነው የተነጋገርነው” ሲሉም አብራርተዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/12098/ * በቪዲዮ ለመመልከት፦ https://youtu.be/zpFBa3ocuyE

አቶ ሳንዶካን ደበበ የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ተሾሙ ላለፈው አንድ ዓመት በፕላን እና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት አቶ ሳንዶካን ደበበ፤ የጠቅላይ ሚኒስ
አቶ ሳንዶካን ደበበ የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ተሾሙ ላለፈው አንድ ዓመት በፕላን እና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት አቶ ሳንዶካን ደበበ፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ (chief of staff) ሆነው ተሾሙ። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የልዩ ጽህፈት ቤታቸውን እንዲመሩ አቶ ሳንዶካንን የሾሟቸው፤ ከሶስት ሳምንት በፊት መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ልዩ ጽህፈት ቤቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ስር ካሉ ስድስት መዋቅሮች አንዱ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ስር ያሉ ሌሎች መዋቅሮች የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት፣ የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት፣ የፕሬስ ሴክሪተሪያት፣ የፖሊሲ እና የአፈጻጸም ክትትል ክፍል እንዲሁም የሪፐብሊኩ ጠባቂ ናቸው። አቶ ሳንዶካን ልዩ ጽህፈት ቤቱን እንዲመሩ ከተሾሙ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር የመጀመሪያ የውጭ ጉዟቸውን ወደ ቻይና ማድረጋቸውን ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል። ሹመቱንም ሆነ የቻይናውን ጉዞ አቶ ሳንዶካን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል። አብይ አህመድ ወደ ስልጣን እንደመጡ የልዩ ጽህፈት ቤታቸው ኃላፊ አድርገው በመጀመሪያ የሾሟቸው አሁን በካናዳ የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑትን አቶ ፍጹም አረጋን ነው። እርሳቸውን በመተካት የልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት በአሁኑ ወቅት የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሆኑት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ናቸው። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/12086/ @EthiopiaInsiderNews

በዘንድሮው ዓመት ሁለት ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለማምረት መታቀዱን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ ኢትዮጵያ በዚህ ዓመት ሁለት ቢሊዮን ዶላር ያህል የሚያወጡ ምርቶችን በሀ
በዘንድሮው ዓመት ሁለት ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለማምረት መታቀዱን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ ኢትዮጵያ በዚህ ዓመት ሁለት ቢሊዮን ዶላር ያህል የሚያወጡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርቶች ለመተካት ማቀዷን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ ገለጹ። ሀገሪቱ ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ 350 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት መቻሏንም አስታውቀዋል። በ2013 የተዘጋጀው የኢትዮጵያ የአስር ዓመት የልማት ዕቅድ፤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ በዋናነት ኤክስፖርት መር ቢሆንም “ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እየወጣባቸው ያሉ ነገር ግን በትንሽ ጥረት ንጽጽራዊ አቅም ሊፈጠርባቸው የሚችሉ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት የመተካት ስትራቴጂን” ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት አቅጣጫ አስቀምጧል። በኢትዮጵያ ጥቅም ላይ ከሚውሉ ምርቶች ውስጥ በሀገር ውስጥ የሚመረቱት 38 ከመቶ ብቻ መሆኑን ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ኢትዮጵያ ከዚህ ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ማድረግ በጀመረችው የተኪ ምርት (import substitute) ስትራቴጂ መሰረት 96 ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት ማቀዷ ተገልጿል። ከእነዚህ ውስጥ ቀዳሚው ትኩረት የሚሰጣቸው፤ በሀገር ውስጥ ግብዓት መመረት የሚችሉ የምርት አይነቶች መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታው ዛሬ ሰኞ ጥቅምት 26፤ 2016 ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። “አብዛኛው የኢንዱስትሪ ችግር የግብዓት [ነው]። ግብዓት ከውጪ ነው የምናመጣው። ስለዚህ የመጀመሪያውን ትኩረት የሚያገኙት የሀገር ውስጥ ግብዓትን ተጠቅመው ማምረት የሚችሉ ኢንዱስትሪዎችን ነው” ሲሉ አቶ ታረቀኝ አስረድተዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/12077/ @EthiopiaInsiderNews

በጃፓን የታተሙ የመማሪያ መጻሕፍት በሶስት ሳምንታት ውስጥ ለትምህርት ቤቶች እንደሚከፋፈሉ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ያለውን የመማሪያ መጻሕፍት እጥረት ለመቅረፍ በው
በጃፓን የታተሙ የመማሪያ መጻሕፍት በሶስት ሳምንታት ውስጥ ለትምህርት ቤቶች እንደሚከፋፈሉ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ያለውን የመማሪያ መጻሕፍት እጥረት ለመቅረፍ በውጭ ሀገር ከታተሙ መጻሕፍት ውስጥ 249 ኮንቴየነር የህትመት ወጤቶች ከትላንት በስቲያ ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸውን የትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ። እነዚህ መጻሕፍት በቀጣዮቹ ሶስት ሳምንታት ለየትምህርት ቤቶቹ በሚሰራጩበት ወቅት፤ አንድ መጽሐፍ ለአራት ተማሪዎች እንዲዳረስ ተደርጎ እንደሚከፋፈሉም አስታውቋል። በዘንድሮው የትምህርት ዘመን ከቅድመ አንደኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ የተመዘገቡ ተማሪዎች ብዛት 20.6 ሚሊዮን ነው። ከእነዚህ ውስጥ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ቁጥር 2.1 ሚሊዮን መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ሆኖም የትምህርት ዘመኑ ከተጀመረ ከአንድ ወር በኋላም የመማሪያ መጻሕፍት ለተማሪዎች አልተሰራጨም። የመማሪያ እና ማስተማሪያ መጻሕፍት በጊዜው ተደራሽ ያለመሆን ጉዳይ፤ የተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ትላንት ረቡዕ ጥቅምት 6፤ 2016 በጠራው ስብሰባ ላይም ጥያቄ አስነስቶ ነበር። በቋሚ ኮሚቴው የተዘጋጁ ጥያቄዎችን በንባብ ያሰሙ አንድ የፓርላማ አባል፤ የመጻሕፍት ግብዓት ባልተሟላበት ሁኔታ “የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ እንዴት ማድረግ ይቻላል?” የሚል ጥያቄ ለትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች አቅርበዋል። * * ዝርዝሩን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/12045/ * * የፕሮፌሰር ብርሃኑን ምላሽ በቪዲዮ ለመመልከት፦ https://youtu.be/unkKh_vYjJY @EthiopiaInsiderNews

#ማስታወቂያ #Advertisement ውድ ተከታታዮችን! “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የበይነ መረብ መገናኛ ብዙሃን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ሌሎችንም ጉዳዮች የተመለከቱ ዜናዎች፣ ዘገባዎች እና
#ማስታወቂያ #Advertisement ውድ ተከታታዮችን! “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የበይነ መረብ መገናኛ ብዙሃን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ሌሎችንም ጉዳዮች የተመለከቱ ዜናዎች፣ ዘገባዎች እና ትንታኔዎችን አዘጋጅቶ ማሰራጨት ከጀመረ ሶስት ዓመት ከመንፈቅ አስቆጥሯል። በመገናኛ ብዙሃናችን የሚቀርቡ ዘገባዎች፤ ሙያዊ ደረጃውን እና ስነ ምግባርን የጠበቁ እንዲሆኑ ያላሰለሰ ጥረት ስናደርግ ቆይተናል። ዘወትር ከምናደርገው ከዚህ ጥረታችን በተጨማሪ በእናንተ በተከታታዮቻችን የሚነሱ ቅሬታዎችን እና ማስተካከያዎችን በገለልተኝነት የሚከታተሉ እና የሚመረምሩ አርታኢ ከዚህ ወር ጀምሮ በመገናኛ ብዙሃናችን መመደባቸውን ለማሳወቅ እንወዳለን። በዚህ መሰረት በ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ድረ ገጽ እና በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችን ላይ በሚወጡ ዜናዎች፣ ዘገባዎች እና ትንታኔዎች ላይ ያላችሁን ቅሬታ በሞባይል ስልክ ቁጥር 0902- 66 66 55 በመደወል አሊያም በpubliceditor@ethiopiainsider.com የኢ-ሜይል አድራሻ በመላክ ማሳወቅ እንደምትችሉ እንገልጻለን። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @EthiopiaInsiderNews

ለዝቅተኛው የ12ኛ ክፍል ውጤት ተጠያቂው ማነው? በዛሬው የፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ ስብሰባ ከተነሱ ጥያቄዎች ውስጥ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋን የሳባቸው፤ የ12ኛ ክፍል ውጤት ለተከታታይ ሁለት ዓመታት ዝቅተኛ መሆን “ተጠያቂው ማነው?” የሚለው ነው። “የትምህርት ስርዓቱን አካሄድ በየዓመቱ ስትከታተሉ የነበራችሁ፣ የምታውቁ ናችሁ ብዬ እገምታለሁ” ያሉት ሚኒስትሩ፤ “እናንተም ኃላፊነት መውሰድ አለባችሁ” ሲሉ የፓርላማ አባላቱ ጭምር ከተጠያቂነት እንደማይድኑ ተናግረዋል። “እኛ ሀገር የተለመደ ነው። አንዱ አንዱን [ጥፋተኛ ማድረግ]። ይሄ የሁላችንም ኃላፊነት ነው። ሁላችንም ነው የወደቅነው። ትምህርት ሲወድቅ ተጠያቂው ሁሉም ነው” ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤ ከእርሳቸው መስሪያ ቤት በተጨማሪ የመገናኛ ብዙሃን፣ ወላጆች፣ ማህበረሰቡ፣ የጸጥታ እና የደህንነት አካላት እና ሌሎችም እንደ የድርሻቸው “ኃላፊነታቸውን መውሰድ” እንዳለባቸው አሳስበዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) * የትምህርት ሚኒስትሩ ስለ ተጠያቂነት የሰጡትን ምላሽ ከቪድዮው ይመልከቱ። @EthiopiaInsiderNews

በ12ኛ ክፍል ውጤት “ራቁታችንን ምን እንደምንመስል አይተነዋል” - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፤ የመስሪያ ቤታቸውን የዘንድሮ እቅድ እና የበጀት ዓመቱን የሩብ ዓመት አፈጻጸም ለማቅረብ ዛሬ ረቡዕ በፓርላማ ተገኝተው ነበር። የዛሬውን ስብሰባ በጠራው የተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለሚኒስትሩ ካቀረባቸው ጥያቄዎች መካከል የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን የሚመለከተው ይገኝበታል። የቋሚ ኮሚቴውን ጥያቄዎች በንባብ ያሰሙት የፓርላማ አባል “በተከታታይ ለሁለት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤት በጣም ዝቅተኛ የሆነበት ምክንያት ምንድነው? ትምህርት ሚኒስቴር የፈተናውን ውጤት እንዴት ያየዋል?” ሲሉ ጠይቀዋል። ፕ/ር ብርሃኑ ለዚህ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ “የ12ኛ ክፍል ውጤት እንደዚህ መሆን፤ ምንምን እንኳ really መጠበቅ የነበረን ነገር ቢሆንም ሁላችንንም አስገርሞናል” ብለዋል። “የፈተናውን አሰጣጥ መቀየር ብቻ ይሄን ካሳየ፤ ከዚህ ተነስተን ብቸኛ ነገር ልንል የምንችለው፤ ከዚያ በፊት ስንሰጣቸው የነበሩ ፈተናዎች በሙሉ የተማሪን እውነተኛ ችሎታ የሚያሳዩ አይደሉም ማለት ነው” ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም ይሰጡ በነበሩ ሀገር አቀፍ ፈተናዎች በትምህርት ቤቶች እና በክልል ደረጃ ሳይቀር በተደራጀ መልኩ “ፈተናዎች የሚሰረቁበት” እንደነበር የጠቀሱት ፕ/ር ብርሃኑ፤ በዚያን ጊዜ የነበሩ ውጤቶች የተማሪዎችን ችሎታ የሚያንጸባርቁ እንዳልነበር አስረድተዋል። “አሁን ለመጀመሪያ ጊዜ refelect አድርጎልናል። አሁን የምንደበቅበት ቦታ የለም። ሰርቀን የምናሳይበት ቦታ የለም። ራቁታችንን ምን እንደምንመስል አይተነዋል” ሲሉም የትምህርት ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

በመብት ተሟጋቾች የተተቸው የሊባኖስ እና የኢትዮጵያ ስምምነት ለፓርላማ ቀረበ የቤት ሰራተኞች መብት እንዲከበር የሚሟገቱ ግለሰቦች እና ተቋማት ትችት ሲያሰሙበት የቆየው፤ የኢትዮጵያ እና የሊባኖስ መን
በመብት ተሟጋቾች የተተቸው የሊባኖስ እና የኢትዮጵያ ስምምነት ለፓርላማ ቀረበ የቤት ሰራተኞች መብት እንዲከበር የሚሟገቱ ግለሰቦች እና ተቋማት ትችት ሲያሰሙበት የቆየው፤ የኢትዮጵያ እና የሊባኖስ መንግስታት የስራ ስምሪት ስምምነት ለፓርላማ ቀረበ። በሁለቱ ሀገራት ስምምነት ላይ ለኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች የሚከፈለው ዝቅተኛ ደመወዝ አለመካተቱ በዛሬው የተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ጥያቄ ተነስቶበታል። ኢትዮጵያ ከ300 ሺህ እስከ 400 ሺህ የሚገመቱ ዜጎቿ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥረው ከሚሰሩባት ከሊባኖስ ጋር የስራ ስምሪት ስምምነት የተፈራረመችው በሚያዝያ 2015 ዓ.ም. ነበር። ስምምነቱ በሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ወደፊት ወደ ስራ ውል የሚገቡ ዜጎችን መብት እና ጥቅም የማስከበር ዓላማ ያለው መሆኑ ዛሬ ለፓርላማ በቀረበው ሰነድ ላይ ተጠቅሷል። ሃያ አምስት አንቀጾች ያሉት ይኸው የስራ ስምሪት ስምምነት፤ የኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን ምልመላ፣ የቅጥር ሁኔታዎች፣ የስራ ውል፣ የመብት ጥበቃ እና ሌሎችንም ጉዳዮች የሚዘርዝር ነው። ስምምነቱ በሊባኖስ በሚገኙ አሰሪዎች እና በኢትዮጵያውያን ሰራተኞች መካከል ተግባራዊ የሚደረግ “ሞዴል የስራ ውልን” ጭምር ያካተተ ነው። 🔵 ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ👉 https://ethiopiainsider.com/2023/12026/

ቪዲዮ:- በትግራይ ክልል ከትላንትና ጀምሮ የታወጀውን የሀዘን ቀን እና የመርዶ ስነ ስርዓት ተከትሎ፤ በአዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት እና ፖለቲከኞች በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ህይወታቸውን ላጡ ሁሉም ኢትዮጵያውያን የጸሎት እና የጧፍ ማብራት መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት አከናውነዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የሰባት ሀገራዊ እና ክልላዊ ፓርቲዎች አመራሮች እና አባላት ተገኝተው ሀዘናቸውን ገልጸዋል። የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በትግራይ ክልል የደረሰው ሀዘን የጋራ መሆኑን ጠቅሰዋል። በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ህይወታቸውን ያጡ የአማራ እና የአፋር ዜጎችን ጭምር ለማሰብ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሀዘን ቀናት ሊታወጅ ይገባ እንደነበር ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ላለፉት ዓመታት የነበረው “የእርስ በእርስ መገዳደል” በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በሌሎችም ክልሎች መቀጠሉ የሚያሳዝን እና መፍትሔ ሊበጅለት የሚገባ እንደሆነም ፖለቲከኞቹ አሳስበዋል። በአዲስ አበባ ካዛንቺስ አካባቢ በሚገኘው የኢህአፓ ጽህፈት ቤት በተካሄደው በዛሬው ስነ ስርዓት ላይ መልዕክቶቻቸውን ካስተላለፉት ውስጥ፤ የሀዘን ቀን ባታወጀበት ትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱት የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ትዴፓ)፣ የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ራዴፓ) እና የትንሣኤ 70 እንደርታ ፓርቲ (ትሰእፓ) አመራሮች ይገኙበታል። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ)፣ የአንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ፓርቲ (አኢዴፓ) አመራሮችም እንዲሁ መልዕክቶቻቸውን አስተላልፈዋል። ራሳቸውን ከኢዜማ ፓርቲ ያገለሉ የቀድሞ አመራሮች እና አባላት፤ በዛሬው መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው የሀዘን መልዕክቶቻቸውን አስደምጠዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @EthiopiaInsiderNews

Repost from Ethiopia Insider
ቪዲዮ:- በትግራይ ክልል ከትላንትና ጀምሮ የታወጀውን የሀዘን ቀን እና የመርዶ ስነ ስርዓት ተከትሎ፤ በአዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት እና ፖለቲከኞች በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ህይወታቸውን ላጡ ሁሉም ኢትዮጵያውያን የጸሎት እና የጧፍ ማብራት መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት አከናውነዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የሰባት ሀገራዊ እና ክልላዊ ፓርቲዎች አመራሮች እና አባላት ተገኝተው ሀዘናቸውን ገልጸዋል። የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በትግራይ ክልል የደረሰው ሀዘን የጋራ መሆኑን ጠቅሰዋል። በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ህይወታቸውን ያጡ የአማራ እና የአፋር ዜጎችን ጭምር ለማሰብ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሀዘን ቀናት ሊታወጅ ይገባ እንደነበር ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ላለፉት ዓመታት የነበረው “የእርስ በእርስ መገዳደል” በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በሌሎችም ክልሎች መቀጠሉ የሚያሳዝን እና መፍትሔ ሊበጅለት የሚገባ እንደሆነም ፖለቲከኞቹ አሳስበዋል። በአዲስ አበባ ካዛንቺስ አካባቢ በሚገኘው የኢህአፓ ጽህፈት ቤት በተካሄደው በዛሬው ስነ ስርዓት ላይ መልዕክቶቻቸውን ካስተላለፉት ውስጥ፤ የሀዘን ቀን ባታወጀበት ትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱት የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ትዴፓ)፣ የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ራዴፓ) እና የትንሣኤ 70 እንደርታ ፓርቲ (ትሰእፓ) አመራሮች ይገኙበታል። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ)፣ የአንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ፓርቲ (አኢዴፓ) አመራሮችም እንዲሁ መልዕክቶቻቸውን አስተላልፈዋል። ራሳቸውን ከኢዜማ ፓርቲ ያገለሉ የቀድሞ አመራሮች እና አባላት፤ በዛሬው መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው የሀዘን መልዕክቶቻቸውን አስደምጠዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @EthiopiaInsiderNews

አይ.ኤም.ኤፍ እና ኢትዮጵያ በገንዘብ ድጋፍ ጥያቄ ላይ ከስምምነት ለመድረስ በመጪዎቹ ሳምንታት ሊወያዩ ነው ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት በጠየቀችው የገንዘብ ድጋፍ ላይ ከስምምነት ለመድረ
አይ.ኤም.ኤፍ እና ኢትዮጵያ በገንዘብ ድጋፍ ጥያቄ ላይ ከስምምነት ለመድረስ በመጪዎቹ ሳምንታት ሊወያዩ ነው ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት በጠየቀችው የገንዘብ ድጋፍ ላይ ከስምምነት ለመድረስ በሚያስፈልጉ ማሻሻያዎች ላይ በመጪዎቹ ሳምንታት ውይይት እንደሚደረግ አይ.ኤም.ኤፍ ገለጸ። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ልዑክ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ የኢትዮጵያ መንግስት በጠየቀው ድጋፍ ላይ ውይይት ማድረጉን ተቋሙ ዛሬ ሐሙስ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የተቋሙ ልዑክ በአዲስ አበባ ቆይታ ያደረገው ከመስከረም 14 እስከ 22 ቀን 2016 እንደነበርም መግለጫው ጠቁሟል። ኢትዮጵያ ለኢኮኖሚ ማሻሻያ በጠየቀችው ድጋፍ ላይ ለመወያየት ወደ አዲስ አበባ አቅንቶ የነበረውን ልዑክ የመሩት አልቫሮ ፒሪስ ናቸው። ፒሪስ ከዚህ ቀደም ወደ ኢትዮጵያ የመጡ የአይ.ኤም.ኤፍ ልዑካንን በተደጋጋሚ በመምራት ልምድ ያካበቱ ናቸው። የልዑክ መሪው ከጉብኝታቸው መጠናቀቅ በኋላ በሰጡት መግለጫ፤ የአይ.ኤም.ኤፍ ቡድን በአዲስ አበባ ቆይታው “ጉልህ የፊስካል እና የገንዘብ ቁጥጥርን ጨምሮ የዋጋ ንረትን ለማውረድ እና ኤኮኖሚውን ለማረጋጋት የተወሰዱ ጠቃሚ እርምጃዎችን” መታዘቡን ገልጸዋል። እነዚህ እርምጃዎች የኢትዮጵያን ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ አቅም ወደ ተግባር ለመለወጥ ላለመው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስኬት “ወሳኝ መሰረት” ማስቀመጣቸውንም ፒርስ በመግለጫቸው አመልክተዋል። 🔵 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/12001/ @EthiopiaInsiderNews

ተጨማሪ መረጃ፦ የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ካስፈተኑ 3,106 ትምህርት ቤቶች መካከል 42.8 በመቶ የሚሆኑት አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ
ተጨማሪ መረጃ፦ የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ካስፈተኑ 3,106 ትምህርት ቤቶች መካከል 42.8 በመቶ የሚሆኑት አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ይፋ አድርገዋል። አምስት ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ ማሳለፋቸውንም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። ሌሎች አምስት ትምህርት ቤቶች ደግሞ ለፈተና ካስቀመጧቸው ተማሪዎች ውስጥ 94.5 በመቶ በላይ የሚሆኑትን ማሳለፋቸውንም ጨምረው ገልጸዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) ፎቶ፦ ከፋይል የተወሰደ

በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 845 ሺህ ገደማ ተማሪዎች መካከል፤ ወደ ዩኒቨርስቲ የማለፊያ ነጥብ ያመጡት ተፈታኞች ብዛት 27,267 ተማሪዎች አሊያም 3.2 በመቶዎቹ ብቻ
በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 845 ሺህ ገደማ ተማሪዎች መካከል፤ ወደ ዩኒቨርስቲ የማለፊያ ነጥብ ያመጡት ተፈታኞች ብዛት 27,267 ተማሪዎች አሊያም 3.2 በመቶዎቹ ብቻ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

ቪዲዮ፦ የአውሮፓ ህብረት እና ኢትዮጵያ የ650 ሚሊዮን ዮሮ የባለብዙ ዘርፍ ዓመታዊ መርሃግብር (multi-annual indicative program) የልማት ትብብር ስምምነት በዛሬው ዕለት ተፈራረሙ። የገንዘብ ድጋፉ፤ ለአረንጓዴ ልማት፣ ለሰብዓዊ ልማት፣ ለመልካም አስተዳደር እና ለሰላም ግንባታ ዘርፎች የሚውል መሆኑ ተገልጿል። የልማት ትብብር ስምምነቱን በአውሮፓ ህብረት በኩል የፈረሙት ትላንት ምሽት አዲስ አበባ የገቡት የህብረቱ የዓለም አቀፍ አጋርነት ኮሚሽነር ዩታ ኡርፒላይነን ናቸው። ለ4 ዓመታት በሚቆየው በዚህ የትብብር ስምምነት ሰነድ ላይ፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ኢትዮጵያን ወክለው ፊርማቸውን አኑረዋል። ዛሬ መስከረም 22 በአዲስ አበባው ሃያት ሪጀንሲ የተደረገው ይህ የፊርማ ስነ ስርዓት፤ ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ህብረት ጋር ያላት የልማት ትብብር “ወደ መደበኛው የትብብር ማዕቀፍ የተመለሰበትን ሁኔታ” የሚያመላክት መሆኑን አቶ አህመድ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። “ላለፉት 2 ዓመታት ከአውሮፓ ህብረት ጋር ያለን የገንዘብ ትብብር በተወሰነ ደረጃ ተቀዛቅዞ ነበር” ያሉት የገንዘብ ሚኒስትሩ፤ “አሁን በተሟላ ሁኔታ፤ በ4 ዓመት የትብብር ማዕቀፍ፤ ከዚህ በፊት እንደነበረው በተሻለ የገንዘብ መጠን ሊያግዙን የስምምነት ሰነድ ፈርመናል” ብለዋል። አቶ አህመድ የዛሬው መርሃ ግብር “በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መንግስት መካከል ያለው የዲፕሎማሲ ግንኙነት በከፍተኛ ደረጃ መሻሻሉን” ያሳየ ነው ቢሉም፤ የህብረቱ የዓለም አቀፍ አጋርነት ኮሚሽነር ግን የአሁኑ “የመጀመሪያ እርምጃ ነው” ባይ ናቸው። የአውሮፓ ህብረት ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ግንኙነት ቀድሞ ወደ ነበረበት ለመመለስ የሚከተለው “የደረጃ በደረጃ አካሄድን” እንደሆነ ኮሚሽነሯ በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ በድጋሚ በአጽንኦት አንስተዋል።

ቪዲዮ፦ የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ መንግስት መስጠት ያቋረጠውን ቀጥተኛ የበጀት ድጋፍ ለመቀጠል፤ አሁንም መሟላት የሚገባቸው ጉዳዮች እንዳሉ አስታወቀ። ህብረቱ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ትብብር ወደ ነበረበት ለመመለስ “የደረጃ በደረጃ አካሄድን” እንደሚከተል ገልጿል። ሃያ ሰባት አባል ሀገራትን በስሩ ያቀፈውን የአውሮፓ ህብረትን አቋም ያሳወቁት፤ የአውሮፓ ህብረት የዓለም አቀፍ አጋርነት ኮሚሽነር ዩታ ኡርፒላይነን ናቸው። ኮሚሽነሯ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ጋር ዛሬ ማክሰኞ መስከረም 22፤ 2016 በአዲስ አበባው ስካይ ላይት ሆቴል ውይይት ካደረጉ በኋላ፤ የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያን አሁንም እንደ “ስትራቴጂካዊ አጋር” እንደሚመለከታት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። የአውሮፓ ህብረት እና የኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ግንኙነት፤ በጥቅምት 2013 በትግራይ ክልል ከተቀሰቀሰው ጦርነት ወዲህ ተቀዛቅዞ ቆይቷል። ህብረቱ በጦርነቱ ምክንያት ለኢትዮጵያ መንግስት የሚሰጠውን 90 ሚሊዮን ዩሮ ከሚጠጋው የበጀት ድጋፍ ማገዱ ይታወሳል። ከዚህም በተጨማሪ በተመሳሳይ ምክንያት ለኢትዮጵያ ያዘጋጀውን አንድ ቢሊዮን ዩሮ የልማት እርዳታ ሳይያጸድቅ ቀርቷል። የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ መንግስት የሚሰጠውን ቀጥተኛ በጀት እንደገና ለመልቀቅ አስቦ እንደው ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ጥያቄ የቀረበላቸው ኮሚሽነሯ፤ ይህ የገንዘብ ድጋፍ ከመደረጉ በፊት በኢትዮጵያ በኩል መሟላት የሚገባቸው “ፖለቲካዊ ሁኔታዎች” እንዳሉ ተናግረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) 🔴 ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት ይህን ይጫኑ👉 https://youtu.be/awKunnN0JbI @EthiopiaInsiderNews

የኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልሎችን በሚያዋስነው የባቢሌ አካባቢ፤ በሁለቱ ክልሎች የጸጥታ ኃይሎች መካከል መስከረም 7፤ 2016 ዓ.ም በተደረገ የተኩስ ልውውጥ፤ ቢያንስ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን እና በር
የኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልሎችን በሚያዋስነው የባቢሌ አካባቢ፤ በሁለቱ ክልሎች የጸጥታ ኃይሎች መካከል መስከረም 7፤ 2016 ዓ.ም በተደረገ የተኩስ ልውውጥ፤ ቢያንስ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን እና በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ። በተኩስ ልውውጡ ህይወታቸውን ያጡት ሰዎች በቆሎጂ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መጠለያ ጣቢያ የሚኖሩ እንደነበሩ ኮሚሽኑ ገልጿል። መንግስታዊው የሰብዓዊ መብት ተቋም ይህን የገለጸው ዛሬ ሰኞ መስከረም 21፤ 2016 ባወጣው መግለጫ ነው። ኢሰመኮ በዚሁ መግለጫው በወቅቱ በነበረው የተኩስ ልውውጥ ከተፈናቃዮች በተጨማሪ በአካባቢው በሚኖሩ የሲቪል ሰዎች ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት መድረሱን ይፋ አድርጓል። የመስከረም ሰባቱን ክስተት በተመለከተ ተጎጂዎችን፣ የኦሮሚያ እና የሶማሌ ክልል የጸጥታ አካላትን፣ የቆሎጂ መጠለያ ሠራተኞችን እና የሆስፒታል ባለሙያዎችን ማነጋገሩን የገለጸው ኢሰመኮ፤ በወቅቱ በሲቪል ሰዎች ላይ ጉዳት የደረሰው “የጸጥታ ኃይሎች ተገቢ የሆነውን ጥንቃቄ ባለማድረጋቸው መሆኑን” አመልክቷል። ጉዳቱ እንዲደርስ ባደረጉ የጸጥታ ኃይሎች ላይ “አስፈላጊው ምርመራ ተደርጎ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ” እና ተጎጂዎችም “እንዲካሱ” ኮሚሽኑ ጠይቋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11989/ @EthiopiaInsiderNews