uk
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Відкрити в Telegram

Показати більше
2 485
Підписники
Немає даних24 години
-157 днів
-5230 день
Архів дописів
የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ “ስምሪት የሚሰጡ” ያላቸውን እና ሌሎችንም ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ማዋል መጀመሩን መንግስት አስታወቀ የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ በአማራ ክልል ከተፈጠረው
የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ “ስምሪት የሚሰጡ” ያላቸውን እና ሌሎችንም ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ማዋል መጀመሩን መንግስት አስታወቀ የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ በአማራ ክልል ከተፈጠረው የጸጥታ መደፍረስ ጋር “ግንኙነት ያላቸው፣ ጉዳዮችን የሚያባብሱ፣ ስምሪት የሚሰጡ” ያላቸውን ግለሰቦችን ከትላንት ምሽት አንስቶ በቁጥጥር ስር ማዋል መጀመሩን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። ከትላንትና ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ባለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚወሰዱ እርምጃዎች ጋር በተያያዘ የሚነሱ የሰብአዊ መብት አያያዝ ሁኔታዎችን የሚከታተል አካል እንደሚደራጅም የኮሙኒኬሽን አገልግሎቱ ገልጿል። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ይህንን ያስታወቀው፤ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ዛሬ ቅዳሜ ሐምሌ 29፤ 2015 በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። ጋዜጣዊ መግለጫውን የሰጡት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ፤ በአማራ ክልል ስላለው የጸጥታ ችግር ሰፋ ያለ ጊዜ ወስደው ማብራሪያ ሰጥተዋል። ዶ/ር ለገሰ በዚህ መግለጫቸው በአማራ ክልል የተፈጠረው የጸጥታ መደፍረስ፤ የሰሜኑ ጦርነት የሰላም ስምምነትን “ባልተቀበሉ፣ ጦርነቱን የገቢ ማግኛ እና መክበሪያ አድርገው በወሰዱ፣ ‘የሰላም አማራጮች ጥቅሞቻችን እና ፍላጎታችንን አያሳኩም’ ብለው በገመቱ ወገኖች” ምክንያት የተከሰተ ነው ብለዋል። እነዚህ ግለሰቦች በአማራ ክልል ከተሞች ውስጥ “በትጥቅ የተደገፈ የሰላማዊ ሰልፎች፣ የስርዓት ለውጥ እና ህገ መንግስት የመናድ ተግባራት” ላይ ተሰማርተው ቆይተዋል ሲሉም ወንጅለዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11661/ @EthiopiaInsiderNews

ምስላዊ መረጃ፦ “የህዝብን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ” በሚል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፤ የሚወሰዱ እርምጃዎች እና የተከለከሉ ተግባራት ተዘርዝረዋል። በአዋጁ መሰረት
ምስላዊ መረጃ፦ “የህዝብን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ” በሚል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፤ የሚወሰዱ እርምጃዎች እና የተከለከሉ ተግባራት ተዘርዝረዋል። በአዋጁ መሰረት “ከአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ፈቃድ ውጭ ማንኛውንም የአደባባይ ስብሰባ ወይም ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ” የተከለከለ ነው። በአማራ ክልል “የአመጽ እንቅስቃሴን የሚያበረታታ፣ ሰላማዊ ዜጎችን የሚያሸብር እንዲሁም የጸጥታ መደፍረሱን የሚያባብስ ንግግር፣ የቀጥታም ሆነ የተዘዋዋሪ ቅስቀሳ በማንኛውም መንገድ ማድረግ ወይም ማሰራጨት” መከልከሉም በአዋጁ ላይ ሰፍሯል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መምሪያ ዕዙን “እንቅስቃሴ” እንዲሁም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን “አላማ የሚቃረን እና የሚቃወም” ንግግር ወይም የቅስቀሳ በተመሳሳይ ክልከላ ተደርጎበታል። ለታጣቂ ቡድኖች “በየትኛውም መንገድ” “የገንዘብ፣ የመረጃ፣ የቁስም ሆነ የሞራል ድጋፍ ማድረግ” መከልከሉ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ድንጋጌ ላይ ተቀምጧል። ማንኛውንም ወሳኝ በሆነ የአገልግሎት ዘርፍም ሆነ በምርት ሂደት ላይ “የስራ ማስተጓጎል ወይም የኢኮኖሚ አሻጥር መፈጸም” እንደማይቻልም በአዋጁ ተደንግጓል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @EthiopianInsider1

ምስላዊ መረጃ፦ “የህዝብን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ” በሚል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፤ የሚወሰዱ እርምጃዎች እና የተከለከሉ ተግባራት ተዘርዝረዋል። በአዋጁ መሰረት
ምስላዊ መረጃ፦ “የህዝብን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ” በሚል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፤ የሚወሰዱ እርምጃዎች እና የተከለከሉ ተግባራት ተዘርዝረዋል። በአዋጁ መሰረት “ከአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ፈቃድ ውጭ ማንኛውንም የአደባባይ ስብሰባ ወይም ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ” የተከለከለ ነው። በአማራ ክልል “የአመጽ እንቅስቃሴን የሚያበረታታ፣ ሰላማዊ ዜጎችን የሚያሸብር እንዲሁም የጸጥታ መደፍረሱን የሚያባብስ ንግግር፣ የቀጥታም ሆነ የተዘዋዋሪ ቅስቀሳ በማንኛውም መንገድ ማድረግ ወይም ማሰራጨት” መከልከሉም በአዋጁ ላይ ሰፍሯል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መምሪያ ዕዙን “እንቅስቃሴ” እንዲሁም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን “አላማ የሚቃረን እና የሚቃወም” ንግግር ወይም የቅስቀሳ በተመሳሳይ ክልከላ ተደርጎበታል። ለታጣቂ ቡድኖች “በየትኛውም መንገድ” “የገንዘብ፣ የመረጃ፣ የቁስም ሆነ የሞራል ድጋፍ ማድረግ” መከልከሉ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ድንጋጌ ላይ ተቀምጧል። ማንኛውንም ወሳኝ በሆነ የአገልግሎት ዘርፍም ሆነ በምርት ሂደት ላይ “የስራ ማስተጓጎል ወይም የኢኮኖሚ አሻጥር መፈጸም” እንደማይቻልም በአዋጁ ተደንግጓል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @EthiopiaInsiderNews

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ፤ ከአማራ ክልል በተጨማሪ በሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎችም “እንዳስፈላጊነቱ” ተፈጻሚ እንደሚሆን ተገለጸ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ያወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፤ ከአ
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ፤ ከአማራ ክልል በተጨማሪ በሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎችም “እንዳስፈላጊነቱ” ተፈጻሚ እንደሚሆን ተገለጸ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ያወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፤ ከአማራ ክልል በተጨማሪ እንዳስፈላጊነቱ “በየትኛውም የሃገሪቱ አካባቢ ተፈጻሚነት እንደሚኖረው” ተገለጸ። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ከታወጀበት ጊዜ ጀምሮ ለስድስት ወር ጸንቶ ይቆያልም ተብሏል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ አርብ ሚያዝያ 28፤ 2015 ባደረገው መደበኛ ስብሰባ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ የወሰነው፤ በአማራ ክልል ይታያል ያለውን “በትጥቅ የተደገፈ ህገወጥ እንቅስቃሴ”፤ “በመደበኛ የህግ ማስክበር ስርዓት ለመቆጣጠር ወደ ማይቻልበት ደረጃ የተሸጋገረ በመሆኑ” ምክንያት እንደሆነ አስታውቆ ነበር። በዚህም ምክንያት “የህዝብን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅ” እንዲሁም “ህግ እና ስርዓት ለማስከበር” የአስቸኳይ ጊዜ እርምጃዎችን መውሰድ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ አዋጁ መታወጁን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ገልጿል። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ ምሽት ይፋ ያደረገው የድንጋጌው ዝርዝር፤ የአዋጁ የተፈጻሚነት ወሰን “በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስተዳደር እንዲሁም በክልሉ አስተዳደር የህዝብን ሰላምና ጸጥታ ለማስከበር የሚወሰድ እርምጃን” የሚያካትት መሆኑን አስታውቋል። ከዚህም በተጨማሪ አዋጁ “በክልሉ ወይም በሃገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የጸጥታ ችግር የሚያባብስ ማንኛውም እንቅስቃሴ ወይም ሁኔታን በሚመለከት እንደ አስፈላጊነቱ በየትኛውም የሃገሪቱ አካባቢ ተፈጻሚነት እንደሚኖረው” በድንጋጌው ላይ ሰፍሯል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) * * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11636/ @EthiopiaInsiderNews

በጎንደር ዩኒቨርስቲ የ12ተኛ ክፍል ፈተና ፈታኝ እና ሁለት ፖሊሶች መገደላቸውን ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ በጎንደር ዩኒቨርስቲ የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሲሰጥ የነበረ አንድ ፈታኝ እና ሁለት የ
በጎንደር ዩኒቨርስቲ የ12ተኛ ክፍል ፈተና ፈታኝ እና ሁለት ፖሊሶች መገደላቸውን ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ በጎንደር ዩኒቨርስቲ የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሲሰጥ የነበረ አንድ ፈታኝ እና ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት መገደላቸውን እንዲሁም አንዱ መቁሰሉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ግድያውን የፈጸሙት “የታጠቁ ኢ-መደበኛ ኃይሎች” መሆናቸውን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገልጿል። የትምህርት ሚኒስቴር ይህንን ያስታወቀው የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መጠናቀቅን አስመልክቶ ዛሬ አርብ ሐምሌ 28፤ 2015 በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። ዛሬ ጠዋት የተጠናቀቀውን ይህንን ፈተና 840,859 ተማሪዎች መፈተናቸውን መግለጫውን የሰጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል። ዘንድሮው የፈተና አሰጣጥ “እጅግ ስኬታማ” እንደነበር በዛሬው መግለጫቸው ላይ የተናገሩት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤ ያጋጠሙ ችግሮችንም በዝርዝር ጠቅሰዋል። የትምህርት ሚኒስትሩ ካጋጠሙ ችግሮች ውስጥ በቀዳሚነት የጠቀሱት፤ በጎንደር ዩኒቨርስቲ ሶስት ካምፓሶች በትላንትናው ዕለት ተፈጥሯል ያሉትን ክስተት ነው። * * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11619/ @EthiopiaInsiderNews

በአማራ ክልል “እርስ በእርስ በመገዳደል ከፍተኛ የሆነ ሰብአዊ ኪሳራ እያጋጠመ ነው” - ዶ/ር ይልቃል ከፋለ በአማራ ክልል በተከሰተው ግጭት ምክንያት “እርስ በእርስ በመገዳደል ከፍተኛ የሆነ ሰብአዊ
በአማራ ክልል “እርስ በእርስ በመገዳደል ከፍተኛ የሆነ ሰብአዊ ኪሳራ እያጋጠመ ነው” - ዶ/ር ይልቃል ከፋለ በአማራ ክልል በተከሰተው ግጭት ምክንያት “እርስ በእርስ በመገዳደል ከፍተኛ የሆነ ሰብአዊ ኪሳራ” እያጋጠመ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ተናገሩ። ዶ/ር ይልቃል በክልሉ “በየአካባቢው” ይፈጸማል ያሉት “ትንኮሳ በአስቸኳይ እንዲቆም” እና የድርጊቱ ተሳታፊዎች  ወደ “ሰላማዊ ውይይት እንዲመለሱ” ጥሪ አቅርበዋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ይህንን የተናገሩት የክልሉን ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ አስመልክቶ ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 26፤ 2015 በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። መንግስት የክልል ልዩ ኃይል አባላትን ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማስገባት ስራ ከጀመረ ወዲህ በአማራ ክልል ስለተፈጠረው የጸጥታ መደፍረስ በመግለጫቸው ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ የክልሉ የጸጥታ መዋቅር እና የመከላከያ ሰራዊት “ህግ ለማስከበር እየተንቀሳቀሱ” መሆኑን ገልጸዋል። ለመከላከያ ሰራዊቱ “ያልተገባ ስም በመስጠት መርዘኛ ፕሮፓጋንዳ እየተነዛ ነው” ሲሉ የተቹት ዶ/ር ይልቃል፤ የአማራ ክልል የጸጥታ መዋቅር እና የመከላከያ ሰራዊት በየአካባቢው ሲንቀሳቀስ “መተንኮስ ተገቢም፤ ህጋዊም አይደለም” ሲሉ ድርጊቱን አውግዘዋል። በአማራ ክልል በጸጥታ መዋቅሩ እንዲሁም በነዋሪው ላይ “እርስ በእርስ መገዳደል” እየተስተዋለ መሆኑን የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ይህ ድርጊት እያስከተለ ያለው “ሰብአዊ ኪሳራ ከፍተኛ” እንደሆነም ገልጸዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11597/ @EthiopiaInsiderNews

በትግራይ ክልል ትላንት እና ዛሬ ለሶስት ጊዜ ያህል የመሬት መንቀጥቀጥ ያስከተለው ንዝረት መከሰቱ ተገለጸ በትግራይ ክልል የተለያዩ ከተሞች ትላንት ምሽት እና ዛሬ ጠዋት፤ ለሶስት ጊዜ ያህል የመሬት
በትግራይ ክልል ትላንት እና ዛሬ ለሶስት ጊዜ ያህል የመሬት መንቀጥቀጥ ያስከተለው ንዝረት መከሰቱ ተገለጸ በትግራይ ክልል የተለያዩ ከተሞች ትላንት ምሽት እና ዛሬ ጠዋት፤ ለሶስት ጊዜ ያህል የመሬት መንቀጥቀጥ ያስከተለው ንዝረት መከሰቱን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጂኦፊዚክስ፣ ህዋ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። በክልሉ ዋና ከተማ መቐለ እና በሌሎች አራት ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎች ንዝረቱ በአካባቢያቸው ማጋጠሙን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል። ይህን ንዝረት ያስከተለው የመጀመሪያው እና ዋናው የመሬት መንቀጥቀጥ ትላንት ማክሰኞ ሐምሌ 25፤ 2015 የተከሰተው፤ በኤርትራ ባህር ዳርቻ ዳህላክ ደሴት አካባቢ መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሶሲሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ፕሮፌሰር አታላይ አየለ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል። በሬክተር ስኬል 5.4 ሆኖ የተለካው ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ የተመዘገበው፤ ትላንት ምሽት ሁለት ሰዓት ከ15 ደቂቃ ላይ እንደነበር በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስር ባለ ኢንስቲትዩት የመሬት መንቀጥቀጥን የሚያጠናውን የትምህርት ክፍል የሚመሩት ፕሮፌሰር አታላይ አስረድተዋል። የትላንቱ የመሬት መንቀጥቀጥ “መለስተኛ” (moderate) የሚባል ምድብ ውስጥ የሚወድቅ ቢሆንም “የሚናቅ” እንዳልሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ ተመራማሪ እና ባለሙያው ተናግረዋል። “ይህንን ያህል መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ አዲስ አበባ [ከተማ ውስጥ] ቢፈጠር ብዙ ህንጻዎች ይወድማሉ” ሲሉ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ፕሮፌሰር አታላይ አነጻጽረዋል። * * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11589/ @EthiopiaInsiderNews

በሽብር ወንጀል የተከሰሱ 23 ተከሳሾች፤ ጉዳያቸውን የያዙት ዋና ዳኛ እንዲቀየሩ አቤቱታ አቀረቡ በሽብር ወንጀል ክስ የቀረበባቸው አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች፤ ጉዳያቸ
በሽብር ወንጀል የተከሰሱ 23 ተከሳሾች፤ ጉዳያቸውን የያዙት ዋና ዳኛ እንዲቀየሩ አቤቱታ አቀረቡ በሽብር ወንጀል ክስ የቀረበባቸው አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች፤ ጉዳያቸው የሚመለከተውን ችሎት በሰብሳቢነት የሚመሩት ዳኛ ከቦታቸው እንዲነሱ ጥያቄ አቀረቡ። የተከሳሾችን አቤቱታ በጽሁፍ የተቀበለው ፍርድ ቤቱ፤ አቤቱታውን መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለሚቀጥለው ዓመት ጥቅምት 15፤ 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ለዛሬ ማክሰኞ ሐምሌ 25፤ 2015 ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው፤ ከምስክሮች ጥበቃ ጋር በተያያዘ ብይን ለመስጠት ነበር። ሆኖም ሶስቱ የችሎቱ ዳኞች ወደ አዳራሽ ገብተው የችሎቱን መደበኛ ስራ ለማስጀመር ግራ ቀኙን ከመሰየማቸው በፊት፤ የተከሳሽ ጠበቆች የደንበኞቻቸው ቤተሰቦች “ችሎት ተገኝተው ጉዳዩን እንዳይታደሙ በጸጥታ ኃይሎች ተከልክለዋል” የሚል አቤቱታቸውን አቅርበዋል። የዛሬውን የችሎት ውሎ ለመታደም፤ ወደ ስልሳ የሚጠጉ የተከሳሾች ቤተሰቦች እና ወዳጆች በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተገኝተው ነበር። የፍርድ ቤቱን ውሎ ለመታደም የፈለጉ ሰዎች ከረፋዱ ሶስት ሰዓት ጀምሮ ችሎቱ ከሚሰየምበት “ፍትሕ አዳራሽ” አቅራቢያ ተሰባስበው ሲጠባበቁ ቢቆዩም፤ ችሎት የሚጀመርበት ሰዓት ሲቃረብ በስፍራው የነበሩ የማረሚያ ቤት እና የፌደራል ፖሊስ አባላት ታዳሚዎችን ከአካባቢው እንዲርቁ አድርገዋቸዋል። * * ዝርዝር የችሎት ውሎ ዘገባውን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11584/ @EthiopiaInsiderNews

አዲሱ 12ኛ ክልል፤ በሳምንቱ መጨረሻ ከነባሩ ደቡብ ክልል ስልጣን ሊረከብ ነው የደቡብ ክልል ምክር ቤት ከመጪው አርብ ጀምሮ ለሶስት ቀናት በሚያደርገው መደበኛ ጉባኤ፤ በህዝበ ውሳኔ ለተመሰረተው 12
አዲሱ 12ኛ ክልል፤ በሳምንቱ መጨረሻ ከነባሩ ደቡብ ክልል ስልጣን ሊረከብ ነው የደቡብ ክልል ምክር ቤት ከመጪው አርብ ጀምሮ ለሶስት ቀናት በሚያደርገው መደበኛ ጉባኤ፤ በህዝበ ውሳኔ ለተመሰረተው 12ኛው አዲስ ክልል ስልጣን እንደሚያስረክብ የምክር ቤቱ ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ወ/ሮ አልማዝ ዘውዱ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ከስልጣን ርክክቡ በኋላ የመዋቅር፣ የህገ መንግስት እና የስያሜ ለውጦችን እንደሚያደርግ የሚጠበቀው የነባሩ የደቡብ ክልል የወደፊት አደረጃጀት ሁኔታ በዚህ ጉባኤ ላይ እንደማይነሳ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተሯ ገልጸዋል። አዲሱ የ“ደቡብ ኢትዮጵያ” ክልል የኢፌዴሪ 12ኛ ክልል ሆኖ እንዲደራጅ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሙሉ ድምጽ የወሰነው፤ ከአንድ ወር በፊት ሰኔ መጨረሻ ላይ ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ ላይ ነበር። ይህ ውሳኔ በተላለፈበት ወቅት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር “ነባሩ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል አዲስ ለተመሰረተው ክልል በአፋጣኝ የስልጣን ርክክብ እንዲያደርግ አቅጣጫ ተቀምጧል” ማለታቸው ይታወሳል። የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ይህን ቢሉም የደቡብ ክልል የስልጣን ርክክቡን ለማድረግ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ጉባኤ በኋላ አንድ ወር ፈጅቶበታል። በኢትዮጵያ ካሉ ክልሎች የዚህን ዓመት ማጠቃለያ መደበኛ ጉባኤ ለማካሄድ የመጨረሻ የሆነው የደቡብ ክልል፤ እስከ መጪው እሁድ ሐምሌ 30 በሚቆየው ስብሰባው ከስልጣን ርክክብ በተጨማሪ የክልሉን አስፈጻሚ አካላት የ2015 ሪፖርት ይገመግማል ተብሏል። የክልሉ ፍርድ ቤቶች እና የኦዲተር መስሪያ ቤት ሪፖርትም በምክር ቤቱ ጉባኤ ላይ እንደሚቀርብ ተገልጿል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11580/ @EthiopiaInsiderNews

ገዢው ፓርቲ በፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይት ላይ የሚኖረውን ተሳትፎ “መልሶ እንደሚያጤነው” አስታወቀ ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በሚደረገው ውይይት ላይ የሚያደርገውን ተሳትፎ “እንደ
ገዢው ፓርቲ በፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይት ላይ የሚኖረውን ተሳትፎ “መልሶ እንደሚያጤነው” አስታወቀ ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በሚደረገው ውይይት ላይ የሚያደርገውን ተሳትፎ “እንደገና መልሶ እንደሚያጤነው” የፓርቲው የፖለቲካና የርዕዮተ ዓለም ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ። አቶ ዛዲግ ይህን ያሉት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ እና ምርጫ ነክ ጉዳዮች ላይ ባደረጓቸው ተከታታይ ውይይቶች ወቅት ብልጽግና ፓርቲን የተመለከቱ ጠንከር ያሉ ትችቶች መቅረባቸውን ተከትሎ ነው። የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ውይይት እና ምክክሮችን ማድረግ የጀመሩት ካለፈው ግንቦት ወር መጨረሻ ጀምሮ ነው። በአዲስ አበባው ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል በዛሬው ዕለት በተካሄደ ውይይት፤ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ስድስተኛውን ሀገራዊ ምርጫ፣ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አፈጻጸምን፣ የምርጫ ስነ ስርዓትን እና የአካባቢያዊ ምርጫዎችን በተመለከተ ለሁለት ሰዓታት ገደማ የቡድን ውይይት አድርገዋል። የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮቹ ከቡድን ውይይቱ በኋላ በስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይ ተስተውለዋል ያሏቸውን “ተግዳሮቶች” ዘርዝረዋል። ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ “የገዢው ፓርቲ ተጽዕኖ ነበረበት” ከሚለው አንስቶ፤ ሂደቱ “ነጻ እና ገለልተኛ አልነበረም” እስከሚለው ድረስ በተግዳሮትነት ተነስተዋል። ምርጫው “በብዙ አካባቢዎች አልተካሄደም” የሚለው አስተያየትም ሌላው በችግርነት የተነሳ ነው። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11564/ @EthiopiaInsiderNews

የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በተመረጠላቸው “የትኩረት መስክ” ብቻ እንዲያስተምሩ የሚያደርገው አዲስ አሰራር እንዴት ይተገበራል? በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ 47 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች፤ ራስ ገዝ መሆንን ጨምሮ አዳዲስ አሰራሮችን ለመተግበር እየተዘጋጁ ይገኛሉ። “አጠቃላይ” የትምህርት ዘርፎችን ለተማሪዎች ሲሰጡ የቆዩት እነዚህን ዩኒቨርስቲዎች፤ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ በተለየላቸው “የተልዕኮ እና የትኩረት መስክ” ብቻ የሚያስተምሩ ተቋማት ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዕቅድ መሰረት፤ ከመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የተወሰኑት “አጠቃላይ” ሆነው የሚቀጥሉ ሲሆኑ ሌሎቹ ግን የምርምር፣ የ“አፕላይድ ሳይንስ” እንዲሁም የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲዎች ሆነው ይቀጥላሉ። የምርምር ዩኒቨርስቲ ተብለው የተለዩት፤ “የመጀመሪያ ትውልድ” በሚል መለያ የሚታወቁት የአዲስ አበባ፣ ጎንደር፣ ጅማ፣ መቐለ፣ አርባ ምንጭ፣ ባሕር ዳር፣ ሀዋሳ እና ሐረማያ ዩኒቨርስቲዎች ናቸው። አምቦ፣ ጅግጅጋ፣ ደብረ ብርሃን፣ አክሱም፣ ዲላ እና ድሬዳዋ ዩኒቨርስቲዎች የተካተቱበት “ሁለተኛው ትውልድ” የ15 ዩኒቨርስቲዎች ስብስብ ደግሞ፤ የተግባር ሳይንስ (አፕላይድ ሳይንስ) ላይ ትኩረት የሚያደርግ ይሆናል። ሃያ አንድ ዩኒቨርስቲዎች ያሉበት “የሶስተኛው ትውልድ” የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምድብ፤ በ“አጠቃላይ” ዩኒቨርስቲነት የሚቀጥል ይሆናል። የ“ሶስተኛው ትውልድ” ዩኒቨርስቲዎች ከሚባሉት ውስጥ ቦረና፣ እንጅባራ፣ ቀብሪ ደሃር፣ ወራቤ፣ ኦዳ ቡልቱም፣ ደባርቅ፣ ጅንካ እና ጋምቤላ ዩኒቨርስቲዎች ይገኙበታል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11545/ @EthiopianInsider1

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ 17 ቢሊዮን ብር ዓመታዊ በጀት አጸደቀ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ ለ2016 በጀት ዓመት የሚሆን 17 ቢሊዮን ብር በጀት አጸደቀ። የክልሉ ጊዜያ
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ 17 ቢሊዮን ብር ዓመታዊ በጀት አጸደቀ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ ለ2016 በጀት ዓመት የሚሆን 17 ቢሊዮን ብር በጀት አጸደቀ። የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ካጸደቀው በጀት ውስጥ 74 በመቶው የሚሸፈነው የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል ከሚያስተላልፈው የድጋፍ በጀት ነው። የትግራይ ክልል የሰሜኑ ጦርነት ከተነሳ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በመደበኛ ሁኔታ በጀት ያጸደቀው፤ ባለፈው ሳምንት አርብ ሐምሌ 14፤ 2015 እንደሆነ የክልሉ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር ወ/ሮ ሀንሳ ተክላይ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ለክልሉ መንግስት የሚመደበው በጀት ከዚህ ቀደም ይጸድቅ የነበረው በትግራይ ክልል ምክር ቤት ነበር። የ2016 በጀት በጊዜያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ የጸደቀው የትግራይ ክልል ምክር ቤት ህግ የማውጣት ስልጣኑን ለክልሉ ስራ አስፈጻሚ አካል በመስጠቱ መሆኑን ኮሚሽነሯ አስረድተዋል። የክልሉ ካቢኔ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ባደረገው ስብሰባ፤ ለ2016 በጀት ዓመት 17 ቢሊዮን ብር በጀት ማጽደቁን የጊዜያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ አባል የሆኑት ወ/ሮ ሀንሳ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ይህ በጀት የሰሜኑ ጦርነት ከመቀስቀሱ አስቀድሞ ለ2013 በጀት ዓመት ጸድቆ ከነበረው “ከ18 ቢሊዮን ብር በላይ” ጋር ሲነጻጸር ቅናሽ ማሳየቱን ጠቁመዋል። የአሁኑ በጀት በ2012 በክልሉ ምክር ቤት ከጸደቀው በጀት ጋር ሲነጻጸር ያለው ልዩነት የ300 ሚሊዮን ብር ገደማ ብቻ ነው። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11538/ @EthiopiaInsiderNews

በአማራ ክልል ስር የሚገኘው አዲ አርቃይ ወረዳ መጠሪያውን ሊቀይር ነው በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ውስጥ የሚገኘው አዲ አርቃይ ወረዳ ስያሜውን ለመለወጥ ሁለት አማራጮችን ለህዝብ ውይይት አቀረበ
በአማራ ክልል ስር የሚገኘው አዲ አርቃይ ወረዳ መጠሪያውን ሊቀይር ነው በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ውስጥ የሚገኘው አዲ አርቃይ ወረዳ ስያሜውን ለመለወጥ ሁለት አማራጮችን ለህዝብ ውይይት አቀረበ። የወረዳው ምክር ቤት ስያሜውን “ሰገነት” አሊያም “ሰላም በር” ወደሚል መጠሪያ ለመቀየር የወሰነው፤ ነባሩ መጠሪያ “የክልሉንም ሆነ የወረዳውን ህዝብ የሚገልጽ ባለመሆኑ ነው” ብሏል። ከትግራይ ክልል ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን አጎራባች የሆነው የአዲ አርቃይ ወረዳ ምክር ቤት የስያሜ መቀየር ውሳኔውን ያስተላለፈው፤ ከሁለት ሳምንት በፊት ሐምሌ 1፤ 2015 ባደረገው ስብሰባ እንደሆነ የምክር ቤቱ ምክትል አፈጉባኤ አቶ ደረጀ ጌትነት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የወረዳው ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ጽህፈት ቤት ይህን ጉዳይ በተመለከተ ጥናት የሚያደርግ ኮሚቴ ከስብሰባው አስቀድሞ አቋቁሞ እንደነበር አቶ ደረጀ ገልጸዋል። ጥናቱን ሲያከናውን የቆየው ኮሚቴ በሐምሌ ወር መጀመሪያ በተካሄደው የወረዳው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ፤ ሶስት የስያሜ አማራጮችን አቅርቦ እንደነበር ምክትል አፈ ጉባኤው አመልክተዋል። ከቀረቡት አማራጮች “ሀገረ ሰላም” የሚለው ውድቅ ሲደረግ “ሰገነት” እና “ሰላም በር” የሚሉት መጠሪያዎች ግን ለህዝብ ውይይት እንዲቀርቡ መወሰኑን አክለዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11518/ @EthiopiaInsiderNews

የቀድሞው የብአዴን ከፍተኛ አመራር አቶ ታደሰ ካሳ ከእስር ተለቀቁ ለአራት ዓመት ተኩል በእስር ላይ የቆዩት የቀድሞው የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) ከፍተኛ አመራር አቶ ታደሰ ካሳ ዛሬ
የቀድሞው የብአዴን ከፍተኛ አመራር አቶ ታደሰ ካሳ ከእስር ተለቀቁ ለአራት ዓመት ተኩል በእስር ላይ የቆዩት የቀድሞው የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) ከፍተኛ አመራር አቶ ታደሰ ካሳ ዛሬ ሐሙስ ከእስር መለቀቃቸውን ጠበቃቸው ህይወት ሊላይ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። አቶ ታደሰ ከእስር የተለቀቁት፤ የፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎት በነጻ እንዲለቀቁ ትዕዛዝ ካስተላለፈ አንድ ሳምንት በኋላ ነው። ከጥረት ኮርፖሬት ጋር በተያያዘ በከባድ የሙስና ወንጀል ተከስሰው የተፈረደባቸው አቶ ታደሰን በተመለከተ፤ የፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎት ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ዕለት በዋለው ችሎቱ ነበር። ችሎቱ ጉዳዩን የተመለከተው የአማራ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ2012 ዓ.ም “ጥፋተኛ ናቸው” በማለት አቶ ታደሰ ላይ ያስተላለፈውን ቅጣት በተመለከተ በቀረበለት አቤቱታ መሰረት ነው። ደንበኛቸው እስከ ዛሬ ድረስ ሳይፈቱ የቆዩት፤ ለአንድ ዓመት ከስድስት ወራት የታሰሩበት የቃሊቲ ማረሚያ ቤት “በራሱ መልቀቅ ስለማይችል” እንደሆነ ጠበቃ ህይወት አስረድተዋል። ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ አብዛኛውን የእስር ጊዜያቸውን በባህር ዳር ማረሚያ ቤት ያሳለፉት አቶ ታደሰ፤ በህክምና ምክንያት በተዛወሩበት ቃሊቲ ማረሚያ ቤት የቆዩት “በአደራ” ነበር። * * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11509/ @EthiopiaInsiderNews

የመጀመሪያው ዙር 75 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎች የመበተን ስራ በመጪው መስከረም ሊጀመር ነው ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን የመጀመሪያውን ዙር 75 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎችን የመበተን (demobilize) ስራ በ
የመጀመሪያው ዙር 75 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎች የመበተን ስራ በመጪው መስከረም ሊጀመር ነው ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን የመጀመሪያውን ዙር 75 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎችን የመበተን (demobilize) ስራ በመስከረም ወር እንደሚጀምር አስታወቀ። በተሃድሶ ፕሮግራም ውስጥ እንዲያልፉ እቅድ ተይዞላቸው የነበሩ የቀድሞ ተዋጊዎች ብዛትም በ122 ሺህ ገደማ መጨመሩን ገልጿል። ትጥቃቸውን የሚፈቱ ኃይሎች “ሰላማዊ ኑሮ መምራት እንዲችሉ ለማድረግ” የተቋቋመው የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን፤ 250 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎችን በክህሎት ስልጠና እና በስራ ፈጠራ ወደ ማህበረሰቡ በዘላቂነት እንዲቀላቀሉ ለማድረግ አቅዶ ነበር። ከተቋቋመ ስምንት ወራት ያስቆጠረው ኮሚሽኑ፤ በእነዚህ ጊዜያት ውስጥ የቀድሞ ተዋጊዎች ከሚገኙባቸው ክልሎች እና የተሃድሶ ፕሮግራሙን በገንዘብ ከሚደግፉ አካላት ጋር ውይይት ሲያደርግ ቆይቷል። በፕሮግራሙ ውስጥ ያልፋሉ ተብሎ የሚጠበቁ የቀድሞ ተዋጊዎች ብዛት 371,971 እንደሆነ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽኑ ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 12፤ 2015 ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር በአዲስ አበባ ባደረገው ውይይት ላይ አስታውቋል። ኮሚሽኑን የሚመሩት የቀድሞው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ተሾመ ቶጋ፤ “ከሚመለከታቸው የክልል፣ የመከላከያ እና የእኛ ተቋም ጋር ሆነን በመነጋገር የደረስንበት ዳታ [ነው]” ሲሉ የቀድሞ ተዋጊዎች ብዛት ቀደም ሲል በእቅድ ከነበረው የጨመረበትን ምክንያት አስረድተዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11504/ @EthiopiaInsiderNews

አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ በፍርድ ቤት ውድቅ ተደረገ በሽብር ወንጀል የተከሰሱ አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች
አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ በፍርድ ቤት ውድቅ ተደረገ በሽብር ወንጀል የተከሰሱ አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ፤ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውድቅ ተደረገ። የተከሳሾችን በቁጥጥር ስር መዋል በተመለከተ የጸጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ያወጣውን መግለጫ በድረ ገጻቸው የጫኑ መገናኛ ብዙሃን ዘገባዎቻቸውን እንዲያወርዱም ፍርድ ቤቱ አዝዟል። ይህን ትዕዛዝ የሰጠው ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 12፤ 2015 የዋለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሶስተኛ የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ችሎት ነው። ችሎቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጎ ትዕዛዞችን በሰጠበት ቅጽበት፤ ተከሳሾች በጭበጨባ የታጀበ መፈክር አሰምተዋል። የተከሳሾቹ መፈክር እና ጭብጨባ፤ የችሎት ውሎ ተጠናቅቆ ታዳሚዎች ከአዳራሽ ከወጡ በኋላም አላቋረጠም ነበር። በተከሳሾች ጭብጨባ የተጠናቀቀው ችሎት ለዛሬ ተቀጥሮ የነበረው፤ ጠበቆች ባቀረቡት የተከሳሾች የዋስትና ጥያቄ ላይ ብይን ለመስጠት እና ከዚህ በፊት የተሰጡ ትዕዛዞችን አፈጻጸም ለመከታተል ነበር። የተከሳሾችን የዋስትና መብት በተመለከተ ከ20 ቀናት በፊት በነበረ የችሎት ውሎ በተደረገ ክርክር፤ ጠበቆች የደንበኞቻቸው የዋስትና ጉዳይ ሊታይ የሚገባው “የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በወጣው አዋጅ እና በህገ መንግስቱ እንጂ በወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ህጉ አይደለም” ሲሉ ተከራክረዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11500/ @EthiopiaInsiderNews

ኢትዮ ቴሌኮም ካለፈው ዓመት በ14.5 ቢሊዮን ብር የጨመረ ገቢ ማግኘቱን ገለጸ ኢትዮ ቴሌኮም በ2015 በጀት ዓመት 75.8 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ፡፡ ተቋሙ ካገኘው ገቢ ውስጥ 18.78
ኢትዮ ቴሌኮም ካለፈው ዓመት በ14.5 ቢሊዮን ብር የጨመረ ገቢ ማግኘቱን ገለጸ ኢትዮ ቴሌኮም በ2015 በጀት ዓመት 75.8 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ፡፡ ተቋሙ ካገኘው ገቢ ውስጥ 18.78 ቢሊዮን ብር የሚሆነው የተጣራ ትርፍ መሆኑም ተገልጿል፡፡ መንግስታዊው የቴሌኮም አቅራቢ ኢትዮ ቴሌኮም ይህንን ያስታወቀው የተጠናቀቀውን የ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸሙን በተመለከተ ዛሬ ማክሰኞ ሐምሌ 11፤ 2015 በአዲስ አበባው ስካይ ላይት ሆቴል እየሰጠ ባለው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው፡፡ የተቋሙን የስራ አፈጻጸም ለጋዜጠኞች ይፋ ያደረጉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ፤ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት ተቋሙ "ሊድ" የተባለውን ስትራቴጂ የተገበረበት ዓመት መሆኑን አስታውሰዋል። በዚህ ስትራቴጂ ትግበራ "ውጤታማ" ተግባራት የተከናወኑበት መሆኑን የገለጹት ዋና ስራ አስፈጻሚዋ፤ በበጀት ዓመቱ 116 አዳዲስ አገልግሎቶች ይፋ መደረጋቸውን ገልጸዋል። በ2015 በጀት ዓመትም 75.8 ቢሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን ለጋዜጠኞች አስታውቀዋል። ኢትዮ ቴሌኮም ያገኘው ይህ ገቢ በእቅድ ተይዞ የነበረው 75.05 ቢሊዮን ብር 101 በመቶ መሆኑን ፍሬሕይወት ጠቅሰዋል። ኢትዮ ቴሌኮም በ2015 ያገኘው ገቢ ከ2014 በጀት ጋር ሲነጻጸር የ23.5 በመቶ ጭማሪ ያለው መሆኑንም አመልክተዋል። ተቋሙ በ2014 በጀት ዓመት ያገኘው ገቢ 61.3 ቢሊዮን ብር ነበር፡፡ (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11491/ @EthiopiaInsiderNews

Ethiopia Insider Press Release 001 .jpg1.18 KB

“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ቢሮ ውስጥ የተፈፀመውን ዘረፋ በተመለከተ ከሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን የተሰጠ መግለጫ በሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ሥር የሚተዳደረው “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የበይነመረብ ሚዲያ እሁድ፣ ሐምሌ 9፣ 2015 ለሰኞ አጥቢያ በቢሮው ውስጥ ያለ ካዝና ባልታወቁ አካላት ተሰብሮ፣ ንብረቱ ተዘርፏል። የሚዲያ ተቋሙ በሚሠራቸው ዘገባዎች ሳቢያ ተደጋጋሚ ጫናዎች እየደረሰበት ሲሆን፣ ይህ ዘረፋም የነዚህ ተደራራቢ ጫናዎች ተቀጥያ እንደሆነ ሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ያምናል። ትላንት እሁድ የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ባልደረቦች እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት በዜና ክፍሉ ውስጥ በሥራ ላይ ቆይተው፣ ቢሮውን ቆልፈው ከወጡ በኋላ፣ ዛሬ ጠዋት 1፡00 ሰዓት ገደማ ቀድመው የደረሱ ባልደረቦች የቢሮው በር እንደተቆለፈ ነገር ግን ከፍተኛ ዋጋ የሚያወጡ የዜና ክፍሉ ንብረቶች የተቀመጡበት ካዝና በኃይል ተሰብሮ አግኝተውታል። በዘረፋው ካዝናው ውስጥ የነበሩ ሦስት አዳዲስ እና ዘመናዊ ዲጂታል ካሜራዎች፣ ሁለት ዙም ሌንሶች፣ ሌሎች አራት መደበኛ ሌንሶች፣ አራት ላፕቶፖች እና አንድ ስማርት የሞባይል ስልክ ተወስደዋል። ሐቅ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘረፋውን ቦሌ ክፍለ ከተማ ለሚገኘው ለአደይ አበባ ስታዲየም አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ያመለከተ ሲሆን፣ የጣቢያው ፖሊሶች በ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ቢሮ በመገኘት አሻራ አንስተው፣ የተወሰኑ ባልደረቦችን ቃል ተቀብለዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተመሳሳይ ዘረፋዎች በአስቸጋሪው የኢትዮጵያ የሚዲያ ምኅዳር ውስጥ በሁለት እግር ለመቆም እየተፍጨረጨሩ ያሉ ታዳጊ ሚዲያዎች እና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ እየተስተዋሉ ስለሆነ፣ ሐቅ ሚዲያ እና ኮሚኒኬሽን “ጉዳዩ የተቀነባበረ ሳይሆን አይቀርም” የሚል ምክንያታዊ ጥርጣሬ አለው። ለአብነትም፣ ከዚህ በፊት የኢትዮ 251 ሚዲያ ስቱዲዮ እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) የምርምራ ቢሮ በተመሳሳይ ሁኔታ ተሰብረው መዘረፋቸው ተገልጸው ነበር። “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ላለፉት ሦስት ዓመታት ነጻና ገለልተኛ የሆኑ፣ ከፍተኛ ሙያዊ ሥነ ምግባራቸውን የጠበቁ ዘገባዎችን ለተደራሲዎች በማቅረብ ተዓማኒነት እና ተቀባይነትን እያፈራ የመጣ የበይነመረብ ሚዲያ ተቋም ነው። ይህንንም ተቀባይነት መሠረት በማድረግ ተቋማዊ አቅሙን በማስፋት ለተደራሲዎቹ የቪዲዮ ዘገባዎችን ለማቅረብ ቁሳቁስ በማሟላት የቪዲዮ ዘገባዎች የመሥራት ሙከራ ጀምሯል። ሐቅ ሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ይህ ዘረፋ “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ጥራት ያላቸው ዘገባዎች ለማድረስ እና ተደራሽነቱን ለማስፋት የሚያደርገው ጥረት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራል። ይህ ዓይነቱ በሚዲያ እና በሲቪክ ተቋማት ላይ እየደረሰ ያለ ተፅዕኖ እልባት እንዲያገኝ ሁሉም የሚመለከታቸው እና ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋፅዖ እንዲያደርጉ ጥሪ ያቀርባል። ሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን በዚህ ጉዳይ ላይ የፖሊስ ምርመራ ውጤትን ተከታትሎ ይፋ ያደርጋል።

ቪዲዮ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ አትሌቲክስ ቡድን፤ በሀንጋሪ ቡዳፔስት ከተማ ከመጪው ነሐሴ 13 ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ያህል ለሚካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ይፋዊ ዝግጅት ጀምሯል። አንድ ወር ገደማ ለቀረው ለዚህ ሻምፒዮና ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች ወደ ሆቴል እንዲገቡ ጥሪ የቀረበላቸው ከአንድ ሳምንት በፊት ቢሆንም፤ እስከዚህ ሳምንት አጋማሽ ድረስ በሆቴል ተገኝተው ሪፖርት ያደረጉት “ጥቂት አትሌቶች” ብቻ መሆናቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። የብሔራዊ አትሌቲክስ ቡድኑን ዝግጅት በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ተገኝታ የተከታተለችው “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር”፤ የ5 ሺህ እና 10 ሺህ ሜትር አሰልጣኝ የሆኑትን ረዳት ኮሚሽነር ሁሴን ሽቦን አነጋግራለች። ሙሉ ቃለ ምልልሱን ይህን ሊንክ ተጭነው ይመልከቱ፦ https://youtu.be/QS7l0eehwAs @EthiopiaInsiderNews