2 485
Підписники
Немає даних24 години
-157 днів
-5230 днів
Архів дописів
2 485
በቢጫ ለባሾቹ ምክንያት የእነ ጃዋር ችሎት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠበት!
.
ቢጫ ቀለም ልብስ በለበሱ ግለሰቦች ምክንያት የእነ አቶ ጃዋር መሐመድ የዛሬ ችሎት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠበት።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የፀረ ሽብርና ሕገመንግሥታዊ አንደኛ ችሎት ዛሬ ማለዳ የተከሳሾችን የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሊቀበል ቀጠሮ ይዞ ነበር።
ይህን ተከትሎ አቶ ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባን ጨምሮ በዚህ የክስ መዝገብ የተከሰሱ ተከሳሾች ፍርድ ቤትየቀረቡ ቢሆንም ችሎቱ ግን ተለዋጭ ቀጠሮ በመስጠት አሰናብቷቸዋል።
ይሀህ ሊሆን ቻለው የፍርድ ሂደቱን ለመከታተል ቢጫ ልብስ ለብሰው በፍርድ ቤት የተገኙ ሰዎች ወደ ፍርድ ቤቱ እንዳይገቡ በፖሊስ መከልከላቸውን ተከትሎ ተከሳሾች እና ጠበቆች ባሰሙት አቤቱታ ነው።
ከተከሳሾች መካከል አቶ ጃዋር መሐመድ፣ በቀለ ገርባ እና ሐምዛ አዳነ ሰዎች ቢጫ ቀለም ያለው ልብስ በመልበሳቸው ወደ ፍርድ ቤት እንዳይገቡ መደረጉ አግባብ አይደለም፤ ቢጫ ልብስ በመልበሳቸው ብቻ ለእስር የተዳረጉ አሉ ሲሉ ቅሬታቸውን ለፍርድ ቤት አቅርበዋል።
ባለ ቢጫ ቀለም ልብስ የመልበስ ዘመቻ
ከሰሞኑ በማሕበራዊ ሚዲያዎች ላይ በርካቶች ቢጫ ልብስ የመልበስ ዘመቻ ሲያከናውኑ ቆይተዋል። ይህም ተከሳሾች በማረሚያ ቤት እና ፍርድ ቤት ሲቀርቡ የሚለብሱትን ባለ ቢጫ ቀለም ቱታ ለመወከል ነው።
ተከሳሾች ፍርድ ቤት ሲቀርቡ፤ ለተከሳሾች የሞራል ድጋፍ ለመስጠት ቢጫ ቀለም ያላቸውን ልብሶች በመልበስ በፍርድ ቤት እንደሚገኙ የዘመቻው አካል የሆኑት ይናገራሉ።
ባለፉት ሁለት ቀጠሮዎች በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ የክስ መዝገብ ሥራ የተከሰሱ ተከሳሾች ፍርድ ቤት በቀረቡብት ወቅት ቢጫ ቀለም ያለው ልብስ ለብሳ ከፍርድ ቤት የተገኘችው መሠረት ዳባ፤ ይህ ዘመቻችንን ለተከሳሾች የሞራል ብርታትን ለመስጠት ነው ትላለች።
"እነሱ ከሚለብሱት የልብስ ቀለም ጋር ተመሳሳይ ልብስ በመልበስ 'እኛም ከእናንተ ጋር ነን'፣ 'ከእናንተ ጋር ታስረናል' የሚል መልዕክት ማስተላለፍ ፈልገን ነው" ስትል ለቢቢሲ ተናግራለች።
ባለ ቢጫ ቀለም ልብስ የመልበስ ዘመቻ አስተባባሪ የሆነው ወቢ ቡርቃሳ የጀመሩት ዘመቻ በርካቶችን በማሳተፍ ከታሰበው በላይ ብዙ ሰዎች ጋር መድረሱን ይናገራል።
በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ #oromoyellowmovement የሚል መሪ ቃል ሲጠቀሙ ቆይተዋል።
@ethiocheck
2 485
ትግራይ እንዴት ሰነበተች? (የመጨረሻ ክፍል)
- የአዲግራት የሁለት ሰዓታት ቆይታ
- "የኤርትራ ወታደሮችን አየኋቸው"
- የትግራይ ተጓዦች በአዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ ምን ገጠማቸው?
* የልዩ ዘገባውን አራተኛ ክፍል ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/2514/
2 485
ትግራይ እንዴት ሰነበተች? (ክፍል 3)
- የውቅሮ እና ዕዳጋ ሐሙስ ከተሞች የወፍ በረር ቅኝት
በፎቶዎች የተደገፈውን ልዩ ዘገባ ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦
https://ethiopiainsider.com/2021/2461/
2 485
ትግራይ እንዴት ሰነበተች? – በጽሁፍ (ክፍል 2)
በመቐለ ያገኘኋቸው አብዛኞቹ ሰዎች የነገሩኝ እና ወጣቶቹም በሙሉ ሀሳብ የሚስማሙበት አንድ ጉዳይ አለ- “የኤርትራ ወታደሮች የሚፈጽሟቸውን ግድያዎችንም ሆነ ዘረፋዎች የኢትዮጵያ መንግስትም ለማስቆም አልቻለም” የሚል።
ይህ ጉዳይ ለብዙዎች “የእግር እሳት” እንደሆነባቸው በስሜት ተውጠው ከሚያቀርቧቸው ገለጻቸው ተረድቻለሁ። በቀረው የኢትዮጵያ ክፍል ያለው ህዝብም፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ድምጹን አምርሮ ባለማሰማቱ ጥልቅ የመከፋት ስሜት እንዳለ ተመልክቻለሁ።
“ህዝብ ማለት መሬቱ ብቻ አይደለም። ሰውም ጭምር ነው” የምትለው አንድ ወጣት “ኢትዮጵያውያን የሚፈልጉት መሬቱን እንጂ እኛን አይደለም” ስትል እንባ በሚተናነቀው ድምጽ ነግራኛለች።
ሙሉ ዘገባውን በጹሁፍ ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/2398/
2 485
ትግራይ እንዴት ሰነበተች? (ክፍል አንድ)
* የፈዘዘችው እና ያኮረፈችው መቐለ
"በመቐለ ሰማይ ላይ ጄቶች በሚያንዣብቡባቸው እና የከባድ መሳሪያ ድብደባ በተከታታይ በሚሰማባቸው ቀናት፤ የተወሰኑ የከተማይቱ ነዋሪዎች አዲ ሃውሲ ወደተባለው ወደዚህ አካባቢ ለመጠለል መጥተው እንደነበር ሰማሁ። አንድም “በአካባቢው ዓለም አቀፍ ተቋማት የሚበዙ በመሆኑ ለጥቃት አይጋለጠም” በሚል ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ጥቃት ቢፈጸም እንኳ በፎቆቹ ቤቶች ምድር ቤት በመጠለል ራስን ከአደጋ ለመጠበቅ በማሰብ ነው ተባልኩ። ይህንኑ እውነታ፤ በዚያው አካባቢ ወደሚገኘው ቤቱ ለምሳ ግብዣ እየወሰደኝ የነበረው አስተናጋጄም አረጋግጦልኛል።
ወደ አስተናጋጄ ቤት መታጠፊያ ጋር ስንደርስ ወደ ውስጥ የሚያስገባው የውስጥ ለውስጥ መንገድ በውሃ ማስተላለፊያ ትልልቅ ቱቦዎች ተዘግቶ ተመለከትኩ። አስተናጋጄ ቀለል አድርጎ ይህ የሆነበትን ምክንያት ያብራራልኝ ገባ። መንገዶቹ በቱቦዎቹ የተዘጉት በአካባቢው ነዋሪዎች እንደሆነ እና ያም የተደረገው መቐለ በመከላከያ ሰራዊት ቁጥጥር ስር ስትውል፤ “የሻዕቢያ ወታደሮች ለዝርፊያ ተሰማርተዋል” የሚል ወሬ በከተማይቱ በመናፈሱ፤ እርሱን ለመከላከል በሚል ተጀምሮ፤ በዚያው መቀጠሉን አጫወተኝ። ያን ቀን የከተማይቱ ነዋሪ ፤ ዋና ዋና መንገዶችንም ጭምር በድንጋይ ዘግቶ መዋሉን አከለልኝ። "
የልዩ ዘገባውን የመጀመሪያ ክፍል ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/2374/
2 485
#GERD
የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የውጭ ጉዳይ እና የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች የሶስትዮሽ ስብሰባ ላይ ታላቁ የሕዳሴ ግድብን አስመልክቶ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር የሰየሟቸው ባለሙያዎች ያቀረቡት ረቂቅ ሰነድን ኢትዮጵያ እና ሱዳን ሲቀበሉት ግብፅ ሰነዱን ሳትቀበለው ቀርታለች።
*መሉ መግለጫው ከላይ ምስሉ ላይ ተያይዟል!
@ethiocheck
2 485
የሰሜን ሸዋ ዞን ፖሊስ በፍቼ ከተማ 2ዐ ሺህ 800 ሀሰተኛ የብር ኖቶችን ይዞ ለመገበያየት የሞከረን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ።
ትላንት በቁጥጥር ስር የዋለው ተጠርጣሪ በከተማው የቀበሌ ዐ4 ነዋሪ ነው፡፡
በአብዮት ፍሬ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚገኝ የማገዶ እንጨት በሀሰተኛ የብር ኖት ለመገበያየት ሲሞክር በሕብረተሰብ ጥቆማ ቁጥጥር ሥር መዋሉን ተገልጿል።
በፍቼ ከተማ በከብት ድለላ ሥራ ላይ የተሰማራው ተጠርጣሪው ግለሰብ በእጁ ላይ የተገኙትን ሀሰተኛ የብር ኖቶች "ሰንጋ ሳሻሽጥ ከገዢው ላይ የተቀበልኩት ነው" ሲል ተናግሯል።
ድርጊቱ ቀደም ሲል በዞኑ አንዳንድ አካባቢዎች ከተያዙት የብር ኖቶች ጋር ተያያዥነት ሊኖረው ስለሚችል ፖሊስ ሁኔታውን ከባንክ ባለሙያዎች ጋር እያጣራ መሆኑን ተናግረዋል ።
ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ወሎ ጉዳዩን ለህግ ለማቅረብ በምርመራ ላይ መሆኑንም ፖሊስ አስታውቋል። ~ ENA
@ethiocheck
2 485
#MekelleUniversity
የመቐሌ ዩኒቨርስቲ በተለያየ ምክንያት ወደየ ቀያቸው መሄድ ላልቻሉ ተማሪዎች የሽኝት ኣገልግሎት ለመስጠት ባሶችን ማመቻቸቱን ገልጿል።
በመሆኑም ባሶቹ MoSHE ከ ትራንስፖርት ሚንስተር ጋር በመተባበር ኣስር (10) ባሶችን የሚያቀርብ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት መንገድ ላይ እንደሆኑ እና እሁድ ገብተው እንደሚያድሩ ማወቅ ተችሏል።
አገልግሎቱ የሚሰጣቸው ተማሪዎች :-
1. መደረሻቸውን ደቡባዊ ትግራይ የሆኑ፤
2. ከክልል ውጪ ላሉት ተማሪዎችን ደግሞ እስከ አዲስ አበባ ለሆኑ፤
3. የትግራይ ተማሪዎች ሆነው ወደ ሌሎች ዩኒቨርስቲዎች የሚሄዱ ካሉ፤
በዚህ መሰረት ያልተመዛገቡ ተማሪዎች በአቅራቢያቸው በሚገኝ የተማሪ ህብረት ቢሮዎች እንዲመዘገቡ መልዕክት ተላልፏል።
ማሳሰቢያ:-
- ባሶቹ ልክ #ሰኞ ጠዋት 12፡00 ሰዓት ከየ #ጊቢው እንደሚነሱ አውቃችሁ ተማሪዎች አስፈላጊዉን የሆነውን ዝግጅት ሁሉ እንድታደረጉ፤
- እንዲሁም ጊቢው ውስጥ ላሉ ተመራቂ ተማሪዎች ጓደኛ እና ወላጅ የሆናችሁ ይህን ተገንዝባችው ተማሪዎችን እንድታሳውቁ ሲል የመቐሌ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ህብረት ገልጾልናል።
Via Abrhaley Arefaine - ETH/HI/EDU/IN/SU V/president and Mekelle University SU President.
@ethiocheck
2 485
#AlNejashiMosque
ከትላንት ምሽት ጀምሮ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በትግራይ ክልል ባለው ታሪካዊው የአል ነጃሺ መስጊድ ላይ የደረሰውን ጉዳት የሚያሳዩ ፎቶች እየተዘዋወሩ ይገኛሉ።
በመስጊዱ ላይ ጉዳት የደረሰው በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ወቅት ጥቃት ተፈፅሞበት እንደሆነ የተለያዩ ወገኖች ይገልፃሉ።
ይህ ጉዳይ ከተነገረ ሰንበትበት ቢልም በትግራይ ክልል ባለው ሙሉ በሙሉ የግንኙነት መቋረጥ፣ የትራንስፖርት አለመኖር ምክንያት በክልሉ ያሉ መረጃዎችን ከገለልተኛ አካላት ማጣራት የሚችልበት ሁኔታ አልተፈጠረም።
አሁን ላይ የትራንስፖርት መጀመር በአንዳንድ ቦታዎች ላይም የስልክ ግንኙነት ዳግም መጀመር ከዚህ ቀደም በሚዲያ ይፋ ያልወጡ ጉዳዮች በፎቶ ማስረጃ እየወጡ ይገኛሉ፤ የአል ነጃሺ መስጊድ ጉዳይም አንዱ ነው።
በአል ነጃሺ መስጊድ ላይ የደረሰው ጉዳት በፎቶ ከተሰራጨ በኃላ በርካታ የእምነቱ ተከታዮች፣ መምህራን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ድርጊቱን እያወገዙት ይገኛሉ።
በየትኛውም የፖለቲካ ልዩነት እና ግጭት የእምነት ቦታዎችን ኢላማ ማድረግ በየትኛውም መስፈርት ወንጀል እና ፈፅሞ ተቀባይነት የሌለው ድርጊት መሆኑንም ገልፀዋል።
የሚመለከተው አካል በአል ነጃሺ መስጊድ እና በውስጥ ባሉት ቅርሶች ላይ ስለደረሰው ጉዳት ዝርዝርና ግልፅ መረጃ እንዲሰጥም እየወተወቱና እያሳሰቡ ይገኛሉ።
እስከዛሬ ድረስ የትኛውም የመንግስት አካል በጉዳዩ ላይ የሰጠው ማብራሪያ የለም።
@ethiocheck
2 485
መንግስት ከቀናት በፊት እራሱን በእሳት አቃጥሎ የገደለውን አካል ጉዳተኛ ጉዳይ በአንክሮ እንዲከታተል የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ፌደሬሽን አሳሰበ።
ፌዴራሽኑ እንዳስታወቀው ከቀናት በፊት ተማሪ አብርሃም ዱሬሳ የመጀመሪያ ዲግሪውን ከዲላ ዩኒቨርሲቲ በህግ ትምህርት ቤት ያገኘ ሲሆን ህይወቱ እስካለፈችበት ቀን ድረስ ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት የመውጫ ፈተና ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል አንዱ ነበር። የመውጫ ፈተናውን ማክሰኞ፣ ረቡዕ እና ሀሙስ በሰላም ተፈትኖ የመጨረሻው የፈተና ዕለት ማለትም አርብ የመፈተኛ ኮዱን ረስቶ ወደ ስድስት ኪሎ ግቢ መሄዱን ፌደሬሽኑ ገልጿል።
ካለ መፈተኛ ኮዱ መግባት ስለማይችል ወደ ቤቱ ሽሮ ሜዳ ተመልሶ የመፈተኛ ኮዱን ይዞ ሲመጣ የመፈተኛ ሰዓት አልፏል ይባላል።ፈተናው ከጠዋቱ 3፡30 የሚጀመር ሲሆን አብርሃም ግን አስር ደቂቃ ዘግይቶ 3፡40 ይደርሳል። ሱፐርቫይዘሩ መግባት እንደማይችል ሲነግረው ስላረፈደበት ምክንያት ሊያስረዳ ይሞክራል።
ተማሪ አብርሃም ዱሬሳም በተለያየ መንገድ ይማፀናል። አይነ_ስውር መሆኑን ታሳቢ አድርገው እንዲተባበሩት ቢለምንም ፈተናውን እንዲወስድ ግን እንዳልተፈቀደለት ተገልጿል።
ፈተናውን መፈተን ባለመቻሉ ሲያለቅስ ። ሲበሳጭ ይውላል። ምሽት ላይ ወደ ቤቱ በመግባትም ቤቱን ዘግቶ በራሱ ላይ ጋዝ አርከፍክፎ ከፍተኛ ቃጠሎ እንደደረሰበትና በኋላም ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ተወስዶ ህክምና ቢያገኝም ቃጠሎው ከፍተኛ ስለነበር ህይወቱ ማለፉን ፌዴሬሽኑ አስታውቋል።
በመሆኑም በተማሪ አብርሃም ዱሬሳ ላይ የተፈጸመዉ ድርጊት ሰብአዊነት የጎደለዉ መሆኑን በመሆኑ መንግስት ክትትል አድርጎ እርምጃ እንዲወስድ ፌዴሬሽኑ ጠይቋል።በኢትዮጵያ ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የአካል ጉዳተኞች እንደሆኑ መረጃዎች ይጠቁማል።
Via Ethio FM
@ethiocheck
2 485
#AddisAbabaPoliceCommission
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው ደራርቱ ቱሉ መሰናዶ ትምህርት ቤት ጀርባ ዛሬ ከቀኑ በግምት 8:30 ሁለት ህፃናት ወድቆ ያገኙትን ቦንብ ሲነካኩ ፈንድቶ የአምስት ዓመት እድሜ ያለው ህፃን ፀጋዬ ተክለማርያም ህይወቱ ሲያልፍ የአምስት ዓመቱ ህፃን ግዛው አንተንአየሁ በእግሩ ላይ ጉዳት ደርሶበት ህክምና እንደተደረገለት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አሳውቋል።
@ethiocheck
2 485
#FDREDefenseForce
የሀገር መከላከያ ሰራዊት በሌተና ጀነራል አበባው ታደሰ እና በሌ/ጀነራል ባጫ ደበሌ ስም #ሀሰተኛ የፌስቡክ ገጽ ተከፍቶ የተዛባና የተሳሳተ መልዕክት እየተላለፈ እንደሚገኝ ገልጿል።
የመከላከያ ሰራዊት ሁለቱ ከፍተኛ ጀነራል መኮንኖች ምንም አይነት ማህበራዊ ገጽ በስማቸው ያልከፈቱ መሆኑን አሳውቆ ፣ ህብረተሰቡ በሀሰተኛ መረጃዎች እንዳይደናገር አሳስቧል።
@ethiocheck
2 485
ሕወሓት በተደጋጋሚ ወደ ባሕር ዳር፣ ጎንደር እና አስመራ ሲያስወነጭፋቸው የነበሩት ተተኳሽ ሮኬቶች በመቐለ ከተማ በግለሰብ መጋዘን ውስጥ ተከማችተው መገኘታቸውን የልዩ ዘመቻ ኮማንድ አስታወቀ።
የመከላከያ ሠራዊት መቐለ ከተማን ከተቆጣጠረ በኋላ የልዩ ዘመቻ ኮማንድ 2ኛ ብርጌድ አንድ ወጋገን ሻለቃ ባደረገው አሰሳ እና ፍተሻ በመጋዘን ውስጥ ያልተተኮሱ 13 ሮኬቶች የተገኙ ሲሆን፣ 7 ሮኬቶች ደግሞ ከማስቀመጫው ሳጥን ወጥተው ተተኩሰው እንደነበርም አስታውቋል።
በተጨማሪም የተተኳሽ ሮኬት ማስወንጨፊያ ከባድ ተሽከርካሪ ከመቐለ ከተማ ዳርቻ ባለ ስፍራ ተደብቆ ተገኝቷል።
Via EBC
@ethiocheck
2 485
የ4 የምክር ቤት አባላት ያለመከሰስ መብት ተነሳ !
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 5ኛ 5 ዓመት 6ኛ የሥራ ዘመን 6ኛ አስቸኳይ ጉባዔ የ4 የምክር ቤት አባላትን ያለመከሰስ መብት አንስቷል፡፡
በምክር ቤቱ ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው ፡-
1. አቶ አድጎ አምሳያ
2. አቶ ሽፈራው ጨሊቦ
3. አቶ ግርማ መኒ
4. አቶ አረጋ ባልቢድ ናቸው፡፡
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ የቀረቡትን የ4ቱን የምክር ቤት አባላት ያለመከሰስ መብት በሙሉ ድምጽ ማፅደቁን የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ አሳውቋል።
@ethiocheck
2 485
አቶ አብነት በዋስ እንዲፈቱ ተደረገ።
የአቶ ሴኩቱሬ የልጅ ባል አብነት ሃይሉሸዋ በዋስ እንዲፈቱ ተደረገ።
አቶ ኣብነት ሃይሉሸዋ ከህወሓት ቡድን ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል ተጠርጥረው ምርመራ ሲደረግቸው ቆይቷል።
ተጠርጣሪው በምስክርነት ዞረው በዋስ እንዲወጡ የተደረገ ሲሆን ነገር ግን ከሃገር እንዳይወጡ እግድ ተጥሎባቸዋል።
በሌላ በኩል ፦
የ "ማይካድራውን ጭፍጨፋ" #አስተባብራለች የተባለችው ወታደር ታጎስ ገ/ትንሳኤ ጉዳይዋ በሀገር መከላከያ የጦር ፍርድ ቤት እንዲታይ መዝገቡ ወደ መከላከያ የጦር ፍርድ ቤት መዞሩ ተገልጿል። #ኤፍቢሲ
@ethiocheck
2 485
አቶ አትንኩት ሽቱ በቁጥጥር ስር ዋሉ።
የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ አትንኩት ሽቱ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከል ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ምስጋናው እንጅፈታ አረጋግጠዋል።
ም/ኮሚሽነሩ ፥ አቶ አትንኩት የተያዙት በክልሉ በተፈጠረው የሰላም እጦት ችግር እጃቸው እንዳለበት ተጠርጥረው ነው ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ አትንኩት ዛሬ ረፋድ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
@ethiocheck
2 485
አቶ አትንኩት ሽቱ በቁጥጥር ስር ዋሉ።
የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ አትንኩት ሽቱ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከል ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ምስጋናው እንጅፈታ አረጋግጠዋል።
ም/ኮሚሽነሩ ፥ አቶ አትንኩት የተያዙት በክልሉ በተፈጠረው የሰላም እጦት ችግር እጃቸው እንዳለበት ተጠርጥረው ነው ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ አትንኩት ዛሬ ረፋድ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
@ethiocheck
2 485
ምርጫ ቦርድ የመጪውን ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ነገ ይፋ ሊያደርግ ነው
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመጪውን ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ በነገው ዕለት ይፋ ሊያደርግ ነው። ቦርዱ በምርጫ የጊዜ ሰሌዳው ላይ ከ47 የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ለመምከር ለነገ ስብሰባ ጠርቷል።
በአዲስ አበባው ራዲሰን ብሉ ሆቴል በሚካሄደው በነገው የምክክር መድረክ ላይ፤ የድምጽ መስጫ ቀንን ጨምሮ ዝርዝር የምርጫ ክንውኖችን የያዘ የጊዜ ሰሌዳ ለፖለቲካ ፓርቲዎች እንደሚቀርብ የቦርዱ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ ሶልያና ሽመልስ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
ባለፈው ዓመት መጨረሻ ሊካሄድ ቀን ከተቆረጠለት በኋላ በኮሮና ወረርሽኝ ሳቢያ የተራዘመው ስድስተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ፤ በያዝነው ዓመት ግንቦት ወር መጨረሻ አሊያም ሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ እንደሚካሄድ ቦርዱ ቀደም ሲል ጠቁሞ ነበር።
ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/2357/
2 485
እነ ጃዋር መሐመድ ለደህንነታቸው ሲባል የፍርድ ሂደታቸው የሚታይበት ቦታ እንዲቀየር ጥያቄ አቀረቡ
በእስር ላይ የሚገኙት አቶ ጃዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባ፤ ለደህንነታቸው ሲባል የፍርድ ሂደታቸው የሚታይበት ቦታ እንዲቀይር ጥያቄ አቀረቡ። ሁለቱ ተከሳሾች በደህንነት ስጋት ምክንያት ዛሬ አርብ፤ ህዳር 18 በነበረው የችሎት ውሎ ሳይገኙ ቀርተዋል።
በአቶ ጃዋር መሐመድ ስም በሚጠራው የክስ መዝገብ ስር የተካተቱ 24 ተከሳሾች ጉዳያቸው እየታየ የሚገኘው፤ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የሕገ መንግስታዊና ጸረ ሽብር ችሎት ነው። በመዝገቡ በአንደኛነት እና ሁለተኛነት የሰፈሩት አቶ ጃዋር እና አቶ በቀለ፤ ሀገሪቱ አሁን ካለችበት ነባራዊ ሁኔታ እና ቀደም ሲል በእነርሱ ላይ "በመገናኛ ብዙሃን ይቀርብ ነበር" ባሉት ፕሮፖጋንዳ የተነሳ፤ የደህንነት ስጋት እንዳለባቸው በጠበቆች በኩል ለችሎቱ ባቀረቡት ደብዳቤ አመልክተዋል።
ከጠበቆቻቸው አንዱ የሆኑት አቶ ከዲር ቡሎ ለ"ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" እንደተናገሩት፤ ተከሳሾቹ በእነርሱ ላይ አንድ ችግር ቢደርስ ለሀገር ደህንነት ላይ ችግር ሊያስከትል እንደሚችል ጭምር በደብዳቤያቸው ላይ ጠቁመዋል። በዚህም ምክንያት የፍርድ ሂደታቸው በታሰሩበት አቅራቢያ ባለ ቦታ እንዲካሄድ ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጸዋል።
የተከሳሾችን ጉዳይ የሚመለከተው ችሎት በጉዳዩ ላይ ከበላይ አካላት ጋር ተነጋግሮ ውሳኔ ለመስጠት ለታህሳስ 8፤ 2013 ቀጠሮ ሰጥቷል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
2 485
የአነጋጋሪዋ ቃለ መጠይቅ አድራጊ ቤተልሔም ታፈሰ መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው
በኤልቲቪ ቴሊቪዥን ጣቢያ ታቀርባቸው በነበሩ አነጋጋሪ ቃለ መጠየቆቿ የምትታወቀው ቤተልሔም ታፈሰ፤ የስራ እና የግል ህይወቷን የተመለከቱ ማስታወሻዎችን ያሰፈረችበት መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው። “እኔ እና የኤልቲቪ ምስጢሮቼ” የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው መጽሐፍ አሁን በማተሚያ ቤት የሚገኝ ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት መጀመሪያ ለገበያ እንደሚቀርብ ቤተልሔም ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግራለች።
ደራሲዋ ከድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ እስከ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ፤ ከጃዋር መሐመድ እስከ ጌታቸው ረዳ፣ ከዳውድ ኢብሳ እስከ እስክንድር ነጋ፣ ከሌንጮ ለታ እስከ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም፣ ከአንዳርጋቸው ጽጌ እስከ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ያሉ እንግዶቿ ጋር የነበራትን ቆይታ እና የጀርባ ታሪኮች ይተርካል። ከአንዳንዶቹ ጋር የነበራትን ወዳጅነት እና ከእነርሱ ጋር ያሳለፈቻቸውን ጊዜያቶችም ያስቃኛል።
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ ፦ https://
ethiopiainsider.com/2020/2342/
@ethiocheck
