ETHIO TIMES
Відкрити в Telegram
@ethtimes በዚህ ገፅ በየጊዜው የሚወጡ የባንክ እና ኢንሹራንስ ካፖኒዋች እንዲሁም መንግሰታዊ ያልሆኑ /Ngo/ የስራ ማስታወቂያዎችን ያገኙበታል። አዲስ አበባ፡ ኢትዮጵያ
Показати більше3 251
Підписники
Немає даних24 години
-107 днів
-5030 день
Архів дописів
3 251
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥቆማ
#USA
የ2027-2028 የ " ሁበርት ኤች. ሃምፍሬይ " ፕሮግራም ክፍት መደረጉን በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ አሳውቋል።
ምዝገባም ተጀምሯል።
የአሜሪካ መንግሥት ሙሉ ውጪውን የሚሸፍነው ይኸው ፕሮግራም በመካከለኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ባለሙያዎችን (እድሜያቸው ከ32 እስከ 45) የሚመለከት ሲሆን አሜሪካ ውስጥ በተለያዩ ዘርፎች ለአንድ የአካዳሚክ አመት ብቃትን ለማሳደግ እና ለልምድ ልውውጥ እድል የሚሰጥ ነው።
ይህ ፕሮግራም የዲግሪ ፕሮግራም ሳይሆን፣ ባለሙያዎች ብቃታቸውን የሚያሳድጉበትና ከአሜሪካውያን አቻዎቻቸው ጋር ጠንካራ የሥራ ትስስር የሚፈጥሩበት ልዩ መድረክ ነው።
የ2027-2028 መስኮች ምን ምን ናቸው ?
➡️ ኮሙኒኬሽን እና ጋዜጠኝነት (Communications and Journalism)
➡️ ሕግ እና መልካም አስተዳደር (Law and Governance)
➡️ የተፈጥሮ ሀብት ፖሊሲ (Natural Resources Policy)
➡️ የሕዝብ እና ኢኮኖሚ ፖሊሲ (Public and Economic Policy)
➡️ የሕዝብ ጤና ፖሊሲና አስተዳደር (Public Health Policy and Management)
➡️ የቴክኖሎጂ ፖሊሲና አስተዳደር (Technology Policy and Management)
መመዘኛዎቹ ምንድናቸው ?
አመልካቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
1. በመንግሥታዊም ሆነ በግል ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ፣ የአመራር ብቃት ያላቸውና ለሕዝብ አገልግሎት ቁርጠኝነታቸውን ያሳዩ ባለሙያዎች።
2. ዕድሜያቸው ከ32 እስከ 45 ዓመት የሆኑ።
3. የዩኒቨርሲቲ መጀመሪያ ዲግሪ (የ4 ዓመት የባችለር ዲግሪ ወይም ተመጣጣኝ) ያላቸው።
4. አመልካቾች የመጀመሪያ ዲግሪ ከተጠናቀቁ በኋላ በተሰማሩበት የሙያ መስክ ቢያንስ የ5 ዓመት የሙሉ ጊዜ ፕሮፌሽናል የሥራ ልምድ ያላቸው፤ እንዲሁም በሙያ ዘርፋቸው ውስጥ ያሉ የፖሊሲ ጉዳዮች ላይ ፍላጎት ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል።
5. ለፕሮግራሙ ቆይታ ጊዜ ከሚሰሩበት ተቋም የሥራ ፈቃድ ማግኘታቸውን የሚያሳይ የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ መቻል አለባቸው።
6. በሥራ ገበታቸው ላይ የአመራር ወይም የፖሊሲ ኃላፊነት ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል፤ ይህም የዩኒቨርሲቲ መምህራንን እና እንግሊዘኛን እንደ ውጭ ቋንቋ የሚያስተምሩ መምህራንን (የኃላፊነት ቦታ ላይ ያሉትን) ያጠቃልላል።
7. በጽሑፍም ሆነ በንግግር እንግሊዘኛ ቋንቋ አቀላጥፈው መፃፍም መናገርም የሚችሉ እና ከተመረጡ ለTOEFL ፈተና ለመቀመጥ ፈቃደኛ የሆኑ (ተመጣጣኝ ውጤት 72/100/60)።
8. የኢትዮጵያ ዜጋ የሆኑ ወይም በሀገሪቱ የተሰጠ ሕጋዊ ፓስፖርት ያላቸው ቋሚ ነዋሪዎች።
9. ትምህርቱን እንዳጠናቀቁ ያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት ሀገርንና ማኅበረሰብን ለመጥቀም ቢያንስ ለሁለት ዓመታት ወደ ሀገር ተመልሶ ለማገልገል ቁርጠኝነት ያላቸው።
10. በአሜሪካ ሀገር ውስጥ በሚገኝ ድኅረ-ምረቃ ለአንድ የትምህርት ዓመት ወይም ከዚያ በላይ የተማሩ ባለሙያዎች ለዚህ ፕሮግራም ብቁ አይደሉም (ማመልከት አይችሉም)።
11. ባለፉት 3 ዓመታት ውስጥ በአሜሪካ መንግሥት በሚደገፉ ማናቸውም ፕሮግራሞች ላይ የተሳተፉ አመልካቾች ማመልከት አይችሉም።
ለማመልከት የሚያስፈልጉ ሰነዶች ምን ምንድናቸው ?
ምዝገባው ሙሉ በሙሉ በኢንተርኔት (ኦንላይን) ብቻ የሚከናወን ሲሆን የሚከተሉት ሰነዶች ያስፈልጋሉ።
1. CV ፦ የአመልካቹን አጠቃላይ የሥራ ልምድ እና የሙያ ብቃትን በዝርዝር የሚያሳይ ማብራሪያ።
2. የፕሮግራም ዕቅድ ፦ አመልካቾች በዚህ ፕሮግራም ላይ በመሳተፍ ምን ለማሳካት እንደሚያስቡና ወደፊት ምን ለመሥራት እንዳቀዱ የሚያሳይ ዝርዝር መርሐ-ግብር።
3. የተሟሉ የጽሑፍ መልሶች ፦ ለቀረቡ ጥያቄዎች በሙሉ የተሟላ ምላሽ መስጠት፤ በእንግሊዘኛ ቋንቋ የሚዘጋጁት እነዚህ መልሶች (Essay) የቀረቡትን ዋና ዋና ነጥቦች በጥልቀትና በዝርዝር የዳሰሱ መሆን ይኖርባቸዋል።
4. የድጋፍ ደብዳቤ ፦ የሁለት ሰዎች የድጋፍ ደብዳቤ ያስፈልጋል። አንዱ አሁን ከሚሰሩበት ተቋም ኃላፊ/አሰሪ መሆን አለበት።
5. የትምህርት ማስረጃ ፦ ለመጀመሪያ ዲግሪ (Bachelor's) የተወሰዱ ኮርሶችን እና የተገኙ ውጤቶችን የሚያሳይ በእንግሊዘኛ የተዘጋጀ የውጤት መግለጫ መያያዝ አለበት።
👉 የማመልከቻ ጊዜ፦ እስከ ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም (July 19, 2026) ድረስ ነው።
👉 የማመልከቻ ድረ-ገጽ፦ https://apply.iie.org/huberthhumphrey
👉 ለተጨማሪ መረጃ ፦ et.usembassy.gov/announcements/
ስታመለክቱ ግልጽ ያልሆነላችሁ ጥያቄ ካለ በ PASaddisexchanges@state.gov ላይ በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲን ማነጋገር ይቻላል።
ማሳስቢያ ፦ ማመልከት የሚቻለው በኦንላይን ብቻ ሲሆን ማመልከቻ ይዛችሁ ወደ አሜሪካ ኤምባሲ እንዳትሄዱ።
❌ በፕሮግራሙ ወቅት ማንኛውም የቤተሰብ አባል አብሮ መሄድ አይችልም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
3 251
Premier League: Arsenal are champions to end 22-year wait Arsenal fc,the gunners,2023/24 season:አርሰናል እግር ኳስ ክለብ, 2023/24
3 251
Vacancy at Amhara Bank
✅Amhara Bank S.C invites qualified applicants for the various positions
✅ Place of Work: Addis Ababa City Branches, Adama City Branches, Bishoftu, Abrehajira, Addis Zemen, Aderkay, Alem Ketema, Aleta Wondo, Amhara Saint, Anbesami, Arbaya, Arerti, Asketema, Assella, Ataye, Azena, Azezo, Balchi, Bekoji, Bonga, Bulgaria, Chiro, Choke, Gondar , Dansha, Dargie, Densa, Dilla, Dire Dawa, Dukem, Ebinat, Enewari, Gambella, Gedebye, Ginager, Guhala, Harar, Hassena Ager, Hosaena, Janamora, Jijiga, Jimma, Jinka, Kemissie, Lemi, Logia, Majete, Maksegnit, Manbuk, Masero Denb, Maykadira, Mekoy, Meragna, Woldia, Meti, Molalle, Quara, Rema, , Semera, Shahura, Shashemene, Sheno, Shinfa, Simada, Tach Gaint, Tulu Awulia, Wad, Woliso, Yejubie, Yifag, Yirgalem, Yirgachefe https://vacancy.amharabank.com.et/
3 251
Abay bank:https://www.ethiopianreporterjobs.com/companies/abay-bank-sc/ Goh bank:https://www.ethiopianreporterjobs.com/companies/goh-betoch-bank-sc/ Tsehay bank:https://www.ethiopianreporterjobs.com/companies/tsehay-bank-sc/ Nib bank:https://www.ethiopianreporterjobs.com/companies/nib-international-bank/
3 251
Vacancy at FlyDubai
Relocation to Dubai
መሉ ወጪያቹህና Visa በAilinesዉ ነዉ የሚሸፈነዉ
Position: Cabin Crew (UAE Assessment Centre)
Pay & Benefits
Basic salary + Housing allowance + Transportation allowance: AED 8,275
Plus Variable Flying pay: Avg. Monthly AED 4,500 (Based on average of 90 flying hours)
Qualification
👉Your minimum qualification is high school graduate (Grade 12)
👉You need to be fluent in written and spoken English
👉Must be at least 21 years old.
Deadline April 24/2026
https://careers.flydubai.com/jobs/1788?lang=en-us
3 251
530- ቦታዎች (For Fresh Graduate)
Vacancy at Immigration And Citizenship Service (ICS Ethiopia)
❇️ Number of Positions:: 530+ position / For Fresh Graduate and EXp
✅ Qualification: any field of study
📌ሰለ ሰራው ሙሉ መረጃ ለማየት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ👇👇
👉Read Detail :- https://ethioworks.com/immigration-and-citizenship-service-ics-ethiopia-vacancy/.
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
