cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

ኦርቶዶክስዬ

የማርያም ልጅ ሆኜ ተፈጥሬ እንዴት አንገቴን እደፋለሁ ወዳጆች ዝም አንበል ሁላችንም ስለ ማርያም እንስበክ ምድረ ጸረ ማርያምን ሁሉ እናሳፍራቸው ።

Більше
Рекламні дописи
212
Підписники
Немає даних24 години
+47 днів
+1630 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

#ተአብዮ_ነብሴ ተአብዮ ነብሴ ለእግዚአብሔር (3) ሰአሊለነ ማርያም (2) ሀበወልድክሂር መዳሕኔዓለም የአብ ሙሽራ ነሽ የወልድም እናቱ ለመንፈስ ቅዱስ ነሽ ፅራሃዊቱ በፊትሽ ሰገዱ ቅዱሳን መላእክት     ለምኝልን ማርያም (2) ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም ከዋክብት ብርሃናት ሳይታይ ደመና ታስበሽ ኖረሻል በአምላክ ህሊና ገብርኤል ነገረሽ የክብርሽን ዜና ለምኝልን ማርያም (2) ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም የወርቅ ታቦት ነሽ በሰማይ ያለሽ የፅድቅ ንግስት ነሽ የተመሰገንሽ በእናትነትሽ ተመካ ልብሽ ለምኝልን ማርያም (2) ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም የአለሙን ጌታ በእቅፍሽ አየነው በመሀፀንሽ አድሮ ቃል ስጋ የሆነው እግዚአብሔር ስላንቺ ምስጋናው ብዙ ነው ለምኝልን ማርያም (2) ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም የዳዊት ልጅ ማርያም ትምክህታችን የአማኑኤል እናት መሰብሰቢያችን የእግዚአብሔር ከተማ መማፀኛችን ለምኝልን ማርያም (2) ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም ድንግል በክሊሄም በነፍስም በስጋ ጎዶሎ ይምላል አንቺን የተጠጋ ክርስቶስ ወልደሽ ክሳችን ተዘጋ ለምኝልን ማርያም (2) ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም በፊትሽ ልማፀን ቆምኩኝ ከደጅሽ ልመናዬ ሁሉ ይግባ ከጆሮሽ ለሚጠራሽማ ማርያም ቅርብ ነሽ ለምኝልን ማርያም (2) ከቸሩ ልጅሽ ከመድሐኒአለም ሰአሊለነ ማርያም (2) ሀበወልድክሂር መዳሕኒአለም     ዘማሪ ገ/ዮሐነስ ገ/ጻድቅ https://t.me/orthodx21 https://t.me/orthodx21 https://t.me/orthodx21
Показати все...
ኦርቶዶክስዬ

የማርያም ልጅ ሆኜ ተፈጥሬ እንዴት አንገቴን እደፋለሁ ወዳጆች ዝም አንበል ሁላችንም ስለ ማርያም እንስበክ ምድረ ጸረ ማርያምን ሁሉ እናሳፍራቸው ።

👍 1
Показати все...
የራማው_ልዑል_ገብርኤል_ተመላለስ_መሃላችን_ስምህን_ጠርተን_ና_ስንል_Yeramaw_Leul_ዝማሬ_መላእክትM4A.m4a5.06 MB
ገብርኤል_መልአክ_ዜናዌ_ሐዲስ_Gebriel_Melak_Zenawe_HadisM4A_128K.m4a6.27 MB
✟ ገብርኤል ሀያል ✟ ገብርኤል ኃያል መልአከ ሰላም መላከ ብስራት የምታወጣ የእግዚአብሔርን ህዝብ ከሚነድ እሳት ፍቅርህ ተስሏል በልባችን ፊትህ ቆመናል ባርከን ብለን የጽናታቸው ዝናው ሲሰማ ከዚያች ቢያብሎን ከሞት ከተማ ህፃናት ሳሉ በራ እምነታቸው ቁመህ ተገኘህ መሃከላቸው አዝ= = = = = ውሃው ሲዘልል ቢያስደነግጥም በጋኖቹም ውስጥ ቢነዋወጥም ጸንተው ዘመሩ ልጅና እናቱ አንተ ስትደርስ ከዚያ ከእሳቱ አዝ= = = = = ቂርቆስም ጸና ሞትን ሳይፈራ አንተ ስላለህ ከነርሱ ጋራ አትፍሪ አላት ስለምን ትፍራ አምነው ድል ነሱት ያንን መከራ አዝ= = = = = እኔም አምናለው አድነኝ ብዬ ቆመህ አማልደኝ ከቸር ጌታዬ ክፉውን ዘመን የማልፍበት ፅናትን ስጠኝ ድል ልንሳበት መዝሙር https://t.me/menfesewizmare
Показати все...
ገብርኤል ኃያል.mp34.21 MB
_ገብርኤል_ስለው_ሰምቶ_ሊቀ_መዘምራን_ቴዎድሮስ_ዮሴፍM4A_128K.m4a4.36 MB
የቅዱስ_ገብርኤል_መዝሙር_ቴዎድሮስ_ዮሴፍ_Kidus_Gebriel_MezmurM4A_128K.m4a4.80 MB
ገብርኤል መልአከ ራማ.mp35.16 MB
🎧የስሙ ትርጓሜዘማሪ ቴዎድሮስ ዮሴፍ 🏮የድሮ መዝሙርች🏮 ●●●●●●●●●●●●●●●● ●ቻናላችን፦ኪነ-ጥበብ
Показати все...
03. 3 የስሙ ትርጓሜ (Natty).mp36.51 MB
Показати все...
ስለቴን ሰማ .mp34.46 MB
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ይህ የአሣ ቅርጽ ጥንት ላይ አባቶቻችን እንደ አርማ ይጠቀሙበት ነበር.. ቅዱስ ቁርባንን የሚያሳይ እንደሆነም ይነገርለታል.. በዋናነት ግን አሣ በግሪክ ἰχθύς (ኢክቱስ) ይባላል.. ከላይ የአሣ ቅርጽ ውስጥ ያሉት ፊደላት በ capital letters ተጽፈው ነው ἰχθύς የሚለው። እና ἰχθύς የሚለውን ደግሞ ፊደላቱን እንዲህ ይተነትኗቸዋል፡ Ἰ - Ἰησοῦς - ኢየሱስ Χ - Χρῑστός - ክርስቶስ Θ - Θεοῦ - የእግዚአብሔር Y - Yἱός - ልጅ Σ - Σωτήρ - አዳኝ
Показати все...
፩. #ንስሐ_ማለት_ምን_ማለት_ነው??      ✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥ ☞ ንስሐ ማለት፦ "ነሰሐ" ከሚል የግዕዝ ግስ የወጣ ቃል ነው፡፡የቃሉ ፍች ሐዘን፣ፀፀት፣ቁጭት፣ምላሽ፣መቀጮ፣ቅጣት ፣ቀኖና፣የኃጢአት ካሣ ማለት ነው፡፡ንስሐ ማለት ደግሞ አንድ ሰው በሠራው ጥፋት፣ባደረገው ስህተት፣በፈጸመው ኃጢአት ማዘኑና መቆርቆሩን፣መፀፀቱን ዳግመኛም ያንን የመሰለ ኃጢአት ላለማድረግ የሚወሰነው ውሣኔ ነው፡፡ በአጠቃላይ ንስሐ ከፍ ብሎ የተገለጠውን ትርጉም ሲኖረው በሰዎች ሕይወት ውስጥ ደግሞ የሚከተሉትን ፍቺዎችን ይዞ እናገኘዋለን፡፡ ❖ ንስሐ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ነው፡፡ ❖ ንስሐ ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ ነው፡፡ ❖ ንስሐ ከኃጢአት እንቅልፍ መንቃት ነው፡፡ ❖ ንሰሐ ወደ መንፈሳዊ ሕይወት መመለስ ነው፡፡ ❖ ንስሐ ከእግዚአብሔር የሚሰጥ እግዚአብሔርን የሚያስወድድ ከንጹሕ ልብ የሚመነጭ ጸጋ ነው፡፡ ❖ ንስሐ ከኃጢአትና ከዲያብሎስ ባርነት ነፃ መውጣት ነው፡፡ ❖  ንስሐ ስለእግዚአብሔር ፍቅርና ስለ ቅድስና ብሎ ኃጢአትን መተው ነው፡፡ ❖ ንስሐ  ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር የሚያስገባ ቁልፍ ነው፡፡ ❖ ንስሐ የመንግሥተ ሰማያት መግቢያ በር ነው፡፡ ፪. የንስሐ ቅድመ ዝግጅቶች ምንላቸው ምን ምን ናቸው?? ☞በአጥቢያችን ከሚገኝ ቤ/ክ  ክህነት ያላቸው በአገልግሎት ላይ ያሉ መልካም መንፈሳዊ ምግባር ያለቸውን አባቶች መርጠን አበ ነፍስ(የንስሐ አባት) መያዝ ☞ የሰራነውን ኃጢአት ማመን ☞ በሰራነው ኃጢአት ከልብ አብዝተን መቆሮቆሮ መፀፀት ማዘንና ማልቀስ ☞ እግዚአብሔር ይቅር እንዲለን በፍጹም ትህትና ራስን በማዋረድ መጠየቅ ☞ በንስሐ ውስጥ መኖር የሚያሰጣቸውን የህሊና እረፍትና በረከት መገንዘብ ☞ ከእኛ ኃጢአት ይልቅ የእግዚአብሔር ቸርነትና ይቅር ባይነት እንደሚበልጥ እና ይቅር እንደሚለን ያለጥርጥር ፍጹም ማመን ☞ ወደ አበ ነፍሳችን ሄደን ንስሐ ለመግባት እና ቀኖናችን ለመቀበል ማሰብ እና መወሰን ☞ ከልጅነት እስከ ዕውቀት የሰራናቸውን ኃጢአቶች ማስታወስ ከተቻለም ለማስታወስ ይረዳን ዘንድ በጽሑፍ መያዝ ☞ ዳግም ወደ ሰራነው ኃጢአት እንደማንመለስ ለራሳችን ቃል መግባትና መወሰን፣ኃጢአትን መጸየፍ ☞ ወደ አበ ነፍሳችን ሄደን የሰራነውን ኃጢአት በሙሉ አንድም ሳያስቀሩ በዝርዝር መናዘዝ ☞ የሚሰጠንን ቀኖና ወይም ቅጣት በትክክል መተግበር ☞ ዳግም ወደ ኃጢአት እንዳንመለስ ራሳችንን በቃለ እግዚአብሔር ማነጽ ፫. ኃጢአት ለንስሐ አባት መናዘዝ ለምን አስፈለገ? ☞ ስልጣነ ክህነት የማሰር የመፍታት ስልጣን ከእግዚአብሔር ስለተሰጣቸው፡፡ ማቴ.፲፰፥፲፰ " እውነት እላችኀለው በምድር የምታስሩት ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፡በምድርም የምትፈቱት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል" ☞ ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያዘዘው ትዕዛዝ ስለሆነ፡፡ሉቃ.፭፥፲፬ "ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ፡ ለእነርሱም ምስክር እንዲሆን ስለመንጻትህ ሙሴ እንዳዘዘ መሥዋዕት አቅርብ አለው" ☞ ኑዛዜ ማድረግ በመጽሐፍ ስለታዘዘ፡፡ዘሌ.፭፥፭-፮፣፲ "ከእነዚህ ነገሮች በአንዲቱ በደለኛ ቢሆን የሠራው ኃጢአት ይናዘዛል፡ስለሠራው ኃጢአት ለእግዚአብሔር የበደልን መስዋዕት ያመጣል.....ካህኑ ስለኃጢአቱ ያስተሰርይለታል....እርሱም ይቅር ይባላል"፡፡ ☞ ከእኛ ይልቅ ለእግዚአብሔር ቅርብ ስለሆኑ እለት እለት እግዚአብሔርን በቅዳሴው ስለሚያመሰግኑ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በየቀኑ እየፈተቱ ስለ እኛ ኃጢአት ይቅር እንዲለን ስለሚለምኑ። "የመዳን ቀን ዛሬ ነው" ፪ቆሮ ፮÷፪ #ንሰሐ_ገብተን_ቅዱስ_ሥጋውን_ክቡር_ደሙን_ለመቀበል_ያብቃን❗🙏 #ወስብሐት_ለእግዚአብሔር #ወለወላዲቱ_ድንግል #ወለመስቀሉ_ክቡር
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.