cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Tikvah-University

Більше
Рекламні дописи
3 075
Підписники
Немає даних24 години
+147 днів
+730 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Фото недоступнеДивитись в Telegram
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማስተማሪያ እና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሚመረቅበት ጊዜ ተራዝሟል፡፡ ሆስፒታሉ ነገ ሰኔ 1/2016 ዓ.ም እንደሚመረቅ ዩኒቨርሲቲው ገልፆ የነበረ ቢሆንም፤ "በሌሎች ክልላዊ የሥራ ጉዳዮች ምክንያት" የምረቃው ጊዜ የተራዘመ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንዲታደመ ለተጋበዙ አካላት ይቅርታ የጠየቀው ዩኒቨርሲቲው፤ በቀጣይ የሆስፒታሉ ምረቃ የሚከናወንበትን ጊዜ እንደሚያሳውቅ ገልጿል፡፡ @tikvahuniversity
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
አነስተኛ ቢዝነሶችን ለማሳድግ ቆርጦ የተነሳው አዲሱ የGig-Innovate ፕሮግራም መመዝገቢያ ጊዜ ሊጠናቀቅ 3 ቀን ብቻ ቀረው! ማመልከቻውን አጠናቀው ዛሬውኑ ያስገቡ! የምታገኙት ድጋፍ፦ - የቢዝነስዎን ሂደቶች የሚያቃልል ቴክኖሎጂ - ኳሊፋይድ ፈይናንሲንግ - የፋይናንስ፣ የህግ አና የቢዝነስ አማካሪዎች መመዝገቢያ ሊንክ 👇 http://mesirat.acceleratorapp.co/application/new?program=mesirat-entrepreneurs-application-form-project-X #MesiratEthiopia #SmallBusiness #Grow #BusinessDevelopment
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
#BahirDarUniversity ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ለ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎቹ ጥሪ ሊያደርግ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በፀጥታ ችግርና ሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች በ2016 ዓ.ም አዲስ ለተመደቡ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ጥሪ ሳያደርግ ቆይቷል። ረቡዕ ግንቦት 28/2016 ዓ.ም ውይይት ያደረገው የዩኒቨርሲቲው ሴኔት፣ በሰኔ ወር መጨረሻ ለተማሪዎቹ ጥሪ እንዲደረግ መወሰኑን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ከተቋሙ ለማረጋገጥ ችሏል፡፡ በዚህም ከሐምሌ ወር አጋማሽ ጀምሮ ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን በዩኒቨርሲቲው በመገኘት መከታተል ይጀምራሉ ተብሏል፡፡ ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ፣ ትምህርት ሚኒስቴር በልዩ ሁኔታ ፈተና እንደሚያዘጋጅላቸውም ታውቋል። @tikvahuniversity
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
#Update የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ከሰኔ 3-10/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ ሰኔ 9/2016 ዓ.ም የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ስለሆነ፣ በዕለቱ ይሰጥ የነበረው ፈተና ሰኔ 11/2016 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡ @tikvahuniversity
Показати все...
የ2016 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የጊዜ ሰሌዳ በአዲስ አበባ የስምንተኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 4 እና 5/2016 ዓ.ም እንዲሁም የስድስተኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 12 እስከ 14/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። በከተማዋ የስምንተኛ ክፍል ፈተናን 86,671 ተማሪዎች እንዲሁም የስድስተኛ ክፍል ፈተናን 86,217 ተማሪዎች እንደሚወስዱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ መግለፁ ይታወሳል፡፡ (የፈተናዎቹን የጊዜ ሰሌዳ ከላይ ይመልከቱ፡፡) @tikvahuniversity
Показати все...
1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ዛሬ ያበቃል! በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) የተዘጋጀ "ብሔራዊ የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ" ፕሮግራም (National Cyber Talent Challenge Program) የምዝገባ ጊዜ ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡ በሳይበር ደህንነትና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ እና ፍላጎት ያላችሁ ኢትዮጵያውያን በቻሌንጁ ላይ መሳተፍ የምትችሉ ሲሆን፤ Cyber Security, Cyber Development, Embedded Systems, and Aerospace የታለንት መስኮች ናቸው፡፡ ምዝገባው ዛሬ ግንቦት 30/2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡ ለመመዝገብ፦ https://talent.insa.gov.et @tikvahuniversity
Показати все...
1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
#Update በሰኔ 2016 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተናን በድጋሚ (Re-exam) ለመውሰድ ያመለከታችሁ በምዝገባ ወቅት የተላከላችሁን የቴሌ ብር የክፍያ ማረጋገጫ (Tele Birr Payment Transaction Code) በመጠቀም የመፈተኛ የይለፍ ቃል (Password) https://exam.ethernet.edu.et በኩል ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የመውጫ ፈተና የምትፈተኑ ዕጩ ተመራቂዎች የይለፍ ቃል (Password) የምታገኙት ከምትማሩበት ተቋም ብቻ መሆኑ ተገልጿል፡፡ Note: ማንኛውም የድጋሚ (Re-exam) ተፈታኝ በምዝገባ ወቅት ያልተሟሉ መረጃዎችን በሲስተሙ በኩል ማሟላት ይጠበቅበታል። ሁሉም ተፈታኞች ወደፊት በሚገለፀው ፕሮግራም መሰረት የሞዴል ፈተናን መውሰድ ይኖርባቸዋል ተብሏል። @tikvahuniversity
Показати все...
👍 1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
በራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ከፍለው ለመማር የማይችሉ ተማሪዎች የባንክ ብድር እንዲያገኙ የሚረዳ ሕጋዊ አሠራር እንዲመቻች ተጠየቀ፡፡ በ2015 ዓ.ም. ፀድቆ ወደ ሥራ የገባውና ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ የሚያደርገው አዋጅ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ከስምንት ወራት በፊት ወደ ሥራ ማስገባቱ ይታወቃል፡፡ በመጪዎቹ ሁለት ዓመታት ተጨማሪ ዘጠኝ ዩኒቨርሲቲዎችን ወደ ራስ ገዝነት ለማሸጋገር ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡ ዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ ሲሆኑ ምንም እንኳ ተጠያቂነቱ ኖሮ በተወሰነ ደረጃ መንግሥት በገንዘብ የሚደግፋቸውም ቢሆኑም፣ ራሳቸውን በራሳቸው ያለ ማንም ጣልቃ ገብነት የፋይናንስ፣ የአስተዳደር፣ የአካዴሚክ፣ የሰው ሃብት እና መሰል ነፃነት አዋጁ ያጎናፅፏቸዋል፡፡ ይሁን እንጂ ራስ ገዝ ሆኖ ሥራ በጀመረው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያዎቹ ጥቂት ወራት ከፍለው ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች ክፍያው በከፍተኛ መጠን እንደጨመረባቸው እየተናገሩ ነው፡፡ ወደፊት ራስ ገዝ የሚሆኑ ዘጠኝ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ ሥራ ሲገቡ አሁን ያለው ሁኔታ ጥሩ ውጤት ያላቸው ተማሪዎች ከፍለው እንዳይማሩ ይገድባል የሚል ሥጋት እየተሰማ ነው፡፡ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጀማል የሱፍ (ዶ/ር) በጉዳዩ ላይ ለሪፖርተር በሰጡት አስተያየት፣ ዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ ሲሆኑ ለተማሪዎች የሚሰጥ ብድር መመቻቸት ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ለሚ ጉታ (ዶ/ር) በተመሳሳይ፤ መንግሥት በውጭው ዓለም የተለመደውን ለተማሪዎች ብድር የሚቀርብበት አሠራር ሊያስብበት ይገባል ብለዋል፡፡ ሙሉውን ያንብቡ 👇 https://www.ethiopianreporter.com/130161/ @tikvahuniversity
Показати все...
👍 2
Фото недоступнеДивитись в Telegram
የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ እንደሚሰጥ ይጠበቃል። የሪሚዲያል ተማሪዎች የፈተና ጊዜን የተመለከቱ በርካታ ጥያቄዎች ለቲክቫህ ደርሰዋል፡፡ ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የተመለከተው ጊዚያዊ የሪሚዲያል ተማሪዎች የፈተና መርግብር፤ ፈተናው ከሰኔ 3-10/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ያሳያል። በዚህም የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ከሰኔ 3 እስከ 6/2016 ዓ.ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከሰኔ 6-10/2016 ዓ.ም ፈተናቸውን እንደሚወስዱ ይጠበቃል። የፕሮግራም ለውጥ የሚኖር ከሆነ የምናሳውቃችሁ ይሆናል። ፈተናው በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ብቻ የሚሰጥ ሲሆን፤ ተቋማቱ ስለፈተናው ገለፃ ለተፈታኞች መስጠት መጀመራቸውን ተመልክተናል። ዘንድሮ 78 ሺህ የሪሚዲያል ተማሪዎች #ከባህርዳር_ዩኒቨርሲቲ ውጪ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን ከታህሳስ ወር ጀምሮ ሲከታተሉ ቆይተዋል፡፡ @tikvahuniversity
Показати все...
👍 1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
በአዲስ አበባ የስምንተኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 4 እና 5/2016 ዓ.ም ይሰጣል። በተመሳሳይ የስድስተኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 12 እስከ 14/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገልጿል። ፈተናዎቹን ለመስጠት በቂ ዝግጅት መደረጉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ገልጿል። በአዲስ አበባ የስምንተኛ ክፍል ፈተናውን 86,671 ተማሪዎች እንዲሁም የስድስተኛ ክፍል ፈተናውን 86,217 ተማሪዎች እንደሚወስዱ በቢሮው የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክተር ዲናኦል ጫላ ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡ ከተፈቀዱ የፈተና ቁሳቁሶች ውጪ፣ ዲጂታል ሰዓትን ጨምሮ ማንኛውንም ኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎችን ይዞ ወደ ፈተና መግባት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ @tikvahuniversity
Показати все...
👍 1 1