cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

ስውር ቁልፎች

ኢትዮጵያን መስራት የሚችሉት ኢትዮጵያውን ብቻ ናቸው። ኢትዮጵያውያን ያልሰሯት ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ አትሆንም። ኢትዮጵያን ሰርተን እናኖራታለን፤ አሊያም ረስተን እናፈርሳታለን! @Siwur_Kulfoch

Більше
Рекламні дописи
1 171
Підписники
+324 години
+97 днів
+1430 днів
Час активного постингу

Триває завантаження даних...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Аналітика публікацій
ДописиПерегляди
Поширення
Динаміка переглядів
01
Media files
2292Loading...
02
Media files
2891Loading...
03
እጅግ የተወደድህ ወንድሜ ክብሩ ካሱ እና እህቴ ኤልሳቤት አሰፋ እንኳን ለከበረው ተቋም አምላክ አደረሳችሁ! እንኳን ደስ አላችሁ! 10 ዓመት በሙሉ ወንድሜ፣ ጓደኛዬ፣ በብዙ አጋዤ፣ የልብ ወዳጄ. . . ነህ፤ ክብርሽ። ትህትናህና ለእኔ የከፈልካቸው የቅንነት ዋጋዎችህ በእኔ ዘንድ ዋጋ አላቸው። ለሰው መልካም በመሆንህ አውቅሀለሁ። ብዙ የጓዳ ሀሳቦችን ተከፋፍለናል፤  ተመካክረናል። አንተ በእኔ ሕይወት ውስጥ በመኖርህ በብዙ አትርፌአለሁ። ሁሉን በዚህ መልኩ መመስከር አልፈልግምና ስለሁሉ በምስጋና ላብቃ። ኤልሲ በክብሩ ውስጥ አንቺን በብዙ አውቄሻለሁ። ታማኝና እውነተኛ እጮኛው መሆንሽን በድፍረት እመሰክራለሁ። ክበሪ እህቴ። ትዳራችሁን እግዚአብሔር ይባርክ! በኑሯችሁ እግዚአብሔር ይኑር! በእውነተኛ ተምሳሌታዊ ሕይወት ጌታ ዘመናችሁን ሁሉ ያለምልም! በፍቅር፣ በትዕግስት፣ በአብሮ ሰራተኝነት፣ ... ጌታ ቤታችሁን ይምራ!! መልካም ጋብቻ!! ወንድማችሁ ምንተስኖት መኩሪያ
4343Loading...
04
Media files
11Loading...
05
ባሳለፍነው ሳምንት  በታቦር ትምህርት ማዕከል(ኢቫን) ተገኝተን ከተማሪዎችና ከትምህርቱ ማሕበረሰብ ብር 6,075 መሰብሰባችን ይታወቃል። ዛሬ በተጨማሪ የሥነ መለኮት ተማሪዎች ብር 2,635 ሰብስበው ለዳጊ ህክምና አውለዋል። በጸሎትም ከጎናችን እንደሆኑ ገልፀውልናል።  ለዳግማዊ አሰፋ ስላሳዩት ፍቅር እናመሰግናለን።
4542Loading...
06
መንፈሳዊ ውጊያ የተሰኘው የወንድማችን ኢያሱ መጽሐፍ ሊመረቅ እነሆ ቀናት ብቻ ቀሩት። የፊታችን እሁድ ሰኔ 02/2016 ዓ.ም በሀዋሳ አላሙራ ሕይወት ብርሃን ቤተ-ክርስቲያን ከቀኑ በ08:00 ይመረቃል! ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።
5411Loading...
07
የሀዋሳ ከተማን ጨምሮ በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ አከባቢዎች እየተበራከተ ብቻም ሳይሆን እጅግ በሚያስፈራ ሁኔታ ዕድሜአቸው 14  ዓመት ከሆናቸው ታዳጊ ልጆች ጀምሮ በልደት ፕሮግራም የተጀመረ የአልኮል መጠጥ እና የጎጂ ሱሶች ልምምድ አስደንጋጭ ደረጃ ላይ ደርሷል። ምንም ገና ግራና ቀኛቸውን ለይተው ያላወቁ ታዳጊዎች እንደ መዝናኛ፣ እንደ ስልጣኔ፣ እንደ ማወቅ . . . ቆጥረው በዚህ ገዳይ ጎዳና እየነገዱ ለውድቀት መዳረጋቸው እንደ አንድ ሰው በብዙ የሚያሳዝነኝ ነው። ችግሩን እያወቅን እና እየታወቀ የሚሰጠው ትኩረት አናሳ መሆን፣ አባባሽ ምክንያቶችን በሕግ አለመከላከልና ምን አገባኝ? ባይነት ትውልድን እያመከነ ነውና ቸል አንበል! ምንተስኖት መኩሪያ
4230Loading...
08
እህቴ አትክልት አማረ እንኳን እግዚአብሔር ረዳሽ! እንኳን ደስ አላችሁ!! ቤታችሁን እግዚአብሔር ይስራ፤ ይባርክም። በኑሮአችሁ ሁሉ ክርስቶስ ይክበር። ትዳራችሁን በፍቅር ያጽና። መልካሙን ሁሉ እመኝላችኋለሁ! መልካም ጋብቻ! ምንተስኖት መኩሪያ
5551Loading...
09
Media files
5312Loading...
10
ታላቁ መጽሐፍ እንደነገረን በአንድ ወቅት ኑኃምን የሚትባል ሴት  ከምትኖርበት ቀዬ ከባሉዋና ከሁለት ልጆቿ ጋር በረሃብ ምክንያት ዳቦ ፈለጋ ሞአብ ወደሚባል ሀገር ትሰደዳለች።  ረሃብ ክፉ ነው በምንም የማያስታግሱት መፍትሔ ነው ያሉበትን ጉዳይ ደግሞ እንኳ ለማሰብ ዕድል የማይሰጥ ፣ ዝም ብሎ እጅ አጣምሮ ሚያረገውን ልይ ካሉ ደሞ ሞት የሚባል ጨካኝ ሰይፉን የሚመዝ  አስፈሪ ና አንገብጋቢ ነው። ኑኃምን ና በተሰቦቿ ከረሃብ ሊያመልጡ ወደ ሞዓብ መሄድን ደግሞ ያለሰቡት ለዚህም ይመስለኛል። ኑኃምን ዕድል ቀንቷት እንድንል በዚያ ሄዳ ከረሃብ አምልጣ አልፎም ልጆቿን ዳረች በጥቅቱም ቢሆን ሁሉም መልካም፣  ኑሮ የሰመረላት ይመስላል ፤ ነገር ግን በዚህ አልቀጠለም የሞዓብ ሀገር  ዳቦ ሰጥቷት ረሃቧን ያስታገሳት ቢመስልም  ቤተሰቧን ፣ደስታዋን ፣ሙላቷን፣...  ነጥቋታል።  አገኘን ያልነው ነገር ምንስ ነጥቆን ይሁን?..    ይህ ሆነና ይህች ሴት  የገጠማት ፈተና  በዳቦ ተጽናንታ በሞዓብ ምድር መሰንበት የሚያስችላት አልነበረም ፤  ከዚያ ሀገር መውጣት  አማራጭ  የሌለው ነው ምክንያቱም ባዶዋን ያስቀራት ሥፍራ ነውና። ዛሬም ዳቦ አግኝተንበት  ህልማችን፣ ተስፋችን ፣ ደስታችን ፣መላታችንን ፣.. የተሰረቅንበት  ቦታ ሆነን የሆነው አንደ ሆኑዋልና ከዚህ ኋላ ወዴት?! ብለን ሙታችንን ታቅፈን የተቀመጥን በተስፋ መቁረጥ የደነዘዝን  ስንቶች ነን??  ሩት ከሞዓብ ምድር መውጣቷ  ወደ ቀዬዋ መመለስ ትክክለኛ ውሳኔ ነው። በእርግጥ ሩት በዚህ ሁሉ  የሳተችው ዋና ነገር  #ምሪት ነው የእግዚአብሔርን ፈቃድ መጠየቅ። ከቤተልሔም መውጣት አማራጭ የለለው ጉዳይ ይሆናል ግን መውጣት ስለተቻለ ዕድል ስለተመቻቸ  አይወጣም!  ምን ላድርግ ፣ እንዴት  ልሁን ነው የሚባለው፤   ግን እኛ በፍጹም ልባችን በእግዚአብሔር መዳገፍ ሲያቅተን የመሰለንን ሁሉ እግሬ አውጭኝ ይሉት በመሰለን ራሳችንን የሚናድን ይመስል እንታትራለን።  ህይወት በግምት ና በስለት ከሆነ የእግዚአብሔርን ከለላ ማራቅና ባለቤትነቱን መካድም ነው።   ይሳሐቅን እግዚአብሔር ወደ ግብፅ አትውርድ እኔ በምልህ ምድር ተቀመጥ ስለው እሺ በማለቱ  የአምላኩን አብሮነትና በረከቱን መቀበል ችሏል።  የእግዚአብሔርን ምርት መጠየቅ ብቻ ሳይሆን መታዘዝም ነው ለሕይወት የሚሆነን። የእስራኤል ንጉሥ የነበረ አክአብ ወደ ሬማት ዘገለዓድ ሰልፍ ልወጣ ምሪት መጠየቁ መልካም ቢሆንም አለመታዘዙ ግን በሰልፍ መዳ ከመሞት አልታደገውም።   በየትኛውም የህይወት መስመር እግዚአብሔርን ለመስማት ሰምቶ ለመታዘዝ የተሰጠ ልብ ያስፈልገናል። የሕይወታችን መሪ እግዚአብሔር ነውና እንመራ! 🙏                       ....         ✍ 22/9/16                                    @astyon 🙏
5703Loading...
11
ዛሬ በታቦር ትምህርት ማዕከል(ኢቫን) ተገኝተን ከተማሪዎችና ከትምህርቱ ማሕበረሰብ ብር 6,075 ተሰብስቧል። ተማሪዎችና አጠቃላይ የትምህርቱን ማሕበረሰብ ለዳግማዊ አሰፋ ስላሳዩት ፍቅር እናመሰግናለን።
3921Loading...
12
ቃሉን ዘማሪ ባህሪና ጸጋን እግዚአብሔር አስታርቆ የቸረህ ወንድማችን ዘማሪ በረከት ለማ እንኳን ጌታ ረድቶህ "ያቦቅን ስሻገር" ለተሰኘው የአልበም ምረቃ አበቃህ። በየዘመኑ የራሱ የሆኑ ቅሬታዎች ያሉት እግዚአብሔር በእኛም ዘመን ቃሉን የሚዘምሩ፣ ለተሰጣቸው ጸጋ ታማኝ የሆኑ እና በመልካም አኗኗር የተመሰከረላቸው ለእግዜር የተረፉ አሉ። ወንድሜ ቤኪም አንዱ ነው። ትህትናው፣ ታዛዥነቱ፣ ቁጥብነቱ . . . ገና እሩቅ እንደሚጓዝ ያሳብቃል። የፊታችን እሁድ ግንቦት 25/2016 ዓ.ም ዕለተ እሁድ በሚያገለግልባት የሀዋሳ አዳሬ ሕይወት ብርሃን ቤተ-ክርስቲያን የመዝሙር አልበሙን ያስመርቃል። ሁላችሁም ተጋብዛችኋል! ምንተስኖት መኩሪያ
5683Loading...
13
ልጅ ደስታ ነው፤ ልጅ ተስፋ ነው። ቤተሰብ በብዙ ናፍቆትና ውጣ ውረድ የአምላክ ሥጦታ የሆነን ልጅ ሲያገኝ እንደገና በልጁ ውስጥ ይወለዳል። ድንገት ይህንን ደስታ የሚያሰናክል ነገር ሲገጥም ህመሙ ለወላጅ ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው። ያውም በከፍተኛ የጤና እንከን መፈተን ምንኛ ከባድ ነው? ሕጻን አሜን ፍቅረአብ ገና በጨቅላ እድሜዋ በልብ ህመም ምክንያት አስቸኳይ የሆነ ከሀገር ውጪ ህክምና አስፈልጓታል። ወዳጆቼ ህመሙ ጊዜ የሚሰጠው አይደለምና ከታች በምስሉ ላይ በምትመለከቱት የባንክ የሒሳብ ቁጥር አቅማችሁ የፈቀደው ሁሉ አድርጉላት! ምንተስኖት መኩሪያ
8683Loading...
14
ዛሬ ነገን ከሚሆኑ ታዳጊዎች ጋር መመካከርና እድል አግኝቶ አብሮ መሰንበት ምንኛ ደስ ይላል። ዛሬ ከሀዋሳ የዩኒዬን አካዳሚ የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ጋር የሕይወት ተሞክሮ፣ ስለወጣትነት፣ ስለአቻ ግፊት፣ ስለንባብ እና የቀረቡልንኝን ጥያቄዎች  የመወያያ ጊዜ ነበረኝ። በቆይታዬም በእጅጉ ደስተኛ ነኝ። መምህርትንና ተማሪዎችን ስለሁሉ ነገር ከልብ አመሰግናለሁ። ስላበረከታችሁልኝም የምስጋና ሥጦታ ክብረት ይስጥልኝ! ምንተስኖት መኩሪያ
6342Loading...
15
https://www.youtube.com/watch?v=JsM-1PJmayU
2150Loading...
16
Media files
5061Loading...
17
ሁሌም ለመልካም ሥራ ደጋግ እጃችሁን ስጠይቅ ስለማትነፍጉኝ ሁላችሁንም ከልብ አመሰግናለሁ። ሌሎችንም በማስተባበር እየተወጣችሁ ስላላችሁት ተግባር ምስጋናዬ ይድረሳችሁ። አሁንም ለዳጊ የጀመርነውን የማሕበራዊ ሚዲያ እንቅስቃሴ እንበርታ!
3961Loading...
👍 16
Фото недоступнеДивитись в Telegram
እጅግ የተወደድህ ወንድሜ ክብሩ ካሱ እና እህቴ ኤልሳቤት አሰፋ እንኳን ለከበረው ተቋም አምላክ አደረሳችሁ! እንኳን ደስ አላችሁ! 10 ዓመት በሙሉ ወንድሜ፣ ጓደኛዬ፣ በብዙ አጋዤ፣ የልብ ወዳጄ. . . ነህ፤ ክብርሽ። ትህትናህና ለእኔ የከፈልካቸው የቅንነት ዋጋዎችህ በእኔ ዘንድ ዋጋ አላቸው። ለሰው መልካም በመሆንህ አውቅሀለሁ። ብዙ የጓዳ ሀሳቦችን ተከፋፍለናል፤  ተመካክረናል። አንተ በእኔ ሕይወት ውስጥ በመኖርህ በብዙ አትርፌአለሁ። ሁሉን በዚህ መልኩ መመስከር አልፈልግምና ስለሁሉ በምስጋና ላብቃ። ኤልሲ በክብሩ ውስጥ አንቺን በብዙ አውቄሻለሁ። ታማኝና እውነተኛ እጮኛው መሆንሽን በድፍረት እመሰክራለሁ። ክበሪ እህቴ። ትዳራችሁን እግዚአብሔር ይባርክ! በኑሯችሁ እግዚአብሔር ይኑር! በእውነተኛ ተምሳሌታዊ ሕይወት ጌታ ዘመናችሁን ሁሉ ያለምልም! በፍቅር፣ በትዕግስት፣ በአብሮ ሰራተኝነት፣ ... ጌታ ቤታችሁን ይምራ!! መልካም ጋብቻ!! ወንድማችሁ ምንተስኖት መኩሪያ
Показати все...
👍 1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ባሳለፍነው ሳምንት  በታቦር ትምህርት ማዕከል(ኢቫን) ተገኝተን ከተማሪዎችና ከትምህርቱ ማሕበረሰብ ብር 6,075 መሰብሰባችን ይታወቃል። ዛሬ በተጨማሪ የሥነ መለኮት ተማሪዎች ብር 2,635 ሰብስበው ለዳጊ ህክምና አውለዋል። በጸሎትም ከጎናችን እንደሆኑ ገልፀውልናል።  ለዳግማዊ አሰፋ ስላሳዩት ፍቅር እናመሰግናለን።
Показати все...
መንፈሳዊ ውጊያ የተሰኘው የወንድማችን ኢያሱ መጽሐፍ ሊመረቅ እነሆ ቀናት ብቻ ቀሩት። የፊታችን እሁድ ሰኔ 02/2016 ዓ.ም በሀዋሳ አላሙራ ሕይወት ብርሃን ቤተ-ክርስቲያን ከቀኑ በ08:00 ይመረቃል! ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።
Показати все...
👍 2
Фото недоступнеДивитись в Telegram
የሀዋሳ ከተማን ጨምሮ በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ አከባቢዎች እየተበራከተ ብቻም ሳይሆን እጅግ በሚያስፈራ ሁኔታ ዕድሜአቸው 14  ዓመት ከሆናቸው ታዳጊ ልጆች ጀምሮ በልደት ፕሮግራም የተጀመረ የአልኮል መጠጥ እና የጎጂ ሱሶች ልምምድ አስደንጋጭ ደረጃ ላይ ደርሷል። ምንም ገና ግራና ቀኛቸውን ለይተው ያላወቁ ታዳጊዎች እንደ መዝናኛ፣ እንደ ስልጣኔ፣ እንደ ማወቅ . . . ቆጥረው በዚህ ገዳይ ጎዳና እየነገዱ ለውድቀት መዳረጋቸው እንደ አንድ ሰው በብዙ የሚያሳዝነኝ ነው። ችግሩን እያወቅን እና እየታወቀ የሚሰጠው ትኩረት አናሳ መሆን፣ አባባሽ ምክንያቶችን በሕግ አለመከላከልና ምን አገባኝ? ባይነት ትውልድን እያመከነ ነውና ቸል አንበል! ምንተስኖት መኩሪያ
Показати все...
👍 1
እህቴ አትክልት አማረ እንኳን እግዚአብሔር ረዳሽ! እንኳን ደስ አላችሁ!! ቤታችሁን እግዚአብሔር ይስራ፤ ይባርክም። በኑሮአችሁ ሁሉ ክርስቶስ ይክበር። ትዳራችሁን በፍቅር ያጽና። መልካሙን ሁሉ እመኝላችኋለሁ! መልካም ጋብቻ! ምንተስኖት መኩሪያ
Показати все...
👍 4
ታላቁ መጽሐፍ እንደነገረን በአንድ ወቅት ኑኃምን የሚትባል ሴት  ከምትኖርበት ቀዬ ከባሉዋና ከሁለት ልጆቿ ጋር በረሃብ ምክንያት ዳቦ ፈለጋ ሞአብ ወደሚባል ሀገር ትሰደዳለች።  ረሃብ ክፉ ነው በምንም የማያስታግሱት መፍትሔ ነው ያሉበትን ጉዳይ ደግሞ እንኳ ለማሰብ ዕድል የማይሰጥ ፣ ዝም ብሎ እጅ አጣምሮ ሚያረገውን ልይ ካሉ ደሞ ሞት የሚባል ጨካኝ ሰይፉን የሚመዝ  አስፈሪ ና አንገብጋቢ ነው። ኑኃምን ና በተሰቦቿ ከረሃብ ሊያመልጡ ወደ ሞዓብ መሄድን ደግሞ ያለሰቡት ለዚህም ይመስለኛል። ኑኃምን ዕድል ቀንቷት እንድንል በዚያ ሄዳ ከረሃብ አምልጣ አልፎም ልጆቿን ዳረች በጥቅቱም ቢሆን ሁሉም መልካም፣  ኑሮ የሰመረላት ይመስላል ፤ ነገር ግን በዚህ አልቀጠለም የሞዓብ ሀገር  ዳቦ ሰጥቷት ረሃቧን ያስታገሳት ቢመስልም  ቤተሰቧን ፣ደስታዋን ፣ሙላቷን፣...  ነጥቋታል።  አገኘን ያልነው ነገር ምንስ ነጥቆን ይሁን?..    ይህ ሆነና ይህች ሴት  የገጠማት ፈተና  በዳቦ ተጽናንታ በሞዓብ ምድር መሰንበት የሚያስችላት አልነበረም ፤  ከዚያ ሀገር መውጣት  አማራጭ  የሌለው ነው ምክንያቱም ባዶዋን ያስቀራት ሥፍራ ነውና። ዛሬም ዳቦ አግኝተንበት  ህልማችን፣ ተስፋችን ፣ ደስታችን ፣መላታችንን ፣.. የተሰረቅንበት  ቦታ ሆነን የሆነው አንደ ሆኑዋልና ከዚህ ኋላ ወዴት?! ብለን ሙታችንን ታቅፈን የተቀመጥን በተስፋ መቁረጥ የደነዘዝን  ስንቶች ነን??  ሩት ከሞዓብ ምድር መውጣቷ  ወደ ቀዬዋ መመለስ ትክክለኛ ውሳኔ ነው። በእርግጥ ሩት በዚህ ሁሉ  የሳተችው ዋና ነገር  #ምሪት ነው የእግዚአብሔርን ፈቃድ መጠየቅ። ከቤተልሔም መውጣት አማራጭ የለለው ጉዳይ ይሆናል ግን መውጣት ስለተቻለ ዕድል ስለተመቻቸ  አይወጣም!  ምን ላድርግ ፣ እንዴት  ልሁን ነው የሚባለው፤   ግን እኛ በፍጹም ልባችን በእግዚአብሔር መዳገፍ ሲያቅተን የመሰለንን ሁሉ እግሬ አውጭኝ ይሉት በመሰለን ራሳችንን የሚናድን ይመስል እንታትራለን።  ህይወት በግምት ና በስለት ከሆነ የእግዚአብሔርን ከለላ ማራቅና ባለቤትነቱን መካድም ነው።   ይሳሐቅን እግዚአብሔር ወደ ግብፅ አትውርድ እኔ በምልህ ምድር ተቀመጥ ስለው እሺ በማለቱ  የአምላኩን አብሮነትና በረከቱን መቀበል ችሏል።  የእግዚአብሔርን ምርት መጠየቅ ብቻ ሳይሆን መታዘዝም ነው ለሕይወት የሚሆነን። የእስራኤል ንጉሥ የነበረ አክአብ ወደ ሬማት ዘገለዓድ ሰልፍ ልወጣ ምሪት መጠየቁ መልካም ቢሆንም አለመታዘዙ ግን በሰልፍ መዳ ከመሞት አልታደገውም።   በየትኛውም የህይወት መስመር እግዚአብሔርን ለመስማት ሰምቶ ለመታዘዝ የተሰጠ ልብ ያስፈልገናል። የሕይወታችን መሪ እግዚአብሔር ነውና እንመራ! 🙏                       ....         ✍ 22/9/16                                    @astyon 🙏
Показати все...
👍 8