uk
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Відкрити в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 13 342 підписників, посідаючи 1 756 місце в категорії Транспорт та 2 537 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 13 342 підписників.

За останніми даними від 18 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 91, а за останні 24 години на 11, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 41.16%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 15.44% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 491 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 060 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 11.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 18 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Транспорт.

13 348
Підписники
+1124 години
+477 днів
+9130 день
Архів дописів
የሶዶና አካባቢው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት የፕሮጀክት አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ ሶዶ ፣ ታህሳስ 30 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢመአ)፡ በኢትጵያ መንገዶች አስተዳደር የደቡብ ፕሮጀክት ማኔጅመንት ፕሮግራም ዳይሬክተር ስር ከሚገኙት የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች ዉስጥ አንዱ የሆነዉ የሶዶና አካባቢው ግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት የፕሮጀክት አፈፃፀም ግምገማ በማድረግ በቀሪ ስራዎች ላይ ዉይይት አካሄደ፡፡ የሶዶና አካባቢው ግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ባደረገው ሪፎርም ከተቋቋሙት ጽ/ቤቶች መካከል አንዱ ነዉ፡፡ ጽ/ቤቱ የ2016 በጀት አመት የግማሽ አመት እቅድ አፈፃፀሙን በመገምገም በግማሽ ዓመቱ የተመዘገቡ ውጤቶችና የተስተዋሉ ችግሮችን በዝርዝር አይቶ  ችግሮቹን ለመቅረፍ የሚያስችሉ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ያስቀመጠ ሲሆን ፣ ከእቅድ ግምገማ ባሻገር በፕሮጀክት ማኔጅመንት ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አማካኝነት የእርስ በእርስ መማማር እና ስልጠናም ተካሂዷል፡፡ ጽ/ቤቱ ባለፉት ስድስት ወራት ለመፈፀም ካቀደው ስራ 72 በመቶውን ለማሳካት ችሏል፡፡ ከላይ የተጠቀሰዉ አፈጻጸም መልካም ቢሆንም በቀጣይ ቀሪ ስድስት ወራቶች  የተስተዋሉ የአፈፃፀም ክፍተቶችን ጨምሮ በበጀት አመቱ የታቀደውን ዕቅድ ማሳካት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በአትኩሮት መስራት እንደሚገባ የጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ሰለሞን ሞላ የስራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የሶዶና አካባቢው ግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት የግንባታ ወጪያቸዉ 22 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ 13 ፕሮጀክቶችን የሚያስተዳድር ሲሆን ፣ አጠቃላይ ርዝማኔአቸውም 550 ኪሎ ሜትር ነው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et Facebook https://www.facebook.com/www.era.gov.et

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ !! መልካም የገና በዓል! የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ  እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ !! መልካም የገና በዓል! የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

የጂንካ - መንደር ዲዛይንና ግንባታ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 25 ቀን 2016 ዓ.ም. (ኢመአ)፡ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙው የጂንካ - መንደር ዲዛይንና ግንባታ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው፡፡ የፕሮጀክቱን ግንባታ በማካሄድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ሲሆን ፣ ሃይዌይ ኢንጂነርስ ኤንድ ኮንሰልታንትስ ሃ/የተ/የግል ማህበር የማማከርና የቁጥጥር ስራውን በማከናወን ላይ ይገኛል ፡፡ 52.86 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውን ይህ ፕሮጀክት ለማካሄድ አገልግሎት ላይ የሚውለው የገንዘብ 1,373,268,271.09 ( አንድ ቢሊየን ሶስት መቶ ሰባ ሶስት ሚሊየን ሁለት መቶ ስልሳ ስምንት ሺህ ሁለት መቶ ሰባ አንድ ብር ከዜሮ ዘጠኝ ሳንቲም ሲሆን ) የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው ፡፡ ፕሮጀክቱ የሚገኝበት አካባቢ መልክዓ-ምድር ለምነት ያለው ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ተደጋጋሚ የሆነ የመሬት መንሸራተት ችግር መከሰቱ ፣ የወሰን ማስከበር እና ተያያዥ ችግሮች ፣ የስራ ተቋራጭ አስፈላጊውን የግንባታ ማሽነሪዎች እና ግብዓቶችን በውል ስምምነቱ እና በትግበራ ዕቅድ መሰረት አቅርቦ በሙሉ አቅም መስራት አለመቻሉ ፣ የዋጋ ንረትና የግንባታ አቅርቦት ችግሮች እና የግንባታ ግብዓቶች እጥረት መኖር በግንባታ ሂደቱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖዎችን አሳድሮ ቆይቷል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጅንካ እና አካባቢው ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከስራ ተቋራጩ ጋር ተደጋጋሚ ውይይት በማካሄድ እና አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ በማድረጉ ችግሮቹን በመቅረፍ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 80 በመቶ ሊደርስ ችሏል፡፡ የመንገዱ የመጀመሪያው 42 ኪሎ ሜትር ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ፣ የጂንካ ከተማ 3.02 ኪሎ ሜትር የመንገድ ግንባታ ስራ እንዲሁም ቀሪ ከቶልታ እስከ መጨረሻ የሚገኘው 7.56 ኪሎ ሜትር የፕሮጀክቱ ክፍል ከዚህ ቀደም ያልነበረ እና አዲስ መንገድ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ መንገዱ የሚያልፍበት አቅጣጫ የመምረጥ ፣ የመንገድ ግንባታው ጥናት፣ ቅየሳ እና ዲዛይን ፣ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ዲዛይን እና ግንባታ ፣ 3 የድልድይ ዲዛይን እና ግንባታ ፣ 154 የፍሳሽ ማስወገጃ Pipe Culvert እና 24 Slab Culvert ፣ 3,073,627.79 ሜ3 የአፈር ቆረጣ ፣ 885,834.57 ሜ3 የአፈር ሙሌት ፣ 144,451.68 ሜ3 የሰቤዝ እና 111,317.32 ሜ3 ቤዝ ኮርስ የማንጠፍ ስራዎችን ባካተተ መልኩ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ፕሮጀክቱ ከተጀመረ እስካሁን 49.37 ኪሎ ሜትር ወይም 93.41% የዲዛይን ፣ 51.70 ኪሎ ሜትር ወይም 97.81% የጠረጋ ፣ 44.31 ኪሎ ሜትር ወይም 98.43% የአፈር ቆረጣ ፣ 32.79 ኪሎ ሜትር ወይም 83.88% የአፈር ሙሌት ፣ 39.03 ኪሎ ሜትር ወይም 73.84% የሰቤዝ ፣ 34.29ኪሎ ሜትር ወይም 64.87% የቤዝ ኮርስ ስራ እና 31.25 ኪሎ ሜትር ወይም 59.12% አስፋልት የማንጠፍ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ በቀጣይ 13.83 ኪሎ ሜትር ወይም 26.16% የሰቤዝ ፣ 18.57 ኪሎ ሜትር ወይም 35.13% የቤዝ ኮርስ እና 21.61 ኪሎ ሜትር ወይም 40.88% አስፋልት ማንጠፍ ስራዎችን በማካሄድ ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ለአካባቢው እና ለክልሉ ብሎም ለሃገሪቷ የሚኖረው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ከፍተኛ ሲሆን ፣ በተለይም በኦሞ ወንዝ አካባቢ ለተገነቡና በመገንባት ላይ ለሚገኙት ፋብሪካዎች ግብዓትና ምርት ማመላለሻነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ ይታመናል፡፡ በተጨማሪም አብዛኛው የአካባቢው ማህበረሰብ አርሶ አደሮች በመሆናቸው በአካባቢው የሚመረቱትን የግብርና ምርቶች በቀላሉ ወደ ገበያ ለማውጣት አመቺነት በመፍጠር ለአምራችና ሸማቹ ማህበረሰብ ተጠቃሚነትን ይፈጥራል፡፡ የዚህ መንገድ አካል የሆነው የመንደር-ሐና አስፋልት መንገድ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et Facebook https://www.facebook.com/www.era.gov.et

በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ስረዓተ ጾታን የተመለከተ ፖሊሲ እየተዘጋጀ ነዉ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሴቶችና ስረዓት ፆታ ላይ ያተኮረ ፖሊሲ በማዘጋጀት ወደ ስራ ለመግባት ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ ይህንኑ አስመልክቶ ኢመአ ላለፉት ቀናት ከተቋሙ ሰራተኞች ጋራ ሰፊ ዉይይት ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ ዉይይቱ በቢሾፍቱ ከተማ ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ፣ በዛሬዉ ዕለት ተጠናቋል፡፡ በነበረዉ የዉይይት መድረክ ላይ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የተውጣጡ ሰራተኞች እና የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡ በመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ላይ የሚስተዋሉ የስረዓተ ፆታ እና ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ የሚስተዋሉ ችግሮች በጥናት የተለዩ ሲሆን ፣ በቀጣይ ክፍተቶቹን ለመድፈን የህግ ማዕቀፍ እንደሚያስፈልግ ታምኖበታል፡፡ በዚህም ከተቋሙ ሰራተኞች የተሰበሰቡ ሃሳቦችን እንደ ተጨማሪ ግብዓት በመዉሰድ የህግ ማዕቀፉ በቅርቡ እንደሚጸድቅ ይጠበቃል፡፡ ጥናቱን ያካሄደዉ ዴቭሎፕመንት ሪሰርች ኤንድ ትሬንግ ፒለሲ ወይም (DAB) የተባለ አገር በቀል አማካሪ ድርጅት ነዉ፡፡ (DAB) በማህበራዊ እና ኢኮኖያዊ ጉዳዮች ዙሪያ ጥናት እና ምርምር በማድረግ የሚታወቅ ተቋም ነዉ፡፡ ለጥናቱ መካሄድ የአፍሪካ ዴቭሎፕመንት ባንክ ድጋፍ አድርጓል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et Facebook https://www.facebook.com/www.era.gov.et

HoA Monitoring and Supervision SPN_231229_095518.pdf4.20 KB

የዳዬ-ጭሪ-ናንሴቦ 71 ኪሎሜትር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ከአንድ ዓመት ባነሰ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው ሐዋሳ፣ ታኅሣሥ 19፣ 2016 (ኢ መ አ):- የሲዳማ እና ኦሮሚያ ክልሎችን የሚያስተሳስረው የዳዬ-ጭሪ-ናንሴቦ 71 ኪሎሜትር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ከአንድ ዓመት ባነሰ ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ነው። በፕሮጀክቱ አሁን ላይ ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው 81 በመቶው ተጠናቅቋል። ከግንባታ ሥራዎች መካከልም የ42 ኪሎሜትር የአስፋልት ማንጠፍ፣ የሰብቤዝ፣ ቤዝኮርስ፣ የኮንክሪት እና የአስፋልት ጠጠር ማምረት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። በተጨማሪም የስድስት አነስተኛ እና መካከለኛ ድልድዮች ግንባታ ተጠናቅቋል። ቦታው ድረስ በተደረገ የመስክ ቅኝት፥ በዳዬ እና ጭሪ ከተማዎች ያልተጠናቀቁ የወሰን ማስከበር ሥራዎች በግንባታው ላይ እክል መፍጠሩ የተመለከተ ሲኾን፥ ችግሩ በሚቀረፍበት ሁኔታ ላይ ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሠራ ይገኛል። ግንባታውን ዓለም አቀፉ ቻይና ው ይ ኮርፖሬሽን ሊሚትድ፣ ከፌደራል መንግስት በተመደበ ከ1ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እያከናወነ ይገኛል። ክላሲክ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ግንባታውን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራ ይሠራል። የመንገድ ፕሮጀክቱ መነሻውን በሲዳማ ክልል ዳዬ ከተማ በማድረግ በኦሮሚያ ክልል እየተገነባ ከሚገኘው የኤዶ-ሴሮፍታ-ወርቃ መንገድ ፕሮጀክት ጋር ይገጥማል። በመሆኑም የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ የኹለቱን ክልሎች የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር በእጅጉ ያሳልጣል። ከዚህም ባሻገር በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የቡና፣ ገብስ እንዲሁም የእንሰት ምርት ውጤቶች በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ማድረስ ያስችላል። የጤና፣ ትምህርት እና መሰል የማኅበራዊ ተቋማት ተደራሽነት ከማስፋቱም ባለፈ በሥፍራው የሚገኙትን አነስተኛ መንደሮች ወደ ከተማ የሚያድጉበትን ምቹ ዕድል የሚፈጥር ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et Facebook https://www.facebook.com/www.era.gov.e

ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በባሕር ዳር ከተማ በመገንባት ላይ የሚገኘውን  አዲሱን የአባይ ወንዝ ድልድይ ጎበኙ፡፡ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ፣ የብሔራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ተመስገን ጥሩነህ ፣ የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ ፣ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በባሕር ዳር ከተማ በመገንባት ላይ የሚገኘውን  አዲሱን የአባይ ወንዝ ድልድይ ተመልክተዋል። ድልድዩ እጅግ ግዙፍና ዘመናዊ ድልድይ የሚሰራበትን ቴክኖሎጂዎች እና ከሀገር ውጭ የሚከናወኑ ልዩ የጥራት መለኪያዎችን በመጠቀም ነው ግንባታ የተካሄደው። ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ መንግስት በተሸፈነ 1,551,189,441.00 ብር ወጪ (revised contract price) በቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ ሲካሄድ ቆይቶ በአሁኑ ወቅት ከትንንሽ ስራዎች ውጪ ስራው ተጠናቋል። የፕሮጀክቱ የማማከር እና ቁጥጥር ስራ ደግሞ በቦቴክ ቦስፈረስ ኮንሰልቲንግ እና በስታዲያ ኢንጅነሪንግ በጣምራ ሲከናወን ቆይቷል። የድልድዩ አጠቃላይ እርዝማኔ 380 ሜትር ነው። ድልድዩ  በግራና በቀኝ በአንድ  ጊዜ 6 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ እንዲችል ተደርጎ ከመገንባቱም ባሻገር A5 ሜትር የእግረኛ መንገድ እንዲሁም 3.5 ሜትር የብስክሌት ተጠቃሚዎችን መስመር ባካተተ መልኩ ነው የተገነባው፡፡ በድልድዪ መነሻና መዳረሻ በኩል የሚገነባዉ 4.7 ኪ.ሜ የሚረዝመዉ የአስፓልት ንጣፍ ሲጠናቀቅ ድልድዩ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ይሆናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et Facebook https://www.facebook.com/www.era.gov.et

የወልዲያ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ይገኛል በወልዲያ ከተማ እየተገነባ የሚገኘዉን የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ስራዎች በዘንድሮ አመት መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው፡፡ የፕሮጀክቱ የእስካአሁን አጠቃላይ የግንባታ አፈጻጸም 58 በመቶ ደርሷል፡፡ ለመንገድ ግንባታዉ የተመደበዉ 1,207,407,635.08 ወጪ የሚሸፈነዉ በኢትዮጵያ መንግስት ነዉ፡፡ የመንገድ ግንባታዉን እያከናወነ የሚገኘዉ የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ሲሆን ፣ የማማከር እና ቁጥጥር ስራዉን ደግሞ ልደት እና ስማርት ኮንሰልቲንግ በጣማራ እያካሄዱት ይገኛሉ፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ መሃል ከተማዉን በማቋረጥ እስከ ስቴዲየም ያለዉን ዋና መስመር የሚሸፍን ይሆናል፡፡ የቀድሞ የመንገድ ይዘት ከ7 ሜትር ያነሰ ስፋት የነበረው ሲሆን ፣ እጅግ ጠባብና ለትራፊክም አስቸጋሪ የሆነ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት እየተገነባ የሚገኘዉ የመንገዱ የጎን ስፋት በዋናዉ መስመር 30 ሜትር እና ወደ ስታዲየም በሚወስደዉ በኩል ደግሞ 12 ሜትር ተጨማሪ ስፋት እንዲኖረዉ ተደርጎ ነዉ እየተገነባ የሚገኘዉ፡፡ በተጨማሪም የእግረኛ እና የብስክሌተኞች መተላለፊያ እንዲሁም የአረንጓዴ ሥፍራ ግንባታን ያካተተ ነው። ፕሮጀክቱ ሁለት የድልድይ ስራን ጨምሮ ፤ 3 ፓይፕ ከልቨርቶች ፣ 7 ስላብ ከልቨርቶች እና 1 ቦክስ ከልቨርት አካቶ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ በእስከአሁኑ የግንባታ ሥራዎች የመሬት ጠረጋ ፣ የሙሌት ፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ፣ የድልድይ ግንባታ እንዲሁም የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ ሥራዎች በመሠራት ላይ ናቸው። በተጨማሪም የአስፓልት ንጣፍ ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ የመንገዱ ግንባታ ሲጠናቀቅ በከተማዋ ውስጥ እንዲሁም መግቢያና መውጫ ላይ የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ በእጅጉ ይቀንሳል፡፡ ከዚህም ባለፈም በወልዲያ ከተማ የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ የሚቀርፍ ከመሆኑም ባሻገር ለከተማዋም ውበትን ያጎናፅፋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et Facebook https://www.facebook.com/www.era.gov.et

አካባቢያዊና ማህበራዊ ደህንነትን መሰረት ያደረገ አውደጥናት ተካሄደ ቢሾፍቱ ፣ ታህሳስ 9 ቀን ፣ 2016 (ኢ መ አ):-በመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ምክንያት የሚደርሱ አካባቢያዊና ማህበራዊ ጫናዎችን መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ አዉደጥናት ተካሄደ ። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን በሚያካሂድበት ወቅት ለአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ትኩረት በመስጠት ስራዎቹን እንደሚያከናውን ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን ከሁሉንም ባለድርሻ አካላት ጋር መስተጋብር በመፍጠር ከአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ለሚፈጠሩ ሁኔታዎች ፣ አፋጣኝ መፍትሄ ለመስጠት እንዲቻል አውደጥናቱ ተዘጋጅቷል፡፡ በዕለቱ የኢትየጵያ መንገዶች አስተዳደር የሚገነባቸው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን አስመልክቶ ከአካባቢያዊና ማህበራዊ ደህንነት ጋር በተገናኘ የሚከሰቱ ጉዳዮች እና ሊተገበሩ የሚገባቸዉ አስፈላጊ የሆኑ ጥንቃቄዎችን እንዲሁም መሰረታዊ ለዉጥ የሚያመጡ ሁኔታዎችን አስመልክቶ ጥናታዊ ፅሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። ተቋሙ ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ማህበራዊ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ እና በአካባቢያዊ ጥበቃና ደህንነት ላይ ዘላቂነት የሚያረጋግጥ ለውጥ አምጪ ስራዎች መስራት እንደሚገባው ተጠቁሟል፡፡ በተያያዘም ከመንገድ ግንባታዎች ጋር በተገናኘ የሚስተዋሉ የአሰራር ክፍተቶችን ለመቅረፍ እንዲቻል ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር በመቀናጀት መፍትሄ የሚያመጡ ዘዴዎችን ለማመቻቸት የሚያስችል ምክክር ከተሳታፊዎች ጋር በማድረግ የመፍትሄ ሃሳቦችን ለማስቀመጥ ተችሏል፡፡ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ደህንነት ጥበቃና እንክብካቤ የመተግበርና የማስተግበር ኃላፊነቶች የጋራ በመሆናቸው ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባም ተመላክቷል። ምክክሩ በሁለት ዙር ተከፍሎ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ በአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሚታዩ ችግሮችን በመቅረፍ ጠቃሚ አቅጣጫን ለማስቀመጥ ያግዛል፡፡ ከዚህም ባሻገር በመንገድ ግንባታ ወቅት ከአካባቢያዊና ማህበራዊ መስተጋብሮች ጋር በተገናኘ ደህንነትን ታሳቢ ያደረጉ የህግ ማዕቀፎችን በመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ይበልጥ ተግባራዊ እንዲሆኑ ከማስቻል አኳያ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ታምኖበታል፡፡ በአውደ ጥናቱ ላይ የስራ ተቋራጮች ፣ አማካሪ ድርጅቶች ፣ የአካባቢና ማህበራዊ አፈፃፀምን የሚከታተሉ ባለሙያዎች ፣ የመንገድ ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ሀላፊዎች እና ሲኒየር መሃንዲሶች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

የወልዲያ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ይገኛል በወልዲያ ከተማ እየተገነባ የሚገኘዉን የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ስራዎች በዘንድሮ አመት መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው፡፡ የፕሮጀክቱ የእስካአሁን አጠቃላይ የግንባታ አፈጻጸም 58 በመቶ ደርሷል፡፡ ለመንገድ ግንባታዉ የተመደበዉ 1,207,407,635.08 ወጪ የሚሸፈነዉ በኢትዮጵያ መንግስት ነዉ፡፡ የመንገድ ግንባታዉን እያከናወነ የሚገኘዉ የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ሲሆን ፣ የማማከር እና ቁጥጥር ስራዉን ደግሞ ልደት እና ስማርት ኮንሰልቲንግ በጣማራ እያካሄዱት ይገኛሉ፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ መሃል ከተማዉን በማቋረጥ እስከ ስቴዲየም ያለዉን ዋና መስመር የሚሸፍን ይሆናል፡፡ የቀድሞ የመንገድ ይዘት ከ7 ሜትር ያነሰ ስፋት የነበረው ሲሆን ፣ እጅግ ጠባብና ለትራፊክም አስቸጋሪ የሆነ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት እየተገነባ የሚገኘዉ የመንገዱ የጎን ስፋት በዋናዉ መስመር 30 ሜትር እና ወደ ስታዲየም በሚወስደዉ በኩል ደግሞ 12 ሜትር ተጨማሪ ስፋት እንዲኖረዉ ተደርጎ ነዉ እየተገነባ የሚገኘዉ፡፡ በተጨማሪም የእግረኛ እና የብስክሌተኞች መተላለፊያ እንዲሁም የአረንጓዴ ሥፍራ ግንባታን ያካተተ ነው። ፕሮጀክቱ ሁለት የድልድይ ስራን ጨምሮ ፤ 3 ፓይፕ ከልቨርቶች ፣ 7 ስላብ ከልቨርቶች እና 1 ቦክስ ከልቨርት አካቶ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ በእስከአሁኑ የግንባታ ሥራዎች የመሬት ጠረጋ ፣ የሙሌት ፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ፣ የድልድይ ግንባታ እንዲሁም የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ ሥራዎች በመሠራት ላይ ናቸው። በተጨማሪም የአስፓልት ንጣፍ ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ የመንገዱ ግንባታ ሲጠናቀቅ በከተማዋ ውስጥ እንዲሁም መግቢያና መውጫ ላይ የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ በእጅጉ ይቀንሳል፡፡ ከዚህም ባለፈም በወልዲያ ከተማ የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ የሚቀርፍ ከመሆኑም ባሻገር ለከተማዋም ውበትን ያጎናፅፋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et Facebook https://www.facebook.com/www.era.gov.et

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid03TMYkK7C2VLQns5AhUXG4dNmvbefBRoZDkEcPdP6tm7NVWbgmUHucpn1NQKSgSK9l&id=100064848694581&mibextid=Nif5oz በክልሉ ከ4 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነቡ ያሉ ሦስት የአስፓልት መንገዶች ግንባታ አፈጻጸም አበረታች ነው ጋምቤላ ፤ ታህሳስ 5/2016፦ በጋምቤላ ክልል አኝዋሃ ዞን ከ4 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ እየተገነቡ ያሉ ሦስት የአስፓልት መንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታ አፈጻጸም አበረታች መሆኑን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለፁ።