uk
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Відкрити в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 13 369 підписників, посідаючи 1 753 місце в категорії Транспорт та 2 530 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 13 369 підписників.

За останніми даними від 20 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 129, а за останні 24 години на 8, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 38.47%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 15.24% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 143 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 037 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 11.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 21 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Транспорт.

13 373
Підписники
+824 години
+697 днів
+12930 день
Архів дописів
ከዲቾቶ ተነስቶ በልሆ የሚዘልቀው መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ፡፡ የዲቾቶ - ጋላፊ መገንጠያ /ዶቢ- ኤሊዳር - በልሆ የሲሚንቶ ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ ፡፡ አዲሱን የታጁራ ወደብ ለመጠቀም የሚያስችለው ፕሮጀክቱ በአፋር ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን 78 ኪ.ሜ ርዝመት አለው ፡፡ የመንገዱ ግንባታ ያካሄደው መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የተባለ የመንግስት ልማት ድርጅት ነው ፡፡ ኢንጂነር ዘውዴ እስክንድርና ከሲም አማካሪ መሃንዲስ በጋራ ፕሮጀክቱን በአማካሪነት እና በተቆጣጣሪነት ተሳትፈዋል፡፡ መንገዱን ለመገንባት 2.4 ቢሊዮን ብር ወጪን ጠይቋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት መንገዱን ለመገንባት የዋለውን ወጪ ሸፍኖታል፡፡ መንገዱ በገጠራማው አካባቢ የመንገድ ግራና ቀኝ ትከሻን ጨምሮ 10 ሜትር የሚሰፋ ሲሆን በኤሊዳር ከተማ ደግሞ 21.5 ሜትር ስፋት አለው ፡፡ የዲቾቶ-ጋላፊ መገንጠያ / ዶቢ - ኤሊዳር - በልሆ የመንገድ ፕሮጀክት ዲዛይን እና ግንባታን በጋራ ባካተተ መልኩ ነው የተገነባው ፡፡ የግንባታው አይነት ከለመድናቸው የአስፋልት መንገድ በተለየ በሲሚንቶ ኮንክሪት ደረጃ የተገነባ ነው ፡፡ ይህም የሆነው አካባቢው ባለው ከፍተኛ ሙቀት ሳቢያ ከአስፋልት ይልቅ በሲሚንቶ ኮንክሪት መገንባቱ አየሩን ተቋቋሞ ግልጋሎት የመስጠት አቅሙን የተሻለ እንደሚያደርገው በመታመኑ ነው ፡፡ በተጨማሪም የሲሚንቶ ኮንክሪት መንገድ በአነስተኛ ጥገና እስከ 40 አመት አገልግሎት መስጠት ስለሚያስችለው ለጥገና የሚወጣውን ወጪ በእጅጉ እንዲቀንስ ይረዳዋል ፡፡ ፕሮጀክቱ የአገሪቷ የወጪ ገቢ ንግድ የሚካሄድበት ኮሪደር እንደመሆኑ መስመሩን የሚጠቀሙ በርካታ ቁጥር ያላቸው የጭነት ተሽከርካሪዎች ክብደት የመሸከምም አቅም እንዲኖራቸው ታሳቢ ያደረገ ነው ፡፡ ከዚህ ባሻገር ባካባቢው ያለውን የፖታሽ ክምችትም ሆነ ሌሎች ማእድናት በቀላሉ ካለምንም ውጣ ውረድ ወደ አቅራቢያ ወዳለ ወደብ ለማድረስ ያግዛል ፡፡ የዲቾቶ - ጋላፊ መገንጠያ - ኤሊዳር - በልሆ መንገድ መገንባቱ አዲሱን የታጁራ ወደብ ለመጠቀም የሚያስችል ከመሆኑም ባሻገር በነባሩ ጅቡቲ ወደብ ይፈጠር የነበረውን የትራንስፖርት ጫና ያቃልላል፡፡ መንገዱ ወደ ታጁራ ወደብ መዳረሻም ብቻ ሳይሆን ወደ አሰብ ወደብ የሚዘልቀው የመንገድ አካል ጭምርም ነው። ይህም ሲባል ከአጠቃላይ ከፕሮጀክቱ 78 ኪሎ ሜትሩ ውስጥ ከዲቼቶ ተነስቶ ሜሎዶኒ መገንጠያ ድረስ ያለው 64 ኪ .ሜ ወደ አሰብ ወደብ የሚዘልቀው መንገድ ይጋራል። ከሚጋሩበት ከሜሎዶኒ መገንጠያ እስከ አስብ ወደብ መዳረሻ ቡሬ ድረስ ያለውን 71.6 ኪ.ሜ (የሜሎዶኒ መገንጠያ - ማንዳ - ቡሬ ) መንገድ ስራ ፕሮጀክት በሁለት ቢሊዮን ብር ወጪ በቻይናው ሻንዶንግ ሊኪኖ ግሩፕ ለመገንባት የሚያስችል የውል ስምምነት ፊርማ በሀምሌ ወር 2012 ዓ.ም ተፈርሞ በቀጣይ ወደ ስራ የሚሸጋገር ይሆናል፡፡

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የስራ አመራሮች የሸገር ማስዋብ እና የእንጦጦ ፓርክ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት
+3
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የስራ አመራሮች የሸገር ማስዋብ እና የእንጦጦ ፓርክ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት የባለስልጣኑ መ/ቤት አሻራውን በዚህ ታላቅ አገራዊ ፕሮጀክት ያሳረፈ በመሆኑ የሚያኮራ መሆኑን አውስተዋል። በቀጣይም ኢመባ በገበታ ለአገር ፕሮጀክት ሊገነቡ ከታሰቡት ውስጥ አንዱ የሆነውን የሃላላ ኬላ- ጨበራ ጩርጩራ -ጊቤ ሶስት - ኮይሻ የተቀናጀ ልማት ግዙፍ ፕሮጀክት ላይ ተሳትፎውን የሚቀጥልበት ይሆናል ብለዋል ። በተሳትፎውም ይህን እምቅ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ጸጋ እንዲሁም በአካባቢው ያሉትን ውብ ተፈጥሮ እና ባህል የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ከኮንሴፕት ዲዛይን ጀምሮ እስከ የመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታ ድረስ ትልቅ ድርሻ እንደሚኖረው ተገልጿል ። ስለሆነም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አገራዊ አሻራ የማኖር ተግባሩን አጠናክሮ ስለመቀጠሉ ማሳያ ሊባል ይችላል ። ከዚህም በተጨማሪ መላው የባለስልጣኑ አመራር እና ሰራተኛ የአንድ ወር ደሞዙን ለገበታ ለአገር ፕሮጀክት ትግበራ እንዲውል ወስኗል ። በመጨረሻም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አመራሮች በእንጦጦ ፖርክ አገር በቀል ችግኞችን ተክለዋል።

የደወሌ ድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሸከርካሪዎች ተርሚናል ግንባታ ስራ እየተካሄደ ነው፡፡ በዛሬው ዕለት በትራንስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ በክቡር አቶ ካሳሁን ጎፌ እና በኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ የተመራ ልኡክ የደወሌ ድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሸከርካሪዎች ተርሚናል ግንባታ ስራ እንቅስቃሴ የተመለከተ ቅኝት አደርገዋል ፡፡ በቅኝቱም የስራ ሃላፊዎቹ የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመከላከል ያግዛል የተባለው የዚህን የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሸከርካሪዎች ተርሚናል ግንባታን አጠቃላይ እንቅስቃሴ እና ቀሪ ስራዎችን ተመልክተዋል፡፡ በዚህም በእስካሁኑ የተሸከርካሪዎች ማቆሚያ (parking) ግንባታ መጠናቀቁንና ሌሎች የአገልግሎት መስጫ መዕከላት የሆኑትን እንደ የጤና ምርመራና ህክምና ማእከል እንዲሁም የማረፊያና መመገቢያ ቦታዎች ግንባታ በቀጣይ እንደሚከናወን ለልኡካኑ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡ የዚህ የጭነት ተሽከርካሪዎች ተርሚናል ግንባታ የሚካሄደው በኢትዮጵያና በጅቡቲ ድንበር አቅራቢያ በሶማሌ ክልል ደወሌ ላይ ባለ 9ሺ ሄክታር መሬት ላይ ነው ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሆነው የድሬደዋ ዲስትሪክት የዚህን ድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሸከርካሪዎች ተርሚናል ግንባታ ስራ እያካሄደው ይገኛል፡፡ የተርሚናሉ መገንባት የአገሪቷ ዋነኛ የገቢ ወጪ ንግድ መስመር የሆነውና ከፍተኛ ተሽከርካሪ የሚያስተናግደውን የድሬደዋ ደወሌን መስመር ከኮቪድ- 19 ወረርሺኝ በመከላከል ቀልጣፋ እና ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ታሳቢ ያደረገ ነው ። በዚህም መስመሩን የሚጠቀሙ የድንበር ተሻጋሪ ሹፌሮች ከዚህ ቀደም የሚገጥማቸውን እንግልት እንደሚያስቀረው ይጠበቃል ፡፡ በተጨማሪም ለወረርሽኙ ያላቸውን ተጋላጭነት ከመቀነስ አንጻር ከፍተኛ ድርሻ ይኖረዋል ። በመሆኑም ድንበር ተሻጋሪ ሹፌሮች ጉዞ ከመጀመራቸው በፊት በሁለቱ ሀገራት ክልል ውስጥ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ እንዲሁም ድንበር ላይ የሚወስዷቸው ጥንቃቄዎች ከፍ በማድረግ ለወረርሽኙ ያላቸውን ተጋላጭነት ለመቀነስ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ይጠበቃል፡፡

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ሰራተኞች አረንጓዴ አሻራ የማሰረፍ መርሃ ግብራቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል። በዛሬው እለትም በእንጦጦ ፖርክ የኢ .መ .ባ ዋናው ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘን ጨምሮ
+4
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ሰራተኞች አረንጓዴ አሻራ የማሰረፍ መርሃ ግብራቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል። በዛሬው እለትም በእንጦጦ ፖርክ የኢ .መ .ባ ዋናው ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘን ጨምሮ የባለስልጣኑ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና መላው የተቋሙ ሰራተኞች በችግኝ ተከላው ላይ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ በዚሁ የአረንጓዴ አሻራ የማሳረፍ የችግኝ ተከላ መርሀግብር ላይ ከ3 ሺ በላይ አገር በቀል ችግኞች በስፍራው ተክለዋል ፡፡ ባለስጣኑ መ/ቤት በተያዘው አመት 2 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል አቅዶ ለተግባራዊነቱ በሰፊው እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ በዚህም በተቋም ደረጃ ሰኔ 15 ቀን 2012 ዓ.ም የባለስልጣኑ ከፍተኛ የስራ ህላፊዎች በተገኙበት በጉለሌ የእጽዋት ማእከል 500 አገር በቀል ችግኞችን በመትከል ነበር በይፋ የተጀመረው። እስካሁንም በሁሉም በተቋሙ ስር ባሉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ፣ ማስልጠኛ ማእከላት እና በሚያስገነባቸው የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይም የችግኝ መትከል ተግባሩ በሰፊው እተካሄደ ነው፡፡ በዚህም እቅዱን ለማሳካት በቀሪ ጊዜያት መርሃ ግብሩ ተጠናክሮ ይቀጥላል ። ባለፈው አመት የባለስልጣን መ/ቤቱ ከ 1 ነጥብ 5 ሚልዮን በላይ ችግኞች የተከሉ ሲሆን አብዛኛዎቹ በተደረገላቸው እንክብካቤ መጽደቅ ችለዋል፡፡ ተቋሙ የተከላቸው ችግኞች እስኪጸድቁ ድረስ መላ ሰራተኞችን በማሳተፍ አስፈላጊው እንክብካቤ በዘላቂነት ለማድረግ እቅድ ተይዞ እየተተገበረ ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣንን ተቋማዊ የለውጥ እንቅስቃሴን ዛሬ ጎበኙ። ተቋሙ ያካሄዳቸውን የአሰራር ለውጦች፣ የመስሪያ ቦታን ምቹ ማድረግ፣ ለመንገድ ግንባታ መ
+3
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣንን ተቋማዊ የለውጥ እንቅስቃሴን ዛሬ ጎበኙ። ተቋሙ ያካሄዳቸውን የአሰራር ለውጦች፣ የመስሪያ ቦታን ምቹ ማድረግ፣ ለመንገድ ግንባታ መሰናክል የነበሩ የአሰራርና የማንዋል ዝርዝር ለውጦችን ማካሄዱን በተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ ገለጻ ተደርጎላቸዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የተጓዘበትን የ70አመታትን ታሪክ የሚያስቃኝ ቋሚ ኤግዚቢሽንንም የሃይማኖት አባቶቹ ጎብኘተዋል። በተለይም ባለፋት ሁለት አመታት መሰረታዊ ለውጥ መካሄዱን ተከትሎ በመንገድ ግንባታ ዘርፍ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮች እየተቃለሉ መምጣታቸውን አንስተዋል። በቀጣይም መንግስት ለዘርፋ የመደበው ግዙፍ በጀት ለመንገድ ግንባታው በአግባቡ እውን እንዲሆን የሃይማኖት አባቶች የሃገሪቱን ልማት ይበልጥ እንዲደግፋ ዋና ዳሬክተሩ ጠይቀዋል። በጉብኝቱ የተሳተፋ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አባላት በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የወሰዳቸውን ማሻሻያዎች አድንቀዋል ሁለተናዊ ለውጡ ለሌሎችም ተቋማት አርአያ እንደሚሆን አብራርተዋል። በመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የሚታዩ በተለይም ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት የበኩላቸውን ሃላፊነት እንደሚወጡም አረጋግጠዋል።

ከ19.9 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 12 መንገዶችን ለመገንባት የሚያስችል ውል ስምምነት ፊርማ ተካሄደ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ከ 19.9 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 12 መንገዶችን በአስፋልት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል ውል ስምምነት ፊርማ ከተቋራጮች ጋር አካሄደ ፡፡ አስራ ሁለቱ የሚፈረሙት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች በደምሩ 825.23 ኪ.ሜ እርዝማኔ ያላቸው ሲሆን ለግንባታቸው የሚወጣው ወጪ የሚሸፈነው የአስሩ በኢትዮጵያ መንግስት ፣ የሁለቱ ደግሞ ከአለም ባንክ በተገኘ ብድር ነው፡፡ የውል ስምምነት ከፈጸሙት የስራ ተቋራጮች መካከል ስድስቱ አገር በቀል የስራ ተቋራጮች ሲሆኑ የተቀሩት አራቱ አለም አቀፍ የውጭ ስራ ተቋራጭ ድርጅቶች ናቸው፡፡ መንገዶቹን ገንብቶ ለማጠናቀቅ እንደመንገዶቹ ሁኔታ ከአንድ አመት ከአምስት ወር ጀምሮ እስከ አራት አመት ጊዜ ተሰጥቷቸዋል፡፡ የግንባታ ፕሮጀክቶቹ የመንገድ ግራና ቀኝ ትከሻን ጨምሮ በገጠር በአማካይ 8 - 10 ሜትር ስፋት ሲኖረው በከተማ ተጨማሪ ስፋት አንዲኖረው ተደርጎ የሚገነባ ይሆናል ፡፡ በተጨማሪም ግንባታው የአነስተኛ፣ ከፍተኛ ፍሳሽ ማስተላለፊያ ቱቦዎች ፣ ችና ድልድዮችንም አካቷል፡፡ የመንገዶቹ ግንባታ ሲጠናቀቅ ከዚህ በፊት በአካባቢው የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ የአካባቢው ህብረተሰብ በቀላሉ ወደ ፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ ከዚህም ባለፈ ክልሎችን ከክልሎች እንዲሁም በየክልሎቹ ውስጥ የሚገኙ ዞኖችንና ወረዳዎችን እርስ በእርስ ያስተሳስራል፡፡ ከተፈረሙት መንገዶች መካከልም ወደ ጎረቤት አገር የሚያዘልቁ መንገዶችም በመኖራቸው አገራዊ ፋይዳቸው ላቅ ያለ ያደርገዋል ፡፡ የተሽከርካሪዎችን የጉዞ ጊዜና ወጪን በከፍተኛ ደረጃ የሚቀንስ ከመሆኑም በተጨማሪ የምርትና የሸቀጥ ልውውጥ ያለምንም እንግልት በቀላሉ እንዲከናወን ከማድረግ አኳያ የተፈረሙት መንገዶች ጠቀሜታ ዘርፈ ብዙ ያደርገዋል፡፡ እነዚህ መንገዶች በአገሪቱ ካለው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲሁም መንግሥት ከያዘው የድህነት ቅነሳ ስትራቴጂ አንጻር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ ይታመናል፡፡ ስለሆነም የመንገድ ኘሮጀክቶቹ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ እንዲጠናቀቁ በአካባቢው የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በተለይም ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ ለሚነሱ ጉዳዮች ከፍተኛ ትብብር እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ያሳስባል፡፡

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን 2 ሚልየን ችግኞችን ለመትከል የያዘውን እቅድ እውን ለማድረግ ዛሬ መርሃ ግብሩን ጀምሯል። በጉለሌ የዕጽዋት ፓርክ በተካሄደው የችግኝ ተከላ የማስጀመር መርሃ ግብር ላይ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ፣ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች ፣ ዳይሬክተሮችና ቡድን መሪዎች ታደመዋል። በዚህም ከ500 በላይ አገር በቀል ችግኞችን የስራ ሃላፊዎቹ በስፍራው ተክለዋል። በፕሮግራሙ ላይ የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ በሃገር አቀፍ ደረጃ የአረንጓዴ አሻራን ለማሳረፍ የተያዘውን ሀገራዊ ሃላፊነት ለመወጣት የሁለት ሚሊየን የችግኝ ተከላ ፕሮጀክት በመቅረጽ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ከዋናው መስሪያቤት የማኔጅመንት አባላት በተጨማሪም ዛሬ በሁሉም ቅርንጫፍችና በተወሰኑ ፕሮጀክቶች ላይ 3መቶ ሺህ ሃገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል። በቀጣይም እቅዱን ለማሳካት በተቋሙ ባሉ ሁሉም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እና ማስልጠኛ ማዕከላት መላው ሰራተኛን በማሳተፍ የችግኝ ተካላ መርሃ ግብሩ ቀጣይነት እንዳለው ተናግረዋል። ባለፈው አመት ባለስልጣን መ/ቤቱ ከ 1 ነጥብ 5 ሚልዮን በላይ ችግኞች መተከላቸውን ያወሱት ዋና ዳይሬክተሩ አብዛኛዎቹ በተደረገላቸው እንክብካቤ መጽደቃቸውን ገልጸዋል። አሁንም የተከልናቸውን ችግኞች እስኪጸድቁ ድረስ መላ የተቋሙን ሰራተኞች በማሳተፍ አስፈላጊው እንክብካቤ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። ሀገራችን በያዝነው አመት በአረንጓዴ አሻራ ብሔራዊ መርሃ ግብር 5 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል እቅድ ትይዞ እየተተገበረ ይገኛል ።

ከአሳይታ እስከ ጅቡቲ ድንበር የሚዘልቀው የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ እየተካሄደ ነው፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያን እና ጅቡቲን በአጭር ርቀት የሚያገናኘው የአሳይታ-አፋምቦ መጋጠሚያ-ጅቡቲ ድንበር የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ውስጥ የሚገኘውን 48 ኪ.ሜ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በማካሄድ ላይ የሚገኘው ሀገር በቀሉ አሰር ኮንስትራክሽን ድርጅት ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን የሚያካሂደው ደግሞ ይዲዲያ ኮንሰልቲንግ የተባለ አገር በቀል ድርጅት ነው፡፡ ለመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ የሚውለው 1.5 ቢሊዮን ብር የግንባታ ወጪም በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን መንገዱ በሚጠበቀው ፍጥነትና የጥራት ደረጃ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ የመንገዱ ግንባታ የተጀመረው ነሃሴ 20 ቀን 2011 ዓ.ም ሲሆን ፣ በተሰጠው የ 3 (ሶስት) ዓመት የኮንትራት ውል መሰረት ነሃሴ 19 ቀን 2014 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡ ከአሳይታ እስከ ጅቡቲ ድንበር የሚዘልቀው ይህ መንገድ ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት የመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታ ያልነበረው አዲስ ፕሮጀክት ነው፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የአሳይታ እና የአፋምቦ ከተሞችን በቅርብ ርቀት ያስተሳስራል፡፡ ከዚህ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በተጨማሪ ከታጁራ ወደብ ጋር የሚያገናኘው የዲቾቶ-ጋላፊ መንገድ ግንባታም በመካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ እነዚህ ሁለት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ በአሁኑ ወቅት በሚሌ-ጋላፊ-ጅቡቲ ነባር መንገድ ላይ እየደረሰ ያለውን የትራፊክ ጫና ይቀንሳሉ ተብሎ ይታመናል፡፡ ይህ አካባቢ በከፍተኛ የመስኖ ልማት ይታወቃል፤ በመሆኑም የመንገዱ መገንባት ለነዋሪዎቹ ከሚያስገኛቸው ሌሎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታዎች ባሻገር ይህን ምርት ካለምንም ውጣ ውረድ ወደ መሐል ገበያ ለማጓጓዝ ያስችላል፡፡

ከ1 ነጥብ2 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኘው የመልካሳ - ሶደሬ - ኑርኤራ - መተሃራ መገንጠያ መንገድ ፕሮጀክት በዋነኛነት በወሰን ማስከበር ችግሮች ምክንያት መዘግየቱ ተገለጸ። በዛሬው ዕለት የመንገድ ፕሮጀክቱ የሚገኝበት ደረጃን እና እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የመስክ ቅኝት የትራንስፖርት ሚኒስቴር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂ. ሀብታሙ ተገኝ እንዲሁም የባለስልጣኑ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት ተካሂዷል። በመስክ ቅኝቱም ወቅት በተደረገ ውይይት የመንገድ ፕሮጀክቱ ግንባታ በተያዘለት የጊዜ ዕቅድ መሰረት ላለመከናወኑ በዋነኛነት በመንገድ ግንባታ ውስጥ ያሉ ቤቶችና የኤሌትሪክ መስመሮች ያለመነሳት ከፍተኛ ችግር መፍጠሩ ተገልጿል። ችግሩን ከመፍታት አኳያ በስካሁን ከሚመለከታቸው የመስተዳደር አካላት እና የመንግስት መስሪያ ቤቶች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች የተካሄዱ ቢሆንም በሚፈለገው ደረጃ ችግሮቹ ሊፈቱ አልተቻለም። ይህም ለመንገድ ፕሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ያለመጠናቀቅ ዋነኛ መንስኤ ሆኖ ተጠቅሷል። በወቅቱ የተገኙት የባለስልጣኑ መስሪያ ቤት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂ. ሀብታሙ ተገኝም መንገዱ ካለው ኢኮኖሚያዊና ማሃበራዊ ጠቀሜታ አንጻር በመንግስት ከፍተኛ መዋለ ንዋይ የመደበለት ፕሮጀክት መሆኑን አውስተዋል። የመንገዱ መገንባት በአካባቢው ሰፊ ኢንቨስትሜንትን ተደራሽ እንዲሆን እና ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ካለው የላቀ አስተዋጽዖ አንጻር በውይይቱ ላይ የተነሱትን ችግሮች በመፍታት ትኩረት አግኝቶ እንዲሰራ አሳስበዋል። በዚህ ውይይት የተገኙት የትራንስፖርት ሚኒስቴር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌም ለመንገድ ፕሮጀክቱ መዘግየት እየተሰጡ ያሉ ምክንያቶች መቋጫ መፍትሄ ሊያገኙ እንደሚገባ ተናግረዋል። አክለውም መንገዱ በተያዘለት የጊዜ ገደብ መጠናቀቅ ለአካባቢው ህብረተሰብ ብሎም ለመንግስት የሚኖረው ጠቀሜታ ከፍተኛ ከመሆኑ አንጻር የሚመለከታቸው የመስተዳድር አካላት ፣ የፌደራል አካላት የስራ ተቋራጩም ችግሮቹን ለመፍታት በጋራ መስራት እንደሚገባቸው በአጽኖት ገልጸዋል። ይህ 94.ኪ. ሜትር ርዝመት ያለው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በስካሁኑ የተሰራው 19% ነው። ሙሉ ወጪው በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈነው የመልካሳ - ሶደሬ - ኑርኤራ - መተሃራ መገንጠያ መንገድ ግንባታን እያከናወነ የሚገኘው ሀገር በቀሉ የንኮማንድ የስራ ተቋራጭ ነው። የማማከርና ቋጥጥር ስራውን የሚያካሂደው ECDSWC ነው። የዚሁ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የጎን ስፋት በወረዳ 19 ሜትር በቀበሌ 12 ሜትር ሲሆን በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 11 ሜትር ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ግንባታ ዘጠኝ ድልድዮችን ያካተተ ሲሆን የተለያዩ ፉካዎችና ከልቨርቶችን የሚያካትት ይሆናል። በተመሳሳይ ከቦሌ መገንጠያ -ወተርዲኖ ሆርቲ ካልቸር እና የቦሌ -አቦምሳ የመንገድ ፕሮጀክት የግንባታ ሂደት የተመለከተ ውይይት ተካሂዷል ። ይህ 30.5 ኪ.ሜትር የሚሸፍነው የመንገድ ፕሮጀክት ከ359 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እሸቱ ለማ በተባለ ሀገር በቀል የስራ ተቋራጭ ግንባታውn እየተካሄደ ይገኛል። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት በሁለት አመት ስድስት ወር ለማጠናቀቅ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም በስካሁን አፈጻጸም 33% መሆኑ ተገልጻል። ለዚህም በዋነኛነት የስራ ተቋራጩ አፈጻጸም ጋር በተያያዘ እና እንዲሁም እየታዩ ያሉ የወሰን ማስከበር ችግሮችን በአስቸኳይ ተፈተው የግንባታ ሂደቱ እንዲፋጠን የስራ ሃላፊዎቹ አሳስበዋል።