uk
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Відкрити в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 13 373 підписників, посідаючи 1 753 місце в категорії Транспорт та 2 530 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 13 373 підписників.

За останніми даними від 20 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 129, а за останні 24 години на 8, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 38.47%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 15.24% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 143 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 037 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 11.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 22 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Транспорт.

13 373
Підписники
+824 години
+697 днів
+12930 день
Архів дописів
Notice of Invitation for Bids Package VIII

ከ1.8 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተንታ መገንጠያ- ወገልጤና - ኩርባ መንገድ ግንባታ በይፋ ተጀመረ ፡፡ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሰሜን ወሎ ዞን ውስጥ የሚገኘው የኩታበር - ተንታ መገ
+4
ከ1.8 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተንታ መገንጠያ- ወገልጤና - ኩርባ መንገድ ግንባታ በይፋ ተጀመረ ፡፡ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሰሜን ወሎ ዞን ውስጥ የሚገኘው የኩታበር - ተንታ መገንጠያ መንገድ ፕሮጀክት የጅማሮ መርሀግብር ላይ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተመሰገን ጥሩነህ፣ የትራንስፖርት ሚኒስተር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ፣ አቶ ጃንጥራር አባይ የጠቅላይ ሚንስትሩ የመሠረተ ልማት አማካሪ ሚንስትር፤የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢነጂነር ሃብታሙ ተገኘ ፣ የፌደራልና ክልል ባለሥልጣናት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል፡፡ የፕሮጀክቱ ስም የተንታ - ወገልጤና - ኩርባ መገንጠያ የመንገዱ ርዝመት 79.24 ኪ.ሜትር የመንገድ የጎን ስፋት በከተማ 19 ሜትር እና በገጠር 10 ሜትር የመንገዱ ደረጃ አስፋልት ኮንከሪት ግንባታዉን አንዲያከናዉን ጨረታዉን ያሸነፈዉ ተቋራጭ ሔቢ ኮንስትራክሽን የተባለ የሥራ ተቋራጭ ድርጅት አማካሪ ድርጅት ኢንጅነር ዘውዴ እስክንድር እና ዋይ ኤል ኤስ ኢንጅነሪንግ ፒ.ኤ.ል.ሲ ለዚህ መንገድ የሚውለው የግንባታ ወጪ / በብር/ 1,873,489,476.53 (አንድ ቢሊየን ስምንት መቶ ሰባ ሶስት ሚሊዮን አራት መቶ ሰማንያ ዘጠኝ ሺህ አራት መቶ ሰባ ስድስት ብር ከ ሃምሳ ሶስት ሣንቲም) መንገዱ የሚጠናቀቅበት ጊዜ 3 / ሶስት/ ዓመት የግንባታዉን ወጪ የሚሽፈነዉ አካል በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል። https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/3680739071967056

ከአዲስ አበባ በአራት አቅጣጫ ፈጣን መንገዶችን ሊገነባ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ! https://www.facebook.com/1935015763378489/posts/2523807864
ከአዲስ አበባ በአራት አቅጣጫ ፈጣን መንገዶችን ሊገነባ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ! https://www.facebook.com/1935015763378489/posts/2523807864499273/?app=fbl

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የችግኝ መንከባከብ እንቅስቃሴውን አጠናክሮ ቀጥሏል። “ተክለን እንከባከባለን” ተብሎ ቃል በተገባው መሰረት በዛሬው ዕለት በዋናው መስሪያ ቤት የሚገኙት የኢትዮጵያ መንገ
+2
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የችግኝ መንከባከብ እንቅስቃሴውን አጠናክሮ ቀጥሏል። “ተክለን እንከባከባለን” ተብሎ ቃል በተገባው መሰረት በዛሬው ዕለት በዋናው መስሪያ ቤት የሚገኙት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ሰራተኞች ለችግኝ እንክብካቤ የሚያስፈልጉትን መሳሪያዎች በመያዝ በነቂስ ወጥተዋል። የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሰራተኞች በተነሳሽነት የመጀመሪያው ዙር የችግኝ ተከላ መረሃ ግብር በተካሄደበት አንዱ ስፍራ በሆነው የጉራራ ተራራ ቦታው ድረስ በመሄድ ችግኞቹ ያሉበትን ደረጃ በማየት ውሃ የማጠጣትና የመኮትኮት ስራዎችን አከናውነዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በመላው ሀገሪቷ ላይ ከሚገነባቸው መንገዶች ጎን ለጎን የአረንጓዴ ልማትን ለማስቀጠል የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ የኢመባ አካባቢ፣ማህበራዊና የስራ ቦታ ደህንነት ዳይሬክተር ኢንጂነር ገነት አለማየሁ አሳስበዋል። አያይዘውም ይህ ችግኞችን የመንከባከብ መርሃ ግብር ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባና የተተከሉትን ችግኞች በመንከባከብ ለሚመጣው ትውልድ አረንጓዴ ኢትዮጵያን ለማስረከብ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በአፅእኖት እንደሚሰራ አክለው ተናግረዋል። ችግኞቹ የተተከለበት ስፍራ ጥብቅ ደን ቢሆንም ሰዎች የሚተላለፉበትና እንስሶች የሚውሉበት ቦታ በመሆኑ በቀጣይ ዘላቂነት ባለው መንገድ ለመንገባከብ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸውልናል። https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/3677792262261737

ተቋርጦ የነበረው የነቀምት-ቡሬ የመንገድ ግንባታ ስራን መልሶ ለማሰጀመር እየተሰራ ነው። የግንባታ ስራቸው የሚጀመሩት ሁለት ኮንትራቶች ነቀምት- እንዶዴ (ኮንትራት አንድ) እና አጋምሳ-ቡሬ (ኮንትራት
+1
ተቋርጦ የነበረው የነቀምት-ቡሬ የመንገድ ግንባታ ስራን መልሶ ለማሰጀመር እየተሰራ ነው። የግንባታ ስራቸው የሚጀመሩት ሁለት ኮንትራቶች ነቀምት- እንዶዴ (ኮንትራት አንድ) እና አጋምሳ-ቡሬ (ኮንትራት ሶስት) ናቸው።107. 7 ኪ.ሜትር የሚረዝሙትን ሁለት ኮንትራቶች የግንባታ ስራ በቶሎ ለማስጀመር በአሁኑ ወቅት ጨረታ መውጣቱን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ገልጿል። በወጣው ጨረታ መሰረት አስፈላጊው የቴክንክና የፋናንሻል ግምገማ ተካሂዶ የስራ ተቋራጩ እንደሚታውቅና በቀጥይ ወደ ግንባታ እደሚሽጋገር ይጠበቃል። ቀድም ብሎ ሁለቱን የመንገድ የግንባታ ኮንትራቶችን የውል ስምምነት ጨረታ አሸነፎ ግንበታውን የጀመረው ኤልሳሜክስ የተባለው የህንድ የስራ ተቋራጭ በገባው ውል መሰረት ስራውን ለማከናውን ባለመቻሉ ውሉ እንዲቋራጥ መደረጉ ይታወሳል። ይህን ተከትሎም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ከስራ መቋረጥ ጋር ተያይዞ ያለውን ወጪና ኪሳራ በኮንትራት ውሉ መሰረት ካሳ የሚገኝበትን ውሳኔ ያገኘ ሲሆን ይህንንም ውሳኔ በማስፈጸም ሂደት ላይ ይገኛል። የኦሮሚያና የአማራ ክልልን የሚያገናኘውና 258 ኪ.ሜትር ርዝመት የሚሸፍነው የነቀምት-ቡሬ መንገድ ፕሮጀክት ለአሰራር ምቹ እንዲሆን ሲባል በሶስት ምዕራፍ ተከፍለው ነቀምት- እንዶዴ፣ እንዶዴ -አጋምሳና ኣጋምሳ-ቡሬ ተብለው ሲከናወኑ ቆይተዋል። 87.65 ኪ.ሜትር የሚሸፍነውና ኮንትራት ሁለት አንዶዴ -አጋምንሳን የመንገድ ፕሮጀክት በብር 1.75 ቢልየን በሆነ ወጪ ጨረታውን አሽንፎ እያከናወነ የሚገኘው ጂምሲ /GMC/ የተባለ የስራ ተቋራጭ ነው። ይህን የመንገድ ፕሮጀክት በሶስት አመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ የጊዜ ገደብ ተይዞለታል። https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/3673995282641435

ጃፓን ለኢትዮጵያ የመንገድ ግንባታ የሚውል የ89 ሚልዮን ዶላር ብድር ፈቀደች ። የተገኘው ብድር የጅማ - ጭዳ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታን ለማከናወን ጥቅም ላይ ይውላል። ዛሬው እለት በኢት
+2
ጃፓን ለኢትዮጵያ የመንገድ ግንባታ የሚውል የ89 ሚልዮን ዶላር ብድር ፈቀደች ። የተገኘው ብድር የጅማ - ጭዳ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታን ለማከናወን ጥቅም ላይ ይውላል። ዛሬው እለት በኢትዮጵያ የጃፓን አማባሳደር ማትሱንጋ ዳኡሲኬ የገንዘብ ሚንስትር ዴኤታው አቶ አድማሱ ነበበ፤ የብደር ስምምነቱን ተፈራረመዋል። መንግስት ያቀዳቸውን የመንገድ ልማት ፕሮጀክቶች እውን ለማድረግ የተገኘው ብድር የላቃ አስተዋጾ እንዳለው ሚኒስትር ድኤታው ተናገረዋል። አማባሳደር ማትሱንጋ ዳኡሲኬ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ጃፓን በርካታ የልማት ስራዎችን በትብብር እያካሄዱ መሆናቸውን ጠቅሰው ፤ይህው የዛሬው ስምምነትም ለቀጣይነቱ ማሳያ ነው ብለዋል። በቅርቡ የአፍሪካ ጃፓን የጋራ የልማት ትብብር የጋራ ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አበይ አህመድ ጃፓን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍና የብድር ማዕቀፍ እንድታስፋፋ መጠየቀቸውን ተከትሎ የተሰጠው አንዱ ግብረመልስ መሆኑንም አምባሳደሩ ተናግረዋል። በመርሃ ግበሩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሰልጣን ዋና ዳሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኝ፤ በበኩላቸው የተገኘው ብድር ፕሮጀክቱን በፍጥነት ለማስጀመር ትልቅ የምስራች ነው ብለዋል። አካባቢው የወጪ ንግድ ግብአት በተለይም ቡና እና የቅመማ ቅምም ምርቶችን በስፋት ከሚመረተባቸው አካባቢዎች አንዱ በመሆኑ የመንገዱ እውን መሆን ከፍተኛ ኢኮኖሚዌና ማህበራዌ ጠቀሜታዎችን ያጎናጽፋል። የተገኘው ብድር በመንገድ መሰረተ ልማት መጓዳል ለትራንስፖርትና ለሌሎች ማህበራዊ ችግሮች ሲዳረግ የነበረውን የአካባቢውን ህዝብ ዕፎይታን የሚያሰገኝም እንደሆነ አበራረተዋል። አርሶ አደሩ ያመርተዉን ምርት የተሳለጠ የትርንስፖርት አማርጭ በመጠቀም በቀላሉ ወደ ገብያ በማቅረብ ተጠቃሚ ለማድርግም ይረዳል።

በድንገተኛ ናዳ ምክንያት የተዘጋው የጣርማበር መንገድ ለትራፊክ ክፍት ሆነ። እንደሚታወቀው ጣርማበር አካባቢ በጣለው ዝናብ የመሬት ናዳ ተከስቶ መንገዱን መዝጋቱና ለመክፈት ጥረት እየተደረገ እንደሆነ
በድንገተኛ ናዳ ምክንያት የተዘጋው የጣርማበር መንገድ ለትራፊክ ክፍት ሆነ። እንደሚታወቀው ጣርማበር አካባቢ በጣለው ዝናብ የመሬት ናዳ ተከስቶ መንገዱን መዝጋቱና ለመክፈት ጥረት እየተደረገ እንደሆነ መግለጻችን ይታወሳል። በዚህም ሳብያ ትራንስፖርቱ ተቋርጦ የነበረ ሲሆን በአሁን ሰአት መንገዱ በተደረገለት ማስተካከያ መደበኛ የትራንስፖርት አገልግሎት መጀመሩን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ይገልጻል። በዚሁ አጋጣሚ አሽከርካሪዎችና የመንገዱ ተጠቃሚዎች መንገዱ ክፍት እስኪሆን ላሳዩት ትእግስት ምስጋናውን ያቀርባል።

በድንገተኛ ናዳ ምክንያት የተዘጋውን የጣርማበር መንገድ ለትራፊክ ክፍት ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ ነው። በአካባቢው በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ሳብያ ጣርማበር አካባቢ የመሬት ናዳ ተከስቶ መንገዱን በመዝ
በድንገተኛ ናዳ ምክንያት የተዘጋውን የጣርማበር መንገድ ለትራፊክ ክፍት ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ ነው። በአካባቢው በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ሳብያ ጣርማበር አካባቢ የመሬት ናዳ ተከስቶ መንገዱን በመዝጋቱ ትራንስፖርቱ ተቋርጧል። በአሁን ሰአት የተዘጋውን መንገድ ለመክፈት የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ቦታው ላይ ማሽኖችን አሰማርቶ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል። ከሁለት ሰአታት በኋላም የተዘጋውን መንገድ ክፍት እንደሚደረግና መደበኛ የትራንስፖርቱ እንደሚጀመር የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ይገልጻል። አሽከርካሪዎችም መንገዱ እስኪከፈት በትእግስት እንዲጠባበቁ የባለስልጣኑ መ/ቤት ትብብራችሁን ይጠይቃል።

ምርጥ መንገዶች ለኢትዮጵያ ብልጽግና Best Roads for Prosperous Ethiopia
ምርጥ መንገዶች ለኢትዮጵያ ብልጽግና Best Roads for Prosperous Ethiopia

የጋሸና - ብልባላ -ሰቆጣ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በያዝነው በጀት አመት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡ በሁለት ኮንትራክተሮች ች ተከፍሎ ግንባታው እየተካሄደ የሚገኘውን
+3
የጋሸና - ብልባላ -ሰቆጣ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በያዝነው በጀት አመት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡ በሁለት ኮንትራክተሮች ች ተከፍሎ ግንባታው እየተካሄደ የሚገኘውን የጋሸና- ብልባላ - ሰቆጣ 204.8 ኪ.ሜ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታን ሰሞኑን ተቋማችን የስራ ቅኝት አካሂዷል ። ይህ መንገድ ከዚህ ቀደም በአስፋልት ደረጃ ግንባታው ሲካሄድ የነበረ ሲሆን ፣ በአካባቢው ካለው የቱሪስት ፍሰት እና የኢኮኖሚያዊ አዋጭነት አንፃር ተገምግሞ ወደ አስፍልት ኮንክሪት እንዲያድግ ተደርጓል፡፡ እንዲሁም ታሪካዊውን የላሊበላ ውቅር አቢያተ ክርስቲያናትን የመንገዱ መተላላፊያ ከረዥም ጊዜ አኳያ ተጽህኖ እንዳያደረስበት በማሰብ አማራጭ የዲዛይን ለውጥ በማድረግ የግንበታ ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል በዚህ የመንግስት ውሳኔ እና የተቋማችን ያላሰለስ ጥረት የአካባቢው ነዋሪ ከፍተኛ መስጋና ማቅረቡ ይታወሳል። የዲዛይን ስራውን ዳግም መከለስ እንዲሁም የደረጃ ማሰደጉን ሂደት እና ውሳኔ ተከትሎ ተጨማሪ የጊዜ ፍጆታ እንዲጠይቅ ተጨባጭ ምክንያት ሆኗል ። ለሁለቱም መንገድ ፕሮጀክቶች የሚውለውን አጠቃላይ ከ3ንጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በኢትዮጵያ መንግሥት ይሸፈናል፡፡ https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/3643620359012261

ራዕይ፦ ዓለማቀፋዊ ብቃት እና ምርጥ መንገዶች ለበለጸገች ኢትዮጵያ በ2022 ተልዕኮ፦ በተቋማዊ ብቃት እና በውጤታማ የሀብት አጠቃቀም ዘላቂ መንገዶችን ማስፋፋት እና ማስተዳደር እሴት፦ ቅንነት ቤተሰባዊነት ያለማቋረጥ መማር ሠራዊት ዘላቂነት ልህቀት ፈጠራ

የአሰብ-ቡሬ መንገድ ግንባታ መጠናቀቁ ተሰማ! 71 ኪሎ ሜትር የሚረዝመውና ከኤርትራ አሰብ ወደብ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ቡሬ የሚያመጣው መንገድ ግንባታ መጠናቀቁ ተሰማ፡፡ የኤርትራ ፕሬስ እንደጻፈው በ
የአሰብ-ቡሬ መንገድ ግንባታ መጠናቀቁ ተሰማ! 71 ኪሎ ሜትር የሚረዝመውና ከኤርትራ አሰብ ወደብ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ቡሬ የሚያመጣው መንገድ ግንባታ መጠናቀቁ ተሰማ፡፡ የኤርትራ ፕሬስ እንደጻፈው በሁለቱ አገራት ፀብ ምክንያት ለ20 ዓመታት ከአገልግሎት ውጭ የኖረውን የአሰብ-ቡሬ መንገድ ወደሥራ ለመመለስ የእድሳት ሥራው ተጠናቋል፡፡ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፕሬዘዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በነበራቸው ውይይት ኢትዮጵያ የአሰብን ወደብ መጠቀም እንደምትፈልግ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ ለዓመታት ያለአገልግሎት በመቆየታቸው የፈራረሱትን መንገዶች ማደስና እንደአዲስ መስራት ማስፈለጉን ሁለቱ መሪዎች መተማመናቸው አይዘነጋም፡፡ በዚህም ሁሉቱም አገራት የቤት ስራቸውን ሲሰሩ ከርመዋል፡፡ ኤርትራም ከ1 ዓመት በኋላ ከአሰብ ወደ ቡሬ የሚያመጣትን መንገድ እንደ አዲስ ገንብታ ማጠናቀቋ ነው የተሰማው፡፡ ከአዲስ አበባ ኤርትራ 882 ኪሎ ሜትር መንገድ ሲኖር 71 ኪሎ ሜትሩ ብቻ በኤርትራ ግዛት ውስጥ ይገኛል፡፡ (EP - AhduTV)

👍👍👍

አደገኛው የሊማሊሞ መንገድ ታሪክ ሊሆን እየተቃረበ ነው፡፡ በተለያዩ ከያንያን እና ገጣሚያን ስለአደገኛነቱ ቅኔ የተቀኙለት የሊማሊሞ አደገኛ መንገድ ቅርስ እንዲሆን በማሰብ በምትኩ በሌላ አቅጣጫ ተለዋጭ የሊማሊሞ መንገድ ግንባታ ስራ ከወዲሁ ተጀመሯል፡፡ በአዲሱ ዲዛይን መሰረት ከደባርቅ እስከ ዛሪማ 68.62 ኪ.ሜ ርዝመት ኖሮት ዲዛይንን እና ግንባታን በጋራ ባካተተ መልኩ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የሚገነባ ይሆናል፡፡ የግንባታ ስራውን 2.ነጥብ 14 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እያካሄደ የሚገኝው ቤይጂንግ ኧርባን ኮንስትራክሽን ግሩፕ የተባለ የቻይናው አለም አቀፍ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ የማማከር ስራው ደግሞ በባንግላዲሹ ቢ ሲ ኤል ከአገር በቀሉ አይኮን ጋር በትብብር ያካሂዱታል፡፡ ተቋራጩ በጥር ወር 2011 ዓ.ም ነበር ግንባታውን የጀመረው ። በስካሁኑ የስራ እንቅስቃሴውም የዲዛይን፣ የአፈር ጠረጋ ድልዳሎ እና ሙሌት ስራዎች እያካሄደ ይገኛል፡፡ ግንባውም በ2015 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የመንገዱ የጎን ስፋት በዞን 31 ሜ ፣ በወረዳ 21 ሜ እና በገጠር 10 ሜትር ነው፡፡ ግንባታው የሶስት ትልልቅ ድልድዮች ፣ የውሃ መፋሰሻ ቱቦዎች እና ቦዮች ስራን ያካተተ ነው፡፡ ሊማሊሞ ገደላማ ፣ ጠመዝማዛ እና ለትራንስፖርት እጅግ አደገኛና ለአሽከርካሪም ፈተና ናቸው ተብለው ከሚታወቁ የሀገራችን አደገኛ መንገዶች መካካል ግንባር ቀደሙ ነው፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ መንገዶች በለስልጣን ከደባርቅ - ዛሪማ አዲስ መስመር መፈለግ አዲስ ዲዛይን መስራት እና የሊማሊሞ ተለዋጭ መንገድ መገንባት አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት የግንባታ ስራው ከወዲሁ እንዲጀመር አድርጓል፡ የመንገዱ መገንባት ከአዲስ አበባ -ጎንደር - ሽሬ አስመራ የሚዘልቀው የዋናው መንገድ አካል በመሆኑ ከደባርቅ - ዛሪማ ያለው የአስፋልት ንጣፍ ተቆርጦ ለአመታት የቆየውን መንገድ የተሟላ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ ነባሩ የሊማሊሞ መንገድም በቀጣይ የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ አካል እንደመሆኑ መጠን ይህንን ወጣገባ መንገድን ለሳይክል ጉዞ ለሚያደርጉ የሀገር ውስጥና የውጭ አገር ቱሪስቶች አይነተኛ መዳረሻ ቦታ ይሆናል ተበሎም ታቅዷል ፡፡ መንገዱ ተጠናቆ እውን ሲሆን ሰፊ የምርት ልውውጥን ከፍተኛ የትራንስፖርት መሳለጥን ከመፈጠሩም በላይ ለቱሪዘም ሴከተሩም የበኩሉን ሚና ያበረከታል ። ተጨማሪ እውነታዎች ሰለ ሊማሊሞ የመንገድ ገዕታ የዛሬ 82 አመት ገደማ ነበር ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረ ግዜ የሊማሊሞ መንገድን ጨምሮ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ሽሬ ድረስ የሚዘልቀው መንገድ በአስፋልት የተገነባው ፡፡ ሊማሊሞ የሚለው መጠርያ በጊዜው መንገዱን በመገንባት ላይ የነበረ ጣልያንያዊ የመንገድ ቀያሽ በስራ ላይ እያለ ገደሉ ውስጥ ገብቶ ሕይወቱ በማለፉ አሱን ለማስታወስ ተብሎ መንገዱን በርሱ እንደተጠራ ይነገራል፡፡ አስፋልት የነበረው መንገዱ ከአገልግሎት ብዛት እና ከእርጅና መጫጫን ጋር ተደማምሮ በሂደት የገጠር ጠጠር መንገድ መስሏል ፡፡ ከፍተኛ የአለት ናዳና የመደርመስ አደጋ መስመሩን በእጅጉ ጎድቶታል፡፡ አንድ አንድ ቦታ የመንገዱ የጎን ስፋት እየጠበበ ሄዶ እስከ 4 ሜትር በመድረሱ ሁለት ተሽከርካሪ በአንድ ግዜ ማስተናገድ አይችልም ፡፡ በዚህ ሁኔታ ላይ ደግሞ በተለይ በክረምት ወቅት የመነገዱ ተጠቃሚዎች በዙ ይሉለታል፡፡ መንገዱን ለማስፋት አካባቢው ጠባብና ገደላማ ከመሆኑ እንዲሁም ተደጋጋሚ የአፈር እና የድንጋይ (አለት)ናዳ ስለሚያጋጥም እንደ ዶዘር የመሰሉ የግንባታ ማሽነሪ እንኳንስ መንገዱን ለመስራት አይደለም ለማለፍ እንኳ ስለማያስቸግር የጥገና ስራውን በእጅጉ ፈታኝ አድርጎት ቆይቷል፡፡ አዲሱ የደባርቅ - ዛሪማ መንገድ ግንባታ ከነባሩ ሊማሊሞ መንገድ በስተግራ በኩል የሚሰራ መንገድ ሲሆን ፤ መንገዱ ከደባርቅ መሃል ከተማ አንስቶ የዘፈና፣ የቢጢቆ፣ የጫንቅ፣ የአደማራ ጊዮርጊስ፣ የአብረሃም፣ የአዳጋት፣ የቲራይና የማይጥምቀት አምበር ትናንሽ መንደሮችን አቋርጦ ዛሪማ ከተማ መግብያ አጠገብ ከምትገኘው ዛሪማ ወንዝ ጋር ሲደርስ ከዋናው መንገድ ጋር ይገናኛል፡፡ የሞት መንገድ የተሰኘው የሊማሊሞ መንገድ ከደባርቅም ሆነ ከዛሪማ ለመምጣትም ሆነ ለመመለስ ብቸኛው አማራጭ ነበር። አዲሱ ተለዋጭ መንገድ በሚጠናቀቅበት ጊዜ ግን ብዙ ቀበሌዎችን እና ትንንሽ የገጠር ቀበሌዎች ስለሚያገኛኝ ነዋሪነታቸውን ከወደ ቆላው ላደረጉ የአካባቢው ህዝቦች ድርብ ጥቅም ይዞ ይመጣል። በኢሳያስ መብራቱ

ተቋማዊ የስራ መናበብ እና የባለድርሻ አካላት የጋራ ቅንጅት በሴክተሩ የተቀመጠውን የመንገድ ልማት ግብ ለማሳካት መሰረት እየሆነ መምጣቱን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሰልጣን ዋና ዳሬክተር ኢንጂነር ሃብታ
+1
ተቋማዊ የስራ መናበብ እና የባለድርሻ አካላት የጋራ ቅንጅት በሴክተሩ የተቀመጠውን የመንገድ ልማት ግብ ለማሳካት መሰረት እየሆነ መምጣቱን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሰልጣን ዋና ዳሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተናገሩ ። https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/3600207273353570

Road Construction Projects Bid For Packge VI & VII

የስራ ማስታወቂያ
የስራ ማስታወቂያ