uk
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Відкрити в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 13 348 підписників, посідаючи 1 755 місце в категорії Транспорт та 2 537 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 13 348 підписників.

За останніми даними від 18 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 91, а за останні 24 години на 11, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 41.16%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 15.44% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 491 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 060 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 11.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 19 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Транспорт.

13 351
Підписники
+1124 години
+477 днів
+9130 день
Архів дописів
የጋምቤላ - አቦቦ - ፑኚዶ ዲዛይንና ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ አፈጻጸም ላይ ይገኛል ከፕሮጀክቱ ግንባታ75.72 በመቶ የሚሆነው ስራ የተገባደደ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ፡፡ 103 ኪ .ሜ የሚረዝመው ይህ መንገድ ቀድሞ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ እና አሁን በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ተሸሽሎ እየተሰራ ይገኛል ፡፡ በእስካሁኑ አፈጻጸም የጠረጋ ስራ ፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ፣የከተማ ውስጥ የእግረኛ መንገድ ፣የአፈር ቆረጣና ሙሌት ስራዎች ማከናወን ፣ የሰብ ቤዝ እና የቤዝ ኮርስ ንጣፍ ስራ ማከናወን ፣ የአስፋልት ማልበስ ሥራ እና የስትራክቸር ስራዎች ተከናውነዋል ፡፡ የመንገዱን ግንባታ ለማከናወን 1,310,919,269.00 ( አንድ ቢሊዮን ሶስት መቶ አስር ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ አስራ ዘጠኝ ሺህ ሁለት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ብር ) የጠየቀ ሲሆን በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው ፡፡ መንገዱ በገጠራማ ሥፍራዎች 10 ሜትር ፣ በቀበሌ ከተማዎች 12 ሜትር በወረዳ ከተማዎች ደግሞ 21.5 ሜትር ሆኖ ነው እየተገነባ ያለው ፡፡ ግንባታውን እያካሄደ የሚገኘው የስራ ተቋራጭ China Railway 21st Bureau Group Co. Ltd. Jv with Jiangxi Water & Hydropower Contractor Co. Ltd ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ Prominent Engineering Solutions እያከናወነው ይገኛል ፡፡ ፕሮጀክቱ በዋናነት የአኝዋክ ዞንን ፣ አቦቦ ና ጎግ ወረዳን ከጋምቤላ ከተማ ጋር ያስተሳስራል ፡፡ አካባቢው ከሚታወቅባቸው ምርቶች መሃከል የአሳ ምርት ፣ የበቆሎ ምርት ፣ የሰሊጥ ምርት እና የወተት ምርት ተጠቃሽ ናቸው ፡፡ በአካባቢው በርካታ የቱሪስት መስህቦችም ይገኛሉ ፤ ለአስረጂነት ያህል የጋምቤላ ክልል ብሔራዊ ፓርክ አረንጋዴ ጥቅጥቅ ደን እና በውስጡ የያዛቸው የተለያዩ የዱር እንስሳት ፣ የተለያዩ ሰው ሰራሽ ግድቦች እንዲሁም የአካባቢው ማህበረሰብ ባህልን ማንሳት ይቻላል ፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው ጦርነት ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ድልድዮች ተጠግነው አገልግሎት መስጠት ጀመሩ፡፡ በአማራ እና በትግራይ ክልሎች የሚገኙና በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት ደርሶባቸው የነበሩ ሶስት ድልድዮች ተገቢው ጥገና ተደርጎላቸው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል፡፡ እነዚህ ሶስት ድልድዮች በአስተዳደር መስሪያ ቤቱ የድልድይ እና ስትራክቸር ሥራዎች ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት ጥገና ተደርጎላቸው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል፡፡ ከመቀሌ በ122 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው እና ከመቀሌ ወደ ሀውዜን ለመጓዝ የሚያስችለው የ አደሀ ድልድይ በብረት ድልድይ ደረጃ ተሰርተው አገልግሎት መስጠት ከጀመሩ ድልድዮች መካከል አንዱ ነው፡፡ አጠቃላይ የድልድዩ ርዝመት 36.6 ሜትር ሲሆን ፣ በአሁኑ ወቅት ጥገናው ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡ ከዚህም ባሻገር ከአላማጣ በ10 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው እና አላማጣን ከመሆኒ ጋር ለማገናኘት የሚያስችለው የአደገረብ ድልድይ በብረት ድልድይ ደረጃ ተሰርቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡ አጠቃላይ የድልድዩ ርዝመትም 36.6 ሜትር ነው፡፡ በተጨማሪም ከሰቆጣ ከተማ በ33 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው እና የሰቆጣ ፣ ፃዳ እና ማይጨው አካባቢዎችን የሚያገናኘው 48 ሜትር ድልድይ በብረት ድልድይ ደረጃ ተጠግኖ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡ ከዚህ ቀደም በአፋር ፣ በአማራ እና በትግራይ ክልሎች ስድስት ድልድዮች ጥገና ተደርጎላቸው አገልግሎት መስጠት ስለመጀመራቸው መዘገባችን ይታወሳል። እነዚህ ድልድዮችም ከወልዲያ ወደ ቆቦ የሚያሻግረው 109.73 ሜትር የአልወሃ ድልድይ ፣ ከሚሌ-ጭፍራ-ወልዲያ የሚያሻግረው 48 ነጥብ 86 የሚረዝመው የጨረቲ ድልድይ ፣ ሁመራ እና ሽሬን የሚያገናኘው 27. 43 ሜትር የተከዜ 3 ድልድይ ፣ ከቆቦ የገጠር አካባቢዎችጋር የሚያገናኘው 48 ነጥብ 86 የጎቡ ድልድይ ፣ ከአምደወርቅ ወደ እብናት በሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኘው 48 ነጥብ 86 የተከዜ ድልድይ እና ከኮረም ወደ ሰቆጣ የሚወስደው 42 ነጥብ 67 ሜትር የጽላሬ ድልድይ ናቸው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሄልቬታስ ስዊስ ኢንተር ኮፐሬሽን ከተባለ መንግስታዊ ያልሆነ አለም አቀፍ ድርጅት ጋር ተፈራረመ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሄልቬታስ ስዊስ ኢንተር ኮፐሬሽን (HELVETAS Swiss Intercooperation) ከተባለ ዓለማቀፍ ድርጅት ጋር ተንጠልጣይ የእግረኛ መሻገሪያ ድልድዮችን በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ለመገንባት የሚያስችለውን የትብብር መግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡ በዚሁ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት አማካኝነት ባለፉት 20 ዓመታት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከ110 በላይ ተንጠልጣይ የእግረኛ መሻገሪያ ድልድዮች ተገንብተው ለማህበረሰቡ መሰረታዊ የተደራሽነት ችግርን በመቅረፍ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡ ተንጠልጣይ የእግረኛ መሻገሪያ ድልድዮች ፕሮግራም በመልክአ ምድራዊ አቀማመጣቸው ምክንያት ተነጥለው የሚገኙ አካባቢዎችን ፤ በአቅራቢያቸው ከሚገኙ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መዳረሻዎች ጋር በአቋራጭ በማገናኘት እና ዙሪያ ጥምጥም ጉዞዎችን ለማስቀረት የሚያስችል እና የማህበረሰቡን የመዳረሻ ችግር በእጅጉ የሚቀርፍ ፕሮግራም ነው፡፡ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እና በሄልቬታስ ስዊዝ መካከል የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድም በሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የተንጠልጣይ የእግረኛ መሻገሪያ ድልድዮችን በስፋት ለመገንባት እና ለወደፊትም መሰል ድልድዮችን በሀገር ውስጥ አቅምና ግብዓት ለመገንባት የሚያስችል አቅምን ለመፍጠር ጭምር የታሰበ ፕሮግራምን ለመተግበር የሚያስችል ነው፡፡ ፕሮግራሙን ለማስፈፀም አገልግሎት ላይ የሚውለው ገንዘብ በዋናነት በኢትዮጵያ መንግስት እና በሄልቬታስ ስዊስ ትብብር የሚሸፈን ነው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የቢላሎ - ቀርሳ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ
+3
የቢላሎ - ቀርሳ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ

የቢላሎ - ቀርሳ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ አፈጻጸም 93% ላይ ደርሷል አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓም (ኢመአ)፡ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ አርሲ ዞን እየተገነባ ያለው የቢላሎ - ቀርሳ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ አፈጻጸም 93% ላይ የደረሰ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ፡፡ መንገዱ 92 .23 ኪ.ሜ የሚረዝም ሲሆን ቀድሞ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ እና አሁን በአስፋልት ደረጃ ተሻሽሎ እየተሰራ ይገኛል፡፡ በእስካሁኑ አፈጻጸም የሰብ ቤዝና ቤዝኮርስ ሥራዎች ፣ የውሃ ማፋሰሻ ቱቦ ቀበራ ፣ የስትራክቸር ስራዎች የ 10 ድልድይ ስራዎች እና የአስፋልት ንጣፍ ስራዎች ተከናውነዋል ፡፡ የመንገዱን ግንባታ ለማከናወን 1,704,769,988.45 ( አንድ ቢሊዮን ሰባት መቶ አራት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሰድሳ ዘጠኝ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ስምንት ብር ከአርባ አምስት ሳንቲም ) የጠየቀ ሲሆን ወጪው በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው ፡፡ መንገዱ በገጠራማ ሥፍራዎች 7 ሜትር ፣ በቀበሌ ከተማዎች 14 ሜትር በወረዳ ከተማዎች ደግሞ 21 ሜትር ሆኖ ነው እየተገነባ ያለው፡፡ ግንባታውን እያካሄደ የሚገኘው የስራ ተቋራጭ ቻይና ኮሚዩኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ (CCCC) ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ሽላዲያ አሶሴት ከኢንሲራድ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ሲስተም እና ሂትከን ኢንጅነሪንግ ጋር በጣምራ እያከናወኑት ይገኛሉ ፡፡ መንገዱ በዋናነት ቢላሎ ከተማን፣ ኤጎ ከተማን፣ ቀርሳ ከተማን እና ጎልጆታ ከተማን የሚያገናኝ ሲሆን ይኸውም የአሰላ እና ሻሸመኔ ከተማን ለማገናኘት ቀላል ያደርገዋል፡፡ ይህ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የሚያልፍባቸው ዞን እና ወረዳዎች በስንዴ፣ ገብስ እና ድንች አምራችነት በሃገራችን ከሚታወቁ ቦታዎች ውስጥ ስለሆኑ እነዚህን የግብርና ምርቶች ወደ መሃል ሃገር ገበያ ለማምጣት ጉልህ ሚና አለው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የሞርካ-ግርጫ-ጨንቻ 72 ኪ.ሜ የአስፓልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+5
የሞርካ-ግርጫ-ጨንቻ 72 ኪ.ሜ የአስፓልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

የሞርካ-ግርጫ-ጨንቻ 72 ኪ.ሜ የአስፓልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈፃፀም 56 በመቶ ደርሷል፡፡ በእስካሁኑ የፕሮጀክት እንቅስቃሴ 2 ድልድይ ፣ 23 ስላብ ከልቨርት ፣ 89 ፓይፕ ከልቨርት ፣ 42.86 ኪሜ ሰብ ቤዝ ፣ 38.07 ኪሜ ቤዝ ኮርስ ፣ 34 ኪሜ አስፋልት ኮንክሪት የማልበስ ስራ ተጠናቋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የዛላመና እና ቡሎቆሬ አካባቢ የሚገኙ ተራራዎች የቁፋሮ ስራ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደርም በኩል በፕሮጀክቱ የስራ እንቅስቃሴ ላይ ያጋጠሙትን የወሰን ማስከበር እና የመሬት መንሸራተት ችግሮች ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦ በመስራት የዲዛይን አማራጭ ለመፍጠር ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ በተያያዘም በመሬት መንሸራተት ምክንያት ለሁለት ተለያይቶ የነበረውን የመንገድ ክፍል የአፈር ማጠናከርያ ቴክኖሎጂ (Soil Nailing using GRSS Technique) የተያዘው የዝናብ ወቅት እንዳበቃ ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናል፡፡ የግንባታ ስራውን ቤጂንግ ኧርባን ኮንስትራክሽን ግሩፕ /ቢዩሲጂ/ እያከናወነው ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃላ/የተ/የግ/ማ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ መንገዱ በወረዳ ከተማዎች 21.5 ሜትር ፣ በቀበሌ ከተማዎቸ 12 ሜትር ፣ በገጠር ደግሞ 8 ሜትር አጠቃላይ የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ለመንገዱ ግንባታ የሚውለው 1,967,496,759.60 (አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ ስልሳ ሰባት ሚሊዮን አራት መቶ ዘጠና ስድስት ሺህ ሰባት መቶ ሀምሳ ዘጠኝ ብር ከስልሳ ሳንቲም) በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡ የሞርካ-ግርጫ-ጨንቻ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ በዋናነት የሞርካ ፣ ዋጫ ፣ ወይዛ ፣ ሁሉ ቆዴ ፣ ዛዳ ፣ ዶኮ ፣ ጨንቻ ከተሞችን በቅርበት የሚያስተሳስር ይሆናል፡፡ በተጨማሪም የአካባቢውን ማህበረሰብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ግንኙነት እንዲያድግ በማድረግና በአካባቢው የሚገኙ የተለያዩ ምርቶችን እንደ አፕል ፣ ድንች ፣ ገብስ ፣ ባቄላ ፣ ካሮት እና የወተት ተዋፅኦ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

Second Round Trainee List of Project Managers and Resident Engineers

ለመላው የእስልምና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1ሺህ 444ኛው (ዓመተ-ሒጅራ) የዒድ አል-አደሃ(አረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ ዒድ ሙባረክ!

Call for Project Managers and Resident Engineers Training (2 Round)

33.60 ኪ.ሜ የሚረዝመው የሳይ - ማጂ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል፡፡ ከፕሮጀክቱ ግንባታ 96 በመቶ የሚሆነው ስራ የተገባደደ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን በቅርቡ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው፡፡ በእስካሁኑ አፈፃፀም የስብ ቤዝና ቤዝኮርስ ሥራዎች ፣ የውሃ ማፋሰሻ ቱቦ ቀበራ ፣ የስትራክቸር ሥራዎች ፣የሁለት ድልድይ እና የአስፋልት ንጣፍ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ የመንገዱን ግንባታ ለማከናወን 772,077,818.33 (ሰባት መቶ ሰባ ሁለት ሚሊዮን ሰባ ሰባት ሺህ ስምንት መቶ አስራ ስምንት ብር ከሰላሳ ሶስት ሳንቲም) በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡ መንገዱ በገጠራማ ሥፍራዎች 10 ሜትር ፣ በቀበሌ ከተማዎች 12 ሜትር ፣ በወረዳ ከተሞች ደግሞ 19 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ነው፡፡ ግንባታውን እያካሄደ የሚገኘው የስራ ተቋራጭ የንኮማድ ኮንስትራክሽን ኃ.የተ.የግ.ኩ. ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ክላሲክ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃ.የተ.የግ.ማ እያከናወነው ይገኛል፡፡ መንገዱ በዋናነት የማጂ እና ሳይ ቀበሌን እንዲሁም የምዕራብ ኦሞ ዞን እና የኦሞ ዞን ከተሞችን በመንገድ መሰረተ ልማት በማስተሳሰር የአካባቢው ህብረተሰብ ደረጃውን የጠበቀና ቀልጣፋ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል፡፡ በተያያዘም የመንገዱ መገንባት በአካባቢው የሚመረቱ የበቆሎ እና የድንች ምርቶችን በቀላሉ ወደ ገበያ ለማውጣት ብሎም ወደ ኩራዝ ስኳር ፋብሪካ ለመጓዝ እንደ አማራጭ መንገድ በመሆን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የባህር-ዳር ጢስ እሳት የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል። መነሻዉን ባህር-ዳር ከተማ አድርጎ መዳረሻ የአባይ ፏፏቴ (ጢስ-እሳት) ላይ ያደረገዉ ይህ መንገድ አሁን ላይ የግንባታ ሂደቱ በተሻለ ፍጥነት ላይ ይገኛል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ 21.2 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው ሲሆን በመንግስት በተመደበ 957,930,208.44 ብር ነዉ እየተገነባ የሚገኘዉ፡፡ የባህር-ዳር ጢስ እሳት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በማካሄድ ላይ የሚገኘው ሜልኮን ኮንስትራክሽን ኃ.የተ.የግ.ማህበር ነዉ፡፡ የመንገድ ግንባታውን ጥራት በመቆጣጠር ረገድ ደግሞ ጎንድዋና ኢንጅነሪንግ ኃ.የተ.የግ.ማህበር፤ ከዋይ.ኤል.ኤስ ኢንጅነሪንግ ኃ.የተ.የግ.ማህበር በጣምራ እያከናወኑት ይገኛሉ፡፡ ከዚህ በፊት የነበረዉ የመንገዱ ይዘት በጠጠር ደረጃ የነበር ሲሆን እጅግ ጠባብ እና ለትራንስፖርት አስቸጋሪ ነበር፡፡ አሁን ላይ የመንገዱ የጎን ስፋት የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በከተማ 34.5 በቀበሌ 31.5 እና በገጠር 21.6 እንዲኖረዉ ተደርጎ ነዉ እየተገነባ የሚገኘዉ፡፡ ፕሮጀክቱ ሁለት ድልድዮች፤ሰላሳ አምስት የውሃ መፍሰሻ ቱቦዎች እና ጢስ አባይ ላይ የሚሰራውን የእግረኛ መሻገሪያ ድልድይ የሚያካትት ነዉ፡፡ ይህ መንገድ በዚህ ደረጃ የጎን ስፋት እንዲኖረዉ የተደረገበት ምክኒያት መንገዱ ወደ ጢስ አባይ የቱሪስት መዳረሻ የሚያደርስ በመሆኑ ከመደበኛዉ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ የተለየ ፍሰት እንደሚኖረዉ ታሳቢ በማድረግ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ለማድረግ ነዉ፡፡ በተጨማሪም የመንገድ ግንባታው የባይስክሌት ሌይን፣የእግረኛ መሄጃ እና አረንጓዴ ቦታዎች (Green Area) ቦታን ያካተተ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ የዲዛይን እና የቅየሳ ስራ፤የተለዋጭ መንገድ እና የትራፊክ ማኔጅመንት ስራ፣የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ስራዎች፣ የቤዝኮርስ ንጣፍ ስራ፤የአስፋልት ንጣፍ ስራ፣የድልድዮች የግንባታ ስራ፤የውሃ ማፋሰሻ ቱቦ ቀበራ፤የፕሮዳክሽን ስራዎች (አስፋልት፣ቤዝኮርስ እና ኮንክሪት ጠጠር እንዲሁም ፓይፕ፣ ዲች ከቨር እና ታይልስ ማምረት)፤የመንገድ ዳር መብራቶች እና የመንገድ ምልክት ስራዎች፤የወሰን ማስከበር ስራዎች ባካተተ መልኩ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ከፕሮጀክቱ ጅማሮ አንስቶ አስካሁን አፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የሰቤዝ ስራ፤ የቤዝ ኮርስና አስፋልት ጠጠር ማምረታ ስራ፤ የወሰን ማስከበር እየተሰራ ይገኛል፡፡ በዚህም መሰረት የፕሮጀክቱ የእስካሁን አፈፃፀም 38.2 በመቶ ወይም 8.1 ኪሎ ሜትር ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ የተለያዩ ችግሮች የነበሩ ቢሆንም አሁን ላይ የወሰን ማስከበር ስራዉ 92 በመቶ የተጠናቀቀ በመሆኑ ግንባታው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ይህ አካባቢ ለም መሬት ያለበት በመሆኑ ጤፍ፣ሸንኮራ-አገዳ፣ሽንኩርት፣ጫት እና የተለያዩ አትክትልና ፍራፍሬዎች በስፋት በማምረት ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ አርሶ አደሩ ያመረተዉን ምርት በቀላሉ ወደ ማእከላዊ ገቢያ ለማድረስ ይረዳቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የታላቁ አባይ ወንዝ ፏፏቴ (ጢስ አባይ) የሚገኝበት በመሆኑ መንገዱ ሲጠናቀቅ ለአካባቢዉ ማህበረሰብ ብሎም ሀገራችን ከቱሪዝም ኢንዱስትሪዉ የምታገኘዉን ገቢ ይበልጥ ያሳድጋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የሶዶ-ዲንኬ 86 ነጥብ 22 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል የወላይታ እና ጋሞ ዞኖችን የሚያገናኘው የሶዶ-ዲንኬ 86 ነጥብ 22 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። በፕሮጀክቱ አሁን ላይ የ75 ነጥብ 74 ኪ.ሜ አስፋልት የማንጠፍ ሥራ የተከናወነ ሲሆን፥ ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው 92 በመቶው ተጠናቅቋል። ቀሪ የግንባታ ሥራዎችን እስከ ታኅሳስ ወር 2016 ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተቀምጧል። በተጨማሪም የ ሥድስት ድልድዮች፣ ከልቨርቶች፣ የሥምንት ኪ.ሜ የመንገድ ትከሻ እንዲሁም የ 28 ኪ.ሜ የውኃ መፋሰሻ ግንባታ ሥራ ተጠናቅቋል። የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል። ግንባታውን ቻይና ሬይልዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ 1,054,003,610.30 (አንድ ቢሊዮን ሃምሳ አራት ሚሊዮን) ብር ወጪ እያከናወነ ይገኛል፡፡ የማማከር እና የቁጥጥሩን ሥራ የሱዳኑ ኒውቴክ ኮንሰልቲንግ ግሩፕ ከሀገር በቀሉ ኔት ኮንሰልት ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ጋር በጥምረት ይሠራሉ፡፡ በፕሮጀክቱ የከተማ ክልል ማለትም በሶዶ እና ሠላም በር ከተሞች ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ የተነሱ ጉዳዮች በወቅቱ እልባት አለማግኘታቸው፣ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ እንዲሁም የግንባታ ዕቃዎች የግብዓት እጥረት እና የዋጋ መናር፣ በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረዋል። ከወሰን ማስከበር ጋር በተገናኘ የተነሱ ጉዳዮችን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ችግሩን መቅረፍ ተችሏል፡፡ በሥራ ተቋራጩ በኩል  ከገንዘብ ፍሰት ጋር የተያያዙ ችግሮቹን ቀርፎ ግንባታውን እንዲያፋጥን፥ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስፈላጊው ድጋፍ እና ክትትል ተደርጓል፡፡ የመንገዱ የቀድሞ ይዞታ በጠጠር ደረጃ የነበረ እና በተለያዩ ጊዜያት የመሸርሸር አደጋ እየደረሰበት የትራንስፖርት አገልግሎቱን ፈታኝ አድርጎት ቆይቷል፡፡ በመሆኑም ሥፍራው ካለው ዕምቅ የተፈጥሮ ሀብት እና በርካታ ሀገራዊ ፋይዳ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ ዕውን ሲሆን የኹለቱን ዞን ወንድማማች ሕዝቦች የእርስ በእርስ ግንኙነት ይበልጥ ያጠናክራል፡፡ በአካባቢው የሚመረቱትን እንደ ቡና፣ ካዛባ፣ በቆሎ፣ ስንዴ፣ ጤፍ እና ቅቤ ምርቶች ወደ መሐል ገበያ ለማቅረብ ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ መንገዱ የማዜ ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ እንደመሆኑ ፓርኩን ለቱሪስቶች ምቹ በማድረግ ረገድ አስተዋጾው የጎላ ነው፡፡ የጤና፣ የትምህርት እና ሌሎች መሰል የማኅበራዊ ተቋማት ተደራሽነትን ያሰፋል፡፡ መንገዱ በከተማ 12 ሜትር የመኪና መንገድ፣ 2.5 ሜትር የፓርኪንግ መስመር (በሁለቱም አቅጣጫ)፣ 3.5 ሜትር የእግረኛ መንገድ (በሁለቱም አቅጣጫ) እና 2 ሜትር የመንገድ አካፋይ አለው፡፡ እንዲሁም በወረዳ መቀመጫ 14 ሜትር የመኪና መንገድ እና 2.5 ሜትር የእግረኛ መንገድ (በሁለቱም አቅጣጫ) ይኖረዋል፡፡ የዚሁ መንገድ ቀጣይ ምዕራፍ የዲንኬ-ሳውላ ኮንትራት ኹለት አስፋልት መንገድ በግንባታ ሒደት ላይ እያለ ከአፈጻጸም ጋር ባጋጠሙ ችግሮች ግንባታው እንዲቋረጥ መደረጉ ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ጊዜም ግንባታውን ለማስቀጠል እንዲቻል ጥሩ አፈጻጸም ያላቸው የሥራ ተቋራጮች እንዲጫረቱ የተጋበዙ ሲሆን ሒደቱንም በማጠናቀቅ በአዲሱ በጀት ዓመት ግንባታው እንደሚጀመር ይጠበቃል፡፡

በፀጥታ ችግር ተስተጎጉሎ የነበረው ኮንትራት 2 አንገረብ-አሽሬ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አሁን ላይ በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል። የአይከል-ዙፋን-አንገረብ ኮንትራት 2 አንገረብ-አሽሬ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 71.5 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውና ከመንግስት በተመደበ በጀት በ1,955,438,532.41 (አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃምሳ አምስት ሚሊዮን አራት መቶ ሰላሳ ስምንት ሺህ አምስት መቶ ሰላሳ ሁለት ብር ከአርባ አንድ ሳንቲም ) በአስፋልት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል። ፕሮጀክቱ የሚካሄድበት መልክኣ ምድራዊ አቀማመጥ 10.5 ኪሎ ሜትር ወይም 14.75% ሜዳማ (Flat ) ፣ 17.2 ኪሎ ሜትር ወይም 24.17% ተራራማ (Mountainous) ፣ 32.00 ኪሎ ሜትር ወይም 44.98% ዳገታማ (Rolling) እና 7.4 ኪሎ ሜትር ወይም 10.40% ሸንተራራማ (Escarpment) ነው። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በመካሄድ ላይ የሚገኘው ቻይና ዉዪ በተባለ ዓለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው። ሮድ ዲዛይን ኤንድ ዴቨሎፕመንት ኮንስልታንት ኃ.የተ.የግ.ማ ደግሞ የመንገድ ግንባታውን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር ላይ ይገኛል። መንገዱ በወረዳ 21.5 ሜትር ፣ በቀበሌ 9.5 ሜትር እና በገጠር ከ 7.5 እስከ 8.25 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም በከፊል በገጠር መንገድ ደረጃ የነበረው ይኸው መንገድ በአሁኑ ወቅት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ከግምት ውስጥ ገብቶ በአስፋልት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ የአፈር ጠረጋ ፣ ቆረጣና ሙሌት ፣ የሰብ ቤዝ ፣ የቤዝ ኮርስ ፣ የአስፋልት ንጣፍ ፣ የስትራክቸር ፣ የሰባት ድልድዮች እና ተጨማሪ የውሃ መተላለፊያ ቦይ ግንባታዎችን ፣ የትራፊክ ምልክቶችን የመትከል እና ሌሎች ልዩ ልዩ ስራዎችን ባካተተ መልኩ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ከፕሮጀክቱ ጅማሮ አንስቶ እስካሁን የስድስት ትላልቅ ድልድዮች ግንባታ የተጠናቀቀ ሲሆን ፣ የ50 ኪሎ ሜትር አስፓልት ስራም አልቋል። ከዚህም ባሻገር ከ80% በላይ የፕሮጀክቱ የአፈር ሙሌት እና ቆረጣ ስራ ተጠናቋል። የስራ ተቋራጩ በቀሪዎቹ ቀጣይ ጊዜአት የመንገድ ላይ ምልክቶችን በመትከል ፣ ኪሎ ሜትር 76 አካባቢ የድንጋይ ቁፋሮ በመጨረስ ፣ ኪሎ ሜትር 70+180 አካባቢ የሚገኘውን ድልድይ ግንባታ በማጠናቀቅ እና ቀሪ የአስፋልት ንጣፍ ስራዎችን በማካሄድ አጠቃላይ የመንገድ ግንባታ ስራውን በሰኔ ወር 2016 ዓ.ም እንደሚያጠናቅቅ ይጠበቃል። ፕሮጀክቱ በሚካሄድበት አካባቢ ተፈጥሮ የነበረው የፀጥታ ችግር ፤ ከወሰን ማስከበር ጋር የተያያዙ ችግሮች ፤ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ ተፈጥሮ የነበረው የሲሚንቶ አቅርቦት እጥረት በፕሮጀክቱ አፈጻጸም ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ቢያሳድሩም እነዚህን ችግሮች በከፊል በመቀረፋቸው በአሁኑ ወቅት ፕሮጀክቱ በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል። ፕሮጀክቱ የሚካሄድበት አካባቢ የሰሊጥ ፣ የጥጥ ፣ የማሽላ እና የቦሎቄ ምርቶች በስፋት የሚመረቱበት ባለ ብዙ ፀጋ ቦታ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ከሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር ይህንኑ ታሳቢ ተደርጎ እና የአካባቢው አርሶ አደሮች ምቹ የትራንስፖርት አገልግሎት በመጠቀም ከምርቶቻቸው ተገቢውን ጥቅም እንዲያገኙ ለማስቻል ታስቦ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ከዚህም ባሻገር የማሰሮ እና የአሸሬ ወረዳዎችን እንዲሁም የዙፋን ፣ የማይነገድ እና የዶጋው ቀበሌዎችን በአቋራጭ በማገናኘት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብራቸውን ይበልጥ ያጠናክራል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et