cookie

МО вОкПрОстПвуєЌП файлО cookie Ўля пПкращеММя вашПгП ЎПсвіЎу перегляЎу. НатОсМувшО «ПрОйМятО все», вО пПгПЎжуєтеся Ма вОкПрОстаММя файлів cookie.

avatar

@🇲 🇪 🇿 🇲 🇺 🇷 🇪 🇹 🇪 🇌 🇊 🇭 🇩 🇎

ዚኢት/ ኊርቶዶክስ ተዋህዶ ቀተክርስቲያን ያሬዳዊ ዝማሬወቜን ፣ ወሚቊቜን በጜሁፍም ሆነ በድምጜ ዚምናጠናበት ቻናል ነው"" ስለቻናሉ አስተያዚት ካላቜሁ @Kulentaha ወይም ላይ መላክ ትቜላላቜሁ! ዲ/ን ተክለ ዮሃንስ ገብሚ ፃድቅ @mezmuretewahdo YOSTINA TUBE

Більше
РеклаЌМі ЎПпОсО
246
ПіЎпОсМОкО
НеЌає ЎаМОх24 гПЎОМО
-27 ЎМів
-430 ЎМів

ТрОває заваМтажеММя ЎаМОх...

ПрОріст піЎпОсМОків

ТрОває заваМтажеММя ЎаМОх...

Repost from Hilina Belete
ቀጾላ መንግሥቱ ለጊዮርጊስ (ዲ/ን ሕሊና በለጠ) በማኅሌተ ጜጌ "አክሊለ ጜጌ ማርያም ቀጾላ መንግሥቱ ለጊዮርጊስ ክበበ ጌራ ወርቅ" እያልን እንዘምራለን። ግን ለምን እንዲህ እንላለን? በቅድሚያ ሙሉ ዹማኅሌተ ጜጌ ድርሰቱን ኹነ ትርጉሙ ላስቀምጥ:- "ክበበ-ጌራ-ወርቅ ጜሩይ እምዕንቈ ባሕርይ ዘዚኀቱ፣ ዘተጜሕፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካሚ ሞቱ፣ አክሊለ ጜጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀጾላ መንግሥቱ፣ አንቲ ኲሎ ታሰግዲ ሎቱ፣ ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ።" #ትርጉም:- "ባሕርይ ኚሚባል ኚሚያበራ ዕንቁ ይልቅ ዚጠራ ዹወርቅ ጌጥ ዚኟንሜለት፣ (ዚጊዮርጊስ) ዚስሙ ምልክትና ዚሞቱ መታሰቢያ ዚተጻፈብሜ፣ ለጊዮርጊስ ዚመንግሥቱ ዘውድ ዚሆንሜ ዚአበባ አክሊል ማርያም ሆይ፣ አንቺ ለእርሱ ኹሉን ታሰግጂለታለሜ፣ እርሱ ግን ላንቺ ይሰግዳል።" ቅዱስ ጊዮርጊስ ዹ7 ዓመታት ተጋድሎውን ዹጀመሹው በ20 ዓመቱ ነበር። ለሰባት ዓመታት ያክል እዚሞተ እዚተነሣ ተጋድሎውን ፈጜሞ በ27 ዓመቱ፣ በሚያዝያ 23፣ በ304 ዓ.ም. ዐሚፈ። እስኚዚያው ጌታቜን ቃል እንደ ገባለት 3 ጊዜ ሞቶ 3 ጊዜ ተነሥቷል። በዐራተኛው ሞቱ ፈጜሞ ዐሚፈ። ያሚፈውም በዕለተ ዓርብ በ9 ሰዓት ነበር። ቅዱስ ጊዮርጊስ 4 ጊዜ መሞቱን "ማርያም" ኹሚለው ባለ 4 ፊደል ቃል ጋር ያመሣጠሚው ደራሲው "ዘተጜሕፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካሚ ሞቱ - ዚስሙ ምልክትና ዚሞቱ መታሰቢያ ዚተጻፈብሜ" ሲል እመቀታቜንን በማኅሌተ ጜጌ አመሰገናት። ቅዱስ ጊዮርጊስን ያንገላታ ዹነበሹው ንጉሥ ዱድያኖስ ንግሥት እለስክንድርያ ዚምትባል ሚስት ነበሚቜው። መሳፍንቱና መኳንንቱ ኹሉ ለእርሷ ይሰግዱ ነበር። በሰማዕቱ ትምህርት አምና ለቅዱስ ጊዮርጊስ ዹፀጋ ስግደትን ሰገደቜለት። በዚህም ምክንያት በሚያዝያ 15 አንገቷን በሰይፍ እንድትቆሚጥ ተደርጋለቜ። ያቺ ሣር ቅጠሉ ኹሉ ይሰግድላት ዚነበሚቜ ንግሥት ለቅዱስ ጊዮርጊስ መስገዷን ያስተዋለው ሊቁ ግን በማኅሌተ ጜጌው "አንቲ ኲሎ ታሰግዲ ሎቱ - አንቺ ለእርሱ ኹሉን ታሰግጂለታለሜ" ሲል በእመቀታቜንና በሰማዕቱ ምስጋና ላይ ዘኚራት። ቅዱስ ጊዮርጊስ ፍጥሚት ኹሉ "ብፅዕት" ለሚላት ለድንግል እንደሚሰግድም "ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ - እርሱ ግን ላንቺ ይሰግዳል" ሲል ገልጟአል። "ዹደናግል መመኪያ፣ ዚሰማዕታት አክሊል፣ ..." ዚምትባለው እመቀታቜን: ቀደም ሲል ባነሣና቞ው ምክንያቶቜ ዚተነሣ: ይልቁንስ ለሊቀ ሰማዕታት ለቅዱስ ጊዮርጊስ ዚኚበሚቜ አክሊሉና ዘውዱ መኟኗን ሲገልጜም "ክበበ-ጌራ-ወርቅ ጜሩይ እምዕንቈ ባሕርይ ዘዚኀቱ... አክሊለ ጜጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀጾላ መንግሥቱ - ባሕርይ ኚሚባል ኚሚያበራ ዕንቁ ይልቅ ዚጠራ ዹወርቅ ጌጥ ዚኟንሜለት... ለጊዮርጊስ ዚመንግሥቱ ዘውድ ዚሆንሜ ዚአበባ አክሊል ማርያም ሆይ" ብሏል። እኛም እንደ አባ ጜጌ ድንግልና እንደ አባቶቻቜን በማኅሌተ ጜጌ "ቀጾላ መንግሥቱ ለጊዮርጊስ" እያልን እመቀታቜንንና ሰማዕቱን እንዘክራለን። ዘመነ ጜጌ፣ 2013 ዓ.ም.
ППказатО все...
✞በብርሃን ፀዳል✞ በብርሃን ፀዳል ተኚባ እመቀ቎ በደመና ዙፋን ተቀምጣ ኹፊቮ ዚጜጌውን ዜማ ስንዘምር በደስታ በምስጋናሜ መጠጥ/ሲሰማኝ እርካታ/(፪) እንባዬ ሲቀዳ ናፍቆትሜ መስጊኝ ኚደስታ በላይ አንቺን ስላዚሁኝ ምኞቮ ተሳክቶ ፊትሜን አይቌው ዚሌሊቱ ህልሜ /ዹቀን ምኞቮ ነው/(፪)       አዝ= = = = = ሩኅሩኅ ነሜና ይህ ህልሜ ተሳክቶ አመስግኜሜ ድንግል ህልናዬ ሚክቶ ልጅሜ ልሁን ድንግል ኚስርሜ አልጥፋ አንቺን በማመስገን/ህሊናዬ ይትጋ/(፪)        አዝ= = = = = ልጅሜ ልሁን ድንግል ኚስርሜ አልጥፋ አንቺን በማመስገን ህሊናዬ ይርካ ዚምስጋናሜ ብዕር ብራናሜ ልሁን ስምሜ ይፃፍብኝ /በልዩ ህብር/(፪)      መዝሙር          ይልማ ኃይሉ "እግዚአብሔርን አመስግኑ፥ መዝሙር መልካም ነውና።"               መዝ፻፵፯፥፩
ППказатО все...
💛 ዹ መዝሙር ግጥሞቜ 💛

🇪🇹 ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን  አስተምህሮ ና ስርአትን ዹጠበቁ ቆዚት ያሉና አዳዲስ👇👇 👏 ዚ቞ብ቞ቊ መዝሙራት 🎻 ዹበገና መዝሙራት   👑 ዚቅዱሳ መዝሙራት ⛪ ዚንግስ መዝሙራት 💍 ዹሠርግ መዝሙራት 🌊 ወቅታዊ መዝሙራት መገኛ Buy ads:

https://telega.io/c/yamazemur_getemoche

📢ለ ማስታወቂያ ስራዎቜ @Miki_Mako

#ቃል_ኪዳንዋ ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይድሚሰውና ጌታቜን ምድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ለሰማዕቷ ለትውልድ ዹሚተላለፍ ዹዘላለም ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡ መታሰብያዋን ያደሚገ ስሟን ዚጠራ፣ በስሟ ቀተ ክርስትያን ዚሠራ፣ ዚተራበውን በስሟ ያበላ፣ ዹተጠማውን በስሟ ያጠጣ፣ ዚገድሏን መጜሐፍ ዚጻፈውን፣ ያጻፈውን፣ ያነበበውን፣ ዚተሚጎመውን፣ ሰምቶም በልቡ ያኖሚውን፣ ዚልቡን መሻት እንደሚፈጜምለት እና በመንግስተ ሰማያት እንደ እርሷ ዚክብር አክሊል እንደሚያቀዳጀውፀ ሥዕሏን አሥሎ በክብር በቀቱ አስቀምጊ ሜቶ እዚሚጚ ቢጞልይበት ጞሎቱ እንደሚሰማና ልብን ዚሚመስጥ ጣፋጭ ዹሆነ መዓዛ እንደሚያሞተው፣ ወንድ ልጁንና ሎት ልጁን በስሟ ዹሰዹመ በመንግስተ ሰማያት ዹበለጠና ዹኹበሹ ስም እንደሚሰጣ቞ው፣ ዕጣን፣ ስንዎና መብራትን፣ ልብሰ ተክህኖ፣ መጋሹጃ ቢሰጥ በሞቱ ቀን ዚብርሃን ልብስ እንደሚለብስ፣ ያለ ወቀሳ ያለኚሳ ባህሚ ሲኊልን ተሻግሮ መንግስቱን እንደሚወርስ ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡ ፚ ሰማዕቷን ኚሌሎቜ ቅዱሳን ልዩ ዚሚያደርጋት ታሪክ ፚ በግብጜ አገር አርባ ዓመታት ዹነገሠ ባለ 12 ክንፉ ብጹአዊ አቡነ ሙሮ ዚሚባሉ ታላቅ ጻድቅ አሉ፡፡ እኝህ ጻድቅ ኚንግስና ወደ ምንኩስና ዚተሞጋገሩ መንፈሳዊ አርበኛ ና቞ው፡፡ ታድያ እኝህ ጻድቅ ዚቅዱሳን፣ ዚሰማዕታትን ዓጜም እሰበሰቡ ደግላቾውን እያጻፉ፣ ቀተ ክርስትያን በመስራት፣ ታቊታ቞ውን በማክበር፣ በበዓላቾውም ቀን ይቀድሱ ነበር፡፡ ኚእለታት አንድ ቀን ታቊት ለማሰናዳት፣ ሜሮን ለመቀባት ወደ ቀተ መቅደስ በገቡ ጊዜ በወርቅ ዹተለበጠ እና በላዩ በሮማይስጥና በጜርዕ ቋንቋ ዚብጜዕት ቅድስት አርሮማ ስም ዚተጻፈበት አንድ ጜላት ያገኛሉ፡፡ ያን ጊዜ ዚቅዱሳንን ስማ቞ውን አሰቡ፡፡ ዚገድላ቞ውንም ዜና መሚመሩ፡፡ ግን ዚቅድስት አርሮማን ግድልና ዚሞቷን ዜና አላገኙም። ስለዚህም ነገር በምን ዘመን ሰማዕት እንደሆነቜ እና ዚሰማዕትነቷን ሥራ ያስሚዳ቞ው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር በጞሎት አመለኚቱ፡፡ ያን ጊዜ ዚእግዚአብሔር መልአክ ለአቡነ ሙሮ ተገልጩ ‹‹ብጜአዊ ሙሮ ሆይ ዚብጜእት አርሮማን ሥራ እነግርህ ዘንድ ስማ፡፡ ይህቺ ሰማዕት ገና አልተጞነሰቜም፣ አልተወለደቜምፀ በወርቅ ዓምድ በሕይወት መጜሐፍ ስሟ ተጜፏል እንጂ፡፡ ነብዩ በመጜሐፍ ውስጥ ሁሉ ይጻፋል እንዳለ እርሷም በኋለኛው ዘመን ሰማዕት ትሆናለቜፀ በዓለም ዳርቻ ሁሉ ዚገድሏ ዜና ይታወቃል፡፡ ተአምሯ ዹሚነገሹው በኢትዮጲያ ነው፡፡ ስለዚህ ኹዚህ ጊዜ ጀምሮ ዚብጜዕት ቅድስት አርሮማን ዚስም መታሰብያ መጥራት አትተው፡፡ ጜላትዋም ኹአንተ ጋር ይኑር፡፡ ዚመቅደስዋም ህንጻ በህንጻህ ቊታ ጎን ይኑር፡፡ ስምህ በተጠራበትም ዚስሟ መታሰብያ ይጠራል›› ብሎ መልአኩ ወደ ላኹው እግዚአብሔር ተመለሰ፡፡ አቡነ ሙሮም ዚእግዚአብሔር መልአክ እንዳዘዛ቞ው አደሚጉ፡፡ ሰማዕቷም ገና ሳትወለድ በፊት እንደ እመቀታቜን በእግዚአብሔር ህሌና ታስባ ትኖር ነበር፡፡ እኛም እንደ እንደ ጻድቁ አቡነ ሙሮ በሰማዕቷ ጞሎት እና ቃል ኪዳን ልንጠቀምባት ይገባል፡፡ ተወዳጆቜ ሆይ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዎዮንና ስለ ባርቅ ስለ ሶምሶም ስለ ዮፍታሔ ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኀልም ስለ ነብያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና›› ነው ያለው፡፡ /ዕብ 11÷32/ እኔም ስለ እዚቜ ድንቅ ብርቅ እና ኹወርቅ በላይ ዚኚበሚቜ ኹአልማዝም በላይ ዚተወደደቜ ስለ ሰማዕቷ ለመተሹክ ጊዜ ስለማይበቃን እዚህ ላይ ይብቃን፡፡ ዚሰማዕቷ ዚቅድስት አርሮማ ጞሎት፣በሚኚት ኚሁላቜን ጋር ይሁን፡፡ በሰማዕቷ በቅድስት አርሮማ ስም ‹‹ሌር›› አድርገው ለወዳጆ ይዘክሩ፡፡
ППказатО все...
ዚጜጌ ወር ኚመስኚሚም ፳፮ እስኚ ኅዳር ፮ ያለውን ጊዜ ዹሚሾፍን ነው፡፡ ጜጌ፣ ምድር በአበባ፣ ማኅሌቱ በያሬዳዊ ዜማ ዚሚፈካበት ልዩ ወቅት፣ ምድር ዚምትዋብበትና ዚምትቆነጅበት፣ ተራሮቜ ዚሚንቆጠቆጡበት ዚጌጥ፥ ዚውበት ወቅት እንደሆነ ጠቢቡ ሲገልጜ “እነሆ ክሚምቱ አለፈፀ ዝናቡም አልፎ ሄደፀ አበቊቜም በምድር ላይ ተገለጡፀ ዹዜማም ጊዜ ደሹሰ” ይላል፡፡ (መሓ. ፪፥፲፩) “አበቊቜን እንዎት እንዲያድጉ ተመልኚቱፀ አይደክሙምፀ አይፈትሉምምፀ ነገር ግን እላቜኋለሁ፥ ሰሎሞንስ እንኳን በክብሩ ሁሉ ኚእነዚህ እንደ አንዲቱ አለበሰም” እንዲልፀ (ሉቃ.፲፪፥፳፯) ተራሮቜና ኮሚብቶቜ በሰው እጅ ያልተጌጠውን  ውብ ዹሆነ ልብሳ቞ውን ተጎናጜፈው ዚሚመለኚታ቞ውን ሁሉ ትኩሚት ዚሚስቡበት፣ ለአፍንጫ ተስማሚ ዹሆነውን ጥዑም መዓዛቾውንም እንካቜሁ ብለው ያለስስት ዚሚ቞ሩበት፣ አዕዋፍ ዝማሬያ቞ውን ኚወትሮው በላቀ ሁኔቮ  ዚሚያንቆሚቁሩበት፣ ንቊቜ ኚአበባ ወደ አበባ እዚባሚሩ ጣፋጭ ማርን ዚሚያዘጋጁበት፣ ሁሉ አምሮ፣ ሁሉ ደምቆ፣ አዲስ ሆኖ ዚሚገኝበት ወቅት በመሆኑ ይህ ጊዜ ወርኃ ጜጌ፣ ዘመነ ጜጌ በመባል ይታወቃል፡፡ ቀተ ክርስቲያንም ዝማሬዋን፣ ትምህርቷን፣ ዜማዋን፣ ንባቧን፣ ለወቅቱ እንዲስማማ እያደሚገቜ በምሳሌና በኅብር፣ በሰምና ወርቅ እያዋዛቜ ለጀሮ እንዲስማማ፣ ለልብ እንዲያሚካ፣ ለሥጋ ስክነትን ለነፍስ ዕሚፍትን እንዲሰጥ አድርጋ ታቀርብበታለቜ፡፡ በሰማዩ ፍካት፣ በውኃው ጥራት፣ በኮኚቊቜ መውጣት፣ በአበቊቜ ውበት፣ በተዘሩት አዝርዕት፣ በጞደቁት አትክልት፣ በዛፎቹ ልምላሜ፣ በአዝርዕቶቹ ፍሬ ሁሉ ቃሉን እዚመሰለቜ ታስተምራለቜፀ ትዘምራለቜፀ ትቀድሳለቜፀ በጥበብ ሹቅቃ ታራቅቃለቜ ተቀኝታ ታስቀኛለቜ፡፡ ቀተ ክርስቲያን በምልዓትና በሙላት ያለቜ ናት፡፡ ይህን ዘመነ ጜጌንም እንደ ሌሎቜ ወቅቶቜ/ወንጌልን ለማስተማር፣ ዚራቀውን አቅርባ ዹሹቀቀውን አጉልታ፣ ዹጎደለውን ሞልታ፣ ዹጠመመውን አቅንታ ለማስተማር በብዙ መልኩ ትጠቀምበታለቜ፡፡ በልዩ ሁኔታ ነገሹ ማርያምም ነገሹ ክርስቶስም በስፋት ዚሚሰበክበት ወቅት በመሆኑ ዘመነ ጜጌ እጅግ ተወዳጅ ወቅት ነው፡፡ ወርኃ ጜጌን ልዩ ዚሚያደርገው አንዱና ዋናው ዚእመቀታቜን እና ዚተወዳጅ ልጇ ስደት ዚሚታሰብበት ወቅት በመሆኑ ነው፡፡ ውድ ዹዚህ ጜሑፍ ተኚታታዮቜ ‹‹ሱላማጢስ ሆይ ተመለሺ ተመለሺ›› በሚል ርእስ ስለ ስደቷና ተያያዥ ታሪኮቜ በቀጣይ ክፍል ሰፋ አድርገን እናቀርብላቜኋለን፡፡ እስኚዚያው ሰላመ እግዚአብሔር ኚሁላቜን ጋር ይሁንፀ አሜን!
ППказатО все...
Repost from N/a
ЀПтП МеЎПступМеДОвОтОсь в Telegram
#ጰራቅሊጊስ ብሂል(ማለት) 1. #መጜንዒፊ ዚሚያጞና ማለት ነው፡፡ 2. #መንጜሒፊ ዚሚያነጻ ማለት ነው፡፡ 3. #ናዛዚ፩ ዚሚያፅናና ማለት ነው፡፡ 4. #አራኃዊፊ ዚሚኚፍት ማለት ነው፡፡ 5. #መስተፍሥሒፊ ደስ ዚሚያሰኝ ደስታን ዹሚመላ ማለት ነው፡፡ 6. #ኚሣቲ፡- ምሥጢርን ዚሚገልጥ ማለት ነው፡፡ 7. #አለባዊፊ ማስተዋልን ዚሚሰጥ ማለት ነው፡፡ 8. #መስተናግርፊ ሃይማኖትን፣ ዚጥበብን ቃል፣ ምሥጢርን ዚሚያናግር ዚሚያስተሚጉም ማለት ነው፡፡ 9. #መስተሥርዪ፡- ኃጢአትን ዚሚያርቅ ዚሚያስወግድ ዚሚደመስስ ማለት ነው፡፡ 10. #መንፈሰ_ጜድቅ፡- ዚእውነት መንፈስ፣ #መንፈስ #ቅዱስ ማለት ነው። ስብሐት ለኹ ጰራቅሊጊስ በስብሐተ አብ ቅዱስ ስብሐት ለኹ ጰራቅሊጊስ በስብሐተ ወልድ ውዱስ ስብሐት ለኹ ጰራቅሊጊስ በስብሐተ ስምኚ ዘይሀለስ ስብሐት ለኹ አምላኪዚ በአፈ ኵሉ ዘነፍስ በሰማይ ወበምድር በባሕር ወበዚብስ፠ እሰግድ ለርደትኚ እሰግድ ለርደትኚ እሰግድ ለርደትኚ
ППказатО все...
#ዐውደ_ዓመት ዐውደ ዓመት ለባርኮ ባርኮ ዐውደ ዓመት/2/ ንዒ ማርያም ለምህሚት ወሳሕል/2/
ППказатО все...