uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 543 підписників, посідаючи 8 332 місце в категорії Технології та додатки та 2 157 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 543 підписників.

За останніми даними від 27 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 10, а за останні 24 години на -16, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 25.06%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 16.33% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 895 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 539 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 7.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 28 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 543
Підписники
-1624 години
-97 днів
+1030 день
Архів дописів
ዜና እረፍት! በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒነግ ዘርፍ ስራ ባልደረባ የሆኑት አቶ ማርዓለም አምደብርሃን በድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ተቋሙ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልጻል፣ አቶ ማርዓለም አምደብርሃን ከአባታቸው ከአቶ አምደብርሃን በላይ ከእናታቸው ከወ/ሮ እታገኝ አሰፋ በጎንደር ከተማ ቀበሌ 17 ጥቅምት 26 ቀን 1977 ዓ.ም ተወለዱ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በጎንደር ቀበሌ 10 አንደኛ ደረጃ ት/ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ደግሞ በፋሲለደስ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተምረዋል። የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ውጤት በማምጣትም በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል ምህንድስና የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በ2003 ዓ.ም አግኝተዋል። ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በ2009 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል ምህንድስና ተመርቀዋል። አቶ ማርዓለም ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በባለሙያነትና በተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች ተቋሙን በቅንነት፣ በታማኝነት፣ በታታሪነት ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን በባህሪያቸውም እጅግ በጣም ትሁት፣ ሰው አክባሪ፣ ጥሩ ስነምግባርን የተላበሱ ትጉህ፣ ሠራተኛ ነበሩ። ህልፈታቸው እስከተሰማበት ዕለትም በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ የኃይል ማመንጫዎች ስትራቴጂክና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ሆነው በማገልገል ላይ ነበሩ። አቶ ማርዓለም ባጋጠማቸው ድንገተኛ ህመም ምክንያት በተወለዱ በ39 ዓመታቸው ሚያዚያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። አቶ ማርዓለም ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነበሩ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአቶ ማርዓለም አምደብርሃን ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን በድጋሜ እየገለፀ ለቤተሰቦቹ እና ወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናትን ይመኛል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ሥርቆትን ለመከላከል የቋሚ ኮሚቴ አባላት ሚናቸውን እንደሚወጡ ገለጹ ...........//........... የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች  ቋሚ ኮሚቴ የላከው ቡድን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ ሪጅን 2 በመገኘት የመስክ ጉብኝት አደረገ። የቡድኑ አስተባባሪ የተከበሩ አቶ እያሱ ሳላ እንደገለጹት የመስክ ምልከታው ዓላማ የቋሚ ኮሚቴው አባላት የሪጅኑን የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትና የሥራ እንቅስቃሴን በአካል ተገኝቶ በመጎብኘት ግብረ መልስ ለመስጠት ነው። የሰሜን ምስራቅ ሪጅን 2 ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ቢሆነውም የሪጅኑ አመራሮችና ሠራተኞች የአካባቢውን የአየር ንብረት ተቋቁመው ባደረጉት ጥረት በአጭር ጊዜ የተመዘገበው ውጤት አበረታች መሆኑን የቡድኑ አባላት አንስተዋል። ሪጅኑ አገልግሎት አሰጣጡን የተቀላጠፈ ለማድረግ የራሱን ቢሮ መገንባትና የካይዘን አሠራርን በአግባቡ ሥራ ላይ ሊያውል እንደሚገባ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ ሪጅን 2 ዳይሬክተር አቶ ሀሰን መሐመድ በበኩላቸው በሪጅኑ ያሉ ችግሮችን በመፍታት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በሪጅኑ የሠራተኛ ፍልሰት በመኖሩ ሠራተኞች በሪጅኑ ለረጅም ጊዜ እንዲቆዩ ለማድረግ ለሠራተኞች ምቹ ሁኔታ ከመፍጠር በተጨማሪ የአካባቢውን  ወጣቶችን በማሰልጠን ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት እየሰሩ መሆኑንም ተናግረዋል። በሪጅኑ የሚፈጸመው የኤሌክትሪክ መሠረት ልማት ስርቆት በስራቸው ብሎም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ በርካታ ጉዳት እየደረሰ መሆኑም ተገልጿል። ስለሆነም የአካባቢው መስተዳድር፣ ሕዝቡና የሚመለከታቸው አካላት ችግሩን ዘለቄታዊ እልባት ለመስጠት እንዲሰሩ የቋሚ ኮሚቴው አባላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። የቡድን አስተባባሪው የተከበሩ አቶ እያሱ ሳላ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ስርቆት በሀገር ማህበረ ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ጫና እየፈጠረ ያለ ችግር በመሆኑ ችግሩ እንዲፈታ ለሚመለከታቸው አካላት ሪፖርት የሚያቀርቡ መሆኑን ገልጸዋል። ምክር ቤቱም ችግሩን ለመቅረፍ የሚያስችል ጠንከር ያለ ሕግ እንዲወጣ ቋሚ ኮሚቴው ጥረት የሚያደርግ መሆኑን የጠቆሙት አስተባባሪው በሪጅኑ የሚታየውን የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ስርቆት ለመከላከል የአካባቢው መስተዳድር በትኩረት እንዲሰራ አሳስበዋል። በሪጅኑ ለሥራ እንቅፋት የሆኑ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ከዋናው መ/ቤት፣ ክልሉ መንግስት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚገባ የተከበሩ አቶ እያሱ ጠቁመዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሚያዚያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

photo content
+5

ሻምፒዮኑ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በዛሬው ጨዋታ ነጥብ ተጋርቷል .........///........... የኦሮሚያ ፖሊስ ነጥብ መጣሉን ተከትሎ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን ትናንት ያረጋገጠው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ዛሬ ባከናወነው የከፍተኛ ሊግ ውድድር ከይርጋጨፌ ቡና ጋር ያለምንም ጎል አቻ ተለያይቷል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ኳስ ይዞና ተጭኖ  ለመጫወት ቢሞክረም ወራጅ ቀጠና የሚገኘው ይርጋጨፌ ቡና ወደ ታችኛው ሊግ ላለመውረድ የሞት ሽረት ትግል በማድረግ አንድ ነጥብ ይዞ ወጥቷል። ጨዋታው ከመጀመሩ በፊት ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉ በእግር ኳስ ፌደሬሽን አማካኝነት የተበሰረ ሲሆን ተጫዋቾች እና አሰልጣኞች ወደ ሜዳ ሲገቡም የክብር አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ እስከአሁን ካደረጋቸው 22 ጨዋታዎች በ15ቱ አሸንፎ፣ በአምስት አቻ ወጥቶ እና በሁለት ጨዋታዎች ተሸንፎ በ50 ነጥብ እና በ24 ንፁህ ጎል ሻምፒዮን መሆኑን አረጋግጧል። በዚህ የውድድር ዓመት አስር ጎል ማስቆጠር የቻለው አቤል ሀብታሙ የክለቡ ኮከብ ጎል አስቆጣሪ ሲሆን መሳይ ሰለሞን በስድስት እንዲሁም ቢኒያም ካሳሁን በአምስት ጎል ይከተሉታል። ሐዋሳ በተካሄደው የሁለተኛው ዙር መርሐ ግብር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች ሜዳ በመገኘት ክለባቸውን አበረታተዋል። አራት ጨዋታ በቀሩት የከፍተኛ ሊግ ውድድር የምድብ ሀ አሸናፊ የሆነው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የምድብ ለ አሸናፊ ከሚሆነው ክለብ ጋር  የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር እንደሚያከናውን ይጠበቃል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሚያዚያ 19 ቀን 2016 ዓ.ም

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ዳግም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን መቀላቀሉን አረጋገጠ .........///......... በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ትናንት በተከናወነው መርሐ ግብር ኦሮሚያ ፖሊስ ነጥብ መጣሉን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ አምስት ጨዋታ እየቀረው ወደ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል። በዘንድሮ የውድድር ዘመን ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ውድድሩ ከጀመረበት ዕለት ጀምሮ ሊጉን በመምራት እና አምስት ጨዋታ እየቀረው ሻምፒዮናነቱን በማረጋገጡ አዲስ ታሪክ መፃፍ ችሏል። በ1953 ዓ.ም የተመሠረተው አንጋፋው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በስፖርቱ ዘርፍ በርካታ እንቁ ተጫዋቾች ለሀገር አበርክቷል። በተገኘው ድል መላው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ለተቋሙ የሥራ አመራሮች እና ሠራተኞች እንኳን ደስ አለን የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል። በስፓርቱ የተገኘውን ስኬት ተቋማዊ ዕቅዶችን በማሳካት እንዲደግመው ጥሪ አቅርበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሚያዚያ 19 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የግድቡን ግንባታ የሚመለከቱ ውሎች አስተዳደር በተገቢው መንገድ እየተከናወነ ነው ……...///…….... የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታን በተያዘለት ጊዜ ገደብ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት የኮንትራት አስተዳደር ሥራዎች በአግባቡ እየተሰሩ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቱ የኮንትራት አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ቡድን መሪ አቶ ኢዩኤል ሰለሞን እንደተናገሩት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ወጪ 2 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዩሮ ነው። በአሰሪው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በተቋራጩ ዊ ቢውልድ ወይም በቀድሞው ሳሊኒ መካከል ጥብቅ የሆነ የሥራ አካሄድ እንዲኖር ለማድረግ የክትትል ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። በግድቡ ግንባታ ዙሪያ የተቀመጡ ውሎችን አፈፃፀም የመከታተልና የመቆጣጠር ሥራዎች በተገቢው መንገድ እየተከናወኑ መሆኑን አቶ ኢዩኤል ተናግረዋል። የፕሮጀክቱ የኮንትራት አስተዳደር ክፍል በግድቡ ግንባታ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ሥራ ተቋራጮች ላከናወኗቸው ሥራዎች በየወሩ የሚጠይቋቸውን የፋይናንስ ጥያቄዎች በማጣራት ተፈፃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል። የፕሮጀክቱ የግንባታ ጠቅላላ ወጪ እንደ ሲቪል እና ኤሌክትሮሜካኒካል ሥራዎች ዓይነትና መጠን በብር እና በዩሮ የሚከፈሉ መሆናቸውን አቶ ኢዩኤል ገልፀዋል። የፕሮጀክቱ አብዛኛው የሲቪል ሥራ ሀገር ውስጥ በሚገኙ ግብዓቶች እየተከናወነ መሆኑን የጠቀሱት ቡድን መሪው በዚህም ምክንያት ክፍያዎች ተፈፃሚ እየተደረጉ የሚገኙት በብር እንደሆነም ነው ያመለከቱት። እንደ አቶ ኢዩኤል ገለፃ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ከዲዛይን ጀምሮ እስከ ምርት ሂደትና ገጠማ ድረስ በዩሮ የሚከፈል በመሆኑ የሚያስችል የውጭ ምንዛሬ ያስፈልጋል። በኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የኮንትራት አስተዳደር ሂደት ውስጥ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን ከወዲሁ ለመቅረፍ ከጊቤ-III የኃይል ማመንጫ ጣቢያ እና ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የተለያዩ ልምዶችና ዕውቀቶች መወሰዳቸውን ተናግረዋል። የፕሮጀክቱ ግንባታ በፋይናንስ እጥረት ምክንያት እንዳይጓተት ለማድረግ መንግሥት ከመቼውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ አቶ ኢዩኤል አረጋግጠዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

በሪጂኑ የሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች አስተማማኝ ኃይል እያቀረቡ ነው ……….///……… በደቡብ 1 ሪጂን የሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረቡ መሆኑን የሪጂኑ ዳይሬክተር ገለጹ። የሪጂኑ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ እንደገለጹት በሪጂኑ ከሚገኙ 12 ማከፋፈያ ጣቢያዎች 11ዱ ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ አቅም አላቸው፡፡ በሪጂኑ የሚገኙ ሁሉም ማከፋፈያ ጣቢያዎች 1300 ሜጋ ዋት ኃይል የመጫን አቅም ያላቸው ሲሆን ከዚህ ውስጥ ለደንበኞቹ እየቀረበ ያለው 567 ሜጋ ዋት እንደሆነ አንስተዋል፡፡ ከዲላ ማከፋፈያ ጣቢያ በስተቀር ሌሎች ጣቢያዎች ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድና አስተማማኝ ኃይል የማቅረብ አቅም እንዳላቸውም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ የዲላ ማከፋፈያ ጣቢያ በ15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመር ትራንስፎርመር ላይ የመጫን አቅሙ ሙሉ በሙሉ ስለሞላ በአሁኑ ወቅት ኃይል የሚፈልጉ ደንበኞች ከ33 ኪሎ ቮልት በጊዜያዊነት ኃይል እንዲያገኙ እየተደረገ እንደሆነ ጠቁመዋል። በ15 ኪሎ ቮልት ላይ የኃይል ጥያቄው እየጨመረ በመምጣቱ ከደንበኞች የሚቀርቡ ተጨማሪ የኃይል ጥያቄዎችን ለመመለስ ጣቢያው የአቅም ማሳደግ ሥራ እንደሚያስፈልገው አቶ ምትኩ አስታውቀዋል፡፡ ሪጂኑ ከሚያካልላቸው አካባቢዎች መካከል ሀዋሳ፣ ዲላ፣ ሻሸመኔ እና ሻኪሶ ያለው የኃይል ፍላጎት በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን ያነሱት ዳይሬክተሩ የኃይል ጥያቄውን በወቅቱ ለመመለስ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ተጨማሪ ብሬከር የመትከልና የማዘመን ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ እንደ አቶ ምትኩ ገለፃ የሻሸመኔ፣ ሻኪሶ፣ ይርጋለም 1 እና ዲላ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ብሬከር የማዘመን ሥራ እየተሰራ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅትም የሻሻመኔ 33 ኪሎ ቮልት የብሬከር ቅየራ ሙሉ በሙሉ ጠናቀቁንና የሻኪሶ ደግሞ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ የይርጋለም 1 እና የዲላ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የብሬከር የቅየራ ሥራ በጣቢያዎቹ ላይ ጊዜያዊ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ከተተከለ በኋላ እንደሚከናወን ገልጸው በአሁኑ ወቅትም ለባለሙያዎች ስልጠና የመስጠትና ለቅየራ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ወደ ጣቢያዎቹ የማጓጓዝ ሥራዎች መከናወኑን አመልክተዋል፡፡ የደቡብ 1 ሪጂን የሲዳማ ክልልን ሙሉ በሙሉ፤ ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ፣ ባሌ፣ ምስራቅ ባሌ፣ ቦረና፣ ምስራቅና ምዕራብ ጉጂ ዞኖችን እንዲሁም ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌዲዮ ዞንን የሚያገለግል ነው፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

በሪጅኑ በተፈፀመ ሥርቆት ሁለት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ወድቀዋል …………../////…………… ከለገጣፎ - ቃሊቲ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት ሁለት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች መውደቃቸውን የማዕከላዊ አንድ ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመርና ፋይበር ኦፕቲክስ ሥራ አስኪያጅ አቶ በሱፈቃድ በቀለ እንዳስታወቁት በመስመሩ ላይ ሚያዚያ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት አካባቢ በሁለት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ስርቆት ተፈፅሟል፡፡ መስመሩ ላይ የተፈፀመው ሥርቆት የግሪድ ሥርዓቱን በመረበሽ በለገጣፎና ቃሊቲ አካባቢዎች ከፍተኛ የሆነ የኃይል መቆራረጥ ማስከተሉን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ የወደቁ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን ጠግኖ ወደ ኦፕሬሽን ለማስገባት የአንድ ወር ጊዜ ያስፈልጋል ያሉት ሥራ አስኪያጁ በመስመሩ አማካኝነት ኃይል የሚያገኙ አካባቢዎች ኃይል ለማግኘት ወደ ፈረቃ ሊገቡ ይችላሉ ብለዋል፡፡ በሁለቱ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የተፈፀመውን ሥርቆት መልሶ ለመተካት ኃይል በመቋረጡ የሚታጣውን የኤሌክትሪክ ምርት ሽያጭ ሳይጨምር ተቋሙ አስከ 5 ሚሊዮን ብር የሚደርስ ኪሳራ እንደሚደርስበት ጠቅሰዋል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት 9 ወራት ውስጥ ሪጅኑ በሚያስተዳድራቸው መስመሮች ላይ ከ3 ሺህ 500 በላይ የታወር ብረቶች አካላት በሌቦች ተሰርቀዋል ያሉት አቶ በሱ ፈቃድ በዚህም በተቋሙ ላይ ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ መድረሱን ገልፀዋል፡፡ የሪጅኑ የጥገና ባለሙያ አቶ ሰይድ አስማማው በበኩላቸው በአካባቢው የሚፈፀመው ተደጋጋሚ ሥርቆት መደበኛ የጥገና ሥራዎችን ከማስተጓጎሉም በላይ ተቋሙን ለከፍተኛ ወጪ እየዳረገው እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በተለይ ከቃሊቲ - ለገጣፎ በሚያልፉ የኃይል ተሸካሚ ምሰሦዎች ላይ ስርቆቱ እጅግ የከፋ ነው ያሉት ባለሙያው አንድ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ እስከ 8 ጊዜ በሌቦች መሰረቁን ጠቅሰዋል፡፡ በኢ.ኤ.ኃ በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሪጅኖች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ እስማኤል ሙዘይን እንደገለፁት በአካባቢው የሚስተዋለውን ስርቆት ለማስቆም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች ተደርገዋል፡፡ ይሁን እንጂ የተደረጉት ውይይቶች ተጨባጭ ለውጥ አለማምጣታቸውን ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ የአካባቢው ማህበረሰብ በመሰረተ ልማቶቹ ላይ የእኔነት ስሜት አለማዳበሩ፣ የፀጥታ አካላት ክትትል ማነስ እና የህግ መላላት በአካባቢው ለሚታየው ስርቆት በምክንያትነት ይጠቀሳሉ፡፡ ስለሆነም ማህበረሰቡ በአካባቢው የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠብቅ እና የጸጥታ አካላትም ተጠርጣሪዎችን ወደ ህግ በማቅረብ አስተማሪ ቅጣት እንዲወሰድባቸው እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

በኃይል ማመንጫ ጣቢያው የልምድና የዕውቀት ሽግግር ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ ናቸው ……...///…….... በጊቤ II የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኦፕሬሽን እና የጥገና ዘርፎች ላይ የልምድ ልውውጥ እና የዕውቀት ሽግግር ሥራዎች በስፋት እየተሰሩ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ሹመት በላቸው እንደገለፁት በጣቢያው እየተሰራባቸው የሚገኙ የልምድና የዕውቀት ሽግግር ሥራዎች ውጤታማ ሆነዋል። የጣቢያውን ሠራተኞች በኦፕሬሽን እና ጥገና ሥራዎች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት። አዳዲስ መሐንዲሶች እና የቴክኒክ ባለሙያዎች ከነባር የጣቢያው ሠራተኞች ጋር በቅንጅት እያከናወኗቸው የሚገኙ የጥገና እና የኦፕሬሽን ሥራዎች የጣቢያውን የመፈፀም አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻሻሉት መምጣታቸውን ሥራ አስኪያጁ አመልክተዋል። ዘመኑ የደረሰባቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለጥገና እና ኦፕሬሽን ሥራዎች አመቺ ሁኔታ ፈጥረዋል ያሉት አቶ ሹመት በየጣቢያዎቹ የሚገኙትን መረጃዎች ማጥናትም ለልምድና የዕውቀት ሽግግሩ አወንታዊ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመዋል። በጣቢያው የጥገና ባለሙያ የሆነችው ወ/ሪት መልካም ባወቀ እንዳለችው ጣቢያው በጽንሰ ሀሳብ ደረጃ ታውቃቸው የነበሩ ዕውቀቶችን ወደ ተግባር ለመለወጥ እንዳገዛት ተናግራለች። በኃይል ማመንጫ ጣቢያው በቆየችበት አንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ በጥገና ሥራዎች ላይ በርካታ ልምዶችና ዕውቀቶችን እያገኘች መምጣቷንም ነው የገለፀችው። የጣቢያው የጥገና ባለሙያ የሆነው አቶ ፋንታሁን እስከዚያ በበኩሉ በጣቢያው እየተከናወኑ የሚገኙ የጥገና ሥራዎች በቅንጅት የሚሰሩ መሆናቸው ውጤታማ እንዲሆኑ እንዳገዛቸው ተናግሯል። ከጣቢያው ኃላፊዎችና ከተቋሙ የቴክኒክ ድጋፍ ክፍል የተለያዩ ሙያዊ እገዛዎች እየተደረገላቸው እንደሚገኝም ነው አቶ ፋንታሁን ያመለከተው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

የቋሚ ኮሚቴው አባላት በተቋሙ የመስክ ምልከታ አደረጉ ..........//......... የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መ/ቤት በመገኘት የመስክ ምልከታ አድርገዋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ፕ/ር መሐመድ አብዱ እንደገለፁት የቋሚ ኮሚቴው የከተማ የመስክ ምልከታ ዓላማ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እየሰራ ያለውን ሥራ በአካል ተገኝቶ በማየት ጠንካራና ደካማ ጎኖችን ለይቶ ድጋፍ እና ግብረ መልስ ለመስጠት ነው። የመስክ ምልከታው በተቋሙ የሚነሱ፣ ለሥራ እንቅፋት የሆኑና ከመንግስት ከፍተኛ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን በመለየት ለሚመለከተው አካል አቅርቦ ክትትል ለማድረግ እንደሚረዳ ገልጸዋል። የተቋሙ የኮርፖሬት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዷለም ሲዓ የተቋሙን የዘጠኝ ወር እቅድ አፈጻጸም፣ ዋና ዋና የትኩረት መስኮችና ስትራቴጅካዊ ግቦች ለውይይት መነሻ በሚሆን መልክ ለቋሚ ኮሚቴው አባላት አቅርበዋል። የቋሚ ኮሚቴው አባላትም ተቋሙ ከኃይል ማመንጫዎችና ማስተላለፊያ መሰረተ ልማቶች ግንባታ፣ ከፕሮጀክቶች አፈጻጸም፣ ምቹ የሥራ ከባቢን ከመፍጠርና ኃይል ለጎረቤት ሀገራት ከማቅረብ አኳያ ያከናወናቸው ተግባራት አበረታች መሆናቸውን አንስተዋል። የገቢ አሰባሰብና ብድር አመላለስ፣ ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ፣ የኃይል ምንጮችን ማብዛት እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራርንና የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግ በተቋሙ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸዋል። የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ስርቆት በዘላቂነት ለመከላከል የሌሎች ሀገራትን ልምድ በመውሰድ ጭምር ሊሰራ እንደሚገባ የቋሚ ኮሚቴ አባላቱ አሳስበዋል። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የፀጥታ አካላትና እና በየአካባቢው ያሉ የመስተዳድር አካላት በትኩረት መስራት አለባቸው ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር በበኩላቸው ተቋሙ ሀገራችን በኃይል ራሷን እንድትችል ከማድረግ ባሻገር ለጎረቤት ሀገራት በመሸጥ “በአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን” አቅዶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተቋሙ የቋሚ ኮሚቴ አባላቱ በመስክ ምልከታ ወቅት ያነሷቸውን ሀሳቦችና አስተያየቶችን እንደግብዓት በመውሰድ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡ የኃይል መቋረጥ በሚያጋጥምበት ወቅት የማከፋፊያ ጣቢያዎችን በማይጎዳ መልኩ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመናበብ ጥገና እንደሚከናወን የተናገሩት ኢንጂነር አሸብር በአንዳንድ አካባቢዎች በታችኛው መዋቅር ባሉ ሠራተኞች አለመናበብ ሊኖር እንደሚችል ጠቁመዋል። በእንዲህ ዓይነት መንገድ የሚፈጠሩ ችግሮች በሁለቱ ተቋማት መካከል የኃላፊነት መጣረስ ያለና ቅንጅታዊ አሰራሩ የላላ እያስመሰለው ይገኛል ብለዋል። የማከፋፊያ ጣቢያዎችን ተደራሽነት በተመለከተ ተቋሙ በሚሰራቸው አዳዲስ ፕሮጀክቶች ለመመለስ በፌደሬሽን ምክር ቤት ቀመር አስወስኖ እየሰራ መሆኑን ኢንጅነር አሸብር ገልጸዋል። ተቋሙ የተጣለበትን ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት ለመወጣትና በኃይል ዘርፍ ሥር ነቀል ለውጥ ለማምጣት በሙሉ አቅሙ እየሰራ መሆኑን የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈፃሚው የቋሚ ኮሚቴ አባላቱ ሁለንተናዊ ድጋፍ እንዳይለያቸው ጠይቀዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሚያዚያ 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

ፕሮጀክቱ የሠራተኞችን የሥራ ላይ ደህንነት በጠበቀ መልኩ እየተከናወነ ነው .........///……….. የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ፕሮጀክት ለሠራተኞች የሥራ ላይ ደህንነት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የአካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ እንደገለፁት በፕሮጀክቱ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ሠራተኞችን ደህንነት ለማረጋገጥ ጠንካራ የድህንነት መመሪያዎች ተግባራዊ እየተደረጉ ነው። ፕሮጀክቱ በግንባታው ላይ እየተሳተፉ ለሚገኙ ሠራተኞች እንደየሥራቸው ሁኔታ ደረጃቸውን የጠበቁ የአደጋ መከላከያ መሳሪያዎችን እያቀረበ እንደሚገኝ ተናግረዋል። "ቅድሚያ ለድህንነት" የሚለውን መሪ ቃል ተግባራዊ ለማድረግ ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል እየተደረገ መሆኑንም ነው አቶ ግዛቸው የጠቀሱት። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በሥራ ወቅት የተሽከርካሪ አደጋዎች እንዳይከሰቱ ለማድረግ በየቦታው የተለያዩ የትራፊክ ምልክቶችን በማስቀመጥና በሳይቱ ውስጥ የሚገኙ መንገዶችን ጥራት በማስጠበቅ የሥራ ላይ ደህንነት በጥንቃቄ እንዲመራ ተደርጓል። በሳይቱ ውስጥ ለሚገኙ ሠራተኞች ከክፍያ ነፃ የተሟላ የጤና አገልግሎት የሚሰጡ 3 ክሊኒኮች ከበቂ ባለሙያዎችና መሳሪያዎች ጋር መኖራቸውንም ነው የጠቆሙት። በግንባታ ተቋራጩ ዊ ቢውልድ የሳይት የሴፍቲ ሱፐርቫይዘር አቶ ሙሉቀን ተከስተ በበኩላቸው ሥራ ተቋራጩ በዓለም ላይ ካሉት 36 ቅርንጫፎች ውስጥ በሥራ ላይ ደህንነት የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በ3ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በፕሮጀክቱ በሁሉም የግንባታ ዘርፎች ላይ የተቀመጡ የሥራ ላይ ደህንነት ፖሊሲዎችና መመሪያዎች ተግባራዊ እንዲደረጉ የቁጥጥር ሥራ እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። የሠራተኞችን የሥራ ላይ ደህንነት ለማረጋገጥ በአደጋ መከላከያ መንገዶችና በሥራ ቦታዎች አካባቢ ስለሚኖሩ እንቅስቃሴዎች እንዲሁም ከደህንነት መሳሪያዎች አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ተከታታይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎች እየተሰጡ እንደሚገኙም ነው አቶ ሙሉቀን የገለፁት። እንደ አቶ ሙሉቀን ገለፃ በሳይቱ ውስጥ የሚገኙ የኮንትራክሽንና መሰል ተሽከርካሪዎች ከተፈቀደላቸው የፍጥነት ወሰን በላይ እንዳያሽከረክሩ ለማድረግ በትራፊክ ፖሊሶችና በፍጥነት መቆጣጠሪያ ራዳር በመታገዝ ቁጥጥር እየተደረገ ነው። በፕሮጀክቱ የአልኮል መጠጥና ሌሎች አደንዛዥ ዕፆችን ተጠቅመው የሚያሽከረክሩ የመኪና አሽከርካሪዎችን ለመለየት በሥራ ቦታዎች ላይ ድንገተኛ የጤና ምርመራ እንደሚደረግም ነው ሱፐርቫይዘሩ ያመለከቱት። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 16 ቀን 2016 ዓ.ም