uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 544 підписників, посідаючи 8 357 місце в категорії Технології та додатки та 2 176 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 544 підписників.

За останніми даними від 01 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 22, а за останні 24 години на 4, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 25.24%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 16.50% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 921 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 563 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 9.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 02 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 544
Підписники
+424 години
-357 днів
+2230 день
Архів дописів
photo content
+2

ክፍት የሥራ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የሥራ መደቦች ላይ ክፍት የሥራ ማስታወቂያ አውጥቷል፡፡ መስፈርቶቹን የምታሟሉ አመልካቾች እንድትወዳደሩ ተጋብዛችኋል፡፡ ለማመልከት ከዚህ ማስታወቂያ ጋር የተያያዘውን ሊንክ (ማስፈንጠሪያ) ይጠቀሙ፡፡ መልካም ዕድል!https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdRiPcfzTOiv-VCy-KdPDpouo3IMeJQqwh6psmFtro7nghBYg/viewform?usp=sf_link OR https://forms.gle/pwcY62VrCUYcnDNH8

photo content
+7

የፕሮጀክቱ ግንባታ 82 በመቶ ተጠናቋል …......////............ የባህርዳር – ወልዲያ – ኮምቦልቻ ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ አፈፃፀም 82 በመቶ መድረሱን የፕሮጀክቱ ሪዚደንት መሐንዲስ አቶ ሀብታሙ ተሾመ አስታወቁ። አቶ ሀብታሙ እንደገለፁት ከባህርዳር እስከ ወልዲያ እንደሚተከሉ ከሚጠበቁት 640 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ውስጥ የ 593 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ተከላ ተጠናቋል፤ ቀሪ ምሰሶዎችን ለመትከል የሚያስችሉ ሥራዎችም እየተከናወኑ ነው ብለዋል። ከባህርዳር እስከ ወልዲያ የኮንዳክተር ገመድ ለመዘርጋት ከታሰበው 295 ነጥብ 87 ኪሎ ሜትር ውስጥ 121 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ማጠናቀቅ መቻሉንም ነው አቶ ሀብታሙ የተናገሩት። በተለያዩ ችግሮች የዘገዩ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የመሠረት ቁፋሮ ግንባታዎች፣ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ተከላ እና የኮንዳክተር ገመድ ዝርጋታ ሥራዎች በቀጣይ የሚሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የወሰን ማስከበር ችግሮች፣ በፕሮጀክቱ ሠራተኞች ላይ የፀጥታ ስጋቶች መኖር እና በኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶችና ሽቦዎች ላይ የስርቆት ወንጀሎች መስፋፋት ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ አሉታዊ ጫና መፍጠራቸውን ነው አቶ ሀብታሙ የገለፁት። ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ችግሮች የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ከሚያልፍባቸው የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ እና የቀበሌ አመራሮች ጋር ተደጋጋሚ ውይይት እየተደረገ እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ሀብታሙ የፀጥታ ስጋቶችን እና የስርቆት ወንጀሎችን ለመቀነስም የደቡብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ ኃላፊነቱን ወስዶ እንደሚሰራ ቃል መግባቱን ጨምረው ተናግረዋል። እንደ አቶ ሀብታሙ ገለፃ ፕሮጀክቱ የባህርዳር፣ የደቡብ ጎንደር፣ የሰሜን እና ደቡብ ወሎ ዞኖችን የሚያካልል በመሆኑ በየደረጃው ያሉ አመራሮች ችግሮቹን በመፍታት ለግንባታው መፋጠን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ ይገባል። ግንባታውን ታታ ፕሮጀክትስ ሊሚትድ (TATA PROJECTS LTD) የተባለው የህንድ ኩባንያ እያከናወነው ሲሆን በአማካሪነት ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢንጂነሪንግ ቢሮ እየተሳተፈበት ይገኛል። ለኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ግንባታ ከ97 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር እና ከ886 ሚሊየን ብር በላይ ተመድቦለታል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 05 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

ፕሮጀክቱ የከተማዋን የኢንቨስትመንት እና ቱሪዝም አቅም እንደሚያሳድግ ተገለፀ ……...///…….... የአዘዞ - ጭልጋ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት መገንባት የከተማዋን የኢንቨስትመንት እና ቱሪዝም አቅም እንደሚያሳድግ የጎንደር ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። የከተማዋ ምክትል ከንቲባ አቶ ባዩ አቡሃይ እንደገለፁት አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ጎንደርን የኢንቨስትመንት እና የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ ድርሻው የጎላ ነው። በከተማዋ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማሻሻያ እና አቅም የማሳደግ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የአዘዞ - ጭልጋ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመር በተወሰነ ደረጃ በከተማ አስተዳደሩ ሥር እንደሚገኝ የጠቀሱት አቶ ባዩ ፕሮጀክቱ አገልግሎት መስጠት በሚጀምርበት ሰዓት ከተማዋ ሰፊ የኢንቨስትመንት አቅም እንደሚኖራት ገልፀዋል። የፕሮጀክቱ መገንባት ለጎንደር ከተማ ብቻ ሳይሆን በአካባቢው ለሚገኙ እንደ ጭልጋ፣ መተማ እና ወልቃይት ጠገዴ ላሉ አካባቢዎች ፋይዳው የጎላ መሆኑንም ነው የጠቆሙት። ከአዘዞ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጣቢያ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ቀጥታ ወደ ኢንዱስትሪ መንደሮች የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ይስተዋል የነበረው የኃይል መቆራረጥ ችግር መቅረፍ መቻሉንም ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዳይጠናቀቅ የወሰን ማስከበር ሥራዎች ማነቆ ሆነው መቆየታቸውን ያስታወሱት ምክትል ከንቲባው የልማት ተነሺ የማህበረሰብ ክፍሎች ቁጥር መብዛት ዋነኛ ችግር እንደነበር ጠቁመዋል። የከተማ አስተዳደሩ በአሁኑ ሰዓት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ከክፍለ ከተሞች የተውጣጣ ኮሚቴ አቋቁሞ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝም ገልፀዋል። በ15 ቀናት ውስጥ ለልማት ተነሺ የማህበረሰብ ክፍሎች ምትክ መሬት በመስጠት ቦታውን ለፕሮጀክቱ ግንባታ ምቹ የማድረግ ሥራ ይሰራልም ብለዋል። እንደ አቶ ባዩ ገለፃ የወሰን ማስከበር ሥራዎችን እስካሁን ማጠናቀቅ ያልተቻለው ፕሮጀክቱ የዲዛይን ለውጥ ማድረጉ፣ የልማት ተነሺዎችን በቂ መረጃ አለመደራጀቱ፣ ፕሮጀክቱ የእምነት ተቋማትን መንካቱ እና ምትክ መሬት የተሰጣቸው ግለሰቦች ቦታ የማማረጥ ችግሮች ስለነበሩባቸው ነው። የፕሮጀክቱን ግንባታ ለማፋጠን የህጋዊነት ጥያቄ የነበረባቸውን ቦታዎች በማጥናትና ከክልል ቢሮ ጋር በመነጋገር የይዞታ ካርታ እንዲያገኙ የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን ጨምረው ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለጎንደር ከተማ የኢንቨስትመንት ፍሰት መጨመር እና ለቱሪዝም ዕድገት እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 04 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+7

በተቋሙ ለሴቶች እኩልነት የተሰጠው ትኩረት የሚበረታታ ነው ……..///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሴቶች እኩልነት የተሰጠው ትኩረት የሚበረታታ መሆኑን በተቋሙ የሴቶች፣ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ ዳይሬክተር አስታወቁ፡፡ ዳይሬክተሯ ወይዘሮ ሌንሴ ኢደኤ ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን ኮተቤ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቢሮ "እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ" በሚል መሪ ቃል ሲከበር እንደገለፁት ሴቶችን ወደ ኃላፊነት በማምጣት እና በማብቃት በኩል ተቋሙ በትኩረት ሊሰራ ይገባል፡፡ ወደ ስምንት ሺህ ከሚጠጉ የተቋሙ ሠራተኞች ውስጥ የሴቶች ቁጥር 1 ሺህ 256 ብቻ መሆኑን የጠቀሱት ዳይሬክተሯ የሴት ሰራተኞችንና የሴት አመራሮችን ቁጥር ለማሳደግ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሪጅን 2 የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አለማይሁ ዘበርጋ እንደገለፁት በተቋሙ በሁሉም የሥራ ዘርፎች የሴቶች ድርሻ ወሳኝ ነው፡፡ በተቋሙ ሴቶች ወደ ኃላፊነት እንዲመጡና በሥራቸው እንዲታገዙ በማድረግ ሁሉም የበኩሉን መወጣት እንዳለበት ተመሳሳይ ግንዛቤ ሊያዝበት ይገባል ብለዋል፡፡ በተቋሙ የማዕከላዊ ሪጅን 3 የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድርያስ በበኩላቸው በሴቶች ጉዳይ እየተሰራበት ያለውን የእኩልነት መርህ (equality) ወደ ትክክለኛነት (equity) መርህ ማሳደግና የተቋሙን ሴት ሠራተኞች ወደ ተገቢው ቦታ ለማምጣት በትጋት መሰራት አለበት፡፡ በተቋሙ የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ተስፋዬ ዮሐንስ፣ በኢትዮጵያ "ሥርዓተ ፆታ እና በሴቶችና በወንዶች መካከል ያለው አተያይ" በሚል ርዕስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ጽሑፍ አቅርበው ውይይት ተካሂዶበታል፡፡ በዓሉ ማጠናቀቂያ ላይ የተካሄደውን የጥያቄና መልስ ውድድር ወይዘሪት ሳባ ወ/አረጋይ በማሸነፍ የመፅሐፍ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን በዓለምአቀፍ ደረጃ ለ112ኛ፤ በሀገራችን ደግሞ ለ47ኛ ጊዜ ተከብሯል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 03 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+9

በበለስ-ደ/ማርቆስ- ሱሉልታ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመ የስርቆት ወንጀል ጉዳት ደረሰ ........///......... በበለስ-ደ/ማርቆስ- ሱሉልታ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በተፈፀመ የስርቆት ወንጀል ጉዳት መድረሱን የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው የጥገና ባለሙያ አቶ አደባባይ አቻው እንደገለፁት በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችና ሽቦዎች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎች ተበራክተዋል። በቅርቡም በበለስ -ደ/ማርቆስ - ሱሉልታ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በተፈፀመ ዝርፊያ መስመሩ አደጋ ላይ መውደቁን ገልፀዋል። ዝርፊያው የተፈፀመው በተለምዶ አባይ በረሃ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ  እንደሆነ የገለፁት አቶ አደባባይ በአንድ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል። ጉዳት የደረሰበትን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ የመጠገን  ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ባለሙያው ገልፀዋል። በተፈፀመው ዝርፊያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተሸካሚ ምሰሶ አንድ እግር ከነባር ቦታው ሰባት ሜትር ወደ ጎን ቢንሸራተትም የብረት ምሰሶው ተጨማሪ ጉዳት እንዳይደርስበትና ኃይል እንዳይቋረጥ ለማድረግ የመበየድ ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል። የስርቆት ወንጀሉን እንደፈፀሙ የተጠረጠሩ ግለሰቦች በህግ  ጥላ ስር ውለው ምርመራ እየተካሔደባቸው እንደሚገኝም ነው አቶ አደባባይ የጠቀሱት። በከፍተኛ የፋይናንስ ወጪ ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ በሚገኙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከቱ መጥተዋል። በተለያዩ አካባቢዎች አገልግሎት እየሰጡ በሚገኙ የ132፣ 230 እና 400 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች እና ሽቦዎች በሌቦች በተደጋጋሚ በመዘረፋቸው ሳቢያ ለከፋ ጉዳት እየተዳረጉና ለኃይል መቋረጥ ምክንያት እየሆኑ ነው። እንደ ባለሙያው ገለፃ በክልሉ መንግሥት፣ በህብረተሰቡና በባለድርሻ አካላት ትብብር የስርቆት ወንጀሉን ለመከላከል የተለያዩ ጥረቶች ቢደረጉም ችግሩ ግን ተባብሶ ቀጥሏል። ከስርቆት ወንጀሉ ጋር በተያያዘ ተከሰው ፍርድ ቤት በሚቀርቡ ተጠርጣሪዎች ላይ የሚተላለፈው የቅጣት ውሳኔ አስተማሪና ወንጀል ፈፃሚዎችን ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ የሚያደርግ ባለመሆኑ ለወንጀሉ መበራከት ምክንያት ሊሆን እንደቻለ ግምታቸውን ገልፀዋል። ብረታ ብረቶችን በግብዓትነት የሚጠቀሙ፣ ስርቆቱን የሚደግፉና የሚረከቡ የብረታብረት ፋብሪካዎችና ባለሀብቶች እንቅስቃሴ ሊፈተሸ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡   “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 01 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

በማስተላለፊያ መስመሮቹ ኮሪደር አካቢቢ ምንጣሮ ለማከናወን ስምምነት ተፈረመ .........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከህዳሴ እስከ ሆለታ ከተዘረጉ ሁለት ባለ 500 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ማስተላለፊያ መስመሮች ውስጥ ከዳቡስ ወንዝ እስከ ደዴሳ ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ በተዘረጉ የመስመሮቹ ኮሪደር ላይ የሚገኙ ዛፎችን ለመመንጠር በማህበር ከተደራጁ የአካባቢው ወጣቶች ተወካዮች ጋር ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ስምምነቱን በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ዘርፍ የፕሮጀክቶች የዕቅድ ክትትል አስተባባሪ አቶ ልብሰወርቅ አስፋው እና የፕሮግራም 1 መምሪያ ዳይሬክተር ተወካይ ወ/ሮ የትናየት ይመር እና የማህበራቱ ተወካይ ወጣቶች ተፈራርመዋል፡፡ በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ዘርፍ የፕሮጀክቶች የዕቅድ ክትትል አስተባባሪ አቶ ልብሰወርቅ አስፋው እንደተናገሩት መስመሮቹ በሚያልፉባቸው የምዕራብ ወለጋ አካባቢዎች ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት በመስመሮቹ ግራና ቀኝ ኮሪደር ላይ ያሉ ዛፎችን ማጽዳትና እና የኢንስፔክሽን ሥራዎችን ማከናወን ባለመቻሉ ከህዳሴ ግድብ እየመነጨ ያለውን ኃይል በመስመሩ ማስተላለፍ አልተቻለም፡፡ ከግድቡ በአሁኑ ወቅት እየመነጨ ያለው ኃይል በጣና በለስ መስመር ላይ እየተላለፈ ወደ ብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል (ግሪድ) ሲገባ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ የተካሄደው ስምምነት ሁለቱንም መስመሮች ለሥራ ዝግጁ በማድረግ ከህዳሴ ግድብ እየመነጨ ያለውን ኃይል በመስመሮቹ እንዲተላለፍ ለማድረግ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል፡፡ ስምምነቱ መስመሮቹን በማጽዳት ለሥራ ዝግጁ ከማድረግ በተጨማሪ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም አመልክተዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ዛፍ የማጽዳት ሥራ በተቋሙ ሠራተኞች አቅም ማከናወን ባለመቻሉ በአካባቢው በማህበር ለተደራጁ ወጣቶች መስጠት አስፈልጓል። ወጣቶቹ ሥራውን ተቋሙ በሚሰጣቸው መመሪያ መሰረት እንዲያከናውኑ ለማድረግ ሥልጠና መሰጠቱንና በሥራው ላይ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ከመግባባት ላይ መደረሱን ጠቁመዋል። ሥራውን ለማከናወን በአምስት ዋና ቡድን እና በ25 ንዑሳን ቡድን የተዋቀረ 500 የሚሆኑ ወጣቶች እንደሚሳተፉበትም አቶ ልብሰወርቅ ተናግረዋል፡፡ በእያንዳንዱ መስመር 260 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን እና ከመስመሩ በግራና ቀኝ በ 60 ሜትር ኮሪደር የሚከናወነውን ምንጣሮ በሁለት ወራት ውስጥ አጠናቆ ለማስረከብ ከወጣቶች ጋር ከስምምነት መደረሱን አስተባባሪው አንስተዋል፡፡ ምንጣሮውን ለማከናወን የ49 ሚሊዮን ብር ስምምነት መደረጉንም አቶ ልብሰወርቅ ጠቁመዋል፡፡ የማህበራቱ አስተባባሪ ወጣት አብዱልቃድር ዘይኑ በበኩሉ ሥራው ለአካባቢው ወጣቶች ለሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ በሀገራዊ ፕሮጀክት ላይ ለመሳተፍ ዕድል ስለፈጠረላቸው መደሰታቸውን ተናግሯል፡፡ በአሁኑ ወቅት ማህበራቱ ለሥራው የሚያስፈልጉ መሳሪያዎችን እና የሰው ኃይል እንዳዘጋጁ እና ሥራውን በተባለው ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩም አስተባባሪው አረጋግጧል፡፡ የህዳሴ-ዴደሳ-ሆለታ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ሲኢቲ በተሰኘ የቻይና ኩባንያ የተገነባ ሲሆን ለፕሮጀክቱም 28 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበት ግንባታው ታህሳስ 2008 ዓ.ም መጠናቀቁ ይታወሳል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 30 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+9

ተቋሙ ከኢቢሲ ጋር በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመ ........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እያከናወናቸው ያሉ የኃይል መሰረተ ልማቶቸን ለህብረተሰቡ ለማስተዋወቅ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ስምምነቱ ተቋሙ እያከናወናቸው ያሉ ሥራዎችን በዜና፣ በዶክመንታሪ ፕሮግራሞች እንዲሁም የተለያዩ የማስታወቂያ መልዕክቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግን እንደሚያጠቃልል በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ ሥምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍሰሃ ይታገሱ ተፈራርመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ በፊርማ ስነ-ሥነርአቱ ወቅት እንደተናገሩት ተቋሙ የሚሰራውን ሥራ ለህብረተሰቡ ለማዳረስ የሚዲያ ተቋማት ከፍተኛ ሚና ይጫወታሉ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አንጋፋ የኃይል አቅራቢ ተቋም ቢሆንም በህግ የተሰጠው ኃላፊነት በህብረተሰቡ ዘንድ እየታወቀ እንዳልሆነም ጠቁመዋል፡፡ በሀገሪቱ አንጋፋ የመንግስት የሚዲያ ከሆነው ኢቢሲ ጋር በጋራ ለመስራት ስምምነት መደረጉ ተቋሙ እያከናወናቸው ያሉ የኃይል መሰረተ ልማት ሥራዎችን በቴሌቪዥንና በሬዲዮ ቻናሎች ለህብረተሰቡ እንዲደርሱ በማድረግ የተቋሙን መልካም ገጽታ ለመገንባት ያግዛል ብለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ሥምምነቱ ተቋሙ እያከናወናቸው በሚገኙ መሰረተ ልማቶች ላይ እየደረሱ ያሉ ስርቆቶችን ለመከላከል በሚሰራው ሥራ ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር እንደሚረዳ ነው የተናገሩት። የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍስሃ ይታገሱ በበኩላቸዉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተለያዩ የኃይል ምንጮች ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ጨለማን በብርሃን ለመተካት በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ ቢሆንም ተቋሙ እየሰራው ያለው ሥራ በህዝብ ዘንድ በአግባቡ እየታወቀ እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሚዲያ በተቋም ገፅታ ግንባታ ሥራ ውስጥ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት እየሰራ ያለውን ሥራ በብሔራዊ ሚዲያው ለማስተዋወቅ ኢቢሲን በመምረጡ ደስተኛ ነን ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋይናንስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩት ከ624 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት ያፈራው ተቋሙ ከኢቢሲ ጋር አብሮ መስራቱ ህብረተሰቡ የጋራ መገልገያ የሆኑትን የኤሌክትሪክ መሰረተልማቶች በኃላፊነት ስሜት እንዲጠብቅ ግንዛቤ ለመፍጠር ያግዛል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የገበያ ልማት ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዮሴፍ ዮናስ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ራሱን ችሎ ከተቋቋመ በኋላ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ያለውን ልዩነት ህብረተሰቡ በግልጽ እየተረዳ ባለመሆኑ ስምምነቱ ስለ ተቋሙ ግልጽ መረጃ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግና ተቋሙን ለማስተዋወቅ ይረዳል ብለዋል፡፡ ተቋማቱ በጋራ የመስራት ስምምነት ከዳር እንዲደርስ ሲሰሩ የነበሩ የሥራ ኃላፊዎችንም አመስግነዋል፡፡ በኢቢስ የዜና ቻናል ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ አቶ ሁናቸው ታዬ እንደገለጹት በተካሄደው ስምምነት መሰረት ሥራውን ማከናወን የሚችሉ ሠራተኛችን ከመመደብ ጀምሮ ዝግጅት ተደርጓል፡፡ የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች በቀጣይ በኢቢሲ ኮምፕሌክስ ስቱዲዮ ላይ የሚከናወነውን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ጨምሮ በሌሎች ጉዳዮች ላይ በጋራ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 29 ቀን 2015 ዓ.ም

ማርች 8 አስመልክቶ የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች መምሪያ መልዕክት የዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን ክብረ በዓል መነሻ የሥራ ሰዓት ይሻሻል፣ የተሻለ ክፍያ ይኑር፣ ሴቶች በምርጫ ይሳተፉ የሚለውን የመብት ጥያቄ ያነገቡ 15 ሺህ የሚሆኑ ሴቶች አደባባይ መውጣታቸው ነበር፡፡ በሀገራችንም ለዘመናት በህብረተሰቡ ውስጥ ሰርጸው በቆዩት ኋላቀር አመለካከቶች፣ ጎጂ ልማዶችና እምነቶች ውጤት በሆነው የተዛባ የሥርዓተ-ጾታ አመለካከት ምክንያት የሴቶች ማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ከወንዶች ጋር ሲነጻጻር እጅግ በጣም ዝቅተኛ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች መምሪያ ከተሰጡት ኃላፊነቶች ውስጥ በዋናነት የሥርዓተ-ፆታ ጉዳይ በሁሉም የሥራ ሂደቶች ከመነሻ እስከ ፍጻሜ ድረስ ባሉ የሥራ ፍሰቶች እንዲካተት ድጋፍ በማድረግ፣ አፈጻጸሙንም በመገምገም በድርጅቱ የሥርዓተ-ፆታ ክፍተቶች እንዲጠቡና የሴቶች መብቶች እንዲከበሩ፣ ፍትሃዊ የሆነ የሥርዓተ-ፆታ ግንኙነት በተቋሙ ውስጥ እንዲሰፍን በማድረግ የሥርዓተ-ፆታ እኩልነት በማምጣት የድርጅቱ ሴት ሰራተኞች ከወንዶች ጋር እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ ማድረግ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል፡፡ ከነዚህም መካከል በዋና መ/ቤት አገልግሎት መስጠት የጀመረው እና በሌሎች ሪጅኖች ላይ ለማስጀመር ሂደት ላይ ያለዉ የህጻናት ማቆያ ማዕከል የድርጅቱ ሴት ሠራተኞች ከወሊድ በኃላ ወደ ስራ ገበታቸው በሚመለሱበት ወቅት ህጻን ልጆቻቸውን በቅርበት እየተከታተሉና እየተንከባከቡ መስራት እንዲችሉ፣ በልጆቻቸው ምክንያት ከስራ ገበታቸው እንዳይቀሩ ፣ በተመደቡበት የሥራ መስክ ያለምንም ስጋትና ሀሳብ ሙሉ ኃይላቸውን፣ ትኩረታቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ዕውቀታቸውንና ጊዜያቸውን ተጠቅመው ውጤታማ ስራ እንዲሰሩ በማስቻል የሴቶችን ውሳኔ ሰጭነትና የአመራር ሚናቸውን ለማሳደግ የተሰሩ ስራዎች ናቸው፡፡ የዘንድሮውም አለም አቀፍ የሴቶች ቀን ‹‹እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ›› በሚል መሪ ቃል በሀገራችን ለ47ኛ ጊዜ የሚከበር ሲሆን እንደሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ ሴቶች ከወንዶች በተለየ መልኩ በሚደርስባቸው የስራ ጫናና መድሎ ምክንያት ዝቅተኛ የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነት እንዲኖራቸው ሆኗል፡፡ በመሆኑም ይህንን ችግር ለመቅረፍ በድርጅታችን እየተደረጉ ያሉ የድጋፍ እርምጃዎች እጅግ አበረታች በመሆናቸው ለዚህ ሁሉ ድጋፍ የድርጅቱን ከፍተኛ ማኔጅመንትና መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ስራ አስፈጻሚ አባላትን በድርጅቱ ሴት ሠራተኞችና አመራሮች ስም ማመስገን እወዳለሁ፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ47ኛ ጊዜ‹‹ እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ›› በሚል መሪ ቃል የሚከበረውንና የሴቶችን ጉልህ ሚና ለሀገራዊ ሰላም ግንባታ፣ ሀገር በቀል የሥራ ፈጠራ ውጤቶች ለሴቶች ኢኮኖሚያዊ ብቃት፣ ፈጠራንና ቴክኖሎጂን በመጠቀም የሥርዓተ-ጾታ እኩልነትን እናረጋግጥ፣ ሁለንተናዊ የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለሰብዓዊ መብት መከበር እና የሴቶችን እምቅ አቅም በመጠቀም ሀገርን እንገንባ በሚል ዓላማ የሚከበር መሆኑን አውቀን ሁላችንም የድርጅቱ ሠራተኞችና አመራሮች ለዚህ ስኬት በጋራ እንስራ እላለሁ፡፡ እንኳን ለሴቶች ቀን አደረሳችሁ! አደረሰን! ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ - የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች መምሪያ ዳይሬክተር

photo content

ዛሬ ማርች 8 ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን ነው። ዕለቱ እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ በሚል መሪ ቃል ይከበራል። ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች ሴቶችን በተመለከ ያሉ አሃዛዊ መረጃዎች ምን እንደሚመስሉ እናሳያችሁ። • በዓለማችን ከ3 ሴቶች አንዷ በህይወት ዘመኗ ትደፍራለች፣ ዕድሜቸው ከ15 እስከ 44 የሆኑ ሴቶች ከካንሰር፣ ከጦርነት፣ ከመኪና አደጋና የወባ በሽታ ይልቅ አስገድዶ የመደፈር ስጋት ያሳስባቸዋል፣ በየደቂቃው አንድ እናት በወሊድ ምክንያት ትሞታለች (UN) • በአሁኑ ወቅት በዓለማችን 700 ሚሊዮን ያህል ሴቶች ዕድሜያቸው 18 ዓመት በታች ሆነው ያገቡ ሲሆን 250 ሚሊዮን ሴቶች ደግሞ ዕድሜያቸው 15 ዓመት በታች ሆነው ያገቡ ናቸው (UNICEF) • በየዓመቱ በዓለም ላይ ከ600-800 ሺህ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውሮች ይካሄዳሉ፡፡ ከሚካሄደው የህገ ወጥ ሰዎች ዝውውር ከአምስት አራቱ ሴቶች ነው፡፡ (Trafficking.org) • በየአመቱ 62 ሚሊዮን ሴቶች የትምህርት ዕድል አያገኙም፣ የዓለማችን116 ሚሊዮን ሴት ተማሪዎች (25 በመቶ ያህሉን የሴት ተማሪዎችን ቁጥር ይዛል) ይሁንና አንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አያጠናቅቁም፣ በዓለማች ለሴቶች የሚከፈለው ክፍያ ከወንዶች አንጻር ከ60-75 በመቶ ያነሰ ነው (PBS) • 155 ሀገራት ሴቶችን ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚገድብ ህጎች ሲኖራቸው 100 ሀገራት ደግሞ ሴቶች የሚሰሩትን የስራ ዓይነት ገድበዋል (The Guardian) • በዓለማች 200 ሚሊዮን ሴቶች በግዳጅ ይገረዛሉ (WHO) “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 29 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

የወሰን ማስከበር ሥራዎች የልማት ተነሺዎችን መብት እና ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ መከናወኑን መከታተል ይገባል .....///..... በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ የአካባቢና ማህበራዊ ጥበቃ ባለሙያዎች ቡድን የአዘዞ - ጭልጋ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ያለበትን ደረጃ ጎብኝቷል። በባለሙያዎቹ የተመራው የልዑካን ቡድን በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይ የአካባቢ እና ማህበራዊ ጥበቃ ሥራዎችን በመስክ በመገኘት ገምግሟል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቱ የአካባቢ፣ ጤና እና የሙያ ደህንነት ባለሙያ አቶ ኡስማን በንክሪ እንደገለፁት የጉብኝቱ ዋና ዓላማ በዓለም ባንክ የፋይናንስ ድጋፍ የሚገነባውን ፕሮጀክት የአካባቢ እና ማህበራዊ ጥበቃ ሥራዎች እንዲሁም የካሳ ክፍያ ጥያቄዎች ያሉበትን ደረጃ ለመገምገም ነው። የጎንደር ከተማ አስተዳደር ለልማት ተነሺ የማህበረሰብ ክፍሎች ምትክ መሬት ሳይሰጥ መዘግየቱ በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ጫና ስለማሳደሩ በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል። በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ የአካባቢ እና ማህበራዊ ጥበቃ ባለሙያዎች በበኩላቸው በካሳ ክፍያዎች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ተቋሙ እና የከተማ አስተዳደሩ በቅንጅት መስራት እንደሚጠቅባቸው ተናግረዋል። ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ጉዳዮች የከተማ አስተዳደሩ የልማት ተነሺ የማህበረሰብ ክፍሎችን መብት እና ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ ማከናወን እንደሚጠበቅበትም ነው ያሳሰቡት። የልማት ተነሺ የህብረተሰብ ክፍሎችን መልሶ ለማቋቋም የተዘጋጀው የድርጊት መርሃ ግብርን (RAP) ዝርዝር መስፈርቶችን ባሟላ መልኩ የካሳ እና የምትክ መሬት ጥያቄዎች እንዲመለሱላቸው የባንኩ ባለሙያዎቹ አሳስበዋል። በፕሮጀክቱ በአማካይ ከ200 በላይ የሚሆኑ የልማት ተነሺዎች እንደሚገኙ የተጠቆመ ሲሆን ተቋሙ ለአብዛኛዎቹ የመሬት ባለይዞታዎች የካሳ ክፍያዎችን መፈፀሙና አብዛኛዎቹ መነሳታቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል። ዓለም ባንክ ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ የሚሆነውን የፋይናንስ ወጪ የብድር አቅርቦት ሙሉ በሙሉ እንዳመቻቸ ከዚህ ቀደም ሲል መዘገባችን ይታወሳል። የጭልጋ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የፍተሻ ስራ የተጠናቀቀ ሲሆን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ የሙከራ ሥራ ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል። በጉብኝቱ ላይ በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ የአካባቢና ማህበራዊ ጥበቃ ባለሙያዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ተገኝተዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 29 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+6