uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 537 підписників, посідаючи 8 368 місце в категорії Технології та додатки та 2 174 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 537 підписників.

За останніми даними від 30 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 10, а за останні 24 години на -6, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 24.86%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 16.87% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 862 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 620 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 9.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 01 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 537
Підписники
-624 години
-207 днів
+1030 день
Архів дописів
የጣና በለስ- ባህር ዳር የማስተላለፊያ መስመር ላይ ስርቆት ተፈጽሟል .........///......... በጣና በለስ- ባህር ዳር የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች ላይ ስርቆት እንደተፈፀመባቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጂን የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እንዳስታወቁት በመስመሩ ላይ ከተተከሉ የኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎች መካካል በሁለቱ ላይ ሐምሌ 23 ተቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሠዓት አካባቢ በተፈፀመባቸው ስርቆት ወድዋል። ከወደቁት ሁለት ምሰሶዎች በተጨማሪ በሌሎች ሁለት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ኮንዳክተሮችን የሚያገናኙት የታወር አካላት መጎዳታቸውን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። የስርቆት ወንጀሉ መስመሩ በሚያልፍበት በባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ ደናሴ በሚባል ቀበሌ አካባቢ መፈፀሙንና መስመሩ ሙሉ በሙሉ ኃይል ማስተላለፍ ማቋረጡን ተናግረዋል። ይሁንና መስመሩ ኃይል ማስተላለፍ ቢያቋርጥም በሌላ አማራጭ መስመር ኃይል ማስተላለፍ ስለተቻለ ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች አለመኖራቸውን ዳይሬክተሩ አረጋግጠዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ መስመሩ ከህዳሴ የሚመረተው ኃይል ጨምሮ ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት የሚተላለፍበት ነበር። መስመሩን ወደ ሥራ ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ.ም.

photo content
+6

photo content
+9

የዓለም ባንክ ግሩፕ ፕሬዚዳንት የተቋሙን የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ጎበኙ .....///..... በዓለም ባንክ ግሩፕ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋን የተመራ የልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ጎብኝቷል። ፕሬዝዳንቱ በጉብኝታቸው ወቅት እንደገለፁት ያለ ኢነርጂ ህይወትን ማሰብ አይቻልም። ተቋሙ በሚያከናውናቸው የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የውጭ ምንዛሬ ችግሮች እንዳሉ መረዳታቸውን ተናግረዋል። እንደ ሚስተር አጃይ ገለፃ ሀገር በቀል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬ እጥረቱን መቅረፍ ይገባል። የኢንዱስትሪዎቹ መስፋፋት የሥራ ዕድል ከመፍጠር አንፃርም ሚናው የጎላ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ለልዑካኑ ቡድኑ ባደረጉት ገለፃ በዓለም ባንክ ድጋፍ በርካታ የኃይል ልማት ፕሮጀክቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የውጭ ምንዛሬ እጥረት ተቋሙ በሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች ላይ ማነቆ መሆኑንም ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል። እንደ አቶ አሸብር ገለፃ በሃገሪቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማስፋት ዓለም ባንክ የጀመራቸውን  ድጋፎች አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ በበኩላቸው የኃይል ሥርጭት ሥራዎችን ለማስፋፋት ተቋማቸው ስለሚሰራቸው ሥራዎች ገለፃ አድርገዋል። በጉብኝቱ ላይ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ፣ በዓለም ባንክ ግሩፕ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ኡስማን ዲዮን፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሱልጣን ወሊ፣ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰውን ጨምሮ የኢትዮጵያ መንግሥትና የዓለም ባንክ ግሩፕ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። "ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+6

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን ጎበኙ ........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የተቋሙ የተለያዩ የዘርፍ ሥራ አስፈፃሚዎች በሞጆ ከተማ አቅራቢያ እየተገነባ የሚገኘውን የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ጎበኙ። የጉብኝቱ ዋና ዓላማ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን የአፈጻጸም ደረጃ በመስክ ለመመልከት እና በግንባታው ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመፍታት ፕሮጀክቱ በተያለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ለማድረግ ነው። ፕሮጀክቱን አስመልክተው ለተቋሙ ሥራ አስፈጻሚና አመራሮች ማብራሪያ የሰጡት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ የራስ ኃይል መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ኃይለጊዮርጊስ ናቸው። ዳይሬክተሩ በማብራሪያቸው እንደገለጹት ፕሮጀክቱ የሥራ ክፍሉ ባዘጋጀው የፕሮጀክት ክትትል የአሰራር መመሪያ መሰረት እንዲከናወን ተገቢው ክትትል እየተደረገበት ነው። ፕሮጀክቱ በታቀደለት የጊዜ መርሃ ግብር እየተከናወነ ቢሆንም ከውጭ ምንዛሪ እና ከግብዓት አቅርቦት ዋጋ መጨመር ጋር የተያያዙ ሥጋት መኖራቸውን አንስተዋል። የተቋሙ ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው በፕሮጀክቱ ለተነሱት ሥጋቶች መፍትሄ ለመስጠት ተቋሙ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። በግንባታ ወቅት ሊያጋጠሙ የሚችሉ ችግሮችን ቀድሞ በመለየትና በመተንተን መፍትሄ መስጠት ይገባል ያሉት ሥራ አስፈጻሚው ይህም በፕሮጀክቶች ላይ የሚስተዋለውን መጓተት ያስቀራል ብለዋል። እንደ ሥራ አስፈጻሚው ገለፃ የፕሮጀክቱ ወጭዎችን ጨምሮ አጠቃላይ ሂደቱን አደራጅቶ መዝግቦ በመያዝ ለቀጣይ ፕሮጀክቶች ማሳያ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 20 ቀን 2015 ዓ.ም.

photo content
+2

photo content
+9

የተቋሙ ሠራተኛ ችግኞችን መትከል ባህል እንያደርጉ ጥሪ ቀረበ ..........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኛ ችግኞችን መትከል ባህሉ ሊያደርጉ እንደሚገባ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ። ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ የዘርፍ ሥራ አስፈፃሚዎች እና ሠራተኞች ለመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ባለሥልጣን ተጠሪ የሆኑ ተቋማት በተሳተፉበት የችግኝ ተከላ መርሀግብር ላይ በሞጆ - ሀዋሳ የፍጥነት መንገድ ዳርቻ ላይ ችግኝ ተክለዋል። ሥራ አስፈጻሚው ከችግኝ ተከላ መርሀግብሩ በኋላ በሰጡት ቃለመጠይቅ እንደገለፁት በየዓመቱ የሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦችን ከደለል በመከላከል እና የግድቦችን ደህንነት ለመጠበቅ ትልቅ ጠቀሜታ አለው። እንደ ተቋም በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች የሚተከሉ ችግኞች ለውጥ እያመጡ መሆኑን የጠቀሱት ሥራ አስፈጻሚው በየጊዜው የሚተከሉ ችግኞችን ተንከባክቦ ለውጤት እንዲበቁ ለማድረግ ግብረ ኃይል በማቋቁሞ ክትትል ይደረጋል ብለዋል። እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ ሁሉም የተቋሙ ሠራተኛ ችግኝ መትከልን ባህሉ በማድረግ በኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለምግብነት የሚያገለግሉ አትክልቶችን ጭምር በማሳደግ ተጠቃሚ መሆን እንዲችል በትኩረት እየተሠራ ነው። በተቋሙ የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ በበኩላቸው በምግብ ራስን ለመቻል መንግሥት ያስቀመጠውን አቅጣጫ ለመተግበር በኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የተለያዩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸው ገልፀዋል። ሠራተኛው ለምግብነት የሚውሉ አትክልቶችን ተንከባክቦ ለፍሬ በማብቃት ራሱን መጥቀም እንዲችል ማህበሩ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። 6 ሺህ ችግኞች በተተከሉበት የሞጆ ሀዋሳ ፍጥነት መንገድ የችግኝ ተከላ መርሃግብር ላይ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ፕ/ር መሀመድ አብዱ እና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ኃይለሚካኤልን ጨምሮ ዘጠኝ የመንግሥት የልማት ድርጅት ኃላፊዎችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 20 ቀን 2015 ዓ.ም.

photo content

የሳፕ ሲስተም ምዕራፍ ሁለት ትግበራን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ………//………... የሳፕ ሲስተም ምዕራፍ ሁለት ትግበራን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሞደርናይዜሽን መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የፕሮሰስ ሞደርናይዜሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ፈለቀ አፈወርቅ እንደገለፁት ሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ሲስተም ትግበራ ስድስት ሞጁሎችን ያቀፈ ነው። የሳፕ ፕሮጀክት በሦስት ምዕራፎች ተከፍሎ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በቅንጅት ለመሥራት ቢታቀድም የተቋሙ ከፍተኛ ሥራ አመራር በሰጠው አቅጣጫ መሠረት ምዕራፍ ሁለት እና ሦስት በአንድ ላይ ተጠቃለው ወደ ትግበራ መገባቱን ጠቁመዋል። ፋይናንስ፣ የሰው ኃይል አስተዳደር፣ ግዥ፣ ዕቃ ግምጃ ቤት እንዲሁም ከመጀመሪያው ምዕራፍ የቀጠሉ የተለያዩ ሥራዎች በሁለተኛው ምዕራፍ እንደተካተቱ ተናግረዋል። እንደ አቶ ፈለቀ ገለፃ ትራቭል ማኔጅመንት፣ ሪልስቴት ወይም ሊዝ፣ ትሬዠሪና ሪስክ ማኔጅመንት፣ ፈንድና ግራንት ማኔጅመንት፣ ዲስክሎዠር ማኔጅመንት በሁለተኛው ምዕራፍ በፋይናንስ በኩል የሚሰሩ ሥራዎች ናቸው። የተቋሙን የሰው ሀብት ሥራ አመራር ሲስተም ወጥና በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ ሰክሰስ ፋክተር ሞጁል መገዛቱን የተናገሩት አቶ ፈለቀ ሞጁሉ ስድስት ክፍሎች እንዳሉት ጠቅሰዋል። አሪባ የተሰኘ የተቋሙን የግዥ ሥርዓት ማዘመን የሚያስችል ሞጁል መዘጋጀቱንም ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት። ሞጅሉ የተቋሙን የጨረታ ሰነዶች ወደ ዲጂታል በመቀየር የአሰራር ሒደቱን ቀልጣፋና ምቹ ለማድረግ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል። ከሳይበር ሴኪዩሪቲ፣ ከውስጥ ኦዲትና ከሪስክ ማኔጅመንት ጋር ተያይዞ ያሉትን የሥራ ሂደቶች ወጥነት ባለው መልኩ እንዲከናወኑ ለማስቻል ጂ.አር.ሲ በሚል የተገዙ ሞጅሎች መኖራቸውንም ጨምረው አብራርተዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የተቋሙን የዕቃ ግምጃ ቤት በቴክኖሎጂ በታገዘ መልኩ ለማደራጀትና የዕቃዎችን አቀማመጥ ሥርዓት ለማስያዝ እንዲሁም የዕቃዎቹን ዓይነት እና መጠን በቀላሉ ለመለየት የሚያስችሉ ሥራዎች በምዕራፍ ሁለት ተግባራዊ ይደረጋሉ። የአራት የሥራ ዘርፎችን የአሰራር ሥርዓቶች በሳፕ የታገዘ ለማድረግ ፕላንት ሜንቴናንስ የተባለ ሞጁል መዘጋጀቱን የተናገሩት አቶ ፈለቀ ሞጁሉ አራት ዋና ዋና ጉዳዮችን አጠቃሎ መያዙንም ጨምረው ገልፀዋል። ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የኃይል ማመንጫ እና የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ንብረቶችን የሚመዘግብ ከመሆኑም ባሻገር በዕቅድ ላይ የተመሠረቱ የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን ፋይዳው የጎላ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። የኮርፖሬት ፕላኒንግ ሥራዎችን በሲስተም እንዲታገዙ ለማድረግ እንዲሁም በየሥራ ክፍሎቹ በተበታተነ ሁኔታ እየተተገበረ ያለውን የቢ.ኤስ.ሲ የአሰራር ሥርዓት ለማሻሻል የሚያስችል ስፒር የተሰኘ ሞጁል መካተቱንም አመልክተዋል። በምዕራፍ አንድ የትግበራ ወቅት ያልተካተቱ ሞጁሎችን እና ከየሥራ ክፍሎች ተለይተው እየመጡ ያሉ አዳዲስ ፍላጎቶችን በምዕራፍ ሁለት ውስጥ አካቶ ለመሥራት መታሰቡንም ነው አቶ ፈለቀ የተናገሩት። ሞጁሎቹ ሙሉ በሙሉ መተግበር ሲጀምሩ የተቋሙን የአሰራር ሥርዓት ለማዘመን፣ ጠንካራ የሀብት ቁጥጥር ሥርዓት ለመዘርጋት፣ የተቋሙን ወጭ ለመቀነስና ሥራን ለማቀላጠፍ እንዲሁም መረጃዎችን ለማጥራት አስተዋፅኦው ከፍ ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል። በምዕራፍ ሁለት ላይ የሚሳተፉ የተቋሙ ሠራተኞችን ከየሥራ ክፍሎቹ በቡድን በማዋቀር ለትግበራ በተዘጋጁት ሞጁሎች ላይ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎች በአማካሪው በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል ተሰጥተዋል፡፡ የምዕራፍ ሁለት የሳፕ ሲስተም በየሥራ ክፍሎቹ መተግበር ሲጀምር ከ85 በመቶ በላይ የወረቀት ሥራዎችን ዲጂታል የማድረግ አቅም አለው፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 19 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+8

photo content
+9

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሚያዝያ 25 ቀን 2015 ዓ.ም በገንዘብ ያዥ የሥራ መደብ (ጂ-1) ለውጪ አመልካቾች ማስታወቂያ ያወጣ መሆኑ ይታወቃል:: በመሆኑም ተወዳዳሪዎች የጽሁፍ ፈተና ሐምሌ 22 ቀን 2015 ዓ. ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልፅ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ በሚገኘው በተቋሙ ዋና መ/ቤት 20ኛ ፎቅ የጽሁፍ ፈተና ስለሚሰጥ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

photo content
+1

የተቋሙን የፋይናንስ ቁመና የሚያሻሽሉና የብድር ጫናዎችን የሚያቃልሉ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛል …….///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋይናንስ አቅሙ እየተሻሻለ በመምጣቱ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን በራሱ አቅም መገንባት መጀመሩን በተቋሙ የፋይናንስ አስተዳደር መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ መንግስቱ እንደገለፁት ተቋሙ ለፕሮጀክቶች ግንባታ እና ለኦፕሬሽን ሥራዎች ማስፈፀሚያ ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ያገኛቸው ብድሮች በአብዛኛው በአጭር ጊዜና በከፍተኛ ወለድ ይከፈሉ የነበሩ በመሆናቸው የተቋሙን የፋይናንስ ቁመና ጤናማ እንዳይሆን አድርጎት ቆይቷል። በተቋሙ ካፒታል እና ለሥራዎቹ ማከናወኛ ከአበዳሪ ተቋማት ባገኛቸው ብድሮች መካከል ያለው ምጣኔ መስፋት እና ለረጅም ጊዜ አገልግሎት የሰጡ ቋሚ ንብረቶች የዋጋ ክለሳ ከጊዜው ጋር ያልተጣጣመ መሆኑ የፋይናንስ ስርዓቱ ጤናማ ላለመሆኑ አመላካች ምክንያቶች እንደነበሩ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ይሁንና እንደ አቶ አለማየሁ ገለፃ የተቋሙን የፋይናንስ ቁመና የሚያሻሽሉ፣ የብድር ጫናዎችን የሚያቃልሉ፣ የፕሮጀክቶችን የግንባታ ጊዜ አፈፃፀም የሚያፋጥኑ፣ የፋይናንስ ሪፖርት ሥርዓትን የሚያዘምኑ እንዲሁም ገቢን ሊያሳድጉና ወጪን ሊቀንሱ የሚችሉ የአሰራር ስርዓት እርምጃዎች በመወሰድ ላይም ይገኛሉ፡፡ ተቋሙ ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ያገኛቸው ብድሮች ከተቋሙ ካፒታል ጋር ሲነፃፀር ከ99 በመቶ በላይ እንደነበር ያስታወሱት አቶ አለማየሁ በፋይናንስ አስተዳደር ሥርዓቱ ላይ በተወሰዱ እርምጃዎች በአሁኑ ወቅት የብድር ምጣኔው ወደ 80 በመቶ አካባቢ ሊወርድ ችሏል ብለዋል። ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ በተወሰዱ የማሻሻያ እርምጃዎች ለኦፕሬሽን ሥራዎች፤ ለአነስተኛ እና መለስተኛ ፕሮጀክቶች ግንባታ፣ አልፎ አልፎ በአገር ውስጥ ለሚከፈሉ ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ እንዲሁም ለብድርና ወለድ ክፍያ የሚያስፈልጉ ወጪዎችን በተቋሙ ገቢ መሸፈን መጀመሩን አስታውቀዋል። የተቋሙን የፋይናንስ ቁመና ለማሻሻል እየተወሰዱ ያሉት እርምጃዎች የተቋሙን የፋይናንስ ቁመና አስተማማኝ ሊያደርጉ የሚችሉ በመሆናቸው ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ዳይሬክተሩ አረጋግጠዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 17 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+6

photo content
+9

በፕሮጀክቱ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች ተጠናክረው  እንደሚቀጥሉ ተገለፀ .........///........ ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኤሌክትሪክ ለማቅረብ በሚገነባው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ የራስ ኃይል መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በፕሮጀክት ሳይቱ ላይ ዛሬ ችግኝ ተክለዋል። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ኃይለጊዮርጊስ በችግኝ ተከላው መርሃግብር ላይ እንደገለፁት ሀገር በቀል ችግኞችን መትከል የአካባቢን ሥነ-ምህዳር ከማስጠበቅ አንፃር ሚናው የጎላ ነው። መምሪያው ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ከሚያከናውናቸው ግንባታዎች ባሻገር የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች በማከናወን አካባቢውን ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ አካባቢን የማስተላለፍ ሥራ እንደሚሰራ ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። በመምሪያው የፕሮጀክት ማኔጅመንት ሁለት ሥራ አስኪያጅ አቶ ተድላ ሰይፉ  በበኩላቸው እንደሀገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት እየተደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ለመደገፍ መምሪያው የበኩልን ድርሻ እንደሚወጣ ተናግረዋል። ለተተከሉት ሀገር በቀል ችግኞች አስፈላጊውን እንክብካቤ ማድረግ የሁሉም ሠራተኛ እና አመራር ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ በዕለቱ ለምግብነት ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ተክሎችን ጨምሮ ከ550 በላይ ሀገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል። በችግኝ ተከላ መርሀግብሩ ላይ በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ የራስ ኃይል መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ተሳትፈዋል። "ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”          የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ሐምሌ 13 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1