uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 537 підписників, посідаючи 8 329 місце в категорії Технології та додатки та 2 179 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 537 підписників.

За останніми даними від 03 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 31, а за останні 24 години на -1, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 26.36%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 16.21% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 4 097 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 520 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 10.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 04 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 537
Підписники
-124 години
-167 днів
+3130 день
Архів дописів
photo content
+5

ተቋሙ ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ጋር የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ኪራይ ሥምምነት አካሄደ …….////………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከሳፋሪኮም-ኢትዮጵያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጋር የኦፕቲካል ፋይበር ኪራይ ሥምምነት ተፈራረመ፡፡ ሥምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የሳፋሪኮም-ኢትዮጵያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሚስተር አንዋር ሶውሳ ናቸው፡፡ ሥምምነቱ በመጀመሪያ ምዕራፍ 4097 ኪ.ሜ፣ በሁለተኛው ምዕራፍ 2078 ኪ.ሜ እንዲሁም በሶስተኛው ምዕራፍ 2904 ኪ.ሜ የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ኪራይን ያጠቃልላል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ሥምምነቱ ሁለቱ ተቋማት በጋራ ተባብረው እንዲሰሩ መሠረት የሚጥል ነው፡፡ ተቋሙ ከኃይል ማመንጨት እና ማስተላለፍ ባሻገር የቴሌኮም ዘርፉን ዲጂታል ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝም አብራርተዋል፡፡ ሥምምነቱ ለሳፋሪኮም እንደ መልካም ጅማሮ የሚታይ ነው ያሉት አቶ አሸብር የጋራ ተጠቃሚነትን ከፍ የሚያደርግ በመሆኑ ትልቅ ዕድል ነው ብለዋል፡፡ የሳፋሪኮም-ኢትዮጵያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሚስተር አንዋር ሶውሳ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በቴሌኮም ዘርፍ እያሳየች ያለውን አወንታዊ ዕድገት አድንቀው ሥምምነቱ ከተቋሙ ጋር ያለንን በጋራ የመሥራት ፍላጎት የሚያጠናክር ነው ብለዋል፡፡ ኩባንያቸው የዲጂታል ትራንስፎርሜሽኑን ለማሳካት በሚደረገው ርብርብ ውስጥ የበኩሉን አስተዋፅኦ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ጥራትና ደረጃውን የጠበቀ የቴሌኮም አገልግሎት ለህብረተሰቡ ለማቅረብም እየተሰራ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመጀመሪያው ምዕራፍ የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ኪራይ በዓመት እስከ 140 ሚሊዮን ብር ገቢ ያገኛል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እስከ 15 ሺህ ኪ.ሜ የሚሸፍን የኦፕቲከል ፋይበር መስመር ባለቤት ሲሆን ኢትዮ-ቴሌኮም 8745 ኪ.ሜ በኪራይ እንዲሁም ደግሞ ተቋሙ ለውስጥ የመረጃ ልውውጥ እየተጠቀሙበት ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 02 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+6

ሠራተኛውን ተጠቃሚ የሚያደርግ የብድር ስምምነት ተፈረመ …….///…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋሙን ሠራተኞች ተጠቃሚ የሚያደርግ የብድር ሥምምነት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በዛሬው ዕለት ተፈራርሟል፡፡ የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአራዳ ዲስትሪክት የብድር ክፍል ኃላፊ አቶ ቦጋለ ታደሰ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ በፊርማ ሥነ - ሥርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ባንኩ ለአብዛኛዎቹ የኃይል መሰረተልማት ፕሮጀክቶች የፋይናንስ ምንጭ በመሆን የዳበረ የረጅም ዓመታት የሥራ ግንኙነት ተፈጥሯል፡፡ ግንኙነቱን ወደ ሠራተኞችች በማውረድ ሁለቱም ተቋማት የጋራ ተጠቃሚ የሚሆኑበት የብድር ስምምነት መፈራረማቸው ለዓመታት የዘለቀውን ግንኙነት ይበልጥ ያጠናክረዋል ብለዋል፡፡ ተቋሙ የሚያገኘውን የውጭ ምንዛሪ የሚያስቀምጠውና የሚያንቀሳቅሰው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመሆኑ ስምምነቱ የተቋማቱን ግንኙነት ከማሳደግ ባለፈ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች በሚያገኙት የብድር አገልግሎት ሀብት የሚያፈሩበት ምቹ ሁኔታ ስለሚፈጥር ትብብሩ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው ዋና ሥራ አስፈጻሚው አሳስበዋል፡፡ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአራዳ ዲስትሪክት የብድር ክፍል ኃላፊ አቶ ቦጋለ ታደሰ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሀገሪቱ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የገነባ እና እየገነባም የሚገኝ፤ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋርም ለረጅም ዓመታት የዘለቀ ግንኙነት ያለው ግዙፍ ተቋም መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በተቋሙ ለሚሰሩት ፕሮጀክቶች የፋይናንስ ምንጭ ከመሆን ባለፈ ሠራተኞቹን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሠራተኞች በሚጠቀሙበት ዝቅተኛ የወለድ መጠን ተጠቃሚ የሚሆኑበት የብድር ስምምነት መደረጉ የበለጠ የሚያቀራርበ በመሆኑ መደሰታቸውን አቶ ቦጋለ ገልጸዋል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለቤት መግዣ፣ ለመኪና መግዣ እና ለግል ጉዳዮች የሚውል የብድር ዓይነቶችን ማቅረቡን የተናገሩት ኃላፊው የድርጅቱ ሠራተኞች በተመቻቸላቸው ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቀርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሠረታዊ ሠራተኛ መህበር ሊቀ መንበር አቶ መኮንን ክፍሌ እንደተናገሩት የተቋሙ ሠራተኞች በተቋሙ የሥራ ባህርይ የተነሳ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ እንደመሆናቸው ንብረት ለማፍራት ከፍተኛ ቸግር ይገጥማቸው እንደነበር አንስተዋል፡፡ በተለይ በኃይል ማመንጫ የሚሠሩ ሠራተኞች በተለያዩ ምክንያቶች ከኃይል ማመንጫው ሲለቁ ንብረት ስለማይዙ ከፍተኛ ችግር ላይ ይወድቃሉ፡፡ በመሆኑም የዛሬው የመግባቢያ ሰምምነት ይህን ችግር በመቅፍ በኩል ወሳኝ ሚና እንደ አለው አቶ መኮንን አስረድተዋል፡፡ በዚህም የተቋሙ ማኔጅመንት አባላት በሙሉ ፍላጎት ሠራተኛውን ታሳቢ አድርገው ይህን ውሳኔ ማሳለፋቸውና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክም ተገቢውን ምላሽ በመስጠቱ በመላው የተቋሙ ሠራተኛ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በፊርማ ሥነ-ስርአቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 29 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+5

ማስተካከያ ተቋማችን ክፍት በሆኑ የሥራ መደቦች ላይ ቅጥር ለመፈፀም ዓርብ የካቲት 25 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል። ይሁንና በድርጅቱ የፌስቡክና ቴሌግራም አድራሻዎች ላይ ተጭኖ የነበረው ማስታወቂያ ለማንበብ አስቸጋሪ ወይም የደበዘዘ (blured) መሆኑን በሰጣችሁን አስተያየት መሠረት መነበብ እንዲችል በጋዜጣው ላይ ወጥቶ የነበረውን የማስታወቂያ ፅሁፍ በድጋሚ ፖስት ያደረግን መሆኑን እናሳውቃለን።

ኢትዮጵያን የምስራቅ አፍሪካ የታዳሽ ኃይል ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ ነው .........///...... በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ትኩረት በተሰጠው የኢነርጂ ዘርፍ ኢትዮጵያን የምስራቅ አፍሪካ የታዳሽ ኃይል ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ2014 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ዛሬ በሂልተን ሆቴል በገንዘብ ሚኒስቴርና በመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ተገምግሟል፡፡ በዚህ ወቅት የገንዘብ ሚኒሰትሩ አቶ አህመድ ሺዴ እንደገለጹት፥ መንግስት ለኃይል ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት የሰጠ በመሆኑ በጥንቃቄ የሚከታተለውና የሚመራው ዘርፍ ነው፡፡ በኃይል ማመንጨትና ማሰራጨት ዘርፍ ያለው የሪፎርም ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትና የዘርፉ የፕሮጀክት አመራርና አፈጻጸም ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ሚኒስትሩ አሳስበዋል፡፡ በሁለቱም ተቋማት በኩል ከደንበኞች ያልተሰበሰበ ገንዘብ በጊዜ እንዲሰበሰብ በተለይም ወደ ጎረቤት ሀገሮች ኤክስፖርት ከተደረገው ኃይል ያልተሰበሰበውን ገንዘብ ተከታትሎ ገቢ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡ የኃይል ብክነትንና መቆራረጥን መቆጣጠር፣ ወጪ ቅነሳን ተግባራዊ ማድረግ፣ በክልሎች ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን የዘርፉን ያልተማከለ አስተዳደር አጠናክሮ መቀጠል አስፈላጊ መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። የገንዘብ ሚኒስቴር ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር አስፈላጊውን ድጋፍ ለተቋማቱ እንደሚሰጥ ማረጋገጣቸውን ከገንዘብ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 25 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+1

የሥራ ማስታወቂያ
የሥራ ማስታወቂያ

የሀዘን መግለጫ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን 4ኛው ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በሆስፒታል የህክምና እርዳታ ሲደረግላቸው ቆይቶ ከዚህ ዓለም ድ
የሀዘን መግለጫ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን 4ኛው ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በሆስፒታል የህክምና እርዳታ ሲደረግላቸው ቆይቶ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቅዱስነታቸው ዕረፍት የተሰማዉን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለመላዉ ኢትዮጵያውያን መፅናናትን ይመኛል፡፡

እንኳን ለ126 ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
እንኳን ለ126 ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

የነገ ብርሃናችን በዛሬ ላባችን ተጽፏል ......./////...... ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ የኃይል ማመንጨት ሥራውን ዛሬ በይፋ ጀምሯል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ የመጀመሪያው ተርባይን በይፋ ኃይል ማምረቱን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ ከአባይ ተፋሰስ ሀገራት ጋር በጋራ ለመጠቀም ያላትን ቁርጠኝነት ያሳየችበት የትብብር ተምሳሌት ሆኗል። የኢትዮጵያ ህዝብ ከሊቅ እስከ ደቂቅ የተሳተፈበት ታላቂ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተቋሙ ሠራተኞች፣ አመራሮችና የስራ አመራር ቦርድ እንዲሁም የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ያልተቋረጠ ድጋፍና አመራር እንዲሁም ቀጥተኛ ተሳትፎ ፕሮጀክቱ አሁን ላለበት ደረጃ እንዲደርስ አድርገውታል ብለዋል። የግድቡ ግንባታ መሰረት ከተጣለ ጊዜ ጀምሮ በርካታ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ መንገዶች አሻራቸውን ማሳረፋቸውን ሥራ አስፈፃሚው በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ግድቡ በተገነባበት ቦታ ላይ በርካቶች መስዋዕትነት በመክፈል የነገ ብርሃናችንን በዛሬ ላባቸው ጽፈዋል። ለዚህም በተቋሙና በራሳቸው ስም ምስጋናቸውን በማቅረብ ለሁሉም ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 13 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+4

ግድቡ በአንድ ዩኒት የኃይል ማምረት ሥራውን ዛሬ በይፋ ጀምሯል ......./////...... ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዩኒት የኃይል ማመንጨት ሥራውን ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው እንዳመለከቱት የግድቡን ስራ በአግባብ እንዲከናወንና ለዚህ እንዲደርስ ያደረግን እንጂ ያስጀመርን ባለመሆኑ ለቀጣይ ትውልድ በማሰብ ራዕይ ሰንቀው ዲዛይን ያሰሩና ግንባታውን ያስጀመሩ መሪዎችን በስም በመጥራት አመስግነዋል። የአንድነትና የመነሳሳት ተምሳሌት በሆነው በዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክት ላይ የተሳተፉትን ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንዲሁም አስተዋፅኦ የነበራቸውን አካላትና ግለሰቦችም አመስግነዋል። የኢትዮጵያ ፍላጎት ኤሌክትሪክ በማመንጨት በጭለማ የሚኖረውን ህዝብ ኑሮ የሚለውጥና ካለንበት ድህነት ማላቀቅ በመሆኑ ኃይል አመንጭቶ እንደቀደመ ፍሰቱን እንደሚቀጥል ማሳያ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አብርሃም በላይ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ያለፈበትን ሂደት በማንሳት ና ዛሬ የደረሰበትን ደረጃ በመዘርዘር ፕሮጀክቱ ለህዝብና ለእውነት የቆመ መንግስት መኖሩን ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልፀውታል። በፕሮጀክት አያያዝ የተከሰቱትን ጉልህ ችግሮች ከመሸፋፈን ይልቅ የተጠናና በንድፈ ሀሳብ የተመሰረተ የእርምት እርምጃዎች መወሰዳቸውንና ለመጀመሪያ ምዕራፍ ኃይል ማመንጨት መብቃቱን አንስተዋል። የፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ሀገር በጭንቅ ወቅት ሆና እንኳን ለአፍታም ያልተስተጓጎለ መሆኑን ጠቅሰዋል። የመጀመሪያ ምዕራፍ ኃይል ማመንጨት ስራ በስኬት ቢጠናቀቅም ለፍፃሜ ለማድረስ የህዝብና የመንግስት ድጋፍ እንዳይለየው ጥሪ አቅርበዋል። በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የህዝብ ተወካዮችና የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈጉባዔዎች፣ የጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት፣ ሚኒስትሮች፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም፣ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የቀድሞ ፕሬዝዳንትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 13 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+2

እኛም በጣቢያው በነበረን ቆይታ እንዲህ ዓይነቱን ተስፋ ሰጭ የወገን እጆች ሥራ ስንመለከት የጥገና ሥራው በራስ አቅም መከናወኑ ተቋሙ ለውጭ ባለሙያዎችና ኩባንያዎች በውጭ ምንዛሪ ሊያወጣ የሚችለውን ወጪ ማስቀረት ከማስቻሉ በተጨማሪ ቅንጅታዊ አሰራር እና የዕውቀት ሽግግር የተገኘበት መሆኑ መረዳት ችለናል፡፡ በተለይም የተቋሙ የበላይ አመራር አዎንታዊ ድጋፍና ክትትል እየተጠናከረ መምጣቱ፣ ተቋማችን በረጅም ጊዜ እደርስበታለሁ ብሎ ከሚያስበው ራዕይ በቶሎ ለመድረስ ከማስቻሉም በተጨማሪ የባለሙያዎች የራስ መተማመን ስሜት ከፍ ያለበትና ሀገሪቷ ለምታከናወነው ሁለንተናዊ ልማት አጋዥ የሆኑ እነዚህን መሰል እጆች በየተቋሙ ስለመኖራቸው አመላካች ነው፡፡ ውድ የገፃችን ተከታታዮች ሁላችንም በየተሰማራንበት የሙያ ዘርፍ በአቅማችን ልክ ከሠራን የማናስመዘግበው ውጤት የለምና በርቱ! እንበርታ! በማለት ለሀገራዊ ዕድገት የበኩላቸውን ጠጠር ሲወረውሩ የተመለከትናቸው እጆች በጊቤ ሁለት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ያከናወኑትን ተስፋ ሰጪ ስራዎች በዚሁ አጠናቀቅን በሌላ ጽሁፍ እስከምንገናኝ ቸር እንሰንብት!! እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!!

ጠጠር ወርዋሪ እጆች!! ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት መፋጠን ከፍተኛ ሚና ከሚጫወቱ ዘርፎች ውስጥ የኃይል ልማት ዘርፍ አንዱ ነው፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ ለኃይል ልማቱ አመቺ የሆኑ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶች ባለቤት እንደሆነች ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም ቀደም ሲል ከውኃ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ከንፋስ፣ ከከርሰምድር እንፋሎትና ከደረቅ ቆሻሻ ኃይልን በማመንጨት የተጣለበትን ሀገራዊ ተልዕኮ እየተወጣ የሚገኝ የልማት ድርጅት ነው፡፡ ሀገሪቱ የተለመቻቸውን በርካታ የልማት ግቦች ለማሳካት በቂና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ ተቋሙ ከጀመራቸው አዳዲስ የኃይል ማመንጫ ግንባታዎች በተጨማሪ በስራ ላይ ያሉ ነባር ኃይል ማመንጫዎችን በሙሉ አቅማቸው እንዲሰሩ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ነው፡፡ ከእነዚህም ስራዎች መካከል በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ቆመው የነበሩ ዩኒቶችን በራስ አቅም ጠግኖ ወደ ሥራ ማስገባት ይጠቀሳል፡፡ ለዚህ ርዕሰ ጉዳይ አስረጅ የሚሆነን በጊቤ ሁለት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የተከናወነው ሥራ ሲሆን በተቋማዊ ሥራው የተሳተፉትንና ለሀገራዊ ዕድገት ስኬት የበኩላቸውን ጠጠር ሲወረውሩ የተመለከትናቸው እጆች ልናስቃኛችሁ ወደድን፡፡ መልካም ንባብ!!!! የጊቤ ሁለት ኃይል ማንጫ ጣቢያ ከአዲስ አበባ በ250 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሠቦች እና ህዝቦች ክልል በየም ልዩ ወረዳ የሚገኝ ሲሆን 420 ሜጋዋት የማመንጨት አቅም ያለው የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ነው፡፡ በተቋሙ በሥራ ላይ ካሉት 13 የውኃ ኃይል ማመንጫዎች ውስጥ የጊቤ ሁለት የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች አንዱ ነው፡፡ የጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ኃይል እንዲያመነጭ የሚያስችለውን ውሃ የሚያገኘው 180 ሜ.ዋ አመንጭቶ ከሚወጣውን ከጊቤ አንድ ውሃ ነው፡፡ ይህም ከጊቤ አንድ ኃይል አመንጭቶ ከወጣ በኋላ በቅርብ ርቀት በተሰራው መለስተኛ ግድብ ውኃው እንዲያዝ ከተደረገ በኋላ ወደ ጊቤ 2 በመሬት ውስጥ በሚያልፍ ዋሻ (under ground tunnel) አማካኝነት ነው፡፡ ዋሻው 26 ኪሎ ሜትር ርዝመት እና 3 ነጥብ 6 ሜትር ዲያሜትር ስፋት አለው፡፡ ውሃው በዋሻው ተጉዞ ከመሬት ከወጣ በኋላም ከብረት በተሰሩ 1 ነጥብ 3 ኪ.ሜ ርዝመትና 2 ነጥብ 1 ሜትር ዳያሜትር ስፋት ባላቸው ሁለት አሸንዳዎች (Penstock) ከተጓዘ በኋላ እያንዳንዱ አሸንዳ እንደገና ለሁለት በመከፈል ለአራቱም ዩኒቶች ውኃ እንዲደርስ የሚያደርግ የኃይል ማመንጫ ነው፡፡ ይህ ጣቢያ በ2002 ዓ.ም ተመርቆ በይፋ ስራ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ኃይል የማመንጨት ሥራውን በስኬት ሲወጣ እንደነበርና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአንዳንድ ችግሮች ምክንያት አንደኛው ዩኒት ሙሉ ለሙሉ ሲያቆም ሌላኛው ደግሞ ኃይል ማምረት ከሚጠበቅበት 1/4ኛውን ብቻ በማምረቱ ጣቢያው በሙሉ አቅሙ እንዳያመርት እንቅፋት ፈጥሮበት ቆይቷል፡፡ የጣቢያውን ችግሮች ለመቅረፍ የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ የቆዩ ሲሆን እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን መመልከት በራሱ ከፍተኛ ኩራትን ከማላበሱ በላይ እነዚህ አስገራሚና አስደማሚ ሀገር በቀል እጆች የነገይቱን ኢትዮጵያ በብሩህ ተስፋ መነፅር እንድንመለከት የሚያደርጉ ናቸው፡፡ የጣቢያው ሠራተኞች ዩኒቶቹ አገልግሎት እንዳይሰጡ ያደረጋቸውን ችግር ዓይነትና ስፋት በመለየት ለተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ማሳወቃቸውን እና ጥገናውን በራስ አቅም ማከናወን እንዲቻል ከበላይ ኃላፊች ፈቃድ እንዲሰጣቸው ጥያቄ ማቅረባቸውን ይገልፃሉ፡፡ የተቋሙ የበላይ አመራርም የቀረበውን ጥያቄ በመቀበልና በማበረታታት ለሚፈልጓቸው ሌሎች የድጋፍ ጥያቄዎች በሙሉ ትብብር እንደሚደርጉላቸው በማሳወቃቸው የጥገና ቡድኑ በልዩ ተነሳሽነት ወደ ጥገና ሥራ መግባቱን ያስታውሳሉ፡፡ ባለሙያዎቹ እንደሚሉት በወቅቱ ዩኒቶቹ አገልግሎት እንዳይሰጡ ያደረጋቸው ችግር የፖወር ኖዝል ብልሽት ነበር፡፡ ፓወር ኖዝል የመርፌ ቅርጽ ያለው (needle valve) ሲሆን ዩኒቶቹ እንደመጫን አቅማቸው ውሀን ለመመጠን የሚያገለግል የውሃ መቆጣጠሪያ አካል ነው፡፡ ችግሩ ተለይቶ ወደ ጥገና ሥራም ከመገባቱ በፊት ለጥገና ሥራው የሚያስፈልጉ የተለያዩ ሰነዶችን፣ ባለሙያዎችን፣ የጥገና መሳሪያዎችንና ግብዓቶችን የማሰባሰብ ተሰርቷል፡፡ የፖውር ኖዝል ችግርን ለማስተካከል የተበሉ ሲሎችን ለማስተካከል ፓወር ኖዝሎች ማውረድና መፍታት የግድ በመሆኑ እያንዳንዳቸውም 6000 ኪ.ግ የመመዘን ክብደት ያላቸው ስድስት (6) ፓወር ኖዝሎችን ከዩኒት አንድ ላይ መፍታት አስፈልጓል፡፡ ፓወር ኖዝሎቹን በሠው ኃይልና በማሽነሪዎች በመታገዝ በማውረድ፣ የመፈታታት፣ የማፅዳት እና የመቀየር እንዲሁም ሞደፊክ ሰርቶ መልሶ የመግጠም ስራ እንደተሰራ የጥገና ቡድኑ አባላት ይገልፃሉ፡፡ ከፖወር ኖዝል ጥገና ጎን ለጎን Main inlet valve (MIV servomotor) መሳሪያዎች ጥገና ተከናወኗል፡፡ MIV servomotor ወደ ተርባይን የሚገባውን ውሃ መጠን ለመቆጣጠር የሚያገለግል መቆጣጠሪያ ሲሆን በመዝጊያው በኩል የዘይት መፍሰስ ችግር በማጋጠሙ በዩኒት አንድ ላይ ሁለት እንዲሁም በዩኒት ሦስት ላይ አንድ በድምሩ ሦስት (MIV servomotor) የጥገና ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ በዚህም ሙሉ በሙሉ ማመንጫት አቁሞ የነበረውን የዩኒት አንድ የመጫን አቅሙን ወደ 105 ሜጋ ዋት እንዲሁም 25 ሜጋ ዋት ብቻ ይጭን የነበረውን ዩኒት ሦስት ወደ 100 ሜ.ዋ ኃይል እንዲያመነጭ በመደረጉ ጣቢያው 180 ተጨማሪ ኃይል እንዲያገኝ አድርገዋል፡፡ በቀጣይም ይህን መሠል ስራዎች በዩኒት ሁለትና አራት ላይ ለመሥራት ዕቅድ መያዙን ለመረዳት ችለናል፡፡ በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ በማስታወስ የተቋሙን ማኔጀመንት አባላት እና የጄነሬሽን ኦፕሬሽን ጽ/ቤት አመራሮች በእኛ ላይ ከፍተኛ እምነት አሳድረው ጥገናውን እንድናከናውን ፈቃድ በመስጠታቸው እና በየጊዜው አስፈላጊ ድጋፎችን በማድረጋቸው ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ጣቢያውን ለማዘመን እየተሰሩ ካሉ ስራዎች ውስጥ አንዱ የኃይል ጭነትን ለማስተካከል የሚረዳውን የርቀት መቆጣጠሪያ ላይ ብልሽት በማጋጠሙ ለረጅም ጊዜ በማኑዋል ይሰራ የነበረውን የኃይል ጭነትን በማስተካከል በቀላሉ ከኃይል መመንጫ ቤት ሆኖ መቆጣጠር አስችሏል፡፡ ይህም ከባድ የነበረውን ሥራ ቀላል እንዲሆን አድርጎታል፡፡ በተጨማሪም ማሽኑ ያለበትን ችግር በድምፅ ለመለየት የሚያስችል የድምፅ መቅጃ (sound recorder) ተገጥሞ በመሰራት ላይ እንደሆነም አንስተውልናል፡፡በተመሳሳይ መልኩ በምስራቅ አፍሪካ የጀርመን ተራድኦ ድርጅት ድጋፍ Voith በተባለው ድርጅት አማካኝነት በኢትዮጵያውያን ሠራተኞች የጥገና ማኔጀመንት ስርዓት (maintenance management system) ስራዎች እየተሰራ መሆኑን የጥገና ቡድኑ አባላት ነግረውናል፡፡

ተቋሙ በመሰረተ ልማቶቹ ላይ የደረሰበት ጉዳትና ኪሳራ ከ1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ይገመታል …….///……. በአማራ እና በአፋር ክልሎች ህወኃት በፈፀመው ወረራ የወደሙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን ለመጠገን የወጣው ወጪና በተቋሙ ላይ የደረሰው አጠቃላይ ኪሳራ 1 ነጥብ 64 ቢሊዮን እንደሚደርስ የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ በሁለቱ ክልሎች በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠንና ጉዳቱን ለመጠገን የተሰራውን ሥራ አስመልክቶ ተቋሙ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ በመግለጫው ላይ የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደተናገሩት አሸባሪው የህወኃት ቡድን በአማራና በአፋር ክልሎች በፈፀመው ወረራ ምክንያት በክልሎቹ ከሚገኙት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ውስጥ 53 ነጥብ 3 በመቶ የሚሆነው ጉዳት ደርሶበታል፡፡ የደረሰው የኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ጉዳት የኮንዳክተር መበጠስ፣ የታወሮች መውደቅ፣ የተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ተነቅሎ መወሰድ፣ የኦፕቲካል ግራውንድ ፋይበር መበጣጠስ እና የተሽከርካሪዎችና የቢሮ ፋሲሊቲዎች ዘረፋን እንደሚያጠቃልል ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ በደረሰው ጉዳት ከ14 ቀን እስከ 6 ወር የሚደርስ የኃይል አቅርቦት መቋረጡን እና ህብረተሰቡ ለከፍተኛ ችግር ተጋልጦ መቆየቱን ኃላፊው አስታውሰዋል፡፡ እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ የወደሙ መሠረተ ልማቶችን በመጠገን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦቱ በአስቸኳይ እንዲቀጥል ለማድረግ የወጣው የማቴሪያል ወጪ ብቻ ከ 29 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ነው፡፡ ሆኖም ጉዳቱን ሙሉ ለሙሉ በመልሶ ጥገና አስተካክሎ በአስተማማኝ ሁኔታ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ ከ23 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የፋይናስ ወጪ እንደሚጠይቅ እና ይህም በቀጣይ ትኩረት ተደርጎበት እንደሚሰራ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡ ከሐምሌ 26 ቀን 2013 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 9 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በደረሰው የመሰረተልማት ጉዳት 147 ነጥብ 19 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ሳይሸጥ የባከነ ሲሆን በገንዘብ ሲተመን 231 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር ተቋሙን ለኪሳራ መዳረጉ በመግለጫው ተብራርቷል፡፡ ከወልዲያ ተነቅሎ የተወሰደው ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ከሁለት መቶ ሚሊየን ብር በላይ እንደሚገመት፣ በቢሮዎች፣ በማከፋፈያ ጣቢያዎችና በሰራተኞች መኖሪያ ቤቶች የደረሰው የንብረት ውድመትና ዝርፊያ ከ10 ሚሊየን ብር በላይ መሆኑንና ከሰሜን ምስራቅ ሪጅን የተወደሱት ተሸከርካሪዎች 12 ሚሊየን ብር እንደሚገመቱ ኃላፊው አንስተዋል፡፡ የወደሙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን ለመጠገን የወጣው ወጪና በተቋሙ ላይ የደረሰው አጠቃላይ ኪሳራ 1 ነጥብ 64 ቢሊዮን እንደሚደርስ በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡ ምንም እንኳን ተቋሙ በርካታ አካባቢዎችን ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ማድረግ ቢችልም የወልቃይትና ሁመራ አካባቢዎች ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ኤሌክትሪክ አለማግኘታቸውን በተመሳሳይም የላሊበላ፣ ሰቆጣና አካባቢው ችግርም አለመፈታቱን የተጠቆሙት ዋና ደይሬክተሩ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመነጋገር ችግሩን ለመቅረፍ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ በተቋሙ ላይ የደረሰው የ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ኪሳራ የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ የደረሰውን ጉዳት የሚያሳይ እንጂ የባህር ዳር - ወልዲያ - ኮምቦልቻ፣ የመቀሌ - ዳሎል - ሠመራ - አፍዴራ ፕሮጀክት ጉዳቶች ያልተካተቱበት መሆኑን አቶ ሞገስ ገልፀዋል፡፡ በተጠቀሱት ፕሮጀክቶች ላይ የደረሰው የጉዳትመጠንና ኪሳራ ጥናቱ ሲጠናቀቅ ይፋ እንደሚደረግ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 02 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+2