uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 543 підписників, посідаючи 8 332 місце в категорії Технології та додатки та 2 157 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 543 підписників.

За останніми даними від 27 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 10, а за останні 24 години на -16, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 25.06%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 16.33% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 895 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 539 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 7.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 28 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 543
Підписники
-1624 години
-97 днів
+1030 день
Архів дописів
photo content
+9

ተቋሙ የበጀት ዓመቱን የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም መገምገም ጀመረ .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች የተቋሙን የ2016 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈፃፀም በተቋሙ የስብሰባ አዳራሽ መገምገም ጀምረዋል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ የግምገማ መርሃ-ግብሩን ሲያስጀምሩ እንደተናገሩት በዕለቱ በተቋሙ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም እና ተቋሙን በቀጣይ ማሻሻል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ይደረጋል። በአፈፃፀም ውይይቱ ላይ ሁሉም አመራርና ሠራተኛ ለተቋሙ ውጤታማነት ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚጠበቅበትም አሳስበዋል። ግምገማው በተቋሙ የስትራቴጂክ ዕቅድ የትኩረት መስኮች በሆኑት የአስተዳደርና የኦፕሬሽን ልህቀት፣ የማይበገርና አስተማማኝ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፣ የፈጠራና የዲጂታል ሽግግር እንዲሁም በሰው ሃብት ልማት ላይ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተከናወኑ አበይት ተግባራት ላይ ያተኩራል። በአፈፃፀም ግምገማው ላይ የተቋሙን የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ጠንካራና ደካማ ጎኖች፣ የተገኙ መልካም አጋጣሚዎች እና ያጋጠሙ ችግሮች እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ውይይት ይካሔዳል ተብሎም ይጠበቃል። የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና ውይይቱ ከመጀመሩ በፊትም በበጀት ዓመቱ ተቋሙ በህይወት ላጣቸው ሠራተኞች የህሊና ፀሎት ተደርጓል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ግንቦት 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

በሰሜን ሪጅን ያለውን የመለዋወጫ እቃዎች እጥረት ለመቅረፍ እየተሰራ ነው፤ …….//…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሰሜን ሪጅን ያለውን የመለዋወጫ እቃዎች እጥረትን በመቅረፍ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፊያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ የዘርፉ ሥራ አሥፈጻሚ ተወካይ አቶ አበባው ያለው እንደገለጹት በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ተከስቶ በነበረው አለመረጋጋት ምክንያት በሪጂኑ ላይ ያጋጠመውን የመለዋወጫ እቃዎች አቅርቦት ችግር ለመፍታት እየተሰራ ነው፡፡ በአካባቢው በነበረው አለመረጋጋት ምክንያት ያጋጠመውን የኃይል አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ ተቋሙ ጥናት ማድረጉን የገለጹት አቶ አበባው ጥናቱን መሰረት በማድረግ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ይገኛሉ፡፡ በዚህም የሰሜኑን ግሪድ አስተማማኝ ለማድረግ የሚያስችል “ኖርዘርን ግሪድ ሪሃብሊቴሽን” በተባለ ፕሮጀክት የማስተላለፊያ መስመር ኮንዳክተርና ኦፕቲካል ፋይበር (OPGW) ግዥ ተፈጽሞ ሰመራ ከተማ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ አቶ አበባው አክለውም ጉዳት ደርሶበት የነበረውን የአዲግራት ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ለመቀየርና በጭነት ልዩነት ወቅት ቮልቴጅን ለመቀጣጠር የሚረዳ መሣሪያ (shunt reactor) በግዥ ሂደት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በተከዜ የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያም በጭነት ልዩነት ወቅት ቮልቴጅን ለመቀጣጠር የሚረዳ መሣሪያ የተከላ ሥራ በቅርቡ እንደሚጀመርም ጠቁመዋል፡፡ በፕሮጀክቱ አማክኝነት የሰሜኑን ግሪድ በማስተካከል በአካባቢው ያለውን የኃይል መዋዤቅ ይቀርፋሉ ተብሎ የታሰበ ተጨማሪ ትራንስፎርመር ግዥም በሂዳት ላይ እንደሚገኝ አቶ አበባው ተናግረዋል፡፡ በሁሉም ሪጅኖች ላይ ችግር የሆነው የኧርዚንግ ትራንስፎርመር (Earthing transformer) ን እጥረት ለመቅረፍም 40 ባለሰላሳ ሶስት እና ባለአስራ አምስት ኪሎ ቮልት ኮንትራት ተፈርሞ ግዥ ላይ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡ በሰሜን ሪጅን ከፍተኛ የመለዋወጫ እቃ ፍላጎት መኖሩን የሚናገሩት ተወካዩ የመለዋወጫ እቃዎች አብዛኞቹ የውጭ ምንዛሬ የሚጠይቁ በመሆናቸው እቃዎችን በማቅረብ በኩል አልፎ አልፎ የመዘግየት ችግር ሊኖር እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡ አሁን ላይ ለሪጅኑ የሚያስፈልጉት የመለዋወጫ እቃዎች አብዛኞቹ ወደ ተቋሙ እቃ ግምጃ ቤት መግባታቸውን እና ቀሪውን ለማሟላት ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ አቶ አበባው ተናግረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ግንቦት 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ሙስናን እና ብልሹ አሰራሮችን በጋራ መታገል እንደሚገባ ተገለፀ ......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች ሙስናን እና ብልሹ አሰራሮችን በጋራ መታገል እንደሚገባቸው የተቋሙ የፀረ-ሙስና እና ሥነ-ምግባር ዘርፍ አስታወቀ። ዘርፉ ሙስናን እና የሥነ-ምግባር ጥሰቶችን መከላከል ላይ ያለመ የሁለት ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል። በሥልጠናው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በተቋሙ የፀረ-ሙስና እና ሥነ-ምግባር ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መርጋ ተረፈ እንደገለፁት ሙስና በሃገሪቱ ላይ እያሳደረ ያለውን አሉታዊ ተፅዕኖ አጥብቀን ልንታገለው ይገባል። በሀገሪቱ የሙስና እና ብልሹ አሠራር ተጋላጭነትን ለመከላከል እንዲቻል ለትውልድ ሥነ-ምግባር ግንባታ ትኩረት መሰጠት እንደሚገባም ነው አቶ መርጋ የገለፁት። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ዘርፉ ሙስናንና ብልሹ አሰራሮችን የመከላከል፣ ሥነ-ምግባርን የማስተማር፣ የክትትልና የምርመራ እንዲሁም የማማከር ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። ሁሉም የተቋሙ አመራርና ሠራተኛ ሙስናን እና ብልሹ አሰራሮችን ለመታገል ዘርፉ የጀመራቸውን ሥራዎች በማገዝ ኃላፊነቱን እንዲወጣም ነው አቶ መርጋ ጥሪ ያቀረቡት። ለተቋሙ ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናውን የሰጡት በኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሥነ-ምግባር መኮንን አቶ ሙሉነህ ጉግሳ እንደገለፁት ሙስና ዓለም አቀፋዊ ገፅታው እየሰፋ በመምጣቱ ምክንያት ሀገራት የጋራ ኮንቬንሽን እስከማዘጋጀት ደርሰዋል። ለሙስና እና ብልሹ የሥነ-ምግባር ግድፈቶች መስፋፋት ዋነኛ ምክንያትም ግልፅና ተቀባይነት ያላቸው ፖሊሲዎች አለመቀረፃቸው መሆኑን ተናግረዋል። በተቋሙ የሌጋል ካውንስሊንግና ኮምፕሊያንስ ዲቪዥን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ደረጄ አጥናፌ በበኩላቸው ሙስና በአሁኑ ወቅት በኢነርጂ ዘርፉ ላይ ሙስና እያሳደረ ስላለው ተፅዕኖ እና የሙስና ወንጀል ህጎች አተገባበር ዙሪያ ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በሥልጠናው ላይ ስለሙስና ምንነት፣ ፅንሰ-ሃሳብና ያለበት ደረጃ፣ የሥራ ሥነ-ምግባር እንዲሁም በመከላከያ መንገዶቹ ዙሪያ በሰፊው ገለፃ ተደርጓል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የፍፃሜ ጨዋታውን ያከናውናል የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግን የተቀላቀለው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው እሁድ ግንቦት 18, 2016 ዓ.ም ከአርባምንጭ ከነማ ጋር የፍፃሜ ጨዋታውን የሚያከናውን
+6
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የፍፃሜ ጨዋታውን ያከናውናል የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግን የተቀላቀለው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው እሁድ ግንቦት 18, 2016 ዓ.ም ከአርባምንጭ ከነማ ጋር የፍፃሜ ጨዋታውን የሚያከናውን ይሆናል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ለፍፃሜው ጨዋታ ይረዳው ዘንድ ጎፍ በሚገኘው የክለቡ ሜዳ ጠንካራ ልምምድ እየሰራ ይገኛል። በከፍተኛ ሊጉ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የምድብ ሀን በበላይነት ሲያጠናቅቅ አርባምንጭ ከነማ ምድብ ለን በበላይነት ማጠናቀቅ ችሏል። እሁድ 8 ሰዓት በአበበ ቢቄላ ስታዲየም ጨዋታው የሚከናወን ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮች እና ሰራተኞች በስታዲየም ተገኝታችሁ ክለባችሁን እንድታበረታቱ ጥሪ እናስተላልፋለን። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ግንቦት 16 ቀን 2016 ዓ.ም

በመንግስት ፕሮጀክቶች የሚቀርቡ የካሳ ጥያቄዎች የልማት ስራዎችን እያስተጓጎሉ ናቸው ………///………. የፌደራል ፕሮጀክቶች በሚተገበሩበት ወቅት የሚመጣው የካሳ ጥያቄ እጅግ የተጋነነ እና የመንግስትን እቅም እየተፈታተነ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የገንዘብ ሚንስቴርን እና ተጠሪ ተቋማቱን የ2016 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወር የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ገምግሟል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው የሚኒስቴሩን የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ሲገመግም ሚኒስትር ዴኤታው እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) እንደተናገሩት መንግስት በሚያከናውናቸው የልማት ስራዎች የካሳ ጥያቄ ዋነኛ ችግር እየሆኑ መጥተዋል፡፡ የሚጠየቀው የካሳ ጥያቄ ከመንግስት አቅም ጋር የሚጣጣም ባለመሆኑ የልማት ሥራዎችን እያስተጓጎሉ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም መንግስት የተጠየቀውን የካሳ ጥያቄን በሙሉ የመክፍል አቅም የለውም ብለዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ የገቢ ምንጩን እያሰፋ መምጣቱን ገለፀ .…//….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የገቢ ምንጩን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሰፈ መምጣቱን በተቋሙ የገበያ እና ቢዝነስ ልማት መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የሽያጭና ደንበኞች አስተዳደር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ምኒልክ ጌታሁን እንዳስታወቁት ከዚህ በፊት የተቋሙ የገቢ ምንጭ በኃይል ሽያጭ እና በፋይበር ኦፕቲክስ (OPGW) ኪራይ ላይ ብቻ ተገድቦ የቆየ ነበር። በአሁኑ ወቅት ተቋሙ የገቢ ምንጩን በማስፋት በተያዘው በጀት ዓመት ከተለያዩ አገልግሎቶች ገቢ ማግኘት መጀመሩንም ጠቁመዋል። እንደ አቶ ምኒልክ ገለፃ የአዋጭነት ጥናት በማካሄድ፣ የረጲ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ደረቅ ቆሻሻ ካቃጠለበት አገልግሎት እንዲሁም በዳታ ማይኒንግ ሥራ ላይ ለተሰማሩ ድርጅቶች ኃይል በማቅረብና ሰርቨራቸውን በማከፉፈያ ጣቢያዎች ግቢ ላይ ካስቀመጡበት አገልግሎቶች (Anslery Service) ተቋሙ ተጨማሪ ገቢ እያገኘ ነው። በዚህም በ2016 በጀት ዓመት ከተጀመሩ አዳዲስ የገቢ ምንጮች ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ756 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ነው ሥራ አስኪያጁ የገለፁት። ከዚህ ውስጥ 555 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብሩ (10 ነጥብ 1 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር) በዳታ ማይኒንግ ሥራ ላይ ከተሳተፉ ድርጅቶች የኃይል አቅርቦት እና 72 ነጥብ 83 ሚሊዮን ብሩ ደግሞ ድርጅቶቹ ሰርቨራቸውን በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ካስቀመጡበት የአገልግሎት ክፍያ የተገኘ ነው። በተጨማሪም 6 ነጥብ 11 ሚሊዮን ብሩ ከአዋጭነት ጥናት እንዲሁም 121 ነጥብ 78 ሚሊዮን ብሩ ረጲ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ደረቅ ቆሻሻ ካቃጠለበት የአገልግሎት ክፍያ የተገኘ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ አብራርተዋል። ተቋሙ የገቢ ምንጩን እያሰፋ በመሄዱ ገቢው ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ የመጣ ሲሆን ለአብነትም በ2012 በጀት ዓመት ከነበረው የ9 ቢሊዮን ብር ገቢ በ2015 በጀት ዓመት ገቢው ከ21 ቢሊዮን ብር በላይ ደርሷል። በተያዘው የ2016 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራትም ከ20 ነጥብ 28 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን አቶ ምኒልክ ጠቁመዋል። አዳዲስ የገቢ ምንጮች ለተቋሙ የገቢ እድገት ከፍተኛ አስተዋፅዖ እያበረከቱ መሆኑን የተናገሩት ሥራ አስኪያጁ በቀጣይም የተቋሙን ገቢ የሚያሳድጉ የተለያዩ የገቢ ምንጮችን ተግባራዊ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በዳታ ማይኒንግ ሥራ ላይ ለመሳተፋ ለተቋሙ የኃይል አቅርቦት ጥያቄ ካቀረቡት ሃያ አምስት ድርጅቶች እስከ አሁን አራቱ ወደ ሥራ የገቡ ሲሆን ዘጠኝ ድርጅቶች ደግሞ ሰርቨራቸውን በተቋሙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግቢ ውስጥ በማስቀመጥ ከተቋሙ ጋር እየሰሩ መሆናቸውን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያስረዳል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ የማማከር ሥራዎችን ከሚያከናውን ኩባንያ ጋር ሥምምነት ተፈራረመ ........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዳር አል ሃንዳሳህ ሼር እና ፓርትነር (Dar Al Handasah Shair and Partners) ከተባለ ኩባንያ ጋር የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የማማከር ሥራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ሥምምነት በስካይ ላይት ሆቴል ማካሔዱን አስታወቀ። ሥምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የዳር አል ሃንዳሳህ ሼር እና ፓርትነር ኩባንያ (Dar Al Handasah Shair and Partners) የኦፕሬሽን ዳይሬክተር ሚስተር ጣሪቅ አል-ቃኒ ተፈራርመዋል፡፡ ሥምምነቱ ዳር አል ሃንዳሳህ ሼር እና ፓርትነር ኩባንያ ከተቋሙ የኢንጅነሪንግ የሥራ ዘርፍ ጋር በአጋርነት የማማከር ሥራዎችን እንዲያከናውን የሚያስችል ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንደተናገሩት ሥምምነቱ የተቋሙ የኢንጅነሪንግ ዘርፍ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የማማከር ሥራዎችን መስራት የሚያስችለውን ልምድና ተሞክሮ እንዲያገኝ ዕድል ይፈጥራል። ኩባንያው የተቋሙን ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ዲዛይን እና የቁጥጥር ሥራ እየሰራ እንደሚገኝ ያስታወሱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ከተቋሙ የኢንጅነሪንግ የሥራ ዘርፍ ጋር በአጋርነት ለመስራት በአዲስ ምዕራፍ መምጣቱንም ተናግረዋል፡ የዳር አል ሃንዳሳህ ሼር እና ፓርትነር ኩባንያ የኦፕሬሽን ዳይሬክተር ሚስተር ጣሪቅ አል-ቃኒ በበኩላቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ ልምድና ዕውቀት ያለው የማማከር አገልግሎት መስጠት የሚችል ኩባንያ ለመፍጠር እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኢነርጂ ዘርፍ በምስራቅ አፍሪካ ግዙፉ ኩባንያ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ከተቋሙ የኢንጅነሪንግ የሥራ ዘርፍ ጋር በአጋርነት የማማከር አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸውን ሥምምነት ማድረጋቸው ትልቅ ዕድል መሆኑንም ጨምረው ጠቅሰዋል። ፕሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ኩባንያቸው የበኩሉን ሚና እንደሚወጣም ነው የተናገሩት። ሥምምነቱ የፕሮጀክቱን ቀሪ የግንባታ ሥራዎች በመከታተልና የማማከር ሥራዎችን በማከናወን ለአገልግሎት ዝግጁ ማድረግ እንደሆነም ነው የተገለፀው። የሁለት ዓመት የኮንትራት ጊዜ በተሰጠው የአጋርነት ሥምምነት መሰረት በኩባንያው እና በተቋሙ የኢንጅነሪንግ ዘርፍ መካከል የልምድ ልውውጦች፣ የሥራ ላይ ሥልጠናዎች እንዲሁም የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር ሥራዎች እንደሚሰሩም ተጠቅሷል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማማከር ሥራዎችን በኢንጅነሪንግ ዘርፍ ሙሉ በሙሉ በራስ አቅም እንዲከናወን የሚያስችል የስትራቴጂክ ግብ ቀርፆ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ በሥምምነቱ ወቅት ተገልጿል። ዘርፉ ከዓለም አቀፍ አማካሪ ድርጅት ጋር በአጋርነት የማማከር ሥራዎችን እንዲያከናውን የጀነሬሽን ኮንስትራክሽን ዘርፍ ድርሻው የጎላ መሆኑም ተመላክቷል። የፕሮጀክቱን የማማከር ሥራዎች ለማከናወን ከ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ በጀት የተያዘ ሲሆን የፋይናንስ ወጪውም ከዴንማርክ አለም አቀፍ የልማት ኤጀንሲ (DANIDA) በተገኘ ብድርና ስጦታ የሚሸፈን ነው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

ተቋሙ ከይዞታ ማረጋገጫ፣ ከመሠረተ ልማት ሥርቆትና ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ ችግሮች እንዲፈቱለት ጠየቀ፤ ችግሮችን በፍጥነት ለመፍታት ኮሚቴ ይቋቋማል - የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ……..////…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሸገር ከተማ አስተዳደር ከይዞታ ማረጋገጫ፣ ከመሰረተ ልማት ሥርቆትና ከካሳ ክፍያ ጋር የሚስተዋሉ ችግሮች እንዲፈቱለት የከተማ አስተዳደሩን ጠየቀ፡፡ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ከሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) እና ከሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች እንደገለፁት በከተማ አስተዳደሩ ክልል የሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ይዞታዎች ከፍተኛ የመሬት ግብር ክፍያ ቀርቦባቸዋል፤ አንዳንዶቹም ግብር ከተከፈለባቸው በኋላ ዳግመኛ ግብር ተጠይቆባቸዋል፡፡ ለግሪዱ ስጋት የሚሆኑና ለተደጋጋሚ የኃይል መቋረጥ ምክንያት የሆኑ ስርቆቶች እየተፈፀሙ በመሆኑ ከተማ አስተዳደሩ የተሰረቁ የኃይል ተሸካሚ ብረታ ብረቶችን በመቆጣጠርና በዘራፊዎች ላይ አስተማሪና ተመጣጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ በማድረግ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ለዓመታት ያልተጠናቀቁ የይዞታ ማረጋገጫ ጉዳዮች እልባት እንዲያገኙ ከተማ አስተዳደሩ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ በተጨማሪም ቋሚ የግንኙነት መድረኮች በመፍጠር ለችግሮቹ ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ፍላጎት እንዳለው ተቋሙ አስታውቋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) በሰጡት ምላሽ ከተማ አስተዳደሩ ፈጣንና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ከያዘው ዕሴት ጋር የሚጋጩ ጉዳዮችን በመለየት እንዲስተካከሉ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ ለህብረተሰቡ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን ጉዳይ በተለየ ሁኔታ እንደሚመለከት የገለፁት ከንቲባው የተጠቀሱትን ችግሮች በፍጥነት ለመፍታት ኮሚቴ እንደሚቋቋም አረጋግጠዋል፡፡ ከስርቆት ጋር የተነሱትን ጉዳዮችን ይዞ ወደ ወረዳዎች በመውረድ እና ህብረተሰቡን በማሳተፍ ለውጥ ለማምጣት በትኩረት እንደሚሰራ አስታውቀዋል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ ሊሰራቸው ላሰባቸው የስማርት ከተማና ግዙፍ ፕሮጀክቶች የሚያስፈልገውን ኃይል ተቋሙ ታሳቢ አድርጎ እንዲሰራም ጠይቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ተቋሙ ኃይል ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ የአጭር፣ የመካከለኛ እና የረጅም ጊዜ ዕቅድ መንደፉን ገልፀዋል፡፡ ተቋሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በሚሰራቸው ሥራዎች የህብረተሰቡን የኃይል አቅርቦት ጥያቄ እየፈታ መምጣቱን ጠቁመዋል፡፡ የሀገሪቱ ከፍተኛ ኃይል የሚጠቀመው መዲናችን አዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት ከተሞች በመሆናቸው መሰረተ ልማቱን በትኩረት መጠበቅ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተለያዩ አካባቢዎች የሚያጋጥመውን የኃይል መቆራረጥ ችግር ጣት በመጠቋቆም ሳይሆን ተቀራርቦ በመስራት ለመፍታት ተቋሙ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ ኃላፊዎቹ የተጀመረው ግንኙነት በፍጥነት ወደ መሬት እንዲወርድ የጋራ ኮሚቴዎች እንዲዋቀሩና አሰራሩን ህጋዊ ለማድረግ የመግባቢያ ስምምነት እንዲዘጋጅ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 13 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ብረት የሰረቁ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ፤ …//… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከሱሉልታ - ደብረ ማርቆስ በተዘረጋው ባለ 400 ኪሎ ቮልት ጥምር መስመር ላይ ስርቆት የፈጸሙ ሦሥት ግለሰቦች በእስራት መቀጣታቸውን የማእከላዊ አንድ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመር እና ኦፕቲካል ፋይበር ቢሮ ገለጸ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ በፍቃዱ በቀለ እንዳስታወቁት ስርቆት ሚያዚያ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 በሰሜን ሸዋ ዞን በሱሉልታ ወረዳ ልዩ ስሙ ወረ-ኤርሶ ኮሶበር በተባለ ቦታ ተፈጽሟል፡፡ አቶ ቀነኒሳ በቀለ፣ አቶ አዳነ ጥሩነህ እና አቶ አዳነ አሸብር የተባሉ ግለሰቦች የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ብረቶቹን ሰርቀው በማዳበሪያ ይዘው ሲሄዱ በአካባቢው በጥበቃ ስራ ላይ በተሰማሩ የሚሊሻ አባላት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገልጸዋል፡፡ ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 12 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው ችሎት እያንዳንዳቸው በሁለት ዓመት እስራት እንዲቀጡ ውሳኔ ማስተላለፉን አቶ በፍቃዱ ተናግረዋል፡፡ በአጥፊዎቹ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ የሱሉልታ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት እና የአካባቢው ሚሊሻዎች ላደረጉት አስተዋጻኦ ሥራ አስኪያጁ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 12 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ጣቢያው በሙሉ አቅሙ ኃይል እንዲያመነጭ ርብርብ እየተደረገ ነው፤ ……//…… የአሸጎዳ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በሙሉ አቅሙ ኃይል እንዲያመነጭ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀኔሬሽን ኦፕሬሽን ቴክኒካል ድጋፍ ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ኃላፊ አቶ አብዱ ይማም ጣቢያው በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በነበረው የጸጥታ ችግር ምክንያት አቁሞ የቆየውን መደበኛ የኦፕሬሽን ሥራ ቢጀምርም በሙሉ አቅሙ እየሰራ አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡ ጣቢያው በሙሉ አቅሙ የኦፕሬሽን ሥራውን እንዲያከናውን ለማስቻል በሦስት ምዕራፍ የተከፈለ የጥገናና የፍተሻ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ሥራው ከፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲና ከአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ምዕራፍ አንድ ቨርኔት እንዲሁም ምዕራፍ ሁለትና ሦስት ጀነራል ኤሌክትሪክ በተሰኙ ኩባንያዎች እንደሚከናወን ጠቁመዋል፡፡ ሥራውን ለማከናወን ከአጋር ድርጅቶች በቀረበ ምክረ ኃሳብ መሰረት የሳይት ምልከታ በባለሙያዎች መከናወኑንን የተናገሩት አቶ አብዱ በምልከታው መሰረትም ጣቢያው በሙሉ አቅሙ የኦፕሬሽን ሥራውን እንዲያከናውን የሚያስችል የመለዋወጫ እቃዎችን በመለየት እቃዎቹን ከአምራች ፋብሪካዎች ለመግዛት በሂደት ላይ እንደሚገኙም አብራርተዋል፡፡ በተጨማሪም በጣቢያው ጋልልዮ የተባለው የስካዳ መቆጣጠሪያ ጋር ተያይዞ ያለው ሲስተም በአሁን ባለው ሞዴለ የማሳደግ ሥራ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ አብዱ ገለጻ ጣቢያውን ወደ ሙሉ የኦፕሬሽን ሥራ ለማስገባት ከፍተኛ ችግር የነበረውን የባትሪ መለዋወጫ እቃ ለመቅረፍ የአገር ውስጥ ጨረታ ወጥቶ ከአሸናፊ ድርጅቶች ጋር የውል ስምምነት መፈረሙን ተናግረዋል፡፡ ኃላፊው አክለውም በጣቢያው ያለውን የውሃ አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ ጨረታ ወጥቶ በሂደት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ የአሸጎዳ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በሙሉ አቅሙ ኃይል ማመንጨት ሲጀምር በሀገሪቱ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ እንደሚያግዝ የገለጹት ኃላፊው ለዚህም ተቋሙ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የአሸጎዳ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 120 ሜጋ ዋት ኃይል "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ግንቦት 09 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3