uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 560 підписників, посідаючи 8 357 місце в категорії Технології та додатки та 2 160 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 560 підписників.

За останніми даними від 25 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 32, а за останні 24 години на -5, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 26.03%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 15.88% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 4 052 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 472 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 8.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 26 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 560
Підписники
-524 години
+167 днів
+3230 день
Архів дописів
''የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን መጠበቅ ግዴታችን ነው'' የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ….....///…….... የአዳማ ከተማ አስተዳደር የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን የመጠበቅ ግዴታውን እንደሚወጣ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ኃይሉ ጀልዴ ገለፁ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች ከከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ኃይሉ ጀልዴ ጋር በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ስለሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡ የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሸን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለከንቲባው እንደገለፁት በአሁኑ ወቅት በኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ የስርቆት ወንጀሎች እየጨመሩ መጥተዋል። ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት በስርቆትና የተሰረቁ የኃይል መሰረተ ልማቶችን መልሶ ለመገንባት ከአንድ ቢሊየን ብር የሚበልጥ ጉዳት እንደደረሰበት ዳይሬክተሩ አስረድተዋል። በከተማ አስተዳደሩ ስር በሚገኙ ቀበሌዎች እየተስፋፋ የመጣውን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት ለመከላከል የከተማ አስተዳደሩ በሁሉም መዋቅሮቹ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ ጠይቀዋል። በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ክትትልና ቁጥጥር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንዳስታወቁት በአዋሽ መልካሳ-ወለንጪቲ በተዘረጋው መስመር ኡላጋ ቀበሌ ላይ 3 ምሰሶዎች በስርቆት የተነሳ በመውደቃቸው እስካሁን የጥገና ሥራ ማከናወን አልተቻለም። ተቋሙ ከማህበረሰቡ ጋር ተቀራርቦ በመስራት በኩል መልካም ጅምሮች እንዳሉት የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ ይሁን እንጂ በወንጀል ፈፃሚዎቹ ላይ የሚጣለው ቅጣት ጠንካራና አስተማሪ አለመሆኑን አንስተዋል። የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኃይሉ ጀልዴ በሰጡት ምላሽ ከተማ አስተዳደሩ ተጨማሪ የኃይል አቅርቦት እየጠየቀ ባለበት በአሁኑ ወቅት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን መጠበቅ ግዴታው መሆኑን ይረዳል። በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት ለመከላከል በሚከናወነው ሥራ የቅድሚያ ትኩረት ሰጥተው እንደሚከታተሉትና በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮች መመሪያ እንደሚሰጡ አስረድተዋል፡፡ ከኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ አካላት ስርቆት ባሻገር በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ሥር የሚከናወኑ ግንባታዎችን በመከላከል የህብረተሰቡን እና የመስመሩን ደህንነት የማስጠበቅ ሥራ ለመስራት መታቀዱንም ከንቲባው ገልፀዋል። ከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ ሊሰራቸው ላሰባቸው ኢንዱስትሪዎችና ሌሎች አዳዲስ ፕሮጀክቶች የሚያስፈልገውን ኃይል ተቋሙ ታሳቢ አድርጎ እንዲሰራም ጠይቀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ምቹ የሥራ አካባቢ ለመፍጠር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው .........//........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለሠራተኞቹ ምቹ የሥራ ከባቢን ለመፍጠር እየሰራ መሆኑን የጣቢያው አስተዳደር፣ ንብረትና አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ታምራት ቸኮል እንደተናገሩት የማመንጫ ጣቢያው ሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢ ተፈጥሮላቸው ሥራቸውን ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲያከናውኑ የተለያዩ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው። ለሠራተኛው የክበብ አገልግሎት፣ የዕረፍት ጊዜያቸውን የሚያሳልፉባቸው የመዋኛ ገንዳ፣ የዲ ኤስ ቲቪ እና ሌሎች የመዝናኛ አማራጮች መመቻቸቱን ተናግረዋል። ከኃይል ማመንጫ ቤቱ እስከ ሠራተኛ መኖሪያ ያለው 13 ኪሎ ሜትር መንገድ ጠመዝማዛና በተለይ በክረምት ወራት ናዳ የሚበዛበት መሆኑን የጠቆሙት አቶ ታምራት ማሽኖችን ከሌላ ቦታ በማስመጣት የመንገድ ጠረጋ ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል። በተጨማሪም በመንገዱ አስቸጋሪነት ምክንያት ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ መኪኖች በሽፍት የሚተላለፉበት አሰራር መዘርጋቱንም ተናግረዋል። የማመንጫ ጣቢያው ከከተማ የራቀ በመሆኑ ጣቢያው የትራንስፖርት አገልግሎት በመመደብ ሠራተኛው የሚያስፈልገውን ነገር የሚሸምትበት በሳምንት ሁለት የገበያ ቀን ማመቻቸቱንም ጠቁመዋል። እንደ አቶ ታምራት ገለፃ የጣቢያውን ሠራተኞች አቅም ለማጎልበት አጫጭር የሥራ ላይ ሥልጠና ከመስጠት በተጓዳኝ ከዋቻሞ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በኮምፒዩተርና ኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ የትምህርት መስክ መምህራን ማመንጫ ጣቢያው ድረስ መጥተው እንዲያስተምሩ እየተደረገ ይገኛል ነው ያሉት። ጣቢያው የመምህራንን ማረፊያ፣  የመመላለሻ ትራንስፖርት፣ የመማሪያ ክፍል እና በኃይል ማመንጫ ቤቱና በማከፋፊያ ጣቢያው በተግባር የታገዘ ትምህርት የሚማሩበትን ሁኔታ ማመቻቸቱን ገልጸዋል። ጣቢያው ባመቻቸው የትምህርት ዕድል ቀደም ሲል 38 ሠራተኞች የተመረቁ ሲሆን 40 የሚሆኑት ደግሞ በትምህርት ላይ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም ከወልቂጤ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ጋር በመተባበር 20 የሚደርሱ የጣቢያው ሠራተኞች ከደረጃ 1 እስከ 4 ተምረው መመረቃቸውንም ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል። ይህም ሠራተኞች ሥራቸውን ተረጋግተው እንዲሠሩና ሙያዊ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ የሚረዳ ነው ብለዋል። እንደ አቶ ታምራት ገለጻ የሠራተኛውን ምቾት በመጠበቅ በሥራ ላይ ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያግዝ የመኖሪያ ካምፕ እየተገነባ ይገኛል ብለዋል። የግልገል ጊቤ 2 የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 219 ሠራተኞች አሉት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

ጣቢያው በሩብ ዓመቱ ከ102 ጊጋ ዋት ስዓት በላይ ኃይል አምርቷል ......//...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2017 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት 102 ነጥብ 3 ጊጋ ዋት ሠዓት ማምረቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ በቀለ እንደገለጹት ጣቢያው በሩብ ዓመቱ 120 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ስዓት ለማምረት አቅዶ 102 ነጥብ 386 ጊጋ ዋት ሠዓት ኃይል በማምረት የዕቅዱን 84 ነጥብ 84 በመቶ ነው። በ2016 በጀት ዓመት የመጨረሻ ወራት በጣቢያው ግድብ ላይ የነበረው ውሃ በከፍተኛ ደረጃ በመቀነሱ በግድቡ የተሻለ ውሃ ለመያዝ ሲባል በ2017 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሳምንታት ጣቢያው በአንድ ዩኒት ብቻ እንዲሰራ በመደረጉ አፈፃፀሙ ዝቅ ማለቱን ተናግረዋል። አሁን ላይ ግድቡ በቂ ውኃ በመያዙ እና በጣቢያው ላይ የቅድመ መከላከል፤ የትንበያና የሁኔታ አመላካች ጥገና ሥራዎች በእቅድ ተይዘው እየተከናወኑ በመሆኑ በቀጣይ ጊዜያት የተሻለ ኃይል ለማምረት እንደሚቻል ገልጸዋል። ጣቢያው ያለምንም መልሶ ግንባታ ከ36 ዓመት በላይ በማገልገሉ በኦፕሬሽን ሥራው ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩንና የተርባይኖቹን ኃይል የማምረት አቅም ከ38 ነጥብ 25 ሜጋ ዋት ወደ 30 ሜጋ ዋት ዝቅ ማለቱን ተናግረዋል። ጣቢያው ካሉት አራት ተርባይኖች አንዱ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ በመለዋወጫ ዕቃ ምክንያት አገልግሎት እየሰጠ አለመሆኑንም አንስተዋል። ችግሮቹን ለመፍታት በጣቢያው ከሚሰሩ የጥገና ሥራዎች በተጓዳኝ በጣቢያው ላይ የመልሶ ግንባታ ሥራ ለመስራት የሩሲያ ባለሙያዎች በቀጣይ ሳምንት ወደ ሀገር ቤት ገብተው ጣቢያውን ካዩ በኋላ ስምምነቱ ተፈርሞ ወደ ተግባር እንደሚገባ ገልጸዋል። ይህም የኦፕሬሽን ሥራውን በማሻሻል ጣቢያው በሙሉ አቅሙ ኃይል ወደ ማምረት እንዲገባ ያስችለዋል ብለዋል። ጣቢያው በ2016 በጀት ዓመት 434 ጊጋ ዋት ስዓት ለማምረት አቅዶ 603.187 ጊጋ ዋት ስዓት በማምረት የእቅዱን 138 ነጥብ 98 በመቶ ማሳካቱ ይታወሳል። በ1980 ዓ.ም ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የመልካ ዋከና የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በአራት ተርባይን 153 ሜጋ ዋት የማምረት አቅም አለው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ደም ለገሱ ………///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች በተቋሙ ዋና መሥሪያ ቤት የደም ልገሳ ዛሬ አካሂደዋል፡፡ የደም ልገሳ መርሃግብሩ በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲውል ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡ ደም ሲለግሱ ያገኘናቸው የተቋሙ የፋይናንስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደገለፁት በተቋሙ ዋና መ/ቤት የደም ልገሳ ፕሮግራም መዘጋጀቱ የሠራተኛው የሥራ ሰዓት ከመቆጠቡም በላይ ደም ለመስጠት ፈልገው በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ኢትዮጵያ ደም እና ህብረህዋስ አገልግሎት ለመሄድ ያልቻሉትን ሠራተኞች በቅርበት ለማግኘት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ በተቋሙ ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍስሐ ጌታቸው በበኩላቸው ሁሉም የተቋሙ ሠራተኞችና አመራሮች ግንዛቤያቸውን በማሳደግ የደም ባንክ አባል ሆኖ ደም በመለገስ ህይወትን የመታደግ በጎ ተግባርን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባዋል ብለዋል፡፡ ደም ለመጀመሪያ ግዜ ሲለግሱ ያገኘናቸው አቶ ካሰሁን ጸሀይ፣አቶ አብደላ ሻንቆ እና አቶ ታምሩ ባቱ ቢያንስ የሶስት ሰው ህይወት ሊታደግ የሚችል ደም ደ መለገስ በመቻላቸው እንደተደሰቱ እና ተቋሙ ይህን በማመቻቸቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ በቀጣይም መሰል የደም ልገሳዎች ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡ አቶ ሙሉቀን ዮሴፍ እና ወ/ሮ ፋናዩ ዘበነ በበኩላቸው ደም ልገሳውን ለመጀመሪያ ግዜ ቢሰጡም የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ጉዳት ደርሶባቸው ህይወታቸው ከማያውቁት ሰው በተለገሰ ደም በመትረፉ ደም ለመስጠት መወሰናቸውን ገልፀዋል፡፡ አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ እና አቶ ኤርሚያስ ጥላሁን እንደተናገሩት ደግሞ በተለያዩ ጊዜያት ደም መለገሳቸውን አውስተው ደም መሥጠት ዘር፣ጎሳ እና ጾታ ሳይለይ ህይወቱን ሊያጣ የነበረን ሰው ህይወቱን መመለስ ከስጦታዎች በላይ ስጦታ እና የበጎ ተግባርም ምሳሌ እንደሆነ በመረዳታቸው እንደሆነ ተናግረዋል ፡፡ ከ 1984 ዓ.ም. ጀምሮ ለ 118 ጊዜያት ደም የለገሱት በደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት የትምህርት እና የቅስቀሳ ባለሙያ የሆኑት ሲስተር አሰጋሽ ጎሳ እንደተናገሩት ደም መለገስ ምንም አይነት የጎንዮሽ ጉዳት የማያስከትል እና ዘረፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች በደም እጥረት ምክንያት ህይወታቸውን የሚያጡ የበርካታ ወገኖቻቸውን ህይወት መታደግ እንደሚቻል በመረዳት በዚህ በጎ ተግባር ላይ በመሳተፋቸው ሊመሰገኑ ይገባል ብላዋል፡፡ ደም የሚሞት እና የሚያረጅ እንዲሁም ራሱን የሚተካ በመሆኑ ክቡሩን የሰው ህይወት ልናድንበት እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የተቋሙ ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሼን መምሪያ ይህን ፕሮገራሙ አስተባብሮ ማዘጋጀቱ የሚመሰገን ተግባር እንደሆነ ያወሱት ሲስተር አሰጋሽ በልገሳ መርሃግብሩ 27 ዩኒት ደም መለገሱንና በቀጣይም በተሻለ እንደሚሰበሰብ ያላቸውን እምነት ጠቁመዋል ፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር 2ኛ የስራ መደብ መጋቢት 02 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለ
+1
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር 2ኛ የስራ መደብ መጋቢት 02 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ጥቅምት 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ዘነበወርቅ በሚገኘው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ትምህርትና ስልጠና ማዕከል የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም

በዚህ ዓመት መጨረሻ የሠራተኞችን የመኖሪያ ቤት ግንባታ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው ……...//............ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞች መኖሪያ ቤት ግንባታ ፕሮጀክትን እስከ ዓመቱ መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የሳይቱ ሱፐርቫይዘር ገለጹ። ሱፐርቫይዘሩ አቶ ሙሐመድ አሕመድ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ የ250 መኖሪያ ቤቶች፣ የመሰብሰቢያ አዳራሽ፣ ክሊኒክ፣ ቢሮዎችና የሁለት ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ እንዲሁም 6 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ መንገድ ግንባታ ያካተተ ነው። በአሁኑ ወቅት 200 መኖሪያ ቤቶች በተለያየ የግንባታ ደረጃ ላይ እንደሚገኙና ከእነዚህ ውስጥ 175 ቤቶች ቆርቆሮ መልበሳቸውን የጠቆሙት ሱፐርቫይዘሩ የሁለቱ የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ መጠናቀቁንም ገልጸዋል። የውስጥ ለውስጥ መንገድ ግንባታው በመፋጠን ላይ መሆኑን በመጥቀስ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 44 ነጥብ 64 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል። የግልገል ጊቤ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሥራ ጥራቱን ጠብቆ መሉ በሙሉ እስከ ዓመቱ መጨረሻ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል። የግንባታ ሥራውን የሚያከናውነው ዓይናለም ጋሻው ሕንጻ ሥራ ተቋራጭ የሳይቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ አዲሱ ፈንታ በበኩላቸው ግንባታውን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ባይቻልም ከተቋሙ ጋር በትብብር በመስራት በዚህ ወር መጨረሻ የ150 ቤቶች የማጠናቀቂያ ሥራ ለመፈፀም እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። ግንባታቸው ያልተጀመሩ 50 ቤቶች መኖራቸውን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ከዚህ ወስጥ የ18 ቤቶች ግንባታ በሚቀጥሉት ሳምንታት ይጀመራሉ ነው ያሉት። የሲሚንቶ እጥረት፣ ወቅታዊው የዋጋ ንረት እና በአካባቢው ብቁ የሠው ኃይል ያለመኖር ፕሮጀክቱን እየፈተኑት መሆኑን ገልጸዋል። የጣቢያው አስተዳደር፣ ንብረትና አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ታምራት ቸኮል በበኩላቸው የመኖሪያ ቤቱ መገንባት ለሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢን በመፍጠር ሥራቸውን ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲያከናውኑ የሚረዳ ነው ብለዋል። አሁን አገልግሎት እየሰጠ ያለው የሠራተኞች መኖሪያ ቤት ከከተማ ርቆ የሚገኝና የልጆች መማሪያ ትምህርት ቤት የሌለው መሆኑን የጠቆሙት አቶ ታምራት የአዲሱ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት ግንባታ ችግሮቹን በዘላቂነት በመፍታት ሠራተኛው ልጆቹንና ቤተሰቡን ይዞ ተረጋግቶ ለመኖር 㙀ንደሚያስችለው ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ መንገዱ ጠመዝማዛና ናዳ የበዛበት በመሆኑ ምቹ የሥራ ከባቢን ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ላይ ተግዳሮት ፈጥሮ ቆይቷል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

ማመንጫ ጣቢያው ከዕቅድ በላይ ኃይል ማምረት ችሏል ……..///….… በኢትዮዽያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፊንጫ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ሶስት ወራት ከዕቅድ በላይ ኃይል ማምረቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ታደሠ ፈቃዱ እንዳስታወቁት ጣቢያው በሩብ በጀት ዓመቱ 169 ሜጋ ዋት ስዓት ኃይል ለማምረት አቅዶ 218 ሜጋ ዋት ስዓት በማምረት የዕቅዱን 128 ነጥብ 57 በመቶ ማሳካት ችሏል ፡፡ የጣቢያው የማመንጨት አፈፃፀም ከፍ ሊል የቻለው በኦፕቲካል ሊንክ ሞጁል ብልሽት ምክንያት ቆሞ የነበረው አንድ ዩኒት ወደ ስራው በመመለሱ ነው ብለዋል። የጣቢያውን ኃይል የማምረት አቅም የሚያሳድጉ የጥገና ሥራዎች በተያዘላቸው ዕቅድ መሰረት መሰራታቸውም ለአፈጻጸሙ ከፍ ማለት የጎላ ድርሻ ማበርከቱን ጠቁመዋል። የመለዋወጫ ዕቃዎችን ሞዲፋይ አድርጎ በራስ ዓቅም በመጠገን ማሽኖች እንዳይቆሙ መደረጉ በሩብ ዓመቱ በጥንካሬ ሊነሳ የሚችል መሆኑን ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

photo content
+1

የሠራተኞችን ሙያዊ አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው ........//........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞችን ሙያዊ አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ በቀለ እንደተናገሩት የሠራተኞችን አቅም ለማጎልበት የሥራ ላይ ሥልጠና ከመስጠት ባለፈ ከመደወላቡ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ሠራተኞቹ ባሉበት ቦታ መምህራንን በማስመጣት በኤሌክትሪካልና ኮምፒዩተር ምህንድስና የትምህርት መስክ ቅዳሜና እሁድ እያስተማረ ይገኛል፡፡ በዚህም በመጀመሪያው ዙር 21 ሠራተኞች የተመረቁ ሲሆን 17 የሚሆኑት ደግሞ በመማር ላይ ይገኛሉ፡፡ የጣቢያው ኦፕሬሽን ሥራዎች ሳምንቱን ሙሉ 24 ሰዓት የሚከናወን በመሆኑ ትምህርት በሚኖር ጊዜ የተማሪዎች ሥራ በሌሎች ሠራተኞችና በጣቢያው ኃላፊዎች ጭምር እንደሚሸፈን ተናግረዋል። ቀደም ሲል ሠራተኞች ከአሳሳ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ጋር በመነጋገር እስከ ደረጃ 3 እንዲማሩ መድረጉን የተናገሩት አቶ ቴዎድሮስ አሁን ላይ ደግሞ ከበቆጂ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በደረጃ 4 ከሃምሳ በላይ የሠራተኛ ቤተሰቦችና የአካባቢው ወጣቶች እየተማሩ ናቸው ብለዋል። ጣቢያው የመምህራንን ማረፊያ፣ የመመላለሻ ትራንስፖርት፣ የመማሪያ ክፍል እና በኃይል ማመንጫ ቤቱና በማከፋፊያ ጣቢያው ተግባር ተኮር ትምህርት የሚማሩበትን ሁኔታ ማመቻቸቱን ገልጸዋል። ከትምህርትና ሥልጠና ተቋማቱ ጋር በመነጋገር በቀጣይ በሌሎች የትምህርት መስኮች እና በማስተርስ መርሀግብር ለማስተማር አቅዶ እየሰራ ነውም ብለዋል። የሦስተኛ ዓመት የኤሌክትሪካልና ኮምፒዩተር ምህንድስና ተማሪ የሆነው ፍቃዱ ጉዲሳ እንደገለጸው በደረጃ 3 ተመርቆ በጣቢያው ከስድስት ዓመት በላይ የቴክኒክ ባለሙያ ሆኖ ሠርቷል። በጣቢያው የተመቻቸው የትምህርት ዕድል ሠራተኛው ሥራውን እየሰራ ሙያዊ አቅሙን የሚያሳድግበትና የእውቀት አድማሱን የሚያሰፋበት መሆኑን ገልጿል። የጣቢያውን ሥራ በተሻለ ዕውቀት በማከናወን ውጤት ለማስመዝገብ አቅሙ የተገነባ ሠራተኛ መኖሩ አስፈላጊ ነው የሚለው ባለሙያው ለዚህም ጣቢያው ሠራተኛው የሥራ ስዓቱን ጭምር እየተሸፈነ እንዲማር በማድረጉ ምስጋናውን አቅርቧል። ሌላኛዋ የጣቢያው ኦፕሬሽን ባለሙያና የ3ኛ ዓመት የኤሌክትሪካልና ኮምፒዩተር ምህንድስና ተማሪ የሆነችው ካብታም ምንዳ በበኩሏ የትምህርት ዕድሉ ሴቶች ሙያዊ አቅማቸውን እንዲያሳድጉና የተሻለ ደረጃ እንዲደርሱ የሚረዳ መሆኑን ትናገራለች። ቀደም ሲል አንዳንድ ወንድ ሠራተኞች ሩቅ ቦታ ሄደው ሲማሩ እንደነበረ ያወሳችው ባለሙያዋ የጣቢያው ሴት ሠራተኞች ግን ሥራቸውን ለቀው ካልሆነ በስተቀር ለመማር አስቸጋሪ እንደነበረ ተናግራለች። አሁን ላይ ጣቢያው ባመቻቸው የትምህርት እድል ምክንያት ለመማር ሲል ሥራ ለቆ ለመሄድ ማሰቡን ትቶ ባለሙያው ተረጋግቶ ሳይጉላላ ትምህርቱን እየተማረ መሆኑን ገልጻለች። የመዳወላቡ ዩኒቨርስቲ መምህርና የኢንጂነሪንግ ኮሌጅ ዲን የሆኑት ድንቁ ወርቁ ዩኒቨርስቲው የሚሰጠው ትምህርት ተማሪዎቹ በተግባር የሚያውቁትን ዘመኑ ከደረሰበት የእውቀት ደረጃ ጋር አዋህደው እንዲጠቀሙ የሚያስችል ነው ብለዋል። መዳወላቡ ዩኒቨርስቲ የጣቢያውን ውጤታማነት ለማሳደግ በሚያስችሉ የሰው ሀብት ልማት ላይ ከጣቢያው ጋር በትብብር መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። የመልካ ዋከና የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 132 ቋሚና ጊዜያዊ ሠራተኞች አሉት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል ……..///…….. በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 5ኛ ሳምንት ጨዋታ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ከሀዲያ ሆሳዕና ጋር ነጥብ ተጋርቷል፡፡ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ካደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች አንዱን ብቻ በማሸነፍ በሦስቱ አቻ ወጥቶ በአንዱ ተሸንፏል፡፡ የዛሬ ተጋጣሚው ሀዲያ ሆሳዕና ደግሞ ካደረጋቸው 4 ጨዋታዎች አንዱን ሲያሸንፍ ሁለት አቻ ወጥቶ በአንዱ ተሸንፏል፡፡ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በሰበሰባቸው ስድስት ነጥቦች ከሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በስድስት ነጥብ ርቆ 12ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 17 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content