uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 567 підписників, посідаючи 8 356 місце в категорії Технології та додатки та 2 162 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 567 підписників.

За останніми даними від 24 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 24, а за останні 24 години на 19, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 25.91%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 15.83% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 4 035 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 465 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 8.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 25 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 567
Підписники
+1924 години
+197 днів
+2430 день
Архів дописів
የውጤት ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጋቢት 02 ቀን 2015 ዓ.ም በኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር 2ኛ የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከ
የውጤት ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጋቢት 02 ቀን 2015 ዓ.ም በኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር 2ኛ የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል በተ.ቁ 1 እና 2 ላይ የተገለጻችሁ በተሰጠው የጽሁፍ ፈተና አብላጫ ውጤት ያመጣችሁ በመሆኑ ከህዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ በዋናው መ/ቤት ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 18 ቀን 2017 ዓ.ም

የማከፋፈያ ጣቢያውን አቅም በአግባቡ ለመጠቀም ደንበኞቹን መሳብ ያስፈልጋል ……..///…….. የዲቼቶ ማከፋፈያ ጣቢያን በሙሉ አቅም ለመጠቀም ደንበኞችን መሳብ እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤን ጨምሮ ሌሎች የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች የዲቼቶ ባለ 230 /33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን የኦፕሬሽን ሥራ ጎብኝተዋል። የጣቢያው ኃላፊ አቶ ብሩክ አንዳርጋቸው በጉብኝቱ ወቅት እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያው ካሉት ወጪ መስመሮች በሁለቱ ብቻ ለዲቼቶ፣ ጋላፊ፣ ኤሊዳር፣ ውሃ ልማት፣ ሠርዶ እና ስልሳ ለተሰኙ ወረዳዎችና አካባቢዎች ኃይል እያቀረበ ነው። በማከፋፈያ ጣቢያው ላይ ያለው ትራንስፎርመር 25 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ቢኖረውም በአካባቢው ያለው የኃይል ተጠቃሚ አነስተኛ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት ለደንበኞቹ እየቀረበ ያለው ኃይል 3 ሜጋ ዋት የማይደርስ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የጣቢያው የመቆጣጠሪያ ክፍል እና የሠራተኛ መኖሪያ ቤት ላይ በተፈጥሮ ምክንያት የተስተዋለው ችግር እና በጣቢያው ያለው የውሃ ችግር እንዲፈታላቸውም ጠይቀዋል። በዘርፉ የአቅም ማሳደግ፣ ማሻሻልና ማዘመን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ የማነ ኢሳይያስ በበኩላቸው በማከፋፈያ ጣቢያው የመቆጣጠሪያ እና የሠራተኞች መኖሪያ ቤት ላይ ያጋጠመውን ጉዳት በመጠገን ችግሩን ለመፍታት ይሰራል ብለዋል። የጣቢያውን የፓወር ትራንስፎርመር ደህንነት ለመጠበቅ የሚያስችሉ ዕቃዎች መግባታቸውንና የገጠማ ሥራው በቅርቡ እንደሚከናወንም አቶ የማነ አንስተዋል። የማከፋፈያ ጣቢያው በአካባቢው የሚኖረውን ደንበኛ ታሳቢ በማድረግ ባለመገንባቱ እና ደንበኞችም በሚፈለገው መጠን ባለመምጣታቸው የጣቢያውን አቅም በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል አልተቻለም ብለዋል። እንደ ዲቼቶ ሁሉ ከአፍዴራ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል የሚያገኙ ደንበኞች አነስተኛ በመሆኑ የጣቢያዎቹን የመጫን አቅም በአግባቡ ለመጠቀም የሚመለከተው አካል በአካባቢው ላይ ኢንቨስትመንቶችን በማስፋፋት ደንበኞችን መሳብ እንደሚጠበቅበት አቶ የማነ አሳስበዋል። የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ የጣቢያው ሠራተኞች ለተቋሙ ቅድሚያ በመስጠት ንብረቶቹን በአግባቡ መጠቀም እንደሚኖርባቸው አሳስበው እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች በሚፈቱበት ሁኔታ ላይም አቅጣጫ አስቀምጠዋል። የዲቼቶ ማከፋፈያ ጣቢያ ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች የሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያን ጎበኙ ………///……… ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ከአፋር ክልል የተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎች የሠመራ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የአፋር ክልል የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አቶ አህመድ ሁሴን፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ ሁሴን እና ሌሎች የክልሉና የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች የጣቢያውን የኦፕሬሽን ሥራዎች እና በጣቢያው እየተከናወነ ያለውን ተጨማሪ የሸንት ሪአክተር ተከላ ሥራ ተመልክተዋል። የሠመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ኢንድሪስ አህመድ ለሥራ ኃላፊዎቹ ገለፃ ባደረጉበት ወቅት እንደተናገሩት ጣቢያው አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ፣ ስድስት ባለ 33 እና ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት። ጣቢያው ከኮምቦልቻ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ ለሠመራ፣ ሎጊያ፣ ሚሌ፣ ዱብቲ ፣ አሳይታ ከተሞችና ለሠመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ በ33 ኪሎ ቮልት እንዲሁም ለዲቼቶ እና አፍዴራ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በባለ 230 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ኃይል እያቀረበ እንደሆነ አስረድተዋል። በማከፋፈያ ጣቢያው የተተከለው 25 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው አንድ ትራንስፎርመር እስከ 20 ሜጋ ዋት ኃይል እየጫነ እንደሆነም ተናግረዋል። በአፍዴራ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ያለውን የኃይል መዋዠቅ ለማመጣጠን በሠመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ተጨማሪ የሸንት ሪአክተር ተከላ ሥራ እየተከናወነ ስለመሆኑም ገልፀዋል። በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የአፋር ክልል የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ አቶ አህመድ ሁሴን ተቋሙ በክልሉ ያለውን የኃይል ተደራሽነት ለማስፋፋት እያደረገ ያለውን ጥረት አመስግነዋል። በቀጣይ የህብረተሰቡን የኃይል ጥያቄ በዘላቂነት ለመመለስና የክልሉን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ተቋሙ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በወቅቱ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራም አሳስበዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሠሜን ምስራቅ 2 ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሀሰን መሀመድ በበኩላቸው በክልሉ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። በአፍዴራ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባለው የኃይል ተጠቃሚ ማነስ ምክነያት የኃይል መዋዠቅ እንደሚስተዋል ያነሱት ዳይሬክተሩ ይህም ከጣቢያው ኃይል የሚያገኙ አካባቢዎች አስተማማኝ ኃይል እንዳያገኙ እያደረገ እንደሆነ አስታውቀዋል። እንደ አቶ ሀሰን ገለፃ በሠመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ እየተከናወነ ያለው ተጨማሪ የሸንት ሪያክተር ተከላ ሥራ ከአፍደራ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል የሚያገኙት ኢሬፕቲ፣ አፍዴራ፣ ቢዱ እና ኩሪ የተሰኙ ወረዳዎች የ24 ሠዓት የኃይል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከማድረጉም ባለፈ በሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያ፣ በግሪዱና በብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከሉ ላይ የተረጋጋ ኃይል እንድኖር ለማድረግ ያግዛል። በአሁኑ ወቅት 10 የክልሉ ተወላጆች በሪጅኑ በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ በማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬተርነት በልዩ ሁኔታ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉንና በቀጣይ ይህ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል። በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ በበኩላቸው በክልሉ የሚነሱ የኃይል ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመመለስ ተቋሙ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት በሠመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ እየተከናወነ ያለው የሸንት ሪያክተር ተከላ ሥራ የክልሉን ጥያቄ ለመመለስ እየተከናወነ ላለው ሥራ አንዱ አካል እንደሆነም ጠቁመዋል። በቀጣይ የሠመራ ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም በማሳደግ እና የመቆጣጠሪያ ብሬከሮችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመቀየር የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነም ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል። በክልሉ የሰሜኑ ክፍል የሚነሱ የኃይል ጥያቄዎች በቀጣይ ሊከናወኑ ከታሰቡ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ጎን ለጎን የተቋሙን የፋይናንስ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ እንደሚመለሱና ተቋሙም ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ አቶ ሀብታሙ አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

ከተንቀሳቃሽ የማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል ሲያገኙ ለነበሩ አካባቢዎች ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት እየተሰራ ነው ……...///………. ከቦሌ ለሚ ቁጥር አንድ ባለ 132/33/15 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ኤሌክትሪክ ሲያገኙ ለነበሩ አካባቢዎች ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ገለፀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት በጊዜያዊነት ታስቦ የተቀመጠው የተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ከ9 ዓመት በላይ አስቆጥሯል። 50 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው ትራንፎርመር የተገጠመለት የተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ዞን መገንባቱን ተከትሎ ኃይል መስጠት መጀመሩን አስታውሰዋል። ጣቢያው በአሁኑ ወቅት ለቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ዞን፣ አራብሳ፣ ሰሚት፣ ክሬሸር፣ ጎሮ እና አካባቢው ከ34 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝም ነው ዳይሬክተሩ የጠቀሱት። እንደ አቶ አለማየሁ ገለፃ በቦሌ ለሚ ቁጥር ሁለት ባለ 230/33/15 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የተከናወነው የማስፋፊያ ሥራ ለኢንዱስትሪ ዞኑና ለአካባቢዎቹ በቂና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል። ቀደም ሲል የቦሌ ለሚ ቁጥር አንድ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን ይጠቀሙ የነበሩ አካባቢዎችን መስመር በመቀየር ከቦሌ ለሚ ቁጥር ሁለት የማከፋፈያ ጣቢያ ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነውም ብለዋል። የቦሌ ለሚ ቁጥር አንድ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተወካይ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ማህሌት ታዬ እንደተናገሩት ጣቢያው አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ገቢ እንዲሁም በ33 ኪሎ ቮልት ሁለት እና በ15 ኪሎ ቮልት አራት ወጪ መስመሮች አሉት። እንደ ወ/ሮ ማህሌት ገለፃ በአሁኑ ወቅት ከተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል ሲያገኙ የቆዩ አካባቢዎች በቦሌ ለሚ ቁጥር ሁለት የኃይል ማከፋፈያ ስር እንዲጠቃለሉ ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ጠቁመዋል። የተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ድንገተኛ አደጋዎችን ለመከላከልና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት በማያመች ቦታ ላይ እንደተቀመጠ የገለፁት ሥራ አስኪያጇ የሠራተኞችን እና የጣቢያውን ደህንነት በማስጠበቅ በኩል ትኩረት እንዲሰጠውም አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 17 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

በፕሪሚየር ሊጉ የሴቶች ቡድን ሲያሸንፍ ወንዶች ነጥብ ተጋርተዋል ………///………. በኢትዮጵያ የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ባህርዳር ከነማን አንድ ለባዶ ሲረታ በወንዶች ፕሪሚየር ሊግ ደግሞ ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል፡፡ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ እንስቶች ሙሉ የጨዋታ የበላይነት ባሳዩበት የ5ኛ ሳምንት ጨዋታ ባህርዳር ከነማ መከላከል ላይ የተመሠረተ የአጨዋወት ስልት ተግባራዊ አድርጓል። በሁለተኛው አጋማሽ ተቀይራ ወደ ሜዳ የገባችው ሀና ሲሳይ በ90ኛው ደቂቃ ብቸኛዋን የማሸነፊያ ጎል ከመረብ ማሳረፍ ችላለች። የኢትዮ-ኤሌክትሪኳ ሃና ሲሳይ የጨዋታው ኮከብ በመሆን ተሸላሚ ሆናለች። ይህ በእንዲህ እንዳለ ትናንት ምሽት በድሬዳዋ ስቴዲየም በተከናወነው የኢትዮጵያ የወንዶች ፕሪሚየር ሊግ 8ኛ ሳምንት ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከመቻል ጋር አቻ ተለያይቷል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ናትናኤል ገ/ጊዮርጊስ በ57ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ጎል አንድ ለባዶ ሲመራ ቢቆይም በ92ኛው ደቂቃ በተሰጠበት የፍፁም ቅጣት ምት ነጥብ ሊጋራ ችሏል። ሁለቱ ክለቦች በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ አንደኛ እና ሶስተኛ ደረጃ የሚገኙ በመሆናቸው ጠንካራ ፉክክር የታየበት ጨዋታ ያሳዩ ሲሆን መቻሎች መሀል ሜዳውን ተቆጣጥረው በመጫወት ጫና ለማድረግ ሲሞክሩ በአንፃሩ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የመስመር ኳስ ለመጠቀም ጥረት አድርገዋል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ13 ነጥብ በሊጉ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በመጪው ህዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው 9ኛ ሳምንት የወንዶች ፕሪሚየር ሊግ መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከድሬዳዋ ከተማ ጋር ይጫወታል። ህዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው 6ኛ ሳምንት የሴቶች የጨዋታ መርሃግብር ደግሞ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚገጥም ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 17 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች የቦሌ ለሚ የኃይል ማከፋፈያ  ጣቢያን ጎበኙ …...///.....… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች የቦሌ ለሚ ባለ 230/33/15 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ የተካሔደው በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የተከናወነው የማስፋፊያ ግንባታ ሥራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ተከትሎ ነው። በጉብኝቱ ወቅት ለሥራ ኃላፊዎቹ ገለፃ ያደረጉት በማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሐንስ ተስፋዬ እንዳስታወቁት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአካባቢው በ15 ኪሎ ቮልት የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር መጨመር ለማስፋፊያ ግንባታው ዋና ምክንያት ነው። የማስፋፊያ ሥራው የተለያዩ የሲቪልና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታዎችን ጨምሮ አንድ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው ትራንፎርመር የማስቀመጥ፣ የኃይል መቆጣጠሪያ ቤት ግንባታ፣ የጂ.አይ.ኤስ ስዊች ጊር ገጠማና በ230 ኪሎ ቮልት በኩል የቤይ ዕቃዎችን የመትከል እንዲሁም የፍተሻና የሙከራ ሥራዎችን እንደሚያጠቃልል ነው በጉብኝቱ ወቅት የገለፁት። አንድ ዓመት ከስድስት ወር በወሰደው የማስፋፊያ  ሥራ ስድስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንደተገነቡ የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ይህም ለቦሌ አራብሳ፣ በሻሌና አካባቢው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችል ተናግረዋል። የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት በሪጅኑ አቅም በጣቢያው የተከናወነው የማስፋፊያ ሥራ እንደ ተቋም የመጀመሪያ ሊባል የሚችል ነው። በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በተከናወነው የማስፋፊያ ግንባታ አዳዲስ መሐንዲሶች እና የቴክኒክ ባለሙያዎች የልምድና የዕውቀት ሽግግር እንዲያገኙ በር የከፈተ ነውም ብለዋል። የማስፋፊያ ሥራው 15 ሚሊየን ብር ወጪ እንደተደረገበት የገለፁት አቶ አለማየሁ ግንባታው በሪጅኑ አቅም በመከናወኑ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ ማዳን መቻሉን ጠቅሰዋል። በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ በበኩላቸው የተከናወነው የማስፋፊያ ሥራ አዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከመገንባት ጋር እኩል ነው። በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የተከናወነው የማስፋፊያ ሥራ በአካባቢው ለረጅም ዓመታት ተገንብተው የኃይል አቅርቦት ሳያገኙ ለቆዩ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እፎይታን የሚሰጥ እንደሆነም ነው የገለፁት። በጣቢያው ዝግጁ የተደረጉት አዳዲስ ወጪ መስመሮች ለህብረተሰቡ ኃይል መስጠት እንዲችሉ ለማድረግ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የማሰራጫ መስመሮች ዝርጋታ መጀመሩንም ነው ያስታወቁት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

✅ የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ ነሀሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታ
+1
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ ነሀሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች መካከል ከተራ ቁጥር 1 እስከ 5 ያላችሁ በመንገድ ትራንስፖርት ህግና ደንብ በሚፈቅደው አግባብ መሰረት በተሰጠው የተግባር ፈተና የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ በመሆኑ ከህዳር 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃ የታደሰ መንጃ ፈቃድ እና የስራ ልምድ ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ ቀረበው የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም

በጣቢያው ጥገናዎችን በራስ አቅም የማከናወን ልምምድ እያደገ መጥቷል …....///…….... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በግልገል ጊቤ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ጥገናዎችን በራስ አቅም የማከናወን ልምምድ እያደገ መምጣቱን የጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ ገለጹ። ኃላፊው አቶ አሸናፊ ተስፉ እንደተናገሩት ከአሁን ቀደም በጣቢያው ከፍተኛ ውጪ ወጥቶባቸው በውጭ ሀገር ባለሙያዎች ብቻ ይከናወኑ የነበሩ የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም እየተከናወኑ ነው። ጣቢያው በሙሉ አቅሙ ኃይል እንዲያመነጭ የሚያስችሉ ከቅድመ መከላከል ጀምሮ የትንበያ እና የሁኔታ አመላካች የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም መከናወናቸውን ገልጸዋል። ለአብነትም የጣቢያው አራቱም ተርባይኖች ውሃን ለመቆጣጠር የሚያገለግለው ሹል ጫፍ ያለው የብረት አካል ወይም ኖዝሎች በመበላታቸው ምክንያት የአንድ ተርባይን የማመንጨት አቅም ከ105 ሜጋ ዋት ወደ 25 ሜጋ ዋት ቀንሶ እንደነበር ኃላፊው አስታውሰዋል፡፡ በኃይል ማመንጫ ጣቢያው ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ላይ የዋሉ የተርባይን ፓዎር ኖዝሎች በራስ አቅም የጥገና ሰራዎችን በማከናወን ተርባይኖቹ በሙሉ አቅማቸው 105 ሜጋ ዋት እንዲያመነጩ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። የተበሉ ካርበን ብረሾችን በአዲስ የመተካት፤ የስዊችያርድ፣ የመቆጣጠሪያ ክፍል እና የመሳሰሉት የሙቀት መጠን የመቆጣጠር እና የማቀዝቀዣ መሳሪያዎች እንዲሁም ሌሎች የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። ይህም ጣቢያው በሙሉ አቅሙ ኃይል እንዲያመርት ከማስቻሉም በላይ ጊዜንና ወጭን በመቀነስ በኩል ሚናው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። የጥገና ሥራው በራስ አቅም መከናወኑ ተቆሙ ያሉትን ባለሙያዎች አቅም ሙሉ በሙሉ እንዲጠቀም እድል የፈጠረ መሆኑን የጠቆሙት አቶ አሸናፊ ሠራተኞች ሙያዊ አቅማቸውን እንዲያሳድጉና ትልልቅ የጥገና ሥራዎችን መስራት እንችላለን የሚል የራስ መተማመን እንዲኖራቸው አስችሏል ብለዋል። የጣቢያው የጥገና ባለሙያ መልካም ባወቀ በበኩሏ በጣቢያው ከተቀጠረች ሁለት ዓመት ቢሆናትም በራስ አቅም በተከናወኑ የሁለት ተርባይኖች ኖዝል ሥራ ላይ መሳተፏን ገልጻለች። ይህም እሷ እና ሌሎች አዳዲስ የጥገና ባለሙያዎቹ ተግባር ተኮር ዕውቀት ያገኙበትና ትልልቅ የጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም መስራት እንደሚቻል ትምህርት የወሰዱበት መሆኑን ተናግራለች። በጣቢያው የኦፕሬሽን ክፍል ኃላፊ አቶ ሽመልስ አዱኛ እንደገለጸው በጣቢያው በራስ አቅም የተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የኦፕሬሽን ሥራውን በማሳለጥ በኩል ጉልህ ሚና ተጫውተዋል። ቀደም ሲል በተርባይኖቹ ላይ ባጋጠመ ችግር ምክንያት የኦፕሬሽን ሥራዎችን ከአንድ ማዕከል ለመቆጣጠር አስቸጋሪ አድርጎት መቆየቱን ጠቁመዋል። በዚህም የኦፕሬሽን ባለሙያዎች በማንዋል ቁጥጥር ለማድረግ አስገድዷቸው እንደነበር አስታውሰዋል። በተርባይኖቹና በጣቢያው ማሽኖች ላይ በራስ አቅም የተከናወነው የጥገና ሥራ ጣቢያው በሙሉ አቅሙ ኃይል እንዲያመነጭ ከማድረጉም ባሻገር የኦፕሬሽን ሥራውን ከአንድ ማዕከል መቆጣጠር አስችሏል ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ግንባታ ወጪን ተቋሙ በራሱ ገቢ እየሸፈነ ነው ……...///…..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ከፕሮጀክቶች አፈፃፀም ጋር ተያይዞ የሚታዩበትን ውሱንነቶች ለመፍታት የሚያደርገውን ጥረት እንደሚያግዝ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር አስታወቀ፡፡ አስተዳደሩ የተቋሙን የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ከኃይል ሽያጭ፣ ከተቋማዊ የሪፎርም ሥራዎች፣ ከታሪፍ ማሻሻያ፣ ከፕሮጀክቶች አፈፃፀምና ከፋይናንስ እንዲሁም ከሥርዓተ ፆታ ስብጥር አንፃር ገምግሟል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት የተቋሙን ስምና አርማ ለመቀየር እና የካፒታል መጠኑን ለማሳደግ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ያለውን የሥራ ግንኙነት ለማሻሻል የሚያስችሉ ደንቦች ተዘጋጅተው ወደሚመለከታቸው አካላት ተልኳል። መንግሥት የተቋሙን የሀገር ውስጥ ዕዳ በከፊል መሰረዙን እና ቀሪ 1 ነጥብ 6 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ብድር ዕዳን ለመክፈል የሚያስችል ታሪፍ እንዲኖር እየተሰራ በመሆኑ የገንዘብ ሚኒስቴር እና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር አስፈላጊውን እገዛ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታን ባለበት ፍጥነት ለማስቀጠል ከኃይል ሽያጭ ገቢ ላይ በየወሩ 5 ሚሊየን ዮሮ እየተከፈለ ይገኛል። በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ ለታንዛኒያ ሊቀርብ የታሰበው የኃይል ሽያጭ በታቀደው ጊዜ ባለመጀመሩ የውጭ የኃይል ሽያጭ አፈፃፀም ቀንሷል። በኬንያ እና ታንዛኒያ መካከል ያለው ሥምምነት በቅርቡ እልባት ስለሚያገኝ የኃይል ማስተላለፊያ ኮሪደሩ እስከ ደቡብ አፍሪካ ድረስ ኤሌክትሪክ ለማስተላለፍ አመቺ እንደሆነም ነው የገለፁት። በተቋሙ የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ውድነህ የማነ በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ የፕሮጀክቶችን የግንባታ አፈፃፀም ለማሻሻል ታቅዶ እየተሰራ ቢሆንም ከፀጥታና መሰል ችግሮች ጋር በተያያዘ ተግዳሮቶች ማጋጠማቸውን ጠቅሰዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ከመሰረተ ልማት ስርቆትና ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እገዛ ማድረግ አለባቸው። በተቋሙ የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንዳሉት ደግሞ ተቋሙ ከኃይል ሽያጭ ገቢ በርካታ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን እየገነባ ይገኛል። ተቋሙ አጠቃላይ ሀብቱ 719 ቢሊየን ብር እንዲደርስ መንግሥት፣ ገንዘብ ሚኒስቴር፣ የሥራ አመራር ቦርዱ እና አስተዳደሩ ያደረጉት ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ለተደረገው እገዛም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በተቋሙ የንብረት አስተዳደር ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው በበኩላቸው በ2016 በጀት ዓመት የሸገር ከተማ አስተዳደር በውስጡ ለሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ዓመታዊ የይዞታ ግብር የጠየቀው ከፍተኛ የገንዘብ መጠን እልባት እንዲያገኝ ጉዳዩ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት መድረሱን ተናግረዋል። በተቋሙ የሰው ኃይል አስተዳደር ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው በተቋሙ ከሥርዓተ ፆታ ስብጥር እና የማሰልጠኛ ማዕከላትን ከማስፋፋት ጋር በተያያዘ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ ነው። በግምገማው ላይ የማጠቃለያ ሃሳብ የሰጡት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ተወካይ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ ይርጋ እንደገለፁት በየሩብ ዓመቱ የሚደረገው ግምገማ የተቋሙን ውጤታማነት ለማሻሻል ያግዛል። ተቋሙ በ2017 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከኃይል ሽያጭ ያልተሰበሰቡ ገቢዎችን በመሰብሰብና አማራጭ የገቢ ማግኛ አማራጮችን በማስፋት አቅሙን ማጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል። ከፕሮጀክቶች አፈፃፀም ጋር ተያይዘው የሚነሱ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት አስተዳደሩ ድጋፍ እንደሚያደርግም ነው ማረጋገጫ የሰጡት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1