uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 528 підписників, посідаючи 8 328 місце в категорії Технології та додатки та 2 176 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 528 підписників.

За останніми даними від 06 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 6, а за останні 24 години на -3, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 27.84%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 16.05% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 4 323 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 492 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 10.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 07 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 528
Підписники
-324 години
-97 днів
+630 день
Архів дописів
የአዋሽ III የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በከፊል አገልግሎት መስጠት ጀመረ …………./////……….. በአዋሽ ወንዝ ሙላት ሳቢያ በጎርፍ ተጥለቅልቆ አገልግሎት አቋርጦ የነበረው የአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በከፊል አገልግሎት መስጠት ጀመረ። ላለፉት 49 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውና 32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በውሃ መጥለቅለቅ አደጋ ምክንያት ከነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ አገልግሎት መስጠት አቁሞ ነበር፡፡ በወቅቱ ከተርባይን ወለል እስከ ተርባይን ሮተር ማገናኛ ዘንግ (Turbine Rotor Coupling Shaft) ድረስ ያሉት የኤሌክትሮ-መካኒካል እቃዎች በውሃ ተውጠው እንደነበር መዘገባችን ይታወሳል። ለሁለት ወራት አካባቢ አገልግሎት አቋርጦ የነበረው ጣቢያ አንድ ዩኒት ወደስራ ማስገባት በመቻሉ ጣቢያው በከፊል ስራ የጀመረ ሲሆን ቀሪውን አንድ ዩኒት ስራ ለማስጀመር በሂደት ላይ ይገኛል። ጥቅምት 17 ቀን 2013 ዓ/ም

ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ………………….////……………….. የሠመራ አፍዴራ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ፕሮጀክትን የሲቪል እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎችን ግንባታ በማጠናቀቅ
+2
ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ………………….////……………….. የሠመራ አፍዴራ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ፕሮጀክትን የሲቪል እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎችን ግንባታ በማጠናቀቅ የሙከራና ፍተሻ ሥራ ለመስራት መታቀዱን የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስታወቀ፡፡ የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጁ አቶ ኢዮሲያስ ኃይለማርያም እንደተናገሩት በፕሮጀክቱ የማከፋፈያ ጣቢያ የትራንስፎርመር ማስቀመጫ ቤት፣ የኃይል መቆጣጠሪያ ክፍል፣ የመኖሪያ እና የቢሮ ግንባታዎች በመከናወን ላይ ነው፡፡ የግንባታ ስራው ህዳር 2011 ፕሮጀክቱ ለአፍዴራ እና አካባቢው ነዋሪዎች ብሎም ለጨው ማምረቻና የአዮዲን ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ አልሞ የተገነባ ነው፡፡ በአፍዴራ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክት 40 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው አንድ የኃይል ትራንስፎርመር እንደሚገጠምለት ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በረሃማ በሆነ አካባቢ የሚገኝ ቢሆንም ተቋራጩ ጥልቅ ቁፋሮ በማካሔድ ለግንባታ እና ለመጠጥ የሚያገለግል ውሃ ማቅረቡንና ይህም ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ሥራ ሲጀምር ለጣቢያው የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እገዛ ያደርጋል ብለዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የሠመራ አፍዴራ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ፕሮጀክት አካል የሆነውና 195 ኪ.ሜ የሚረዝመው የሠመራ-አፍዴራ ባለ 230 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታም በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/ ጥቅምት 16 ቀን 2013 ዓ.ም.

የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ ………….///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ሴቶችን ተሳትፎና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት በቅንጅት መስ
+2
የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ ………….///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ሴቶችን ተሳትፎና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ የተቋሙ የሴቶች፣ ወጣቶችና ህፃናት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኤዲኤ ገለፁ፡፡ በተቋሙ በሚከናወኑ ፕሮጀክቶች፣ በኦፕሬሽንና በሁሉም የስራ መስኮች ከጥናት ጀምሮ እስከ ትግበራ ድረስ ባለው ሰንሰለት ሴቶችን ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎች በስፋት መከናወን እንዳለባቸው በስርዓተ ፆታና ስርፀት ላይ ትኩረት ባደረገው የአምስት ቀናት ስልጠና መዝጊያ ላይ ገልፀዋል፡፡ ወ/ሮ ሌንሴ እንዳሉት ከህብረተሠቡ 50 በመቶ የሚሆኑትን ሴቶች ያገለለ ልማት ትርጉም ሊኖረው አይችልም፡፡ በመሆኑም ውጤታማ ስራ ለማከናወን ከተፈለገ ሴቶችን በየደረጃው ተሳታፊ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ለአምስት ቀናት በቆየው ስልጠና የስርዓተ ፆታ ምንነትና የተዛቡ አመለካከቶች፣ የስርዓተ ፆታ ትንተና፣ የስርዓተ ፆታ ዓለማቀፋዊና ሀገራዊ ነባራዊ እንዲሁም የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስፈልጉ ስትራቲጂካዊ ሥራዎች ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጧል፡፡ ስልጠናው የተሰጠው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተውጣጡ 25 ባለሙያዎች ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ካሉት አጠቃላይ ሠራተኞች ብዛት 15 በመቶዎች ሴቶች መሆናቸውን የተቋሙ የሰው ሀብት መረጃ ያመላክታል፡፡ ጥቅምት 16 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

በዋና ሥራ አስፈፃሚው የተመራ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ አመራር ቡድን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ጎበኘ ................./////............... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥ
+5
በዋና ሥራ አስፈፃሚው የተመራ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ አመራር ቡድን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ጎበኘ ................./////............... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ የተመራ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ አመራር ቡድን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ጎብኝቷል። የግድቡ ግንባታ አሁን የደረሰበትን ደረጃ፣ ቀሪ ግንባታውን ለማፋጠንና ለሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት እየተሰሩ ያሉት ወሳኝ ስራዎችን በተመለከተ በግድቡ ግንባታ ምክትል ስራ አስኪያጅ ኢ/ ር ኤፍሬም ገ/ኪዳን ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል። የዋናውን ግድብ ፣ የኮርቻ ቅርፅ ግድቡን የኃይልማመንጫ ቤቱንና ውሃው በግድቡ ላይ የሚፈስበትን ስፍራ ቡድኑ ተዘዋውሮ ጎብኝቷል። የስራ አመራር ቡድኑ ጉብኝት ዋና ዓላማ በመጀመሪያ ዙር የውሃ መሊት የተመዘገበውን ስኬት በስፍራው በመገኘት ለመመልከትና የፕሮጀክት አስተዳደሩን ለማገዝ ነው። ይህን መሰል ጉብኝት መዘጋጀቱ የሥራ አመራሩ ፕሮጀክቶችን በቅርበት በመመልከት አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ለመስጠት እንደሚያግዘው ታምኖበታል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስራ አመራር ቡድን የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን በጋራ ሲጎበኝ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው። የግድቡ አጠቃላይ ግንባታ በአሁኑ ወቅት 76 ነጥብ 3 በመቶ ደርሷል። በተያያዘ ዜና የስራ አመራር ቡድኑ በገበታ ለሀገር ፕሮጀክት የተካተተውንና በኮይሻ በመገንባት ላይ የሚገኘውን የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትንም ጎብኝቷል። ጥቅምት 15 ቀን 2013 ዓ/ም

የሕዳሴው ግድብ የኢትዮጵያ ግድብ ነው። ኢትዮጵያውያን፣ አሰቡት፤ ኢትዮጵያውያን ጀመሩት፤ ኢትዮጵያውያን ገነቡት፤ ስለዚህ ኢትዮጵያውያን ይጨርሱታል። አይቀሬ ነው። ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የተሰ
የሕዳሴው ግድብ የኢትዮጵያ ግድብ ነው። ኢትዮጵያውያን፣ አሰቡት፤ ኢትዮጵያውያን ጀመሩት፤ ኢትዮጵያውያን ገነቡት፤ ስለዚህ ኢትዮጵያውያን ይጨርሱታል። አይቀሬ ነው። ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ ! ጥቅምት 14 2013 አዲስ አበባ ኢትዮጵያ በፍጣሪዋ ታምና በሕዝቧ አንድነትና ጽናት የቆመች ሀገር ናት። ጥቂት ሰጥተው ብዙ ሊያዟት በሚሞክሩ ተማምና አታውቅም። ሕይወታቸውን ሰጥተው ሊታዘዟት በተዘጋጁ ልጆቿ እንጂ። ኢትዮጵያን የፈጠራት አምላኳ ነው። የገነቧት ደግሞ ልጆቿ ናቸው። እነዚህ ልጆቿ በከፈሉት መሥዋዕትነት ዓለምን ጉድ ያሰኙ ታሪኮችን ሠርታለች። እነዚህ አስደናቂ ታሪኮችን ስትሠራ አብረዋት ታሪክ የሠሩ ወዳጆች ነበሯት። የከዷት ወዳጆችም ነበሩ። ይህ ለኢትዮጵያ አዲስ አይደለም። ነገር ግን የዓለም ታሪክ ያረጋገጣቸው ሁለት ሐቆች አሉ። ኢትዮጵያን ነክቶ በሰላም የኖረ የለም የሚለው ቀዳሚው ነው። ኢትዮጵያውያን በአንድነት ለአንድ ዓላማ ከቆሙ ድል ማድረጋቸው አይቀርም የሚለው ደግሞ ሁለተኛው። የሕዳሴው ግድብ የኢትዮጵያ ግድብ ነው። ኢትዮጵያውያን፣ አሰቡት፤ ኢትዮጵያውያን ጀመሩት፤ ኢትዮጵያውያን ገነቡት፤ ስለዚህ ኢትዮጵያውያን ይጨርሱታል። አይቀሬ ነው።

በመላው ሀገሪቱ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ መደበኛ አገልግሎት ተመልሷል ****************** በመላው ሀገሪቱ ከረፋዱ 5 ሰአት ጀምሮ ለተወሰኑ ሰዓታት ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ ወደ መደበኛ አገልግሎት ተመልሷል። የኃይል ማመንጫዎችን ከብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር መልሶ የማገናኘት ሥራው በስኬት በመጠናቀቁ ደረጃ በደረጃ ሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ ተደርጓል። ለሰዓታት ኃይል በመቋረጡ የተቸገራችሁትን በሙሉ ላሳያችሁት ትዕግስት እያመሰገንን የገጠመንን ችግር ለመቅረፍ ሙያዊ ኃላፊነታችሁን በትጋት ለተወጣችሁ የተቋማችን ባልደረቦች በሙሉ ላሳያችሁት ርብርብ ምስጋናችንን እናቀርባለን። ጥቅምት 13 ቀን 2013 ዓ/ም

በኢትዮጵያ በአብዛኛው አካባቢ የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ተከስቷል ……………/////……………… ከጣና በለስ ወደ ባህርዳር በሚሄደው የ400 ኪሎ ቮልት የኃይል መስመር ላይ ባጋጠመ የቴክኒክ ችግር ምክን
በኢትዮጵያ በአብዛኛው አካባቢ የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ተከስቷል ……………/////……………… ከጣና በለስ ወደ ባህርዳር በሚሄደው የ400 ኪሎ ቮልት የኃይል መስመር ላይ ባጋጠመ የቴክኒክ ችግር ምክንያት ዛሬ በኢትዮጵያ በአብዛኛው አካባቢ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጣል፡፡ በመስመሩ ላይ የተከሰተው የቮልቴጅ መዋዠቅ በአጠቃላይ የአገሪቱ የኃይል አቅርቦት ላይ ችግር እንዲፈጠር አድርጓል፡፡ በዚህም ምክንያት በዛሬው ዕለት ከረፋዱ 5 ሰአት ጀምሮ የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ተከስቷል። ችግሩን በአፋጣኝ ለመቅረፍ በተሰሩ ስራዎች ከጊቤ 3 ኃይል ማመንጫ በስተቀር አብዛኛዎቹን የኃይል መመንጫዎች ከብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር ማገናኘት ተችሏል፡፡ የአዲስ አበባ አብዛኛው አካባቢ እንዲሁም ባህርዳርና አካባቢዋ ኃይል ማግኘት የጀመሩ ሲሆን ሁሉንም የሀገሪቱን አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ ጥቅምት 13 ቀን 2013

ወቅታዊ እና ጤናማ የሂሳብ ሪፖርት ለማቅረብ እየተሰራ ነው ……………..///…………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ዓመታዊ የኦዲት ሪፖርት ጤናማ እንዲሆን ለማድረግ እና ወቅታዊ የሂሳብ ሪፖርት ለኦዲት
ወቅታዊ እና ጤናማ የሂሳብ ሪፖርት ለማቅረብ እየተሰራ ነው ……………..///…………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ዓመታዊ የኦዲት ሪፖርት ጤናማ እንዲሆን ለማድረግ እና ወቅታዊ የሂሳብ ሪፖርት ለኦዲት አገልግሎት ቦርድ ለማቅረብ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የተቋሙ የፋይናንስ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው አቶ ደመረ አሰፋ እንደገለፁት የተቋሙን የ2012 በጀት ዓመት የሂሳብ ሪፖርትን ለኦዲት አገልግሎት ቦርድ በወቅቱ ለማቅረብ እና ሪፖርቱ ጤናማ እንዲሆን ለማድረግ እየሰራ ነው፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት የሚመረመረውን የተቋሙን የ2012 በጀት ዓመት ሂሳብ ሪፖርት ለኦዲት አገልግሎቱ በወቅቱ ለማቅረብ የሂሳብ መዝጋት ስራ መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ የተቋሙ የኦዲት ሪፖርት ከ2009 በጀት ዓመት ጀምሮ ቀደም ሲል ከነበረበት የትችት አስተያየት (disclaimer) ነፃ መሆኑን ሥራ አስፈፃሚው አስታውሰዋል፡፡ የ2012 በጀት ዓመት ሂሳብን ለኦዲት አገልግሎት በወቅቱ በማቅረብ በ2009 የተሰጠውን የኦዲት አስተያየት ለማስቀጠልና የኦዲት ሪፖርቱ ጤናማ እንዲሆን ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶት በመሰራት ላይ እንደሚገኝም አስታውቀዋል፡፡ የተቋሙን ሂሳብ እንደ ሀገር በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በዓለም አቀፋዊ የፋይናንስ ሪፖርት ስርዓት (IFRS) እንዲሆን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ደመረ በአሁኑ ወቅትም የተቋሙ ቋሚ ንብረት ቆጠራና የዋጋ ክለሳ ስራ በረቂቅ ደረጃ ተጠናቋል ብለዋል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/ ጥቅምት 12 ቀን 2013 ዓ.ም.

የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በሶስት ዓመት ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ ነው - የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ******************* የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በሶስት ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ስለሺ በቀለ(ዶ/ር፣ ኢ/ር ) ገለፁ። 2 ሺህ 160 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ግድብ በኢትዮጵያ ከሕዳሴ ግድብ ቀጥሎ ሁለተኛው ግዙፍ ፕሮጀክት ነው። የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ስለሺ በቀለ(ዶ/ር፣ኢ/ር ) የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በሶስት ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ግድቡ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኘውን የጊቤ ሶስት ውሃ የሚጠቀም በመሆኑ 6 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሊትር ውሃ ብቻ እንዲይዝ ተደርጎ እንደሚገነባም ሚኒስትሩ ተናግረዋል፤ይህም ግድቡን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ዕድል ይሰጣል ብለዋል። ግድቡ “በገበታ ለሀገር” የኮይሻ ፕሮጀክት መካተቱን ጠቅሰው፤ የግድቡ በፍጥነት መጠናቀቅ አካባቢውን የቱሪስት መዳረሻ በማድረግ ረገድ ሚናው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። የፕሮጀክቱ የኮንትራት ስራዎች ተቆጣጣሪ አቶ ኢዩኤል ሰለሞንም በእስካሁን ሂደት የውሃውን ተፈጥሯዊ አቅጣጫ ማስቀየርን ጨምሮ መሰረታዊ የቁፋሮ ስራዎች እና የማስተንፈሻ ግንባታ ቁፋሮው ከግማሽ በላይ መጠናቀቁንም ገልጸዋል። ለአራት ሺህ ዜጎች የስራ ዕድል የፈጠረው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ የግንባታ ስምምነቱ የተፈረመው በመጋቢት 2008 ዓ.ም ነው። የፕሮጀክቱ የግንባታ አፈፃፀም 39 በመቶ መድረሱን ኢዜአን ጠቅሶ ኢቢሲ ዘግቧል።

ተቋሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ለማዕከሉ እገዛ ማድረግ እንዳለበት ያምናል ……………////…………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ከመቄዶንያ የአረጋውያንና የአ
ተቋሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ለማዕከሉ እገዛ ማድረግ እንዳለበት ያምናል ……………////…………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ከመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መረጃ ማዕከል መሥራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢኒያም በለጠ ጋር ተወያዩ፡፡ የማዕከሉ ሥራ አሰስኪያጅ አቶ ቢኒያም በለጠ ማዕከሉ አረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማንን ከጎዳና ላይ በማንሳት እየሰጠ ስላለው አገልግሎት ለዋና ስራ አስፈፃሚው ገለፃ አድርገውላቸዋል፡፡ ከ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ የሆነ ወጪ ማዕከሉ ያስጀመረውን ዘመናዊ ሆስፒታልና የአረጋውያን መኖሪያ ህንፃ ስለደረሰበት ደረጃም ገልፀውላቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንደተቋም ለህንፃው ግንባታ የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ አቶ ቢኒያም ጠይቀዋል፡፡ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ማዕከሉ አረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማንን ከጎዳና በማንሳት እያከናወነ ያለው ተግባር ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው መሆኑን አንስተዋል፡፡ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ለማዕከሉ እንቅስቃሴ ፈተና ቢሆንም ያለምንም የውጭ እርዳታ አገልግሎቱ ሳይስተጓጎል መቀጠሉ የሚበረታታ እንደሆነ አንስተዋል፡፡ ተቋሙም ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ለማዕከሉ እገዛ ማድረግ እንዳለበት ያምናል ብለዋል፡፡ በመሆኑም ማዕከሉ በምን ዓይነት መንገድ ቢታገዝ የተሻለ ይሆናል የሚለውን በመለየት ድጋፍ ለማድረግ ተቋሙ አማራጮችን እንደሚያጠና አቶ አሸብር ተናግረዋል፡፡ መቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በአዲስ አበባ ብቻ እስከ 4000 ሰዎችን ከጎዳና አንስቶ ድጋፍ በማድረግ ላይ የሚገኝ ሀገር በቀል የበጎ አድራጎት ማህበር ነው፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/

የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በዓመት በአማካይ 436 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ያስገኛል …………///……….. በኢትዮጵያ ከአዳማ I እና II እንዲሁም ከአሸጎዳ በመቀጠል በአራተኛነት እየተገነ
የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በዓመት በአማካይ 436 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ያስገኛል …………///……….. በኢትዮጵያ ከአዳማ I እና II እንዲሁም ከአሸጎዳ በመቀጠል በአራተኛነት እየተገነባ ያለው የአይሻ II የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ ሲጠናቀቅ በዓመት በአማካይ 436 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ይኖረዋል፡፡ ዶንግ ፋንግ ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን (DEC) በተባለ የቻይና ኩባንያ በመገንባት ላይ ያለው ፕሮጀክቱ 48 የንፋስ ተርባይኖች ያሉት ሲሆን እያንዳንዳቸው 2.5 ሜጋ ዋት በድምሩ 120 ሜጋ ዋት ወይም በዓመት በአማካይ 436 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ይኖረዋል፡፡ በፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ክላስተር የስምንት ተርባይኖችና ትራንስፎርመሮች ተከላ ሥራ ተጠናቆ ለፍተሻና ሙከራ ሥራ ዝግጁ ሆኗል፤ ስምንቱን ተርባይኖች በኢትዮ ጅቡቲ መስመር አማካኝነት ከብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር አገናኝቶ የሙከራ ሥራ ለማስጀመር ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛል፡፡ በሁለተኛው ክላስተር የሚገኙ ስምንት ተርባይኖች እንዲሁም በሶስተኛው ክላስተር የሚገኙ ሶስት ተርባይኖች ተከላም ተጠናቋል፡፡ የፕሮጀክቱ የሲቪልና ኤሌክትሮ መካኒካል ግንባታ እየተፋጠነ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻፀም 64 በመቶ ደርሷል፡፡ የአይሻ II የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከአዲስ አበባ በ700 ኪሎ ሜትር፣ ከድሬዳዋ ከተማ በሰሜን ምስራቅ 170 ኪሎ ሜትር እንዲሁም ከጅቡቲ በሰሜን ምዕራብ 150 ኪሎ ሜትር መካከል በሶማሌ ክልል አይሻ ደወሌ ወረዳ ይገኛል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/ ጥቅምት 11 ቀን 2013 ዓ.ም.

ፕሮጀክቱን ዘንድሮ ከ90 በመቶ በላይ ለማድረስ እየተሰራ ነው፡፡ …………..////………… የባህርዳር - ወልዲያ - ኮምቦልቻ ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢ
+3
ፕሮጀክቱን ዘንድሮ ከ90 በመቶ በላይ ለማድረስ እየተሰራ ነው፡፡ …………..////………… የባህርዳር - ወልዲያ - ኮምቦልቻ ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታን በተያዘው በጀት ዓመት ከ90 በመቶ በላይ ለማድረስ እየተሰራ ነው፡፡ በፕሮጀክቱ እንደሚተከሉ ከሚጠበቁት 829 ምሰሶዎች ውስጥ በአሁኑ ሰዓት 746 ምሰሶ ለመትከል የሚያስችል የመሰረት ቁፋሮ ተጠናቋል፡፡ ከዚህ ውስጥ ደግሞ 115 ምሰሶዎች ተከላ የተከናወነ ሲሆን ቀሪ ምሰሶዎችን የመትከል እና ገመድ የመዘርጋት ሥራዎችንም በ2013 በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ ነው፡፡ ለፕሮጀክቱ መስመር ዝርጋታ የሚሆኑ አብዛኛዎቹ የምሰሶ መትከያ ብረቶችና ገመዶች የፕሮጀክቱ ዕቃ ግምጃ ቤት ገብተዋል፡፡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታውን የቻይናው ሻንጋይ ኤሌክትሪክ ኮርፖሬሽን በማከናወን ላይ ሲሆን የማስተላለፊያ መስመሩ ግንባታ ደግሞ የህንዱ ታታ ፕሮጀክትስ ሊሚትድ (TATA PROJECTS LTD) እያከናወነው ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱን በማማከር ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢነጂነሪንግ ቢሮ ነው፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/ ጥቅምት 10 ቀን 2013 ዓ.ም.

ግድቡ አሁን ከያዘው በ3 እጥፍ የሚበልጥ ውሃ እንዲይዝ ይደረጋል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ********* ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ በዘንድሮው ዓመት አሁን ከያዘው በ3 እጥፍ የሚበልጥ ውሃ እንደሚይዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በጋራ የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጉብኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው የግድቡ ግንባታ ሂደት በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ መመልከታቸውንም ገልፀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሕዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ለተሳተፉ እና አሁን ያለበት ደረጃ እንዲደርስ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አሁን ያለበት ደረጃ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ኩራት መሆኑን ተናግረዋል። እስካሁን የተሠራው ሥራ ትልቅ ስኬት ቢሆንም በስኬቶች ከመኩራራት በየጊዜው አዳዲስ ግቦችን በመቅረፅ ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና ለመውሰድ እንደሚሠራም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ገልፀዋል። በዚህ ዓመት ግድቡ ከፍ እንዲል ማድረግ እና አሁን ካለው ውሃ ሦስት እጥፍ እንዲይዝ ለማድረግ የሚሠራ በመሆኑ ይህ ዓመት የግድቡ ዋነኛ ሥራ የሚሠራበት ነው ብለዋል። በተያያዘም በዚህ ዓመት ኃይል ማመንጨት የሚጀምሩ ተርባይኖች ዝግጁ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ተርባይኖቹ ለስድስት ወራት ሙከራ ካደረጉ በኋላ ሙሉ ለሙሉ ኃይል ወደ ማመንጨት ይገባሉ ነው ያሉት። የግድቡን የግንባታ ሂደት የጎበኙበት ምክንያት የሥራውን እንቅስቃሴ ለማየት እና ወደ ፊት በግድቡ አካባቢ ለመሠራት ለታቀዱት ከተሞች የአመቺነት ሁኔታን ለማየት እንደሆነ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት። ግድቡ ሲሞላ ብዙ ደሴቶችን ስለሚፈጥር ከወዲሁ ያንን እያዩ መዘጋጀት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። የግድቡ ሁኔታ ኢትዮጵያ ወደ ብልጽግና የምታደርገውን ጉዞ ውጤታማ እንደሚሆን ለሁሉም ወገን የሚያመላክት ነው ያሉት ዶ/ር ዐቢይ፣ "በየጊዜው ያንን እያረጋገጥን ስኬታችንን እውን ማድረጋችን አይቀርም" ማለታቸውን ኢቢሲ ዘግቧል። ጥቅምት 3 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content
+1

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ የታላቁ ህዳሴ ግድብን ጎበኙ ******** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ በጋራ እያደረጉት ባለው ሁለተኛ ቀን ጉብኝታቸው የታላቁ ህዳሴ ግድብን ለመጎብኘት ጉባ ገብተዋል፡፡ የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያው የውሃ ሙሌት ባለፈው ሐምሌ ከተከናወነ በኃላ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስፍራው ሲያቀኑ የአሁኑ የመጀመሪያቸው ነው ፡፡ ሁለቱ መሪዎች በቆይታቸው የታላቁ ህዳሴ ግድብ አሁን ያለውን ገፅታ ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ፣ ገለፃም ተደርጎላቸዋል፡፡ መሪዎቹ ዛሬ ጠዋት የኮይሻ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብን ጎብኝተው እንደነበር ኢቢሲዘግቧል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጎበኙ ..........................///......................
+2
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጎበኙ ..........................///............................ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብን ጎብኝተዋል። ግድቡ በአንድ ጊዜ 2,160 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው ሲሆን በዓመት ደግሞ በአማካይ 6 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ያመነጫል። የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት አጠቃላይ አፈፃፀም በአሁኑ ወቅት 36 በመቶ የደረሰ ሲሆን ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ ከኃይል ማመንጫነት ባሻገር ለቱሪዝም መዳረሻ እንደሚሆንም ይጠበቃል። በግንባታ ላይ የሚገኘውን የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአንድ ወር በፊት መጎብኘታቸው የሚታወስ ነው። ምንጭ: ኢቢሲ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ግድብን ጎበኙ …………////…….. ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ግድ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ግድብን ጎበኙ …………////…….. ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ግድብን ጎበኙ፡፡ በስፍራው እየተሰራ ያለውን እና የ"ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክት አካል የሆነውን ሰው ሰራሽ ሐይቅ የግንባታ ሂደት መመልከታቸውን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡ ጥቅምት 2 ቀን 2013 ዓ.ም.

በተቋሙ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል ተከበረ -----------------------//////----------------------- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓልን በዋናው መ/ቤት
+4
በተቋሙ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል ተከበረ -----------------------//////----------------------- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓልን በዋናው መ/ቤት አክብሯል፡፡ በዓሉ የኮቪድ 19 ስርጭትን ለመከላከል በወጣው ፕሮቶኮል መሠረት በጥቂት ሰዎች ሰንደቅ ዓላማውን በክብረ በመስቀል እንዲከበር ተደርጓል፡፡ የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል ዘንድሮ ለ13ኛ ጊዜ የሚከበር ሲሆን “ሰንደቅ ዓላማችን ለሠላማችን፣ ለአብሮነታችንና ለሀገራዊ ብልፅግናችን” በሚል መሪ ቃል ከዛሬ ጀምሮ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ ክልሎችና ተቋማት ከራሳቸው ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማጣጣም በዓሉን እንዲያከብሩ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በሰጠው አቅጣጫ መሠረት በተቋማችንም እንዲከበር ተደርጓል፡፡ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል በየዓመቱ የጥቅምት ወር መጀመሪያ ሰኞ እንዲከበር መወሰኑ ይታወሳል፡፡ ጥቅምት 2 ቀን 2013 ዓ.ም.

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈፃፀም 76.35 በመቶ ደረሰ *********** የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈፃፀም 76 ነጥብ 35 በመቶ መድረሱን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒ
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈፃፀም 76.35 በመቶ ደረሰ *********** የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈፃፀም 76 ነጥብ 35 በመቶ መድረሱን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን፣ በመስኖ ልማት፣ በኢነርጂ እንዲሁም በተፋሰስና የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ዙሪያ የ2013 የሩብ ዓመት የስራ ዕቅድ አፈፃፀምን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ በተያዘው 2013 ዓ.ም ሁለቱ ተርባይኖች ኃይል እንዲያመነጩ ለማስቻል በሩብ ዓመቱ የግንባታውን አፈፃፀም በ1 ነጥብ 6 በመቶ ለማሳደግ ታቅዶ በ2 ነጥብ 05 በመቶ ለማሳደግ መቻሉን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚንስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ ገልፀዋል፡፡ በዚህም በሩብ ዓመቱ የግንባታውን አፈፃፀም ከታቀደው በላይ ለማከናወን መቻሉን ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በመስኖ ግድቦች ከፍተኛ መጠን ያለው ውሃ በመያዙ የተያዘውን ውሃ ወደ ልማት ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን ዶ/ር ስለሺ ገልፀዋል፡፡ በንፁህ መጠጥ ውሃ እና በኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ዙሪያም በሩብ ዓመቱ አበረታች ሥራ መሰራቱን ሚንስትሩ ጨምረው ገልፀዋል፡፡ የታላቁ ህዳሴ ግድብ የአየር ክልል ከበረራ ነፃ እንዲሆን የተደረገው ያለውን የደህንነት ስጋት ለማስቀረት ነው ብለዋል፡፡ በዕቅዱ መሰረት በተያዘው ዓመት የግድቡ ሁለት ተርባይኖች ኃይል እንዲያመነጩ እንደሚደረግም አረጋግጠዋል፡፡ # ኢቢሲ