cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

መጋቢ ሽመልስ መሰለ [ PASTOR Shimeles ]

Рекламні дописи
201
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

መልእክት ለቤተክርስቲያናችን አባላት ብቻ በመዘምራን ህብረት አገልግሎት እና በፀሎት አገልግሎት ለማገልገል እፈልጋለሁ ሸክሙ አለኝ የምትሉ እህቶች እና ወንድሞች ለአምልኮ ወደ ቤተክርስቲያን ስትመጡ አገልጋዮችን በማግኘት እንድታናግሩ ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች :: ለበረከት ሁኑ !!
Показати все...
ጥቅምት 14/2016 እሮብ የፈውስና አርነት ፕሮግራም የተሰበከው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ርዕስ :-- አታቋርጡ ሉቃስ 1 ¯¯¯¯¯¯ ¹-⁴ የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ። ⁵ በይሁዳ ንጉሥ በሄሮድስ ዘመን ከአብያ ክፍል የሆነ ዘካርያስ የሚባል አንድ ካህን ነበረ፤ ሚስቱም ከአሮን ልጆች ነበረች፥ ስምዋም ኤልሳቤጥ ነበረ። ⁶ ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ። ⁷ ኤልሳቤጥም መካን ነበረችና ልጅ አልነበራቸውም፤ ሁለቱም በዕድሜያቸው አርጅተው ነበር። ⁸ እርሱም በክፍሉ ተራ በእግዚአብሔር ፊት ሲያገለግል፥ ⁹ እንደ ካህናት ሥርዓት ወደ ጌታ ቤተ መቅደስ ገብቶ ለማጠን ዕጣ ደረሰበት። ¹⁰ በዕጣንም ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ በውጭ ቆመው ይጸልዩ ነበር። ¹¹ የጌታም መልአክ በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ታየው። ¹² ዘካርያስም ባየው ጊዜ ደነገጠ፥ ፍርሃትም ወደቀበት። ¹³ መልአኩም እንዲህ አለው፦ ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ። ¹⁴ ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።
Показати все...
መስከረም 6/2016 ዓም እሁድ አምልኮ ጉባኤ ✅✅✅✅✅✅✅✅✅ የጌታ እራትን የወሰድንበት ልዩ ፕሮግራም እግዚአብሔር በምህረቱና በፀጋው እረድቶናል ። በፀሎት //አምልኮ በመምራት/// በቃል ስብከት/// ዲያቆናት /// ሙዚቀኞች///የናታኒም ቲም /// ያገለገላችሁ እግዚአብሔር ይባርካችሁ የቤተክርስቲያናችን ምዕመናን በሙሉ ተባረኩ ። በክርስቶስ ፍቅር እወዳችኋለሁ ርዕስ :- ድል ማድረግ ‼️ የተሰበከው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል “በሳኦል ቤትና በዳዊት ቤት መካከል ብዙ ዘመን ጦርነት ሆነ፤ የዳዊት ቤት እየበረታ፥ የሳኦል ቤት ግን እየደከመ የሚሄድ ሆነ።” 2ኛ ሳሙኤል 3፥1 ዳዊት እንዴት ነበር ድል ያደረገው ❓ 1 ዳዊት የምህረት ልብ ነበረው 2 ዳዊት እግዚአብሔርን አምላኪ ነበር 3 ዳዊት አመስጋኝ ነበር እኛም ዳዊት ያደረገውን በህይወታችን የምንለማመድ ከሆነ ድል እናደርጋለን :: አሜን
Показати все...
የተወደዳችሁ ቅዱሳን እንኳን 2016 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሰን! አደረሳችሁ !! በአመቱ :--- እግዚአብሔር ይባርክህ፥ ይጠብቅህም፤ እግዚአብሔር ፊቱን ያብራልህ፥ ይራራልህም፤ እግዚአብሔር ፊቱን ወደ አንተ ያንሣ፥ ሰላምንም ይስጥህ። ዘኍልቁ 6÷24-26
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ዛሬ ጳጉሜ 5/2015 እሁድ አምልኮ ጉባኤ በፀሎት በአምልኮ የዓመቱን መሪ ቃል በማወጅ እና በባርኮት እግዚአብሔር መልካም ጊዜ ሰጥቶናል ። በተለያየ መልኩ ያገለገላችሁ እግዚአብሔር አምላክ ይባርካችሁ ለቤተክርስትያናችን አገልጋዮች እና ምእመናን ሁልችሁ እንኳን አደረሳችሁ ። መልካም አዲስ ዓመት!! 2016E.C
Показати все...
🟡እንኳን ለ 2016 የዘመን መለወጫ በዓል አደረሰን ! አደረሳችሁ !! ነገ እሁድ ጷጉሜ 5/2015 ዓ.ም ጠዋት ከ3:00 - 6:00 🔷 የአዲሱን አመት መሪ ቃል የምናውጅበት 🔷የጸሎት 🔷የአምልኮ እና 🔷የባርኮት ፕሮግራም ተዘጋጅቷል :: አገልጋዮችና ምዕመናን ሁላችሁም በቤተክርስቲያን በመገኘት በጋራ እግዚአብሔርን እንድናከብር በዘመኑ ላይ የእግዚአብሔርን ቃል እንድናውጅ ይሁን። መልዕክቱንም ለሌሎች እናድርስ !! ተባረኩ !!! 🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸 “በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል።” መዝሙር 65፥11
Показати все...
05:46
Відео недоступнеДивитись в Telegram
7.20 MB
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.