ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
Відкрити в Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
Показати більше637
Підписники
-124 години
-37 днів
-1330 день
Архів дописів
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፲፩ (11) ቀን።
🌹 እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_የዓባይ_ውሃ ከኢትዮጵያ እንዳይወጣ #በጸሎታቸው_አቁመውት ለነበሩ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ኤልያስ_ዘውቅሮ ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
🌹 #አቡነ_ኤልያስ_ዘውቅሮ፦ የትውልድ ሀገራቸው አክሱም ነው፡፡ የአቡነ አረጋዊ 3ኛ የቆብ ልጅ ናቸው፡፡ አባታቸው ውቅሮ የሚገኘው የጥንታዊው የአብርሃ ወአጽብሓ ቤተ መቅደስ አጣኝ ነበሩ፡፡ እኚህ ጻድቅ የሚታወቁበት አንድ ትልቅ ገድል አላቸው፡፡ በቀን 548 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን እየጸለዩ 666 ጊዜ ይሰግዱ ነበር፡፡ ቅዱስ ያሬድ ዓባይ የሀገራችንን አፈርና ዛፉን ሁሉ ጠራርጎ ሲወስድ ቢመለከት ድምጹን ከፍ አድርጎ "ኦ አባይ አይቴ ተሐውር ወለመኑ ተሐዲጋ ለኢትዮጵያ" ብሎ ሲዘምር ዓባይ ቀጥ ብሎ ቆሟል፡፡ መልአኩም ወዲያው መጥቶ "ለምን ትደክማለህ? ለምንስ ተፈጥሮን ትከለክላለህ? ሕጉን አታፍርስ" ሲለው ቅዱስ ያሬድ ደንጎጦ "አጥፍቻለሁ ዓባይ ሆይ ሂድ የተፈጥሮ ግዴታህን ፈጽም" ብሎ አሰናብቶታል፡፡ የኢትዮጵያ ብርሃኗ ቅዱስ ያሬድ በዜማው ዓባይን ቀጥ አድርጎ እንዳቆመው ሁሉ አቡነ ኤልያስ ዘውቅሮም በጸሎታቸው ዓባይን ከኢትዮጵያ እንዳይወጣ አድርገውት ነበር፡፡
🌹 ታቦተ አብርሃ ወአጽብሓን ይዘው ከኢትዮጵያ ጠረፍ ዳር ኑብያ ሄደው ድንጋይ ከዓባይ ዳር ደርድረው ታቦቱን አስቀምጠው ሥዕለ ማርያምን አድርገው መሥዋዕት ሰውተው "ዓባይ ከኢትዮጵያ እንዳትወጣ ገዝቼሃለሁ" ሲሉት ዓባይም ተመልሶ ቆሟል፡፡ ዓባይ ምድረ ኑብያን ሲያጥለቀልቃት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጾ "ለምን የእግዚአብሔርን ስነ ፍጥረት ታስጨንቃለህ?" ብሎ ተቆጣቸው፡፡ ጻድቁም "ውኃው ይሂድ ግን ዛፉን አፈሩን ይዞ ከኢትዮጵያ አይውጣ" ብለው መልአኩን ጠየቁት፡፡
🌹 ቅዱስ ገብርኤልም "ውኃ ሲሞላ ዛፉን ቅጠሉን ይዞ መጓዙን እንዴት ትረሳዋለህ? የጸሎት ጊዜህ ደርሷልና ወደ በዓትህ ተመለስ" ብሎ በቁጣ የእሳት ሰይፉን ሲያዛቸው ግዝታቸውን አንሥተው ታቦታቸውን ይዘው ወደ በዓታቸው ውቅሮ ተመልሰዋል፡፡ አባቶቻችን እንዲህ ናቸው እንኳን ሃይማኖት፣ ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስ፣ ስብዕና ማንነታችንን ይቅርና የሀገራችንን አፈር እንኳን ለባዕድ አሳልፈው የማይሰጡ ቅዱሳን ጻድቃን ነበሩ፡፡ ከአባታች ከአቡነ ኤልያስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ።
🌹 "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፰ (8) ቀን።
🌹 እንኳን #ለሽማግሌው_አባት_ለአባ_መጥራ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍት በዓል፣ ከርእርሱ ጋር ብዙዎችን በሰማዕትነት ለዐረፋበት በዓልና #ተርታ_ነገርንም_እንዳይናገር_ደንጊያ_በአፉ_ጎርሶ_ለኖረ_ለባሕታዊ_ለአባ_አጋቶን_ለመታሰቢያው_በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱስ_ባኮስና #ከቅድስት_በላግያ በሰማዕትነት ከዐረፋ፣ #ከአባ_ሖር ከመታሰቢያውና ሰማዕትነት ከሆኑ ከልጆቹና #ከሶስና ይምሕው በሚባል አገር ከመታሰቢያቸው ከሆነ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
🌹 #ሽማግሌው_አባት_አባ_መጥራ ብዙዎች ሰዎች በሰማዕትነት፦ ይህም ቅዱስ ከእስክንድርያ አገር አማኒ ክርስቲያን ነው። ከሀዲ ንጉሥ ዳኬዎስ በነገሠ ጊዜ የጣዖትን አምልኮ አቁሞ የክርስቲያንን ወገኖች አሠቃያቸው። ትእዛዙም ወደ እስክንድርያ አገር ደርሶ ሰዎቿን ሁሉንም አሠቃያቸው የብዙዎች ምእመናንንም ደማቸውን አፈሰሰ። ያን ጊዜ ክርስቲያን እንደ ሆነ ቅዱስ መጥራን በመኰንኑ ዘንድ ወነጀሉት፤ መኰንኑም ወደርሱ አስቀረበው እርሱም ብቻውን እውነተኛ አምላክ እንደ ሆነ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ።
🌹 መኰንኑም "ለአማልክት ስገድ እኔም ብዙ ገንዘብን እሰጥሃለሁ ታላቅ ክብርንም አከብርሃለሁ" አለው። እርሱም ቃል ኪዳኑን አልተቀበለም "ኪዳንህና ገንዘብህ ካንተ ጋራ ወደ ጥፋት ይሒድ" አለው እንጂ። መኰንኑም በእርሱ ላይ ተቆጥቶ "እኔ በጽኑዕ ሥቃይ እቀጣሃለሁ" አለው።
🌹 ቅዱስ መጥራም ፈርቶ ከበጎ ምክሩ አልተመለሰም እንዲህም አለው እንጂ "እኔ ሰማይና ምድርን ለፈጠረ ለሕያው እግዚአብሔር እሰግዳለሁ። ለረከሱ ጣዖታት ከደንጊያና ከዕንጨት ለተሠሩ ለማያዩ ለማይሰሙ ለማይናገሩ ለማያሸቱ ለማይንቀሳቀሱ እንሰግድ ዘንድ እንዴት ይገባል" አለው። መኰንኑም በሰማ ጊዜ አፈረ። ጽኑ ግርፋትንም እንዲገርፉት አዘዘ።
🌹 ከዚህም በኋላ በክንዱ ሰቀሉት በደረቀች ሽመልም ጎኖቹን ሠነጠቁ ቀደዱትም ክብር ይግባውና ጌታ ኢየሱስም አዳነው። ያለ ጥፋትም በጤንነት አስነሣው መኰንኑም ማሠቃየቱን በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ። ከከተማውም አውጥተው የከበረች ራሱን ቆረጡ። ሌሎች ብዙዎች ሰማዕታትንም ከእርሱ ጋር ራሶቻቸውን ቆረጡ። የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ መጥራ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
🌹 #ባሕታዊ_አባ_አጋቶን፦ ይህም አባት ወደ ቲቤያድ ገዳም ሲመጣ ገና ሕፃን ነበር። ያሳደገው ያስተማረው አባ ጴማን ነው። በመቀጠልም ወደ አስቄጥስ ተጉዞ ከአባ እስክድር እና ዞይለስ ጋር ለጥቂት ጊዜ ኖሯል። ገዳመ አስቄጥስ ለመጀመርያ ጊዜ ሲጠፋ አባ አጋቶን ከደቀ መዝሙሩ ከአባ አብርሃም ጋር በመሆን ከደብረ ትሮኤ ሳይርቅ ከዓባይ ወንዝ አጠገብ መኖር ጀመረ።
🌹 አንድ ጊዜ ስለ አባ አጋቶን፡ትሕትና የሰሙ መነኰሳት ሊያዩት መጡ። የቁጣ ስሜቱን ወተውንና አለመተውን ለማረጋገጥ ብለው "አመንዝራውና ትዕቢተኛው አጋቶን ማለት አንተ ነህ?" አሉት። አባ አጋቶንም "አዎ ትክክል ነው" አላቸው። ቀጥለውም "ፍሬ የሌለው ነገር ዘወትር የምታወራ አጋቶን ማለት አንተ ነህ?" አሉት "አዎ ነኝ" አላቸው። "መናፍቅ አጋቶን ማለት አንተ አይደለህምን?" ሲሉ ጠየቁት ያን ጊዜ ግን "መናፍቅስ አይደለሁም" ሲል መለሰላቸው። በዚህ ጊዜ "እስካሁን የተናገርንብህን ሁሉ ተቀብለህ የመጨረሻውን ለምን ተቃወምክ?" አሉት። አባ አጋቶንም "የመጀመሪያያዎቹን ወቀሳዎች ለነፍሴ ተስማሚዎች ናቸውና ተቀበልኳቸው። ኑፋቄ ግን ከእግዚአብሔር መለየት ነው እናም እኔ ከፈጣርዬ መለየት አልፈልግም" አላቸው። በዚህ የተነሣም የርሱ ሕይወት አስደነቃቸው።
🌹 አንድ ቀን አባ አጋቶን በእጁ የሠራቸውን ነገሮች ለመሸጥ ወደ ገበያ ሲወጣ በመንገድ ዳር አንድ ሽባ ሰው አገኘ። ሽባውም የት እንደሚሄድ አባ አጋቶንን ጠየቀው። "አንዳንድ ነገሮች ለመሸጥ ወደ ገበያ እሔዳለው" አለው። ሽባው ሰውም "እባክህ ተሸከምህ ወደዚያ ውሰደኝ" ሲል ለመነው። አባ አጋቶንም ያንን ሰው ተሸክሞ ወደ ከተማ ወሰደው። ሽባው ሸውዬ "ዕቃዎችን ከምትሸጥበት ቦታ አጠገብ አኑረኝ" አለው። አባ አጋቶንም እንደዚያው አደረገው። አባ አጋቶን የመጀመርያውን ዕቃ ሲሸጥ "ምን ያህል ሸጥከው?" ብሎ ሽባው ሰው ጠየቀው። እርሱም ዋጋውን ነገረው። ያም ሽባ ሰው "እባክህ ዳቦ ግዛልኝ" ሲል ለመነውና ገዛለት።
🌹 አባ አጋቶን ሁለተኛው ዕቃ ሲሸጥ "ምን ያህል ሸጥከው" ሲል ያሰው ጠየቀው። እርሱም ዋጋው ነገረው "እባክህ ይህን ነገር ግዛልኝ" ሲል ለመነው። አባ አጋቶንም ገዛለት። በዚህም መልኩ ሁሉንም ዕቃዎች ሸጦ በጨረሰ ጊዜ ያሽባ ሰው "ወደ በዓትህ ትመለሳለህን?" ሲል ጠየቀው "አዎ" "እንግደውስ እባክ ቀድሞ ወደአገኸኝ ስፋራ አዝለህ መልሰኝ" አለው። አባ አጋቶንም ያን ሽባ ሰው ተሸክሞ ወደ ቀድሞ ቦታው መለሰው። በዚህ ጊዜ ሽባው ሰው "አባ አጋቶን በሰማይና በምድር በረከት ተሞላህ" ብሎ ተናገረው። ወድያው አባ አጋቶን አይኑን አንስቶ ሽባው ቢያየው በቦታው የለም። ሊፈትነው ይህን ያደረገው መልአከ እግዚአብሔር ነበር። ከአባታች ከአባ አጋቶን እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ በበረሐው ጉያ ውስጥ ከሚለው መጽሐፍ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከጻፈው።
✝ ✝ ✝
🌹 "#ሰላም_ለመጥራ_ምስለ_ሰማዕታት_ማኅበሩ። አመ አሰፈዎ መኰንን ከመ ይጸግዎ ሀብታተ ክቡሩ። ዘኢተመይጠ ምንተኒ እምነ ሠናይ ምክሩ። በሕለት ይቡስ እስከ ገቦሁ ሰቈሩ። ወእስከ በሰይፍ ክሣዶ መተሩ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥቅምት_8።
✝ ✝ ✝
🌹 #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እግዚአብሔር ኢያስተጼንሶሙ እምበረከቱ ለእለ የሐውሩ በየውሀት። እግዚኦ አምላከ ኃያላን። ብፁዕ ብእሲ ዘተወከለ ኪያከ"። መዝ 83፥11-12። የሚነበቡት መልዕክታት ፊሊ 1፥19-ፍ.ም፣ ያዕ 1፥2-7 እና የሐዋ ሥራ 14፥19-ፍ.ም የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 21፥12-21። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
🌹 ከሀዲ ንጉሥ ጠማትያኖስም ይዞ ጽኑ ሥቃይን አሰቃየው ከዚያም የከበረች ራሱን በሰይፍ ቆረጠው የተቆረጠች ራሱንም በእጁ ይዞ ሁለት ምዕራፍ ያህል ጐዳና ተጓዘ ሁለተኛም የደቀ መዛሙርቱን የኡሲፎስንና የኡርያኖስን ራሳቸውን ቆረጠ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ዲዮናስዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
🌹 "#ሰላም_ለሄኖስ ዘአቅደመ ጸውዖተ ስሙ #ለእግዚአብሔር"። ትርጉም፦ #የእግዚአብሔር ስሙን መጥራት ለዠመረው (ፊተኛ ለኾነው) #ለሄኖስ_ሰላምታ ይገባል። #ሊቁ_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ_በተአምኆ_ቅዱሳን_ላይ።
✝ ✝ ✝
🌹 #የሴት_ልጅ_ቅዱስ_ሄኖስ፦ ይህም ቅዱስ የእግዚአብሔርንም ስም መጥራት የጀመረ ይህ ሄኖስ ነው። ሄኖስም መቶ ዘጠና ዓመት ኖረ ቃይናንም ወለደው ቃይናንንም ከወለደው በኋላ ሰባት መቶ ዐሥራ አምስት አመት ኖረ ወንዶች ልጆችንና ሴቶች ልጆችን ወለደ በቅዳሜ ቀንም ዐረፈ። መላ ዕድሜውም ዘጠኝ መቶ አምስት ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሄኖስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥቅምት 6 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
🌹 "#ሰላም_ለዲዮናስዮስ_ሱታፌ_ሰማዕተ_እንጦና። ኤጲስቆጶስ ዘሀገረ ባና። አንከሩ ፈድፍደ ወተደሙ ሰብአ አቴና። ለበድነ ሥጋሁ በጊዜ ነጸሩ ይምና። በዐዊረ ርእሳ ምትርት እንዘ ተሐውር ፍና"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥቅምት_6።
✝ ✝ ✝
🌹 #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ንሕነሰ ሕዝቡ ወአባግዕ መሬቱ። ባኡ ውስተ አናቅጺሁ በተጋንዮ። ወውስተ አዕጻዲሁ በስብሐት እመንዎ። መዝ 99፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 10፥1-7።
✝ ✝ ✝
🌹 #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እበውእ ቤተከ ምስለ መባእየ። ወእሁብ ብጽዓትየ ዘነበብኩ በአፉየ። ዘእቤ በከናፍርየ አመ ምንዳቤየ"። መዝ 65፥13-14 ወይም መዝ 112፥8 ወይም መዝ 101፥4። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 5፥5-10፣ 1ኛ ጴጥ 5፥9-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 17፥30-ፍ.ም የሚነበበው ወንጌል ማቴ 1ዐ፥32-ፍ.ም ወይም ሉቃ 2፥36-39። የሚቀደው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም። መልካም የነቢይት ቅድስት ሐና፣ የአባ ጰንጠሌዎን የዕረፍታቸው በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
🌹 "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፮ (6)
እንኳን #ለነቢዩ_ሳሙኤል እናት #ለቅድስት_ሐና ለዕረፍቷ በዓል ቅዱስ አባት፣ ለነቢዩ #ቅዱስ_ዕንባቆም_ለመታሰቢያው_በዓሉ፣ #በሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ እጅ ለተጠመቀ ለሀገረ አቴና ኤጲስቆጶስ #ቅዱስ_ዲዮናስዮስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል፣ #ለሴት_ልጅ #ቅዱስ_ሄኖስ_ለዕረፍቱ_መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ቡና ከሚባል አገር ከሆነ #ከኤጴስቆጶስ_አባ_እንጦንዮስ ከምስክርነቱ መታሰቢያ፣ #ከቅዱሳን_ርዋቅና_እንጦንዮስ፣ #ከአባ_በጸሎተ_ሚካኤል ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
🌹 #የታላቁ_ነቢይና_ካህን_የቅዱስ_ሳሙኤል_እናት #ቅድስት_ሐና፦ ይችም ቅድስት ከሌዊ ነገድ ናት የታኅርም ልጅ ሕልቃና አገባት ፍናና የምትባልም ሌላ ሚስት አለችው እርሷም ወላድ በመሆኗ ሐና ልጅ ስለሌላት መካንም ስለሆነች ሁልጊዜ ትገዳደራት ነበር።
🌹 ሐና ግን ፈጽማ በማዘን አትበላም አትጠጣም ባሏ ሕልቃናም ያረጋጋታል ማረጋጋቱንም አልተቀበለችውም በሊቀ ካህናቱ በኤሊ ዘመንም ወደቤተ እግዚአብሔር ወጣች እያለቀሰችና እያዘነች በእግዚአብሔር ፊት ጸለየች እንዲህም ብላ ስለትን ተሳለች አቤቱ ልጅ የሰጠኸኝ እንደሆነ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ለአንተ የሚያገለግል አደርገዋለሁ።
🌹 ካህኑ ኤሊም አያትና እርሷ የወይን ጠጅ ጠጥታ እንደ ሰከረች አሰበ እርሷ በዝምታ በልቧ ትጸልይ ነበርና በቊጣና በግሣጼ "የወይን ጠጅ ጠጥተሽ ወደዚህ ወደ እግዚአብሔር ቤት ለምን መጣሽ አሁን ሒጂ ስካርሺን በእንቅልፍ አስወግጂ" አላት። እርሷም እንዲህ አለችው "የወይን ጠጅ ከቶ አልጠጣሁም ልጅ ያጣሁ በመሆኔ በልቤ አዝናለሁ እንጂ" ካህን ኤሊም አጽናናት እንዲሁም ብሎ ባረካት የእስራኤል ፈጣሪ የለመንሽውን ይስጥሽ በሰላም ሒጂ በቃሉም አምና ወደ ቤቷ ገባች።
🌹 ከዚህም በኋላ ፀንሳ ወንድ ልጅን ወለደች ስሙንም ሳሙኤል ብላ ጠራችው። ጡትንም በአስጣለችው ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ቤት ይዛው ወጣች ወደ ካህን ኤሊም አቀረበችውና እንዲህ ብላ አስረዳችው "ከአሁን በፊት ልጅን ይሰጠኝ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ስጸልይና ስለምን ያየኸኝ ሴት ነኝ ልመናዬንም ሰምቶ ይህን ልጅ ሰጠኝ አሁንም በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ለእግዚአብሔር አገልጋይ ይሆን ዘንድ አመጣሁት"።
🌹 ከዚህም በኋላ ሐና እግዚአብሔርን አመሰገነችው። ልቤ በእግዚአብሔር አምኖ ጸና የሚለውን ጸሎትና ትንቢት እስከ መጨረሻው ተናገረች። ይቺም በዳዊት መዝሙር መጨረሻ ከሙሴ መኀልይ ቀጥላ ተጽፋለች።
🌹 ከዚህም በኋላ እግዚአብሔርን አገልግላ ጥቅምት 6 ቀን በሰላም ዐረፈች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በነቢይት ቅድስት ሐና ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
🌹 #ነቢይ_ቅዱስ_ዕንባቆም፦ ይህም ነቢይ የስሙ ትርጓሜ አዋቂ የሆነ ማለት ነው። ከስምዖንና ከዮሴፍ ነገድ የዮሳፍጥ ልጅ ነው ዜናውን በግንቦት ወር በሃያ አራት ተጽፎ አለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በነቢዩ ቅዱስ ዕንባቆም ጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን
🌹 የሀገረ አቴና ኤጲስቆጶስ ቅዱስ ዲዮናስዮስ፦ ይህም ቅዱስ በአቴና አገር በእውቀቱና በመራቀቁ የከበረና ከፍ ከፍ ያለ ነው። በአቴናው ከተማ በዐዋቂዎች የመሳፍንት አንድነት ከአማካሪዎች አንዱ እርሱ ነው።
✝ ቅዱስ ሐዋርያ ጳውሎስም ወደዚያ በደረሰ ጊዜ ሃይማኖትን አስተምሮ የክርስትና ጥምቀትን አጥምቆ በአቴና አገር ኤጲስቆጶስ አድርጎ ሾመው። ብዙ ድርሳናትንም ደረሰ ከእርሳቸውም አንዱ ክብር ይግባውና ስለ መድኃኒታችን ስቅለት የደረሰው በዕለተ ዐርብ የሚነበብ አንዱ ነው።
🌹 የእምነቱም ምክንያት እንዲህ ነው ከዕለታት በአንዱ በፍልስፍናው ቤት ተቀምጦ ሳለ የአቴናም ፈላስፎች በእርሱ ዘንድ ተሰብስበው ነበር እርሱ ለሁሉም አለቃ ስለሆነ በዐርብ ቀንም ቀትር ሲሆን ፀሐይ ጨለመ ታላቅ ንውጽውታም ሆነ አሕዛብ ሁሉ ደንግጠው እጅግ ፈሩ ቅድስ ዲዩናስዩስንም በዓለም ውስጥ የሆነውን ጌታችን ሆይ አስረዳን ብለው ጠየቁት። እርሱም ፀሐይን ጨረቃንና ከዋክብትን መረመረ ጸጥ ብለው አገኛቸው ደግሞ ባሕሮችን ትልቁንም በዓለም ዙሪያ ያለውን የውቅያኖስን ባህር መረመረ እሱንም ጸጥ ብሎ አገኛው።
🌹 ከዚህም በኋላ አርስጣላባ የሚባል የፍልስፍና መጽሐፍን አንስቶ ሲመረምር በውስጡ "እልመክኑን" የሚል አገኘ ይህም "ኀቡእ አምላክ ወረደ ወገኞቹም በእርሱ ላይ ተነስተው ሰቀሉት" ማለት ነው በዚያችም ጊዜ ልብሱን ቀዶ ታላቅ ሀዘንን አዘነ ከበታቹ ምሁራን ያየውን ያስርዳቸው ዘንድ ለመኑት እርሱም ሁሉን ነገራቸው እነርሱም ይህን ሰምተው ታላቅ ፍርሃት ፈሩ።
🌹 ደቀ መዝሙሩ ኡሲፎስንም የሆነውን ሁሉ የዚያችንም ቀን ስሟን ሰዐቷን ወርዋን ዘመኑንም እንዲጽፍ አዘዘው ዳግመኛም በጣዖታቱ ቤቶች በደጃፋቸው እልመክኑን እያሉ እንዲጽፉ አዘዘ።
🌹 ከዐሥራ አራት ዓመትም በኋላ ቅዱስ ሐዋርያ ጳውሎስ ወደ አቴና አገረ መጣ ክብር ይግባውና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መውረዱን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከስጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ መወለዱን መከራ መቀበሉን መሰቀሉንና መሞቱን በሶስተኛው ቀን መነሳቱን ማረጉንም በሕያዋንና በሙታን ለምፍረድ ዳግመኛ መምጣቱን አስተማረ።
🌹 የአቴና ሰዎችም የሐዋርያዉን ስብከት በሰሙ ጊዜ እጅግ አደነቁ ወደ ዲዩናስዩስም ሩጠው እንዲህ ብለው ነገሩት አንድ ሰው ዛሬ ወደ አገራችን መጥቶ እኛ የማናውቀውን ወይም ከእኛ በፊት የነበሩ አባቶቻችን የማያውቁትን በአዲስ አምላክ ስም አስተማረን። ዲዮናስዮስም ልኮ ሐዋርያ ጳውሎስን ወደርሱ አስመጥቶ "በሀገራችን ውስጥ በአዲስ አምላክ ስም የምታስተምረው ምንድን ነው" አለው።
🌹 ቅዱስ ጳውሎስም "በአደባባያችሁ መካከል አልፌ ስሔድ በአማልክቶቻችሁ ቤቶች በደጃፋ ላይ እልመክኑን የሚል ጽሑፍ አየሁ ይህም የማይመረመር አምላክ ወረደ ማለት ነው እኔም ለእናንተ የምሰብከው ይህንኑ ነው" ብሎ መለሰ።
🌹 በዚያንም ጊዜ ከዐሥራ አራት ዓመት በፊት ያጻፈውን ያን መጽሐፍ ያመጣው ዘንድ ኡሲፎስን አዘዘው ሁለተኛም ጊዜውንና ወራቱን ሐዋርያውን ጠየቀው እርሱም በመጋቢት ወር በሃያ ሰባት ዓርብ ቀን በስድስት ሰዓት ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያን ጊዜ እንደ ተሰቀለ ፀሐይም እንደ ጨለመ ምድርም እንደተናወጠች አስረዳው።
🌹 የአቴና ሰዎችም ይህን በስሙ ጊዜ ከቅዱስ ዲዮናስዮስ ጋር ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው ዲዮናስዮስንም በእነርሱ ላይ ኤጲስቆጶስን አድርጎ ሾመው የቤተ ክርስቲያንንም ሥርዓት የተረጐመ እርሱ ነው።
🌹 ከዚህም በኋላ በባሕር አቅራቢያ ወደ አለ አገር በመሔድ በሐዋርያት ዘመን አስተማረ ብዙ ወገኖችንም ክብር ይግባውና በጌታችንም አሳመነ ድንቆች የሆኑ ብዙዎች ተአምራትን አደረገ።
🌹 "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፮ (6)
🌹 እንኳን #ከዘጠኙ_ቅዱሳን_አንዱ ለሆኑት በመሠረቱ ገዳም #በደብረ_ጾማዕት በዋሻ ውስጥ #ለአርባ_አምስት_ዓመት ለተጋደሉ ለታላቅ አባት #ለአቡነ_ጴንጠሌዎን_ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
🌹 #አባ_ጰንጠሌዎን፦ ይህም ቅዱስ በሮሜ አገር በንጉሥ ቀኝ ከሚቀመጡ ከከበሩ ሰዎች ወገን የተወለደ ነው። በታናሽነቱም ጊዜ ወደ መነኰሳት ገዳም ወስደውት በበጎ ምክር ዕውቀትን እየተማረ በመጸለይና በመጾም በዚያ አደገ።
🌹 ከዚህም በኋላ ከቅዱሳን ከስምንቱ ባልንጀሮቹ ጋር ወደ ኢትዮጵያ በንጉሥ አልዓሜዳ ዘመን መጣ በአንድነትም ጥቂት ዘመናት ኑረው ከዚህም በኋላ እርስበርሳቸው ተለያዩ ቅዱስ ጰንጠሌዎንም ከታናሽ ተራራ ላይ ወጥቶ ርዝመቱ አምስት ክንድ አግድመቱ ሁለት ስፋቱ ሦስት ክንድ የሚሆን ዋሻ ለራሱ ሠራ ጠፈሩም አንድ ደንጊያ ነው ከጥቂት ቀዳዳ በቀር በር የለውም። በውስጡም ሳይቀመጥ ሳይተኛ ያለመብልና ያለ መጠጥ አርባ አምስት ዓመት ኖረ ቆዳው ከዐጥንቱ እስከሚጣበቅ በዕንባ ብዛትም ቅንድቡ ተመለጠ። በሽተኞችን በማዳን የዕውሮችንም ዐይኖች በመግለጥ ብዙ ተአምራትን አደረገ።
🌹 በአንዲትም ቀን በማታ ጊዜ ዕንጨት ተከለ አሰከሚነጋ ድረስም አድጎ ትልቅ ዛፍ ሆነ ወዲያውም ደረቀና ደቀ መዝሙሩ ፈልጦ አነደደው ፍሙንም በልብሱ ቋጥሮ ለማዕጠንት ወሰደው።
🌹 የናግራንን አገር ያጠፋትን ምእመናኖችንም የገደላቸውን አይሁዳዊ ንጉሥ ሒዶ ሊወጋው ንጉሥ ካሌብ በአሰበ ጊዜ በጸሎቱ ይረዳው ዘንድ ይህን አባት ጰንጠሌዎንን ለመነው እርሱም "በሥራው ሁሉ ላይ ችሎታ ያለው እግዚአብሔር በጠላቶችህ ላይ ድል አድራጊነትን ሰጥቶህ በደኀና በፍቅር አንድነት ትመለሳለህ" አለው።
🌹 ንጉሥ ካሌብም ከናግራን ሀገር በደረሰ ጊዜ ከከሀዲው ንጉሥ ከፊንሐስ ጋር ተዋጋ ድል አድርጓቸውም ከሀድያንን ሁሉ እንደ ቅጠል እስቲረግፉ አጠፋቸው አባ ጰንጠሌዎንንም በጦርነቱ መካከል ጠላቶችን ሲአሳድዳቸው እንዳዩት ብዙዎች ምስክሮች ሆኑ።
🌹 ከዚህም በኋላ ንጉሥ ካሌብ ከድል አድራጊነት ጋር በተመለሰ ጊዜ መንግሥቱን ትቶ በዚህ አባት እጅ መነኰሰ ከዋሻ ውስጥም ገብቶ በጾምና በጸሎት እየተጋደለ ኖረ።
🌹 ይህም ቅዱስ አባ ጰንጠሌዎን ተጋድሎውን በፈጸመ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደርሱ መጣ ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውን የሚያደርግ ገድሉንም ለሚጽፍ ቃል ኪዳን ሰጠው እንግዲህስ ድካም ይበቃሀል ዕረፍ ያን ጊዜም ዐጥንቶቹ ተነቃነቁ በፍቅር አንድነትም ጥቅምት 6 ቀን ዐረፈና በዚያ በዋሻው ውስጥ ተቀበረ።
🌹 "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፬ (4) ቀን።
🌹 እንኳን #ከሰባ_ሁለቱ_አርድእት አንዱ ለሆነው ሐዋርያው #ቅዱስ_ጳውሎስ_በደማስቆ_ላጠመቀው ለሐዋርያ #ለቅዱስ_ሐናንያ_ሰማዕትነት_ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና #ለቅዱስ_ሰርጊስ ባልንጀራ #ለቅዱስ_ባኮስ በከሀዲ ንጉሥ በአንጥያኮስ እጅ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ የቅዱስ ባኮስ ሥጋ ወደ በዓታቸው ከወሰዱ ከቅዱሳን ወንድማማቾች ባሕታውያን ከባባና ከማማ ከመታሰቢያቸው፣ ከከበሩ ሮማውያን ጻድቃን ከጃንደረባው ዮሐንስና ገብረ ክርስቶስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
🌹 #ሐዋርያው_ቅዱስ_ሐናንያ፦ ይህም ቅዱስ ቁጥሩ ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ ነው። በሐዋርያት እጅ ለደማስቆ አገር ኤጲስቆጶስነት ተሾመ እርሱም ክብር ይግባውና ጌታችን በደማስቆ ጐዳና ተገልጦለት ለወንጌል ትምህርት በጠራው ጊዜ ሐዋርያ ጳውሎስን ያጠመቀው እርሱ ነው ።
🌹 እርሱም አስቀድሞ ለግብሪል ወገኖች አስተማረ ብዙዎች በሽተኞችን አዳናቸው ብዙ ሰዎችንም ክብር ይግባውና ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖት መለሳቸው ።
🌹 ከዚህም በኋላ ስሙ ሉቅያኖስ የሚባል መኰንን ያዘው በምድር ላይ ደሙ እንደውኃ እስከሚፈስ ድረስ ገረፈው ጐኖቹንም በብረት በትሮች ሠነጣጠቀ ደረቱንም በእሳት መብራቶች አቃጠለ ። ከዚህም በኋላ ከከተማ ውጭ አውጥተው በደንጊያ ይወግሩት ዘንድ አዘዘ በዚህም ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያው ቅዱስ ሐናንያ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
🌹 #የቅዱስ_ሰርጊስ_ባልንጀራ_ቅዱስ_ባኮስ፦ ይህም እንዲህ ነው እሊህን ቅዱሳን ከሀዲው ንጉሥ መክስምያኖስ በያዛቸው ጊዜ እነርሱ ወታደሮች ነበሩና ትጥቃቸውን ቆርጦ ታላቅ ሥቃይን አሠቃያቸው ከዚህም በኋላ ወደ ሶርያ አገር ወደ ንጉሥ አንጥያኮስ ሰደዳቸው። እርሱም ቅዱስ ሰርጊስን አሠረው ቅዱስ ባኮስን ግን ሰቅለው እንዲደበድቡት በአንገቱም ከባድ ደንጊያ አንጠልጥለው ከኤፍራጥስ ወንዝ ከባሕር እንዲጥሉት አዘዘ ንጉሡም እንደ አዘዘ እንዲሁ አደረጉ።
✝ እግዚአብሔር ግን የቅዱስ ባኮስን ሥጋ ጠብቆ ወደ ወደብ አደረሰው በዚያ ወደብ አቅራቢያም በገድል ተጠምደው የሚኖሩ የአንደኛው ስሙ ማማ የሁለተኛው ባባ የሚባሉ ባሕታውያን አሉ። ለእሊህ ወንድሞችም ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጠላቸውና ሒደው የቅዱስ ባኮስን ሥጋ ወደ በዓታቸው እንዲወስዱ አዘዛቸው።
🌹 በዚያንም ጊዜ መልአክ እንዳዘዛቸው ሔዱ የቅዱስ ባኮስንም ሥጋ አገኙ በአጠገቡም አንድ ቀንና አንድ ሌሊት ሲጠብቁት የነበሩ አንበሳና ተኵላ አሉ እነርሱም ከሰው ሥጋና ከእንስሳ በቀር የማይመገቡ ሲሆኑ ግን ከልዑል አምላክ ዘንድ ስለታዘዙ ነው። እሊያ ቅዱሳንም የቅዱስ ባኮስን ሥጋ ወሰዱ በታላቅ ክብር እያመሰገኑ እስከ በዓታቸውም አድርሰው በዚያ ቀበሩት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ባኮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
🌹 "#ሰላም_ለሐናንያ_ለጳውሎስ_መጥምቁ። ወውስተ ኍልቈ አርዳእ ኊልቊ። እኩያን ዕደው እምአሚነ ክርስቶስ ዘርኅቁ። በበትረ ኀፂን ገበዋቲሁ ሠጠቁ። ወበውግረተ ዕብን ካዕበ ኵለንታሁ ደመቁ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ_አርኬ_የጥቅምት_4።
✝️ ✝️ ✝️
🌹 #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እግዚኦ ስብሐተ ሐዲስ እሴብሐከ። ወበመዝሙር ዘዓሠርቱ አውታሪሁ እዜምር ለከ። ዘይሁቦሙ ለነገሥት መድኃኒተ"። መዝ 143፥9-10። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 13፥47-53።
✝️ ✝️ ✝️
🌹 #የዕለቱ_ቅዳሴ_ምስባክ፦ "ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሃ ኀበ እግዚአብሔር። ነገሥተ ምድር ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር። ወዘምሩ ለአምላክነ"። መዝ67፥31-32። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 7፥29-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 2፥16-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 9፥10-20 የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1ዐ፥17-25። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቄርሎስ ወይም የቅዱስ ባስልዮስ ወይም የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱሳን ነገሥታት የአብርሀ አጽብሐና የአቡነ በርተሎሜዎስ የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
አይከፍተውም አይዘጋውም፡፡
🌹 አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን በአክሱም ሲኖሩ ከሳምንቱ ቀናት ውስጥ ቅዳሜና እሑድ ብቻ የዛፍ ቅጠሎችን ከመመገብ በቀር ሌላ ምግብ ባለመመገብ በታላቅ ተጋድሎ ይኖሩ ነበር፤ አህልም አይቀምሱም፤ በየቀኑም አምስት ሺህ ስግደትን ይሰግዳሉ፡፡ በእርሳቸውም የተጋድሎ ዘመን ደጋግ የሆኑ ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃና አጽብሓ ነገሡ፡፡
🌹 ነገሥታቱም ሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃንን እጅግ በጣም ይወዷቸው ነበር፡፡ አባታችንም በእንዲህ ዓይነት ተጋድሎ ሲኖሩ ከዕለታት በአንደኛው ቀን የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክ ለአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ተገልጣላቸው "ዲቁናና ቅስናን መቀበል ይገባሃል፣ ለጵጵስና ተዘጋጅ፣ እግዚአብሔር ይህችን ከፍ ያለችውን ማዕረግ ሰጥተሃልና የልጄ ወዳጅ ሆይ በጸሎትህና በልመናህ በስብከትህም የኢትዮጵያ ሰዎች ሁሉ ይድናሉ፣ በእጅህ ጥምቀትንና ሥጋ ወደሙን ይቀበላሉ!" አለችው፡፡ ጌታችንም እንዲሁ ተገልጦላቸው "ወደ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አትናቴዎስ ሄደህ ከፍ ያችውን ማዕረግ ተቀብለህ የኢትዮጵያን ሰዎች አጥምቅልኝ፣ ነቢዩ ዳዊት ስለ እነርሱ "ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች" ብሎ ተናግሯልና" አላቸው፡፡
🌹 ነገሥታቱ አብርሃንና አጽብሓ ነገረ ክርስቶስን እያሰቡ ስለ ጥምቀት ልጅነት ይጨነቁ ነበር፡፡ ከሊቀ ካህናቱም ጋር በዚህ ጉዳይ ሲጨዋወቱ ሊቀ ካህናቱ ስለ አቡነ ሰላማ ነገሯቸው፡፡ ነገሥታቱም አቡነ ሰላማን አስጠርተው ስለነገረ ክርስቶስ ምሥጢር እንዲያስረዷቸው ጠየቋቸው፡፡ አባታችንም "ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው አካላዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድ ይወለዳል ካሉበት ጀምሮ የልደቱን፣ የትምህርቱን የጥምቀቱን፣ የስቅለቱን፣ የሞቱን፣ የትንሣኤውንና የእርገቱን ነገር ሌላውንም ሁሉ ተንትነው አስተማሯቸው፡፡ ሐዋርያትም በጌታ ተሾመው ዓለምን ዞረው ማስተማራቸውን እንዲሁ ተረኩላቸው፡፡ ነገሥታቱም ይህንን በሰሙ ጊዜ እጅግ ደስ ብሏቸው ፍሬምናጦስን "ወንድማችን ሆይ! ይህን ሥርዓት በሀገራችን እንድታስፋፋ" አሏቸው፡፡ አባታችን ግን "ለዚህ የሚያበቃ ሥልጣን ያለው እንጂ ለእኔ አይቻለኝም" አሉ፡፡ ነገሥታቱም "ይህን የሚችል ማነው?" ብለው ቢጠይቋቸው "በእስክንድርያ ጳጳሳትን፣ ቀሳውስትንና ዲያቆናትን የሚሾም አባት አለ" አሏቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ነገሥቱ ወደ እስክንድርያው ሊቀ ጳጳሳት ወደ ቅዱስ አትናቴዎስ ደብዳቤ በመጻፍ "አባታችንና መምህራችን ሆይ! የምንጠይቅህን እሺ በጀ በለን ይኸውም ወደ ጽድቅ ጉዳና የሚመራንን ጳጳስ ሹምልን" በማለት ብዙ ወርቅና ብር ገጸ በረከት አስይዘው ከብዙ ሊቃውንት ጋር ፍሬምናጦስን ወደ እስክንድርያ ላኳቸው፡፡
🌹 ከዚህም በኋላ አባታችን ከነገሥታቱ አብርሃና አጽብሓ ጋር ተማክረው ወደ እስክንድሪያ ሄደው በቅዱስ አትናቴዎስ እጅ በአገራችን ላይ ሊቀ ጳጳስ ሆነው ታኅሣሥ 18 ቀን ተሾሙ፡፡ ቅዱስ አትናቴዎስ ከሾሟቸውና ከመረቋቸው በኋላ ለአቡነ ሰላማና አብረውት ለነበሩ ሊቃውንት መጻሕፍተ ብሉያትን፣ መጻሕፍተ ሐዲሳትንና ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን፣ ታቦተ ማርያምን፣ ታቦተ ሚካኤልንና ታቦተ ገብርኤልን አስይዘው ለነገሥታቱም ደብዳቤ ጽፈው ከብዙ ገጸበረከት ጋር በታላቅ ክብር ሸኟቸው፡፡
🌹 ቅዱሳን የሚሆኑ ሁለቱ ነገሥታትም አቡነ ሰላማ ከእስክንድርያ ተሾመው መምጣቸውን በሰሙ ጊዜ "የኢትዮጵያ ሰዎች ሁላችሁ እስከ 40 ቀን ተሰብሰቡ" ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ አባታችንንም በደብረ ሲናም ሄደው አገኟቸውና ከዚያች ቀን ጀምሮ ሕዝቡም ሁሉ እስከ 40 ቀን ድረስ ተጠመቁ፡፡ በዚያችም ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያች በደብረ ሲና አገር ላይ ወረደና ሕዝቡን ሁሉ ባረኮ ተመልሶ ሲያርግ ከአባ ሰላማ በቀር ያየው አልነበረም፡፡ ወደ አክሱምም ሄደው ቅዱሳን ነገሥታቱም የአድባራት ሁሉ የበላይ የምትሆን የቅድስት ጽዮንን ቤተ ክርስቲያን በወርቅና በዕንቊ ሠሯትና አባ ሰላማ ባርከው ቀደሷት፡፡ ታቦተ ጽዮንም ከድንኳን ወጥታ ማንም ካህን ሳይሸከማት አብርሃና አጽብሓ ወዳሠሩላት ቤተ መቅደስ ራሷ በመንፈስ ቅዱስ ገብታ ተገኘች፡፡
አባታችን በእመቤታችንም በዓለ ዕረፍት ጥር 21 ቀን በውስጧ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲቀድሱ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በግራ በቀኝ እየተራዷቸው እርሳቸውም ከምድር ሦስት ክንድ ከፍ ብለው ሥርዓተ ቅዳሴውን ፈጽመው ለነገሥታቱና ለሕዝቡም ሁሉ አቆረቧቸው፡፡ የዚያን ዕለትም እጅግ ታላቅ በዓልን አደረጉ፡፡
🌹 እነዚህም ቅዱሳን ነገሥታት ትምህርተ ወንጌልን እየሰጡ በአክሱም ቤተ መንግሥታቸው ሳሉ ከዕለታት አንደኛው ቀን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መላእክቱን አስከትሎ መጥቶ በአክሱም "ማይ ኰኩሐ" በሚባል ተራራ ላይ ቁሞ አብርሃ ወአጽብሓን ጠርቶ "በዚህች ቦታ ላይ ቤተ መቅደሴን አንጹልኝ" አላቸው፡፡ እነርሱም "ቦታው ባህር ላይ ነው በየት እናንጽልህ?" አሉት፡፡ ጌታችንም በጥበቡ ከገነት ጥቂት አፈር አምጥቶ በባሕሩ ላይ ቢበትንበት ባሕሩ ደርቆ ሜዳ ሆነ፡፡ በዚህ ጊዜ ጌታችን "ቤተ መቅደሴን በዚህ ሥሩ" ብሏቸው ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ ጌታችንም በቆመባት ዓለት ላይ የእግሩ ጫማ ቅርጽ እስከ አሁን ሳይጠፋ በግልጽ ይታያል፡፡ ቦታውም ከዚያ ወዲህ "መከየደ እግዚእ" እየተባለ ይጠራል፡፡
🌹 አብርሃ ወአጽብሓ ከመንግሥት አስተዳደሩ ጋር ክርስትናንና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን በመላ ኢትዮጵያ በማዳረስ እጅግ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አድርገዋል፡፡ ካህናትንና ዲያቆናትን ይዘው በመላ ኢትዮጵያ ሐዋርያዊ ጉዞ በማድረግ ሕዝቡን ሁሉ እያስተማሩ፣ ሃይማኖትን እያጸኑ፣ ሥርዓተ ጥምቀትን እያስፋፉ ብዙ አብያተ ክርስቲያናትን አንጸዋል፡፡ በሀገራችን በአራቱም አቅጣጫ ወንጌልን አስፋፍው ሕግ ሠርተዋል፡፡ የከበሩ ቅዱሳን ነገሥት አብርሃ ወአጽብሓ በእንዲህ ዓይነት ግብር ጸንተው በመኖር እግዚአብሔርንም ሰውንም አገልግለው ለሀገራችንም ብርሃን አብርተውላት ነው ያለፉት፡፡
🌹 ታላቁ አብርሃ በ364 ዓ.ም ጥቅምት 4 ቀን እሑድ ዕለት ዐረፉ፡፡ ከ13 ዓመት በኋላ ታናሹ አጽብሓ በ379 ዓ.ም ጥቅምት 4 ቀን ዐረፉ፡፡ ልደታቸውም ሆነ ሞታቸው አንድ ቀን ነው የዕረፍታቸው ዓመቱ ይለያይ እንጂ፡፡ የተቀበሩበት ቦታም አንድ ነው፡፡ የንግሥና ስማቸው ኢዛናና ዛይዛና ይባላል፡፡ ከቅዱሳን ነገሥታት ከአብርሃ ወጽብሓ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን።
✝ ✝ ✝
🌹 "#ሰላም_ለአብርሀ_ወለአጽብሐ_ዘነበሩ። በመንግሥታት አሐቲ እንዘ ይትፋቀሩ። ለእለ ትካት ሰብእ በትዛዘ ኦሪት ዘሖሩ። ተሰብከ በአፉሆሙ ወንጌለ ክርስቶስ ነገሩ። ወበንዋዮሙ ተሐንፀት ማኅደሩ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ _አርኬ_የጥቅምት_4።
🌹 "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፬ (4) ቀን።
🌹 እንኳን #ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ሃይማኖት #በኢትዮጵያ_ብሔራዊ_ሃይማኖት_እንዲሆን_ላደረጉ ለቅዱሳን ለወንድማማቾች ነገሥታት ያለፈረቃም በፍቅር አንድነት በአክሱም ተቀምጠው ለነገሡ (ለገዙ) #ለቅዱሳን_አብርሀና_አጽብሐ_ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል፣ #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ወሎ ራያ ውስጥ ያለችውን ጥንታዊቷንና ባለታሪኳን ቅዱስ ሉቃስ የሳላት የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ስዕል የምትገኝበት #ደብረ_ዘመዳን_ለመሠረቱ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_በርተሎሜዎስ_ለዕረፍታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
🌹 #ስለ_አቡነ_በርቶሎሜዎስ_ዕረፍት፦ ... ከዚኽ በኋላ በዚያች ቀንና በዚያች ሰዓት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከክብርት እናቱ ከእመቤታችን ወላዲተ አምላክ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ወደ እርሱ መጥቶ ተገለጠለት። ያን ጊዜም መንፈሳዊ አባታችን አባ በርተሎሜዎስ ደንግጦ ወደቀ። እንደምውትም ኾነ። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግፎ አንሥቶ "ወዳጄ፤ የእናቴ የድንግል ማርያምም ወዳጅ በርተሎሜዎስ ሆይ እነሆ ገድልህ ፈጽመሃል። መላእክትህንም በመልካም ተጋድሎ ጨርሰሃል። ስለ ትሕትናህ መረጥሁህ። እነሆ በማይታበል ቃሌ ፍጹም ክብርን ሰጠኹህ። በጸሎትህ አምኖ መቃብርህ ያለበትን ገዳም የሚሳለም ራሱንም ስለ ስምህ ብሎ ዝቅ የአደረገውን ኹሉ ኃጢአቱን ይቅር ብሎ ደስታ የተመላች ገነትን አወርሰዋለሁ"።
🌹 "ዝክርህን የዘከረ፣ ስምህን የጠራ፣ መጽሐፈ ገድልህን የጻፈ፣ ይኽንን መጽሐፈ ገድልህንም የጸለየበት፣ በጆሮውም የሰማውን ኹሉ እኔ ስሙን ስምህ በተጻፈበት የወርቅ ዐምደ ሰሌዳ ውስጥ እጽፍለታለሁ። ዕጣንና ዘቢብ መብራት ቅብዐ ቅዱስንም ለቤተ ክርስቲያንህ የሚሰጥ እኔ በመንግሥተ ሰማያት ዋጋውን አላጎድልበትም። መቃብርህ ወደአለበት ወደ ዚኽ ገዳም የሄደ ወይም መቃብርህን የጠበቀውን እኔ የመቃብር ቦታዬ ወደ አለበት እንደሄደ ቆጥሬ ኃጢአቱን ይቅር እለዋለሁ። በገዳምህ ምንኵስናን ተቀብሎ የመነኰሰውን ኃጢአቱን ይቅር እለዋለሁ። አስኬማውንም አስኬማ መላእክት አደርግለታለሁ። በስምህ እንግዳን የሚቀበል ለባልንጀራውም በሚቻለው ኹሉ በጎ ለሚያደርግ ወደ ቀደመ በደሉ ካልተመለሰ በደሉን አላስብበትም። የተጠማን ለሚያጠጣ የተራበን ለሚያበላም በሺህ ዓመት የሚገለጥ የደስታ ሕወትን ደስ የሚያሰኝ ጽዋዐ ሕይወትን አጠጣዋለሁ"።
🌹 "መቃብርህ በአለበት ገዳም የሚቀበረው ኹሉ፤ ስንኳ የሚቀበረውን ተሸክሞው ወደ ገዳምህ የመጡትንም በደላቸውን አላስብባቸውም። ስምህን ጠርቶ በማናቸውም ነገር በጸሎትህ ታምኖ ቢኾን በገዳምህ በመኖር እስከ ዕለተ ሞቱ የአገለገለውን እስከ ዐሥር ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ። ወዳጄ በርተሎሜዎስ እነሆ የማይታበል ቃል ኪዳኔን ሰጠኹህ። ብርሕት ሀገርንም አወረስሁህ። አንተ ከወንድሞች መካከል ለአንዱም ስንኳ ገድልህን ሳትነግር በምሥጢር ሰውረህ ነበር፤ እኔ ግን የገድልህን ክብር በዓለም ዳርቻዎች ኹሉ ገልጬ በዐሥራ አምስቱ አህጉራተ ገነት በአምስቱ አህጉራተ መንግሥተ ሰማያትም እሾምሃለሁ"።
🌹 ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአባታችን አባ በርተሎሜዎስ ይኽንን ኹሉ ቃል ኪዳን ሰጥቶት በታላቅ ምስጋና ወደ ሰማያት ዐረገ። ከወልደ እግዚአብሔር ክርስቶስ በተሰጠው በዚኽ ቃል ኪዳን ምክንያትም ሰው ሊድን ነውና አባ በርቶሎሜዎስ ስለተሰጠው ቃል ኪዳን እጅግ ተደሰተ። "ለአንተና ለአባትህ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል ለዘለዓለሙ አሜን በእውነት ይኹን ይደረግ" ብሎ በፈጣሪው በጌታችንና በአምላካችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት ወድቆ ሰገደ።
🌹 አባታችን አባ በርቶሎሜዎስ ግን በከንቱ ምስጋና በሰው ዘንድ ተወድሶ እንዳይኾንበት ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻ ተጋድሎውን ለማንም ቢኾን ሊገልጥ አልወደደም ነበር። እርሱ በትዕግሥትና በትሕትና ፍጹም ልቡናውም በፈሪሃ እግዚአብሔር የተመላ ነውና። እኔስ የገድሉን ነገር ለገዳማውያኑ እመሰክራለሁ፤ ከዕለተ ልደቱ እስከ ዕረፍቱም ከሃይማኖትና ከስብሐተ እግዚአብሔር በቀር ከአንደበቱ የዚኽ ዓለም ነገር አልወጣም።
🌹 በዘመኑ ወደ ቅድስት ደብረ ዘመዳ ከገባ መቶ ዘጠና ዓመት ከዘጠኝ ወራት ኖረ። አስቀድሞ የነበረበት ግን አልታወቀም። ከዚኽ በኋላ ግን ዕለተ ዕረፍቱ እንደቀበረ በጸጋ መንፈስ ቅዱስ ዐውቆ ልጆቹ ገዳማውያን መነኰሳትን ሰብስቦ "እግዚአብሔር ለመረጠው ይገባልና ለዚኽ ገዳም ሹመት አትሽቀዳደሙ። ኃይለ እግዚአብሔር የአደረበት የቅድስናውና የትምህርቱ ነገር በዓለም ኹሉ የሚነገርለት ከእኔ በኋላ ታላቅ ጻድቅ ሰው መጥቶ በዚኽች ገዳም ይሾማል። ድንቅ ድንቅ ተአምራትም ይደረጋሉ፤ እናንተ ግን እርሱ የአዘዛችሁን ስሙ" ብሎ የገዳሟን ሥርዐት እንደ ቀድሞው አሳሰባቸው።
🌹 ከዚኽ በኋላም አባታችን አባ በርቶሎሜዎስ ትንሽ ታምሞ በወርኀ ጥቅምት በአራተኛው ቀን በሦስት ሰዓት ዐረፈ። ያን ጊዜም ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ እልፍ አእላፋት ቅዱሳን መላእክትንና ነቢያትን ሐዋርያትንም ጻድቃንንና ሰማዕታትን ኹላቸው ቅዱሳንንም በእየክብራቸውና በእየመዓርጋቸው በእየወገናቸውም አስከትሎ መጣ።
🌹 ቅዱሳን መላእክትና ሊቃነ መላክትም የእግዚአብሔር ሰው ንዑድ ክቡር ገዳማዊ ደግ ጻድቅ አባታችን አባ በርቶሎሜዎስን የብርሃን አክሊል አቀዳጁት። ከፀሐይ ሰባት እጅ የሚያበራ ልብሰ ብርሃንን አለበሱት። በመዝሙር ዳዊት በአንድ ቃል "የጻድቅ ሰው ዕረፍቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው። የጻድቅ ዝክርም በዘለዓለም ይኖራል። ጻድቅስ እንደ ሊባኖስ በዝቶ ያፈራል። እሊኽም በቤተ እግዚአብሔር የተተከሉ ናቸው"። ይኽንና የመሳሰለውንም ኹሉ እየዘመሩ ወደ ሰማያት አሳረጉት። ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስም "ንጽሕት ነፍስ ወደ ዕረፍትሽ ግቢ እኔ እግዚአብሔር ረዳትሽ ነኝና። ከብዙ ፃማ ሥጋም (ደካማ) አሳርፌ ፍጹም ደስታ ወደአለበት ወስጄ በዘለዓለም በዚያ ትኖሪያለሽ" ብሎ የአባታችን የአባ በርቶሎሜዎስን ክብርት ነፍሱን ተቀበሎ ደስ አሰኛት።
🌹 የአባታችን አባ በርቶሎሜዎስ ገዳማውያን ደቀ መዛሙርትም ጽኑ ለቅሶን አለቀሱለት። በግምጃ ልብስም ገንዘው በታላቅ ክብር ወደ ቤተ መቅደስ አግብተው በበዐቱ ቀበሩት። ከአባታችን ከአቡነ በርቶሎሜዎስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ በርቶሎሜዎስ የቅዳሜ።
✝ ✝ ✝
🌹 #ቅዱሳን_ወንድማማቾች_ነገሥታት_ቅዱሳን_አብርሀ_ወአጽብሐ፦ አባታቸው ታዜር እናታቸው ሶፍያ (አህየዋ) ይባላሉ፡፡ መንትዮች የሆኑት እነዚህ ቅዱሳን የተወለዱት ጌታችን በተወለደባት ዕለት በታኅሣሥ 29 ቀን 312 ዓ.ም ነው፡፡ በታላቁ አባት በአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን እየተማሩ አድገው በእሳቸው እጅ በ330 ዓ.ም መጋቢት 29 ቀን ተጠመቁ፡፡ በእነርሱም ጊዜ አማናዊው ጥምቀትና ቊርባን መጣልን፡፡ በሀገራችን 154 አብያተ ክርስቲያናትን ያሠሩ ሲሆን 44ቱ ፍልፍል ናቸው፡፡ በተለይም ገርዓልታ ያለው ቀመር ዓርባዕቱ እንስሳ ፍልፍል ቤተ መቅደስ በሩ በራሱ ጊዜ ይከፈታል ይዘጋል እንጂ ሰው
አባ ጊዮርጊስ ከግዞት የወጣው ዐፄ ቴዎድሮስ ሲሞት ነበር፡፡
🌹 የአባ ጊዮርጊስ ሌላው ተማሪ የነበረው ዐፄ ይስሐቅ በ1399 ዓ.ም መንግሥቱን ሲይዝ አባ ጊዮርጊስን ከግዞት አውጥቶ ወደ ጋሥጫ መለሰው፡፡ በዚያ ጊዜ አባ ጊዮርጊስ እድሜው 42 ዓመት ሲሆን በስደትና በጤንነት መታወክ የተነሣ ከባድ ጉዳት ደርሶበት ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ብዙውን ጊዜውን በጾም፣ በጸሎትና በድርሰት ያውለው ነበር፡፡ አንድ ቀን ቴዎድሮስ የተባለ መስፍን፣ ዳግመኛም የጦሩ አዛዥ የሚሆን፣ አባ ጊዮርጊስን ስለ ርትዕት ሃይማኖት በጠየቀው ጊዜ አባ ጊዮርጊስም "ፍካሬ ሃይማኖት" የተባለውን መጽሐፍ ደርሶ ሰጠው፡፡ ንጉሡና የምሥጢር ሊቃውንት የሆኑ ካህናት ይህንን በተመለከቱና ባነበቡ ጊዜ "በእውነት ዮሐንስ አፈወርቅና አፈ በረከት የሆነው ቄርሎስ በዘመናችን ተነሥተዋል፡፡ ኢትዮጵያም ቍስጥንጥንያን መስላለች፣ ከእስክንድርያም በላይ ከፍ ከፍ ብላለች" ብለው አደነቁ፡፡
🌹 ይህም ፍካሬ ሃይማኖት የተሰኘው ድንቅ ድርሰቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምታምነውንና የምታወግዘውን በግልጽና በዝርዝር የጻፈበት መጽሐፍ ነው፡፡ አባ ጊዮርጊስ በፍካሬ ሃይማኖት ድርሰቱ ላይ የዘረዘራቸው የመናፍቃን ስሞችንና ክህደታቸውን ስንምለከት በዘመኑ የነበሩ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ስለ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ያላቸውን ዕውቀት በግልጽ ያሳየናል፡፡ አባ ጊዮርጊስ መከራ ያልተለየው አባት በመሆኑ አሁንም በቤተ መንግሥት የነበሩ ሰዎች የእርሱን መከበርና መወደድ አይፈልጉትም ነበር፡፡ በተለይም "ፍካሬ ሃይማኖት" የተሰኘውን መጽሐፍ በመጻፉ በዚህም ዝናው የበለጠ ስለተነገረ እነርሱ በሁሉም ዘንድ መከበሩን አልወደዱትም ነበር፡፡ ስለዚህም ነገር ሠርተው ከዐፄ ይስሐቅ ጋር አሁንም አጣሉት፡፡
🌹 ዐፄ ይስሐቅ አባ ጊዮርጊስን አሳስሮ ውኃ ወደማይገኝበት ዓለታማ ቦታ አጋዘው፡፡ በዚያም በመከራ ለብዙ ጊዜ ኖረ፡፡ በዚያ እያለ ዘወትር በጸሎት አብዝቶ ይተጋ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ዐፄ ይስሐቅ ወደ ልቡናው እንዲመለስ አደረገ፡፡ ንጉሡ በአባ ጊዮርጊስ ላይ የፈጸመው ነገር ሁሉ ስለፀፀተው አገልጋዮቹን ጠርቶ አባ ጊዮርጊስን እንዲያመጡት አዘዘ፡፡ ነገር ግን እነዚያ ተንኮል ሠሪዎች የአባ ጊዮርጊስ መምጣት ተንኮላቸውን ስለሚያጋልጠው "አባ ጊዮርጊስ ሞቷል" ብለው አስወሩ፡፡ ይህንን ሲሰማ ዐፄ ይስሐቅ ፈጽሞ አዘነ፡፡
🌹 አባ ጊዮርጊስም ሞቷል እየተባለ መወራቱን ከደቀ መዝሙሩ ስለ ሰማ በሕይወት የመኖሩን ዜና ጽፎ ለዐፄ ይስሐቅ እንዲያደርስለት መልእክቱን በአውሎ ንፋስ አሳስሮ ላከለት፡፡ አውሎ ንፋሱ ለአባ ጊዮርጊስ በመታዘዝ ደብዳቤውን ተሸክሞ በመሄድ ዐፄ ይስሐቅ በድንኳን ተቀምጦ በነበረ ጊዜ ጉልበቱ ላይ አስቀመጠው፡፡ ንጉሡ ምትሐት የተሠራበት ስለመሰለው ደነገጠና መኳንንቱንና ሕዝቡን ሰብስቦ ጉዳዩን ገለጠ፡፡ ወዲያውም ነፋሱ ያመጣለትን መልእክት እሳት አስነድዶ ከዚያ ውስጥ ቢጥለው ሊቃጠል አልቻለም፡፡ ወደ ውኃም ቢጨምረው አልጠፋም፡፡ በዚህ ተደንቆ ወረቀቱን ከፍቶ አነበበው፡፡ ደብዳቤው ከአባ ጊዮርጊስ የተላከ መሆኑን ሲያውቅ ዐፄ ይስሐቅ ደነገጠ፡፡ እነዚያን መልእክተኞች ይዞ ወደ ወኅኒ ከጨመራቸው በኋላ አባ ጊዮርጊስን ከግዞት ያወጡት ዘንድ ላከ፡፡ አባ ጊዮርጊስ ወደ ቤተ መንግሥቱ ሲመጣ ንጉሡ በደስታ ተቀብሎ ማረኝ ብሎ ለመነው፡፡ አባ ጊዮርጊስም ይቅር አለው፡፡ ከዚህም በኋላ ደብዳቤውን በማን እጅ እንደ ላከው ጠየቀው፡፡ አባ ጊዮርጊስም ደብዳቤውን በሰው ሳይሆን በእግዚአብሔር ፈቃድ በነፋስ እንደ ላከው አስረዳው፡፡
🌹 አባ ጊዮርጊስ ከግዞት ከተመለሰ በኋላ እመቤታችን ተገልጣለት መከራው ሁሉ እንደ ሐዋርያት መሆኑን ገለጠችለት፡፡ አእምሮውን ብሩህ፣ ልቡናውን ትጉኅ የሚያደርግ እጅግ ብዙ ምሥጢርም ነገረችው፡፡ ተሰናብታው ከሄደች በኋላ "እጅግ ብዙ መብራት አቅርቡ አምስት ፈጣን ጸሐፊዎችንም አምጡ" ብሎ አዘዘ፡፡ ከዚህም በኋላ እርሱ እየነገራቸው እነርሱ እየጻፉ እረፍት ሳያደርጉ ሦስት ቀን ሙሉ አጽፎ "መጽሐፈ ምሥጢር" የተሰኘውን መጽሐፍ ፈጸመ፡፡ አምስቱ ጸሐፍትም የየድርሻቸውን አጠናቅቀው በአንድ አደረጉት፡፡ አባ ጊዮርጊስም ይህን ተመልክቶ በእጅጉ አደነቀ፡፡ "እኔ የዚህን መጽሐፍ ቃል አልተናገርኩም፤ መንፈስ ቅዱስ በእኔ አፍ ተናገረ እንጂ" ሲል በወቅቱ መስክሯል፡፡ የመጽሐፉንም ስም "መጽሐፈ ምሥጢር" ብሎ የሰየመው ራሱ ነው፡፡ የጻፈው በ1409 ዓ.ም እድሜው 52 በደረሰ ጊዜ ሲሆን በወቅቱም የዚህ መጽሐፍ ቅጅ በነጋድያን እጅ እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ሄዶ ነበር፡፡
🌹 ዐፄ ይስሐቅ ለአባ ጊዮርጊስ "ምድረ ሰዎን" የተባለውን የጳጳሳት መቀመጫ የነበረውን ሀገር በርስትነት ሰጥቶት ነበር፡፡ አባ ጊዮርጊስ በምድረ ሰዎን ንጉሥ ይስሐቅ ክረምቱን ያሳልፍበት በነበረው ቦታ ላይ ቤተ ክርስቲያን ሠራ፡፡ በዚያም በማስተማርና በጾም በጸሎት ይተጋ ነበር፡፡ በጋሥጫ እያለ ዐፄ ይስሐቅ አስጠራው፡፡ በዚያ ጊዜ ንጉሡ የመናገሻ ማርያምን ቤተ ክርስቲያን አሠርቶ ስለነበር እንዲባርክለት ፈልጎ ነበር፡፡ አባ ጊዮርጊስ ምንም እንኳን በዚያ ጊዜ ታሞ የተኛም ቢሆን ወደ ንጉሡ ተጓዘ፡፡ እዚያ ሲደርስ በጣም ተዳክሞ ነበር፡፡ ሥርዓቱን ለመፈጸምም አቅም አልነበረውም፡፡ ስለዚህም ንጉሥ ይስሐቅ በአልጋ ተሸክመውት እንዲዞሩና ቤተ ክርስቲያኗን እንዲባርካት አድርጓል፡፡ ቡራኬውን ከፈጸመ በኋላ ደቀ መዝሙሮቹን ሰብስቦ "ከሞትኩ አባቴ በጸሎተ ሚካኤል መከራ ወደ ተቀበለባትና እኔም ቤተ ክርስቲያን ወዳነፅኩባት ቦታ ወስዳችሁ ቅበሩኝ" ሲል አዘዛቸው፡፡ ለደቀ መዛሙርቱ በቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ የመጨረሻ የስንብት ትምህርቱን አስተማራቸው፡፡ እነርሱም በአልጋ ተሸክመውት ወደ ጋሥጫ እያመሩ ሳለ በመንገድ ላይ ሐምሌ 7 ቀን 1417 ዓ.ም በ60 ዓመቱ ዐረፈ፡፡ ከአባታችን ከአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎቱ ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።
ወደፊት ራሱን የቻለ በቂና ብዙ ጥናት ማድረግ ሳያስፈልገን እንደማይቀር አመላካች ነው፡፡
🌹 የመጀመርያውን ድርሰቱን አርጋኖንን እመቤታችን አብዝታ ስለወደደችለት ዚማት በሚባለው ሀገር በነበረ ጊዜ "ከድርሰቶችህ ሁሉ እንደ አርጋኖን የምወደው የለም" ብላዋለች፡፡ ከዚህ በኋላ የደረሰው ድርሰት ውዳሴ መስቀል ይባላል፡፡ ቀጥሎም መጽሐፈ ስብሐት ዘመዓልት ወዘሌሊት የተባለውን ወይም እርሱ ራሱ መጽሐፈ ብርሃን ብሎ የሰየመውን መጽሐፍ አዘጋጅቷል፡፡ መጽሐፉም የእግዚአብሔርን የምስጋናውን መንገድ ያበራል፣ አብርቶ ያመለክታልና፣ ልዑላነ ብርሃን የሆኑትን የማኅበረ ቅዱሳንንና የትጉኃንን የምስጋናቸውን መንገድ ያመለክታልና፣ የእመቤታችንንም የምስጋናዋን ጣዕም ይገልጣልና መጽሐፉ "መጽሐፈ ብርሃን" ተባለ፡፡ በዘመኑ በነበረው ልማድ ካህናቱ ቍርባን በሚያቀብሉ ጊዜ ሕዝቡ ወደ ካህናቱ መጥተው ሲቀበሉ ንግሥቲቱ ግን ካለችበት ድረስ ካህናቱ ሄደው ነበር የሚያቆርቧት፡፡ አባ ጊዮርጊስ ግን "ይህ ቁርባን ንጉሠ ነገሥት ነውና ንግሥቲቱ ወደዚህ መጥታ ልትቀበል ይገባታል እንጂ እኛ መሄድ የለብንም" ሲል ተቃወመ፡፡ ይህ ነገር ንግሥቲቱንና አባ ጊዮርጊስን ስላጋጫቸው ዐፄ ዳዊት ችግሩን ለመፍታት አባ ጊዮርጊስን ወደ ሀገረ ዳሞት ንቡረ እድነት ሾሞ ላከው፡፡
🌹 ከዚህ በኋላ አባ ጊዮርጊስ ዋናው ትኩረቱ በድርሰቱ ላይ በማድረግ ወደ ጳጳሱ ወደ አቡነ በርተሎሜዎስ ዘንድ በመሄድ የቅዳሴ ድርሰት ለመድረስ እንዲፈቀድለት ጠይቆ ሲፈቀድለት የቅዳሴ ድርሰት ማዘጋጀት ጀመረ፡፡ አባ ጊዮርጊስ ነገረ ሃይማኖትን ጠንቅቆ የተረዳና የሚያስረዳ ስለነበር በዘመኑ የተነሡ የሃይማኖት ክርክሮች ሁሉ እርሱ ከሌለ አይሳኩም ነበር፡፡ በዚያ ጊዜ በሸዋ በይፋት ራሳቸውን ቤተ እስራኤል እያሉ የሚጠሩ አይሁድ ነበሩ፡፡ ከአቡነ ዜና ማርቆስ ጀምሮ ብዙ መምህራን ወደነዚህ ሕዝቦች እየተሠማሩ ወንጌልን አስተምረዋል፡፡ አቡነ ዜና ማርቆስ ወደ ክርስትና ለተመለሱት ቤተ እስራኤላውያን በእመቤታችን፣ በቅዱስ ሚካኤል፣ በአባ ኖብና በሰማዕቱ በጊጋር ስም አራት አብያተ ክርስቲያናትን አሠርተው ነበር፡፡ ይህ ሁሉ ቢሆንም ቤተ እስራኤላውያኑ ሙሉ በሙሉ ወደ ክርስትና አልተመለሱም ነበር፡፡
🌹 ከእነዚህ አይሁድ መካከል አንዱ ከክርስቲያኖች ጋር በነገረ ሃይማኖት ለመከራከር ጥሪ አቀረበ፡፡ "ክርስቲያኖች ከረቱኝ ወደነርሱ ሃይማኖት እገባለሁ እኔ ከረታኋቸውም ወደኔ ሃይማኖት ይገባሉ" ሲል ነገሩን ጥብቅ አደረገው፡፡ ዐፄ ዳዊት ይህን ጉዳይ ሲሰማ በጣም ስለ ተናደደ ሊቃነ ካህናቱን፣ ንቡራነ እዱንና የመጻሕፍት ዐዋቂዎችን ሁሉ ከየሀገሩ እንዲሰባሰቡ አዘዘ፡፡ ነገር ግን በዚህ ጊዜ አባ ጊዮርጊስ ታሞ አልጋ ላይ ነበር፡፡ አይሁዳዊው በአንድ ወገን መምህራኑ በአንድ ወገን ሆነው ክርክሩን ጀመሩ፡፡ የመጀመርያው እድል የተሰጠው ለአይሁዳዊው በመሆኑ ቀጥሎ ያለውን ጥያቄ አቀረበ፡- "እናንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነው የምትሉት ይሄ ክርስቶስ እውነት የእግዚአብሔር ልጅ ከሆነ፣ ወደ ቢታንያ በመጣ ጊዜ አልዓዛር የተቀበረበትን ቦታ ሳያውቅ ቀርቶ "አልዓዛርን የት ቀበራችሁት?" ብሎ እንደ ጠየቀ በወንጌላችሁ ተጽፏል፡፡ ለዚህ መልስ ስጡኝ፣ እኔንም ከመጽሐፈ ኦሪቴ ጠቅሳችሁ ጠይቁኝ?" ሲል የመከራከርያ ነጥቡን አቀረበ፡፡
🌹 ሊቃውንቱም በዚህ ጊዜ ታሞ አልጋ ላይ የነበረውን አባ ጊዮርጊስን እንዲመጣላቸው ፈልገው "እንዲህ ያለው ነገር ያለ እርሱ አይሆንምና አባ ጊዮርጊስ ይምጣ" ሲሉ ለዐፄ ዳዊት ጥያቄ አቀረቡ፡፡ አባ ጊዮርጊስም በአልጋ ላይ እያለ እንዲመጣ ተደርጎ በአልጋ ላይ ሆኖ በጉባኤው ላይ ተገኘ፡፡ ጉባኤተኞቹ የቀረበውን ጥያቄ በነገሩት ጊዜ አባ ጊዮርጊስ የሰጠውን መልስ እንዲህ የሚል ነው፡- "እኔ ግን በወንጌል ሳይሆን በኦሪት እከራከርሃለሁ፡፡ የምኩራብ መጻሕፍት ሁሉ ለቤተ ክርስቲያን የታወቁ ናቸውና፡፡ ምኩራብ ዘራች ቤተ ክርስቲያንም አጨደችው፤ ምኩራብ ፈተለችው ቤተ ክርስቲያን ለበሰችው፤ አዳምን በገነት ሳለ አዳም ሆይ ወዴት ነህ? ብሎ የጠየቀው ማነው? አብርሃምንስ ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት? ብሎ የጠየቀው ማነው? እስቲ መልስልኝ? ሰይጣንንስ ከወዴት መጣህ? ብሎ የጠየቀው ማነው? እግዚአብሔር አብ አይደለምን?" እያሉ የጥያቄ ዓይነት ባሽጎደጎዱለት ጊዜ አይሁዳዊው መልስ አጥቶ ዝም አለ፡፡ መልስ በማጣቱም አፈረ፡፡ ንጉሡ፣ ሊቃውንቱና መኳንንቱም እጅግ ተደሰቱ፡፡
🌹 አባ ጊዮርጊስ ሌላው ያጋጠመው ክርክር ቢቱ ከተባለው ሰው ጋር ያደረገው ክርክር ነበር፡፡ ቢቱ "በምጽዓት ጊዜ የሚመጣው ወልድ ብቻውን እንጂ አብና መንፈስ ቅዱስ አይመጡም" የሚል ኑፋቄ ማስተማር ጀምሮ ነበር፡፡ ቢቱ ከዚህ ኑፋቄው በተጨማሪ የጥንቆላ ሥራም ይሠራ ነበር፡፡ ቢቱ በጥንቆላ ሥራው የተነሣ በቤተ መንግሥቱ ተቀባይነት የነበረው ሰው ነበረ፡፡ ይህን መሰሉን ተግባር አጥብቆ የተዋጋው ዘርዐ ያዕቆብ እስኪመጣ ድረስ ነገሥታቱ ምንም ክርስቲያኖች ቢሆኑ በዚህ መሰሉ ስንኩል ሕፀፅ ይዋጡ ነበር፡፡ ቢቱና አባ ጊዮርጊስ ወደ ንጉሥ ዳዊት ቀርበው በጉዳዩ ላይ መነጋገር እንደሚፈልጉ ገለጡ፡፡ ዐፄ ዳዊትም ጳጳሱና ሊቃውንቱ ባሉበት እንዲነጋገሩ ስለወሰነ ጳጳሱ እንዲመጡ አዘዘ፡፡ በዚህ ጊዜ ተንኮለኛው ቢቱ ከአባ ጊዮርጊስ ጋር ከተከራከረ እንደሚሸነፍ ስላወቀ "ንጉሡ የአባቶቻችንን ሃይማኖት ክዷልና አትምጣ" የሚል ደብዳቤ በአባ ጊዮርጊስ ስም ጽፎ ጳጳሱን ሊጠሩ በሄዱት መልእክተኞች እጅ ላከ፡፡ ወድያውም ለዐፄ ዳዊት ይህንን ነገር አሳበቀ፡፡ ዐፄ ዳዊትም ፈጣን መልእክተኞች ልኮ የፊተኞቹ መልእክተኞች እንዲመለሱ አደረገና ደብዳቤው ተነበበ፡፡ የቢቱ ተንኮል ያልገባው ንጉሥ ዳዊት ይህን ደብዳቤ ሲመለከት አባ ጊዮርጊስን በደም እስኪነከር ድረስ እንዲደበደብ አድርጎ ወደ እስር ቤት አስገባው፡፡
🌹 ዐፄ ዳዊት እስኪሞትና ልጁ ቴዎድሮስ እስኪነግሥ ድረስም በዚያ ቆየ፡፡ ቢቱ ግን በመልአክ ተቀስፎ ሞተ፡፡ አባ ጊዮርጊስ ግን በወኅኒ ቤት እያለ የከበሩ ቅዱሳን ሐዋርያት ጴጥሮስና ጳውሎስ እየመጡ ያጽናኑት ነበር፡፡ "ውዳሴ ሐዋርያት" የተሰኘውንና ከሐምሌ 5 ጀምሮ በ12ቱም ወራት የሚመሰገኑበት የሐዋርያትን ምስጋና የያዘውን መጽሐፍ ያዘጋጀው በወኅኒ ቤት ሆኖ ጴጥሮስና ጳውሎስ ከጎበኙት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡
🌹 አንድ ጊዜ አባ ጊዮርጊስ በእስር ላይ ሳሉ ንጉሡ ዐፄ ዳዊት መሞታቸው ተሰማ፡፡ ሰዎችም ወደ አባታችን መጥተው "ያሳሰረህ ንጉሥ ሞቷል" በማለት ነገሩት፡፡ ይህንንም ተቻኩለው የነገሩት ያሰረው ንጉሥ መሞቱን ሲሰማ ይደሰታል ብለው ነበር፡፡ ነገር ግን አባ ጊዮርጊስ በታላቅ ሀዘን ውስጥ ሆኖ የሰጣቸው መልስ "አይ ንጉሡ ባይሞት እኔም እንደታሰርኩ ብቀር ይሻል ነበር፡፡ ንጉሡ ዐፄ ዳዊትኮ እኔን ባይወደኝ የአምላክን እናት እመቤታችንን ይወዳት ነበር" አላቸው፡፡
🌹 ዐፄ ቴዎድሮስ አባ ጊዮርጊስን ከወኅኒ ቤት አውጥቶት በጥንቱ ቦታ አስቀመጠው፡፡ አባ ጊዮርጊስ ግን የቤተ መንግሥትን ነገር ለመሸሽ ስለ ፈለገ በጋሥጫ ከመቀመጥ ይልቅ ርቆ ጥንት ወደ ነበረበት ወደ ዳሞት በመሄድ ማስተማር ጀመረ፡፡ ወደ ዳሞት ሲሄድ እግረ መንገዱን ወደ ደብረ ሊባኖስ ገብቶ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን መቃብር ተሳልሟል፡፡ በዚያ ጊዜ የደብረ ሊባኖሱ አበ ምኔት እጨጌ ዮሐንስ ከማ ነበሩ፡፡ እርሳቸውም ሰባተኛው የደብረ ሊባኖስ እጨጌ ነበሩ፡፡ አባ ጊዮርጊስን በዕውቀቱ የሚቀኑበት፣ በችሎታው የሚመቀኙት ሰዎች ነገር ሠርተው ከንጉሥ ቴዎድሮስ ጋር ስላጣሉት እልም ካለ በረሃ እንዲጋዝ ተደረገ፡፡
