uk
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Відкрити в Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Показати більше
637
Підписники
-124 години
-47 днів
-1230 день
Архів дописів
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #የካቲት ፲፪ (12) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮያዊው_ጻድቅ አጽፋቸውን አንጥፈው ዓባይ ወንዝ ለተሻገሩት፣ የንጉሡ ልጅ ሞቶ ሊቀበር ሲሂድ ጥላቸው ሲያርፍበት ከሞት ላስነሱት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ሠርጸ_ጴጥሮስ ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለኢትዮጵያኑ ሰማዕታት (#በ1929ዓ.ም #የካቲት_12_ቀን_ከ30,000 በላይ ኢትዮጵያውያን አባቶች፣ እናቶች፣ ወጣቶችና ሕፃናት በሮማዊው የፋሽስት ጦር ሰማዕትነት ለተቀበሉበት) በዓል በሰላም አደረሰን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_ሠርጸ_ጴጥሮስ፦ የትውልድ አገራቸው ሸዋ ደብረ ጽላልሽ ሲሆን በሕፃንነታቸው ወደ ወሎ ሄደው ሐይቅ እስጢፋኖስ ገብተው ብዙ ተጋድለዋል፡፡ከተጋድሎአቸውም በኋላ በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ እጅ መነኰሱ፡፡ በገዳሙ ብዙ ካገለገሉ በኋላ በመልአክ ትእዛዝ ወደ ጎጃም ሲሄዱ ዓባይን የተሻገሩት አጽፋቸውን አንጥፈው እርሱን እንደ ጀልባ ተጠቅመው ነው፡፡ ጻድቁ ታላቋን ተድባበ ማርያምን ለ41ዓመት አጥነዋል፡፡ ❤ የንጉሡ ልጅ ሞቶ ሊቀብሩት ሲወስዱት የአቡነ ሠርጸ፡ጴጥሮስ ጥላቸው ቢያርፍበት ከሞት አፈፍ ብሎ ተነሥቶ ድኖ "አምላከ አቡነ ሠርጸ ጴጥሮስ" ብሎ ፈጣሪውን አመስግኗል፡፡ ጻድቁ ሲያርፉም መቋሚያቸው አፍ አውጥታ ተናግራለች፤ ርዕደተ መቃብራቸው ሲፈጸምም እንባ አፍስሳ አልቅሳላቸዋልች፡፡ ይህቺ ተአምረኛ መቋሚያቸው ዛሬም ጎጃም ውስጥ መካነ መቃብራቸው ባለበት በደብረ ወርቅ ገዳም ትገኛለች፡፡ ጻድቁ ደብረ ወርቅ ገዳምን እንደ መሶብ አንሥተው አስባርከዋታል፡፡ አቡነ ሠርፀ ጴጥሮስ የካቲት12 ቀን ያረፉ ሲሆን ዐፅማቸውም በታላቋ ደብረ ወርቅ ይገኛል፡፡ ከሰማይ የወረደላቸው የወርቅ መስቀላቸውም በዚያው ይገኛል፡፡ጸበላቸው እጅግ ፈዋሽና ኃይለኛ ከመሆኑም በላይ በሰውነት ውስጥ የሚገኝ በሽታንና አጋንንትን የሚያስወጣበት መንገድ ለየት ያለው፡፡ ከአቡነ ሠርጸ ጴጥሮስ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።                

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #የካቲት ፲፪ (12) ቀን። ❤ እንኳን #ለመላእክት_አለቃ ለከበረ #ለቅዱስ_ሚካኤል ወደ ረዓይታዊ ወደ ሶምሶን ተልኮ ኃይልን ሰጥቶት ጠላቶቹን ድል እንዲያደርግ ለረዳበት ወራዊ መታሰቢያ በዓል፣ ተጋዳይ ፍጹም የዋሕና ትሑት ለሆነው ለከበረ አባት #ለአባ_ገላስዮስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ #ከዶርቃስ ከመታሰቢያው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #የከበረ_ቅዱስ_ሚካኤልን በዚች ዕለት እግዚአብሔር ወደ ረዓይታዊ ወደ ሶምሶን ላከው የፍልስዔም ሰዎች ሊገድሉት በጠላትነት በተነሡበት ጊዜ ድል እስከ አደረጋቸውና እስከ ገደላቸው ድረስ ረዳው ኃይልንም ሰጥቶ በአህያ መንጋጋ ከእርሳቸው አንድ ሺህ ሰዎችን ገደለ። ተጠምቶም ለሞት በተቃረበ ጊዜ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ተገለጠለትና አጸናው እግዚአብሔር ከአህያ መንጋጋ አጥንት ውኃን አፈለቀለትና ጠጥቶ ዳነ። ❤ ዳግመኛም ከሚስቱ ጋር ተስማምተው ዐይኖቹን አሳውሩ የራሱንም ጠጒር ላጩ አሠሩትም ከዚያም በኋላ ለጣዖቶቻቸው በዓልን በአዘጋጁ ጊዜ ሶምሶንን ወደ ጣዖቶቻቸው ቤት ወሰዱት በዚያም ሦስት ሽህ ያህል ሰዎች ተሰብስበው ነበር የከበረ ቅዱስ ሚካኤልም ተገለጠለትና ኃይልን መላው የዚያንም ቤት ምሰሶዎች ነቀላቸው ቤቱም በላያቸው ወድቆ ከእርሱ ጋር ሁሉንም ገደላቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                                                         ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ገላስዮስ፦ የዚህ ቅዱስ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ምዕመናን ናቸው በጥበብንና የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተማሩትና ዲቁና ተሾመ። ከታናሽነቱም ጀምሮ ይህን ዓለም ንቆ ተወ የክብር ባለቤት የሆነ የክርስቶስንም ቀንበር በመሸከም በምንኵስና ሁኖ በትጋት እየጾመ እየጸለየና እየሰገደ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ እግዚአብሔር መርጦት በአስቄጥስ ገዳም ባሉ መነኰሳት ላይ ቅስና ተሾመ። ተጋድሎውንና አገልግሎቱን እየፈጸመ ሳለ ለአባ ጳኵሚስ እንደ ተገለጠ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለትና መነኰሳትን ሰብስቦ ፈሪሀ እግዚአብሔርን የምንኵስናንም ሕግ ያስተምራቸው ዘንድ አዘዘው በዚያንም ጊዜ ብዙዎች መነኰሳትን ሰበሰበ መንፈሳዊ የሆ የአድነት ማኅበርራዊ ኑሮንም ሠራላቸው እርሱ በመካከላቸው እንደ መምህር አልሆነም ከእርሳቸው እንደሚያንስ አገልጋይ እንጂ። ❤ ይህ አባት የዚህ ዓለም ጥሪት ሁሉ ንቆ የተወ ሆነ እጅግም የዋህና ቸር ሆነ ከብሉይና ከሐዲስ መጻሕፍቶችም የተሰበሰበ አንድ ታላቅ መጽሐፍን አጻፈ ለማጻፊያውም ዋጋ ዐሥራ ስምንት የወርቅ ዲናር አወጣ ከርሱ ሊጠቀሙ በሚፈልጉ ጊዜ መነኰሳቱ እንዲያነቡት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአትሮንስ ላይ አኖረው። አንድ መጻተኛ ሰውም አረጋዊ አባ ገላስዮስን ሊጎበኝ በገባ ጊዜ ያንን መጽሐፍ አየውና አማረው በጭልታም ከዚያ ሰርቆ ወጣ ወደ ከተማ ውስጥም በገባ ጊዜ ሊሸጠው ወደደ አንድ ሰውም ዋጋው "ምን ያህል ነው" አለው እርሱም "ዐሥራ ሰባት የወርቅ ዲናር ስጠኝ" አለው። ያ የሚገዛውም ሰው "ያልከውን እሰጥሃለሁ ነገር ግን ለወዳጄ እስካሳየው ታገሰኝ" አለው ያሳየውም ዘንድ ወደ አባ ገላስዮስ ወሰደውና "ተመልከትልኝ መልካም ከሆነ እገዛዋለሁ" አለው አባ ላስዮስም "ያመጣውን ሰው ከአንተ ምን ያህል ፈለገ" አለው "ዐሥራ ሰባት የወርቅ ዲናር" አለው ቅዱስ ገላስዮስም "መጽሐፉ መልካም ነው ዋጋውም ቀላል ነው ግዛው" ብሎ መለሰለት። ወደ ሌባውም በተመለሰ ጊዜ አባ ገላስዮስ የነገረውን ሠውሮ "ለአባ ገላስዮስ አሳየሁት እርሱም ዋጋው በዝቷል አለኝ" አለው፡ሌባውም "ያ ሽማግሌ ሌላ የተናገረህ ነገር የለምን" አለው "አዎን የለም" አለው። ሌባውም "እንግዲህ እኔ አልሸጠውም" ብሎ ወደ አባ ገላስዮስ ሒዶ ከእግሩ በታች ወድቆ ለመነው "ሰይጣን አስቶኛልና ይቅር በለኝ መጽሐፍህንም ውሰድ" አለው የከበረ ገላስዮስም "እኔ መጽሐፉን መውሰድ አልሻም" አለው። ሌባውም በፊቱ እያለቀሰና እየሰገደ ብዙ ለመነው በብዙ ድካምም መጽሐፉን ተቀበለው ማንም ያወቀ የለም። እግዚአብሔር ትንቢት የመናገርን ሀብት ሰጥቶት ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ። ❤ በአንዲትም ዕለት ለገዳሙ መነኰሳት ዓሣ አመጡ ባለ ወጡ ዓሣን አብስሎ በቤት ውስጥ አኑሮ አንዱን ብላቴና ጠባቂ አድርጎ ወደ ሥራው ሔደ ብላቴናውም ከዚያ ዓሣ በላ። ባለ ወጡ በመጣ ጊዜ ተበልቶ አገኘውና በብላቴናው ላይ ተቆጥቶ "አረጋዊ አባቶች፡ ሳይባርኩት እንዴት ደፍረህ በላህ" አለው የቊጣ መንፈስም በልቡ አደረና ብላቴናውን ረገጠው ወዲያውኑ ሞተ እንደሞተም አይቶ ደነገጠ ታላቅ ፍርሀትንም ፈራ ሒዶ ለአባ ገላስዮስ የሆነው ሁሉ ነገረው እርሱም "ወስደህ ከቤተ መቅደሱ ፊት አስተኛው" አለው ሰውየውም እንዳዘዘው አደረገ ወደ ማታ ጊዜም አረጋውያን መነኰሳት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተሰብስበው የማታውን ጸሎት አድርሰው ወጡ አረጋዊ አባ ገላስዮስም በወጣ ጊዜ የሞተው ብላቴና ተነሥቶ በኋላው ተከተለው ከመነኰሳትም ማንም አላወቀም እርሱም የገደለውን ባለ ወጥ ለማንም እንዳይናገር አዘዘው። ❤ የተመሰገነ አባ ገላስዮስም ያማረ ትሩፋቱንና ተጋድሎውን ፈጽሞ አድርሶ እግዚአብሔርንም አገልግሎ ይህንንም በጎ መታሰቢያን ትቶ ከዚህ ከኃላፊው ዓለም የሚለይበት ሲደርስ የካቲት12 በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ገላስዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦የየካቲት12 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ይትዐየን መልአከ እግዚአብሔር ዐውዶሙ። ለእለ ይፈርህዎ ወያድኅኖሙ። ጠዐሙ ወታእምሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር"። መዝ 33፥7-8። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 25፥31-ፍ.ም።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወበኀቤየሰ ፈድፋደ ክቡራን አዕርክቲከ እግዝኦ። ወፈድፋደ ፀንዑ እምቀደምቶሙ። እምኌቆሙ እምኆፃ ይበዝኁ"።  መዝ 138፥17-18። የሚበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 5፥6-ፍ.ም፣ ይሁ 1፥9-19 እና የሐዋ ሥራ 28፥30-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 20፥24-29። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ሚካኤል በዓል፣ የአቡነ ሠርጸ ጴጥሮስ የዕረፍት በዓልና የጾም ወራት ለሁላችንም ይሁንልን።                  

                           ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እስመ ዚአየ ውእቱ ኵሉ አራዊተ ዘገዳም። እንስሳ ገዳምኒ ወአልሕምት። ወአአምር ኵሎ አዕዋፈ ሰማይ"። መዝ 49፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ጢሞ 4፥14-19፣ ያዕ 3፥5-11 እና የሐዋ ሥራ 14፥19-ፍ.ም የሚነበበው ወንጌል ማር 1፥12-16። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ወራት ለሁላችን ይሁንልን።               

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #የካቲት ፲፩ (11) ቀን። ❤ እንኳን #ለተጋዳይ_ለታላቁ አባት በቀንና በሌሊት ሰባት መቶ ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን ከስግደት ጋር እየጸለ ለአርባ ዓመት በገዳም ለኖረውና በኋላም ወደ በረሃ ከአንዲት ታናሽ ዋሻ ውስጥም ገብቶ እየተጋደለ ብቻውን ለኃምሳ ዓመት ለኖረ፤ ሁለት አንበሶች እንደሰው ለሚላኩለት #ለባለ_አንበሳው_ለአባ_አውሎግ ለዕረፍት በዓል፣ ለሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ለከበረ ለአባት #ለአባ_በላትያኖስ በንጉሥ ዳኬዎስ እጅ ለአንድ ዓመት ያህል ተሰቃይቶ ኋላም አንገቱን በመሰየፍ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና #ለአባ_ስልዋኖስ ረድእ #ለአባ_በትራ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከኤጲስቆጶስ #ከአባ_አብርሃም_ከመነኰስ_ከአባ_መቃቢስና #ከኮንቲ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ  ረድኤትና በረከት ያሳትፈን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #ባለ_አንበሳው_አባ_አውሎግ፦ የዚህ ቅዱስ ወላጆች ፍጹም በወርቅና በብርም የበለጸጉ ናቸው። በአንዲትም ዕለት "አውሎግ ያለህን ገንዘብህን ሁሉ ሽጠህ ለድኆች ሰጥተህ መከራ መስቀሉን ተሸክመህ ና ተከተለኝ" የሚለውን የከበረ የወንጌልን ቃል አሰበና ወዲያውኑ ገንዘቡን ሁሉ ለድኆችና ለችግረኞች በትኖ ወደ አባ አውሎጊን ሔደ እርሱም በደስታ ተቀበለው። ስለ እርሱ እንዲህ የሚለውን ራእይ አይቶ ነበር "እነሆ ወዳንተ ጐልማሳ ይመጣል ተቀበለውና ከሚያገለግሉ መነኰሳት ጋር ቀላቅለው"። እየፈተነውም ሦስት ዓመት ያህል ኖረ ፍጹም የሆነ ቅድስናውንም በአየ ጊዜ የምንኵስናን ልብስ የመላእክትንም አስኬማ አለበሰው። ከሰንበትም እስከ ሰንበት እየጾመ በብዙ ተጋድሎ ኖረ ምግቡም እንጀራና ጨው ነበረ በቀንና በሌሊትም ሰባት መቶ ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን ስግደት ጋር ይጸልያል በዚህም ተጋድሎ አርባ ዓመት ኖረ። ❤ ከዚያም በኋላ ያሰናብተው ዘንድ መምህሩ አባ አውሎጊንን ማለደውና ወደ በረሀ ሔደ ከአንዲት ታናሽ ዋሻ ውስጥም ገብቶ እየተጋደለ ኃምሳ ዓመት ኖረ። ለፍላጎቱም የሚያገለግሉት ሁለት አንበሶችን እግዚአብሔር ሰጠው በአንዲትም ዕለት ታመመ አንሶቹንም "እጠጣ ዘንድ የሞቀ ውኃ እሻለሁ" አላቸው። አንዱ አንበሳም ወደ ተራራ ሒዶ እረኛ አግኝት ወደ አባ አውሎግ አመጣው በአየውም ጊዜ ሰገደለትና "አባቴ ሆይ ምን ትሻለህ" አለው እርሱም "የሞቀ ውኃ ታጠጣኝ ዘንድ እሻለሁ" አለው እንዳለውም አደረገለት ከዚህም በኋላ አንበሳው እረኛውን ወደ ቦታው መለሰው። ያም እረኛ "ለእግሩ ተረከዝ ዓለሙ ሁሉ መጠኑ የማይሆን ጻድቅ ሰው አገኘሁ" ብሎ ለሰው ሁሉ ተናገረ በሰሙ ጊዜም ሰዎች ሁሉ ወደርሱ ተሰበሰቡ፡ በሽተኞችንም ሁሉ አመጡለትና ፈወሳቸው። ❤ በዚያም ወራትም መምህሩ አባ አውሎጊን ጣዖትን የሚያመልኩ የፋርስ ሰዎችን ወደ ቀናች ሃይማኖት ለመመለስ ወደ ፋርስ አገር ሊሔድ ፈለገ ዳግመኛም ልጁ አውሎግን ከእርሱ ጋር ሊወስደው ወደርሱ መልክተኛ ሊልክ ሽቶ ሳለ መንፈስ ቅዱስ አንበሳውን አስገነዘበውና አጽፉንና ወንጌሉን አንሥቶ ተሸከመ። አባ አውሎግንም ጒዞን አመለከተው ተነሥቶም አንበሳውን ተከትሎ ወደ መምህር አውሎጊን ደረሰ እርሱም በደስታ ተቀበለው። ሲጓዝም ከጤግሮስ ወንዝ ደረሱ ውኃውም ተከፍሎላቸው ተሻገሩ ወደ አገሩም ውስጥ በደረሱ ጊዜ አስተማሩአቸው ወደ ቀናች ሃይማኖትም መለሷቸውና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቋቸው። ❤ በአንዲትም ዕለት ደግሞ ቅዱሳን በተራቡ ጊዜ ምግባቸውን ይፈልጉላቸው ዘንድ አባ አውሎግ አንበሶችን አዘዘ ሒደውም እንጀራ በአህያ ላይ ጭኖ የሚጓዝ ሽማግሌ አገኙ ሕፃንም ከእንጀራው ጋር አለ። አህያውንም ወደ ቅዱሳን አመጡት ከድንጋጤም የተነሳ ብላቴናው ሞተ ቅዱሳንም ጸልየው ሕፃኑ ድኖ ተነሣ ቅዱሳንም ተመገቡ አንቦሶችም አህያውን ከእንጀራውና ከሕፃኑ ጋር ወደ ሽማግሌው መለሱት። ❤ ከዚህም በኋላ አባ አውሎግ ወደ በዓቱ ተመለሰና ጥቂት ታሞ የካቲት11 በሰላም ዐረፈ። በታላቅ ክብርም ተቀበረ እነዚያ አንበሶችም መቃብሩን እየጠበቁ ዐሥራ ሁለት ዓመት ኖሩ ከዚያም በኋላ ወደ ዱር ገቡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አውሎግ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_በላትያኖስ፦ ይህም ቅዱስ ብልህና አዋቂ የሆነ ታላቅ ተጋድሎን የሚጋደል ነው በሮሜ አገርም ሊቀ ጵጵስና ተሹሞ በቅዱስ ጴጥሮስ ወንበር ላይ ዐሥራ ሁለት ዓመት በሰላም ኖረ ሕዝቡን የቀናች ሃይማኖትን እያስተማራቸው ሳለ መኰንኑ ፊልጶስ በንጉሥ ቀላውዴዎስ ላይ ተነስቶ በገደለው ጊዜ በርሱ ፈንታ ነገሠ በምእመናን ላይ ታላቅ መከራን አመጣ በዚህ በንጉሥ በዳኬዎስ እጅ ብዙዎች በሰማዕትነት ሞቱ። በዘመኑም ሰባቱ ደቂቅ ከእርሱ ሸሹ ሦስት መቶ ሰባ ሁለት ዓመት ተኝተው ነቁ እርሱም በኤፌሶን ከተማ መስጊድ ሠርቶ በውስጡ ጣዖታትን አኖረ ሰዎችን ሁሉ ለጣዖታት እንዲሠዉ አስገደዳቸው ለጣዖታት ያልሠዉትንም ገደላቸው። ❤ ይህ የከበረ በላትያኖስም የጣዖታት አምልኮን እንደሚቃወም ሕዝቡም በክብር ባለቤት በክርስቶስ ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ እንደሚያስተምር ንጉሥ በሰማ ጊዜ ወደ ሮሜ አገር ልኮ ወደ ኤፊሶን ከተማ አስመጣውና ለጣዖታት እንዲሠዋ ለመነው። እርሱም ግን ቃሉን አልሰማም ተሣለቀበት አማልክቶቹንም ረገመ እንጂ ንጉሥም ተቆጣ አንዲት ዓመት ያህልም ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃየው ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ የካቲት11 ቀን በሰይፍ ራሱን ቆረጠው የምስክርነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም  በአባ በላትያኖስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን።                             + + + ❤ የአባ ስልዋኖስ ረድእ አባ በትራ፦ ይህም ቅዱስ በደብረ ሲና ካለች በዓቱ በነበረ ጊዜ ትርኅምትን ይጠብቅ ነበር በራትም ጊዜ ለሥጋው የሚያሻውን ይመገባል። ፈርኑ በሚባል አገር ላይ ኤጲስቆጶስ በአደረጉት ጊዜ ትርኅምትን በማብዛት ሰውነቱን እጅግ አደከመ ደቀ መዛሙርቱ "አባታችን ሆይ በገዳም በበአትህ በነበርክ ጊዜ ትርኅምትን እንዲህ አላበዛህም ነበር" አሉት ይህም አባት እንዲህ አላቸው "ያን ጊዜ በገዳም በችግር ውስጥ ነበርኩ ዛሬ ግን ከብዙዎች መካከል በአንድነት አለሁ የምሻውም ሁሉ ብዙ አለኝ ነገር ግን ሥጋዬን ቀጥቼ ብገዛው ይሻላል" እንዲህም እየተጋደለ ኖረ ከዚህም በኋላ የካቲት10 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ በትራ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የየካቲት 11 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለበትራ_ረድአ_ስልዋኖስ_ወምእኑ። ኤጲስቆጶሰ ዘኮነ በሀገረ ፈርኑ። ከመ እንግር ጽድቆ ወኂሩቶ እዜኑ። ለአፉየ ወልሳንየ በመጠኑ። ዘይረድአኒ መንፈሰ ይፈኑ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የካቲት_11።

ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስቆጶሳት የተላኩ መልክቶች ናቸው ወደ ምእመናንም ወንዞች ውኃዎችን እንደሚያፈልቁ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ የሚያፈልቃቸው ሆኗልና። ❤ ይህንንም በጎ ሥራውን ሲፈጽም መልካም ጉዞውንም አከናውኖ ወደ በጎ ሽምግልና ደርሶ እግዚአብሔርንም አገልግሎ የካቲት10 በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም  በቅዱስ ኤስድሮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #የፋርስ_አገር_ኤጲስቆጶስ_አባ_ፊሎ፦ ይህንንም ቅዱስ ለእሳት እንዲሠዋ ለፀሐይም እንዲሰግድ የፋርስ ንጉሥ አዘዘው እምቢ በአለውም ጊዜ ታላቅ ሥቃይን አሠቃይቶ የካቲት10 ቀን ራሱን በሰይፍ ቆረጠው በመንግሥተ ሰማያት የሰማዕትነት አክሊል ተቀበለ። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይገባል አሜን። ምንጭ፦ የየካቲት10 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_እብል_ዕረፍተ_ስሙ_ጽዑጠ። እምብዝኀ ገድሉ እንዘ እንግር ኅዳጠ። ዐሠረ ክርስቶስ ይትሉ #ሶበ_ዮስጦሳ_ተፈልጠ። መንገለ ወልዱ ወብእሲቱ ገጾ ኢሜጠ። ወአፍቅሮ ዘመድ ካዕበ በልቡ ኤሦጠ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_10።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "አስተጋብዑ ሎቱ ጻድቃን። እለ ይገብሩ መሥዋዕተ ዘበሕጉ። ይነግራ ሰማያት ጽድቀ ዚአሁ"። መዝ 49፥5-6። የሚነበበው ወንጌል ማር 6፥30_34።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦"አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ። ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ። ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ"። መዝ 18፥3-4። የሚነበቡት መዕልክታት 1ኛ ቆሮ 12፥4-28፣ ይሁ 1፥17-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 1፥12-15። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥1-9። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የሐዋርያም የቅዱስ ያዕቆብ የዕረፍት በዓልና የጾም ወራት ለሁላችንም ይሁንልን።              

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #የካቲት ፲ (10) ቀን። ❤ እንኳን #ከዐሥራ_ሁለቱ_ሐዋርያት ለአንዱ ለእልፍዮስ ልጅ #ለከበረ_ሐዋርያ_ለቅዱስ_ያዕቆብ በንጉሥ ቀላውዴዎስ ዘመን በአይሁድ እጅ በድንጋይ ተወግሮ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል፣ #ለኢትዮያዊያኑ_ጻድቅ_ለአቡነ_እንድርያስ ኤርትራ አገር የሚገኘው ታላቁ ገዳም ደብረ ጽጌ ሰፍኣ ለመሰረቱ #ለዘጠኝ_መቶ_ዘጠና_ዘጠኝ_ደቀ_መዛሙርቶች በአረማውያን እጅ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል (ታሪካቸውን የካቲት1 ይመልከቱ)፣ ለንጉሥ ኑማርያኖስ ልጅ ለከበረ #ለቅዱስ_ዮስጦስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል፣ ፈርማ ከሚባል አገር በገድል ለተጠመደ ምሁር ለሆነ ዐሥራ ስምንት ሺህ መጽሐፍቶችን ተግሣጻትና ድርሳናት ለጻፈ ለዓለሙ ሁሉ #መምህር_ለአባ_ኤስድሮስ ለዕረፍት በዓልና ለፋርስ አገር ኤጲስቆጶስ #ለአባ_ፌሎ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ #ቅዱሳን_ከኒቅላዎስና_ከስምዖን ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ያዕቆብ_ወልደ_እልፍዮስ፦ ያስተምር ዘንድ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ እንዲህ ሆነ። ከእርሱ ለሚሰሙትም ሁሉ ብዙ ተአምራትን አደረገ። ንጹሕ በሆነ ልቡናም በእግዚአብሔር አመኑ። ራሳቸውንም አጸኑ። ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብም በልቡናው አሰበ። እንዲህም አለ። ሕዝቡ ከእርሱ ሰምተው እንዴት ያምናሉ አለ። እርሱም ሕዝቡ ወደተሰበሰቡበት ወደ ምኩራብ ገባ። ከአይሁድም የተቀመጡ የተሰበሰቡ ብዙ ሰዎችን አገኘ። በፍጹም ታላቅ ደስታ ያስምራቸው ዘንድም በመካከላቸውም ገባ። ለሁሉም በቃሉ ማስተማሩን አበዛ። ያለመፍራትም ሃይማኖቱን ገለጠ። አንድ ለሆነው ለእግዚአብሔር ልጅ ምስክር ሆነ። "የሕይወት ቃል ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለም ሁሉ አምላክ ነው። በእውነትም የእግዚአብሔር ልጅ ነው። እርሱ ዓለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ ከአብ ጋር ነበርና። እርሱ በአብ አለ፤ አብም በእርሱ አለ። እርሱ የአብ ቃል ነው። እርሱ ሰውን በአርአያችንና በምሳሌያችን እንፍጠር አለ። እርሱ በሰማይ አለ። እርሱ ከአባቱ ጋር አለ። እርሱ በኪሩቤል ሰረገላ ይቀመጣል። ሱራፌልም ያመሰግኑታል። እርሱ በድንግል ማርያም ማሕፀን የተወሰነ በልዕልና በገናንነቱ ሥልጣን ነው። እርሱ ድንግል ማርያም የወለደችው ጌታችን እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ሰው የሆነ አምላክ ነው"። አንድ ሰው ስንኳን ሳይፈራ በተሰበሰቡት መካከል የሐዋርያው ምስክርነት ይህ ነበር። በእውነት አንድ ለሆነው ለእግዚአብሔር ልጅ ልደትም ምስክር ሆነ። እርሱ ነበርና። በሞቱም፣ በትንሣኤውም፣ ወደ አባቱ ወደ ሰማይ ስለማረጉም ምስክ ሆነ። ለተሰበሰቡትም በክርስቶስ ስለማመን አስተማራቸው። ❤ የተሰበሰቡትም የሐዋርያውን ትምህርት በሰሙ ጊዜ ከእርሱ ጋር ካለው ከአባታቸው ከሰይጣን የተነሳ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ላይ ፈጽመው ተቆጡ። ሁሉም ተሰብስበው ተቀመጡ። የተሰበሰቡት ሁሉ ደሙን ፈለጉ። ነገሩን የሰሙትም የተባረከ ሐዋርያን ያዙት። ከንጉሥ ከቀላውዴዎስም ወሰዱት። የሐሰት ምስክሮችንም በእርሱ ላይ አስነሡ። ለንጉሡም "ይህን ጥፋተኛ ሰው በሀገሩ በአውራጃው ይዘናል" አሉት፤ "እኔ የእግዚአብሔር የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ነኝ ይላቸዋል። ለንጉሡ እንዳይገዙም ይከለክላል" አሉት። ስለተባረከው ሐዋርያ ይህን ነገር በሰማ ጊዜም እስከሚሞት ድረስ በድንጋይ ይወግሩት ዘንድ አዘዘ። አይሁድንም እግዚአብሔር ረገማቸው። ንጉሡ አይሁድን እንዳዘዛቸውም በድንጋይ ወገሩት። ከዚህ በኋላ ቡሩክ የሚሆን የእልፍዮስ ልጅ የሐዋርያው የቅዱስ የያዕቆብ ምስክርነት የካቲት ዐሥር ቀን ሆነ። በኢየሩሳሬም ቤተ መቅደስ ተቀበረ። ለአብ ለወልድና ለመንፈስ ቅዱስ ክብር ምስጋና ይገባል። ከሐዋርያው ከቅዱስ ያዕቆብ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። ምንጭ፦ ገድለ ሐዋርያት።                                                       ✝ ✝ ✝ ❤ #የንጉሥ_ኑማርያኖስ_ልጅ_ሰማዕቱ_ቅዱስ_ዮስጦስ፦ ይህም ቅዱስ በጦር ሜዳ እያለ እኅቱ ከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስን አግብታ ንጉሥም አደረገችው ከጦርነትም በተመለሰ ጊዜ የክብር ባለቤት ክርስቶስን ዲዮቅልጥያኖስ ክዶ አገኘውና እጅግ አዘነ። የአገሩም ሰዎች በአዩት ጊዜ ወደርሱ ተሰብስበው ዲዮቅልጥያኖስን "እኛ እንገድለዋለን አንተም ጌታችን በመንግሥትህ ዙፋን ላይ ትቀመጣለህ" አሉት እርሱ ግን ይህን ስለአልፈለገ እንዳይገድሉት ከለከላቸው ከምድራዊት መንግሥት ሰማያዊት መንግሥትን መርጧልና። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ቀርቦ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ ንጉሡም ፈርቶታልና "ጌታዬ ዮስጦስ ሆይ ይህን ታደርግ ዘንድ ያስገደደህ ማነው?" አለው የከበረ ዮስጦስም "በምስክርነቴ ደሜን እንዳፈስ ካልጻፍክ ሕዝቡን በአንተ ላይ አስነሥቼ ከመንግሥትህ እንደማስወጣህ የክብር ባለቤት ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሕያው ነው" ብሎ ማለ። በዚያንም ጊዜ ንጉሡ ፈርቶ ከሚስቱ ከታውክልያ ከልጁ ከአቦሊ ጋር ወደ ግብጽ አገር እንዲወስዱአቸው አዘዘ የእስክንድርያንም ገዥ አብዝቶ እንዲሸነግላቸው ምናልባት ልባቸው ቢመለስ እንዳያሳዝናቸውም አለዚያ እያንዳንዱን እንዲለያያቸው አዘዘው። ❤ ወደ ግብጽ አገርም በደረሱ ጊዜ ከእርሳቸው ጋር የንጉሥ ደብዳቤ አገልጋዮችም አሉ። የእስክንድርያም ገዥ በአያቸው ጊዜ እጅግ ፈራ ሊሸነግለውም ጀምሮ ቅዱስ ዮስጦስን "ጌታዬ እንዲህ አታድርግ ክብርህ ይሻልሃል" አለው የከበረ ዮስጦስም "ነገር አታብዛ" አለው መኰንኑም ፈርቶ ቅዱስ ዮስጦስን ወደ ላይኛው ግብጽ ወደ እንዴናው ከተማ ሰደደው ልጁ አቦሊን ወደ አገረ ብስጣ ሚስቱ ታውክልያን ወደ አገረ ፃ ላካቸው ከአገልጋዮቹም የሚአገለግሏቸው አንዳንድ ሰጣቸው የከበረ ዮስጦስንም በእንዴናው ከተማ ብዙ ከአሠቃዩት በኋላ የካቲት10 ቀን ራሱን ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ ከሥጋውም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ ለበሽተኞችም ታላቅ ፈውስ ሆነ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕትነት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ኤስድሮስ_ዘአገረ_ፈርማ፦ የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ በምስር አገር የከበሩ ባለጸጎች ናቸው ለእስክንድርያ ሊቀነ ጳጳሳትም አባ ቴዎድሮስና አባ፡ ቄርሎስ ዘመዶች ናቸው ከእርሱም በቀር ልጅ የላቸውም መንፈሳዊ ትምህርትን ሁሉ የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍት ሁሉ አስተማሩት ግልጽ አድርጎ አጠናቸው ጠበቃቸውም ዳግመኛም የዮናናውያንን የፍልስፍና ትምህርት የከዋክብትን አካሔድና ዓለምን መዞራቸውን ተማረ በእውቀቱና በጥበቡም ከብዙዎች ከፍ ከፍ አለ በገድልም የተጠመደ ትሑትና የሚተጋ ሆነ። ❤ በአገሮችም ያሉ ሰዎች ስርሱ በሰሙ ጊዜ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ ተማክረው ከኤጲስቆጶሳቱ ጋር ተስማሙ። በሌሊትም ወጥቶ ሸሸ ወደ ፈርማ ገዳም ደርሶ በዚያ መነኰሰ ከዚያም ወጥቶ ወደ አንዲት አነስተኛ ወሻ ገብቶ ብቻውን በውስጧ ብዙ ዘመናት ኖረ ብዙ ድርሳናትንና ተግሣጻትንም ደረሰ ከእርሳቸውም ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንት የደረሳቸው አሉ የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍቶችን ብሉያትና ሐዲሳትን ተረጐመ። የመጻሕፍትም ቊጥራቸው ዐሥራ ስምንት ሺህ ነው እሊህም ድርሳናት ተግሣጻት ጥያቄዎችና መልሶች ወደ

መልአኩን ሱርያን ላከ እርሱም በክብር ባለቤት ክርስቶስ ስም የሚደርስበትን ሥቃይ ሁሉ ነገረው "እነሆ ከአንተ ጋር እንድኖር እንዳጸናህም እግዚአብሔር አዞኛልና አትፍራ" አለው። ❤ በዚያንም ጊዜ ተነሥቶ ወደ እንዴናው ከተማ ሔደ በመኰንኑም ፊት ቁሞ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ መኰንኑም ልብሱን አራቁተው ይገርፋት ዘንድ አዘዘ። ይህንንም አደረጉበት ከዚህም በኋላ በጐኖቹ ውስጥ መብራቶችን አስገብተው ለበለቡት እሳት ግን አልነካችውም መኰንኑም ለጣዖት እንዲሰግድ ብዙ ገንዘብ አመጣት የተመሰገነ ጳውሎስም "ወላጆቼ ሲሞቱ ዐሥራ ሰባት የወርቅ መክሊት ትተውልኝ ነበር። ስለ ክብር ባለቤት ክርስቶስ ፍቅር ትቼ ለድኆች መጸወትኩት ወደዚህ ወደተናቀ ገንዘብህ እንዴት እመለሳለሁ" አለው። ❤ መኰንኑም ሰምቶ ብረቶችን በእሳት አግለው በአፉና በጆሮዎቹ እንዲጨምሩ አዘዘ ይህንንም አደረጉበት ሱርያል መልአክም ወርዶ ዳሠሠውና አዳነው ሁለተኛም እባቦችን በላዩ ሰደዱ አልነኩም ምላሱንም ቆረጡ ጌታችንም አዳነው። መኰንኑም ወደ እስክንድርያ ከተማ በሚሔድ ጊዜ ከእርሱ ጋር ወሰደው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመርከብ ውስጥ ተገለጠለትና አጽናናው የዚህም ቅዱስ ኤሲም የሚባል ወዳጅ አለው እኅቱ ቴክላም። በጌታችንም ሥጋው ከሥጋቸው ነፍሱ ከነፍሱሳቸው ጋር እንደሚሆን ነገረው ያን ጊዜ እሊህ ቅዱሳን በእስክንድርያ ከተማ በእስር ቤት ነበሩ የከበረ ጳውሎስም ወደርሳቸው በደረሰ ጊዜ እርስበርሳቸው  ተሳሳሙ በመገናኘታቸውም ነፍሳቸው ደስ ብሏት እግዚአብሔርን አመሰገኑት። ❤ መኰንኑም ወደ እንዴናው ከተማ በሚመለስ ጊዜ የቅዱስ ጳውሎስን ራስ ቆርጠው ሥጋውን ከጥልቅ ባሕር ወረወሩ የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ ምእመናንም ሥጋውን በሥውር ወስደው በአማሩ ልብሶች ገነዙት በእርሱም ዘንድ አኖሩት ከእርሱም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕቱ በቅዱስ ጳውሎስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የየካቲት 9 ስንክሳር።                              ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለጳውሎስ ቅሡፈ ዘባን በተጠብጥቦ። ወበመኃትወ ነድ ውዑየ ገቦ። #ሱርያል_መልአክ እንዘ ይሜግቦ። በድሮ ፈጺሞ ወሃይማኖቶ ዐቂቦ። ዘምስለ ኤሲ ወቴክላ ተወፈየ ዐስቦ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_ 9።                                    

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #የካቲት ፱ (9) ቀን። ❤ እንኳን #ለከበረ_በሶርያ_አገር ላሉ መነኰሳት አባት ለሆነ እንደ ኢያሱ ፀሓይን ገዝቶ ላቆመ፣ ዝናብንም በጸሎቱ ላዘነበ፤ ሳይቀመጥ ሃምሣ አራት ዓመት ቁሞ ለኖረ #ለታላቁ_አባት_ለአባ_በርሱማ ለዕረፍት በዓልና ለከበረ ለሶሪያዊ ከሃድያን ይዘው ምላሱን በመቁረጥ፣ በእሳት በማቃጠል፣ የብረት ችንካሮችን በእሳት አግለው በአፉና በጆሮዎቹ ለቸነከሩበትና በመጨረሻውም አንገቱን ለሰየፉት #ለቅዱስ_ጳውሎስ ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ #ከከበረ_ሰማዕት_ከቅዱስ_ጴጥሮስ ከመታሰቢያው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_በርሱማ_ዘሶርያ፦ የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ ሳሚሳጥ ከሚባል አገር ሰዎች ውስጥ ናቸው አንድ በዋሻ ውስጥ የሚኖር ሰው በእርሱ ላይ ትንቢትን ተናገረ ከመወለዱ አስቀድሞ ለአባቱ እንዲህ አለው "የትሩፋቱ ዜና በሶርያ አገር ሁሉ የሚሰማ ጣዕም ያለው ፍሬ ከአንተ ይወጣል ከእርሱ የሚሆነውንም አሰረዳው"። ተወልዶም አድጎ እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ በደረሰ ጊዜ ወላጆቹን ሸሽቶ ወደ ኤፍራጥስ ወንዝ ደርሶ በዚያ ስሙ አብርሃም ከሚባል ሰው ዘንድ ተቀመጠ እርሱም ወላጆቹን ስለፈራ ኪዚያ ገዳም ሰደደውና ሒዶ በአለት ውስጥ ኖረ በዚያም ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ ወሬውም በሶርያ አገሮች ሁሉ በተሰማ ጊዜ ብዙዎች ደቀ መዛሙርት ወደርሱ ተሰበሰቡ የዚያ ቦታ ውኃ ግን እጅግ መራራ ነበር በላዩ በጸለየ ጊዜ ተለውጦ ጣፋጭ ሆነ። እግዚአብሔርም በእጆቹ ድንቅች ተአምራቶችን አደረገ ከእርሳቸውም በአንዲት ጊዜ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ከበአቱ ርቆ ሳለ የፀሓይ መግቢያ ሰዓት ተቃረበ የክብር ባለቤት ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመነው ወደ በአቱም እስቲደርስ ያን ጊዜ ፀሓይን አቆመለት። ❤ በሌላም ጊዜም እንዲህ ሆነ ረዓም የምትባል አገር ነበረች ሰዎቿም ከሀዲዎች ናቸው በላያቸውም ዝናብ ተከለከለ በተጨነቁም ጊዜ ወደ ከበረ አባ በርሱማ መጥተው ለመኑት እርሱም ገሠጻቸው እንዲህም አላቸው "ከክህደታቸሁ ተመልሳችሁ በእግዚአብሔር ብታምኑ እርሱ ብዙ ዝናብን ያወንብላችኋል" እነርሱም "እናምንበታለን አሉት"። በዚያን ጊዜ ጌታችንን ለመነውና ብዙ ዝናብ ዘነበላቸው የአገሩ ሰዎችም ሁሉ በጌታችን አመኑ። እዲሁም ሰዎቿ ከሀድያን የሆኑ ሌላ አገር ነበረች እነርሱንም ገሥጾ መክሮ አስተምሮ እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ መለሳቸው የጣዖቶቻቸውንም ቤቶች አፈረሰ። ❤ ይህም ቅዱስ ለራሱ ቦታ አዘጋጅቶ በዚያ ሳይቀመጥ ሃምሣ አራት ዓመት ቁሞ ኖረ ከመትጋት የተነሣ ሲደክመው ከናሱ ግድግዳ ላይ ተደግፎ ያሸልባል በየሰባት ቀንም ይጾማል። የከበረ አባ ስምዖን ዘዓምድ ሊያየው ወዶ ወደርሱ ላከ የትሩፋቱንና የቅድስናውን ዜና ከብዙዎች ሰዎች ሰምቶ ነበርና እርሱም ወደ አባ ስምዖን መጥቶ እርስበርሳቸው በረከትን ተቀባበሉ ከዚያም በኋላ ወደ ገዳሙ ተመለሰ። በሶርያም አገርም አስተማረ በፊታቸው ተአምራትን በአደረገ ጊዜ በትምህርቱ ብዙዎች አመኑ። ዳግመኛም ወደ ታናሹ ቴዎዶስዮስ ንጉሥ ሒዶ በቀናች ሃይማኖት አጸናው ንጉሡም ብዙ ገንዘብን ሰጠው እርሱ ምንም ምን አልወሰደም በአንጾኪያም አገር በኤጲስቆጶሳቱ ሁሉ ላይ ሥልጣን እንዲኖረው ንጉሥ ጻፈለትና ኀቲም ቀለበትን ሰጠው። ❤ በከሀዲው ንስጥሮስ ምክንያት ሁለት መቶ ኤጲስቆጶሳት በኤፊሶን ከተማ በተሰበሰቡ ጊዜ ከእሳቸው ጋር ይህ ቅዱስ አለ። ከእርሳቸውም ጋር ንስጡርን አወገዘው ዳግመኛም በአንጾኪያ አገር ያሉ መኳንንት መሳፍንትን ሹማምንት ሁሉም ይታዘዙለት ዘንድ ንጉሥ ደብዳቤን ጻፈለት እርሱም በጎ ሥራ እንዲሠሩ በሃይማኖት እንዲጸኑ የሚያዝዝ ደብዳቤ በመጻፍ በንጉሥ ኀቲም ቀለበት እያተመ ለአገሮች ሁሉ የሚልክ ሆነ። ክፋዎች ሰዎችም ጠሉት በንጉሥም ዘንድ ነገር ሠሩበት እንዲህም አሉት" እሆ አባ በርሱማ እንደ ዓለም ሰው ሁኖ ይበላል ይጠጣል መልካም ልብስንም ይለብሳል" ንጉሥም ስለ አባ በርሱማ የተነገረውን ያረጋግጥ ዘንድ ከባለሟሎቹ አንዱን ላከ። የንጉሡም ባለሟል ወደ አባ በርሱማ በደረሰ ጊዜ በእርሱ ላይ ከተነገረው ምንም ምን ያገኘው የለም ከዚህም በኋላ ወደ ንጉሥ ወሰደው ንጉሥም ቀድሞ ከሚያውቀው ከመንፈሳዊ ሥራው ልውጥ ሁኖ ያገኘው ነገር የለም ንጉሡም ታላቅ ክብርን አከበረው ወደ ቦታውም መለሰው። ❤ መናፍቁ ንጉሥ መርቅያንም የኬልቄዶንን ጉባኤ በሰበሰበ ጊዜ የንጉሥ አማካሪዎች አባ በርሱማን እንዳያስመጣ ንጉሡን መከሩት እንደማይፈራና እንደ ማያፍር በሰው ፊትም እንደማያዳላ ተከራክሮ ረትቶ እንደሚሳፍራቸውም ስለሚያውቁ ነው። አንዱ ክርስቶስ ወደ ሁለት የከፋፈሉበት ይህ ጉባኤ በተፈጸመ ጊዜ የከበረ አባ በርሱማ ተጣላቸው ነቀፋቸው ቃላቸውንም በመሻር አወገዛቸው እርሱም ወደ ንጉሥ ወንጅለው በጽሑፍ ከሰሱት ንጉሡም ልኮ ወደርሱ አስቀረበው ግን በላዩ ስለ አደረ መንፈስ ቅዱስ ጸጋ ሊቃወመው አልቻለም በሊቁ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ላይ ስለ አደረገው ክፋት ንግሥቲቱን ረገማት ከጥቃት ቀንም በቀር አልኖረችም በክፉ አሟሟትም ሞተች። ከዚህም በኋላ መናፍቃን የሚቃወሙት ሆነ ምእመናን እንዳይታዘዙለት ወደ ሀገሮች ሁሉ ጽፈው የሚልኩ ሆኑ እነርሱ ግን አልተቀበሏቸውም እርሱ መታዘዛቸውንም አልተዉም። ዳግመኛም በጐዳና ሸምቀው ይገድሉት ዘንድ ሁለት መቶ መናፍቃን ሰዎች ከመናፍቃን ኤጲስቆጶሳት ጋር ተስማምተው ወደ እርሳቸው እንዲመጣና በአንድነት ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደ ሚሔዱ ሁነው ላኩበት መጥቶም አብሮ በተጓዘ ጊዜ ደንጊያዎችን አንሥተው ጣሉበት ደንጊያዎታቸውም ወደ ራሳቸው የሚመለሱ ሆኑ በፍርሃትም ከእርሱ ሸሹ። ❤ እግዚአብሔርም ከዚህ ዓለም እሥረኛነት ሊአወጣው በወደደ ጊዜ መልአኩን ወደርሱ ልኮ ከአራት ቀን በኋላ ከዓለም እንሚፈልስ ነገረው በዚያንም ጊዜ በዙሪያው ወዳሉ አገሮች ምእመናንን ያጽናናቸው ዘንድ ረድኡን ላከው እርሱም ሲዞር የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ራስ ወደምትኖርበት ቦታ ደረሰና የከበረች የቅዱስ ዮሐንስን ራስ እጅ ነሣት ስለ ከሀዲው ስለ ንጉሥ መርቅያን በማልቀስ ለመነ። እንዲህ የሚልም ቃል ከመጥምቁ ዮሐንስ ራስ ወጣ " አባ በርሱማ ወደ እግዚአብሔር ስለ ከሰሰው ያ መርቅያን ሙቷልና አትፍራ"። የከበረ አባ በርሱማ ረድኡን ባረከው የካቲት9 በሰላ አረፈ። ከበአቱም ደጃፍ ከምድር እስከ ሰማይ የሚደርስ የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ ታየ። ምእመናንም ሁሉ ከሩቅ አይተው ወደርሱ መጡ አርፎም አገኙት። ከሥጋውም ተባረኩ በላዩም አለቀሱ ከእርሱም ስለመለየታቸው እጅግ አዘኑ እደሚገባውም እየዘመሩና እያመሰገኑ ገንዘው በመቃብር አኖሩት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ በርሱማ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የየካቲት9 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ሶርያዊው_ሰማዕቱ_ቅዱስ_ጳውሎስ፦ የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ የሶርያ ሰዎችና በእስክንድርያ ከተማ የሚኖሩ ነጋዴዎች ናቸው ከዚህም በኋላ በእስሙናይን ከተማ የሚኖሩ ሆኑ። ወላጆቹም ሲሞቱ ብዙ ገንዘብ ተውለት ከዚህም በኋላ ከሀድያን ነገሥታትና መኳንንት በክርስቶስ የሚያምኑ ምእመናንን እንደሚያሠቃዩአቸውና እንደሚገድሏቸው ሰማ በዚያንም ጊዜ ተነሥቶ ገንዘቡን ሁሉ ለድኆችና ለችግረኞች በተነ። ከዚያም በኋላ የወደደውን መንገድ ይመራው ዘንድ ወደ ክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸለየ ጌታችንም

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ  አሜን"። ❤                          ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_አንገርጋሪ_ግእዝ_ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "#ስምዖን_ተወክፎ_ዳዊት_ዘመሮ_ነቢያት ቀደሙ አእምሮ ሐዋርያት ተራው አሠሮ ሰብአ ሰገል ሰገድ ሎቱ እሙነ ኮነ ልደቱ"። ትርጉም፦ #ስምዖን_ተቀበለው #ዳዊት_ዘመረለት_ነቢያት አስቀድመው አወቁት ሐዋርያት ፍለጋውን ተከተሉ የጥበብ ሰዎች (ሰብአሰገል) ሰገዱለት ልደቱ በእርግጥ ሆነ።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_እግ_ነግ_ዓራራይ_ዜማ፦ "#በቤተ_ልሔም_ተወልደ ወበናዝሬት ተሐፅነ #ወስምዖን_ተወክፎ ውስተ ሕፅኑ #ዳዊት_ዘመሮ #ወዮሐንስ_ለንጸሮ_ለሙሴ_ገሃደ_ተናገሮ"። ትርጉም፦ #በቤተ_ልሔም_ተወለደ በናዝሬትም ሰገደ #ስምዖን_ተቀበለ (ሰብአ ሰገል) ሰገዱለት ልደቱ በእርግጥ ሆነ #ዳዊት_ዘመረለት_ዮሐንስ_ተመለከተው_ለሙሴ_በግልጥ_ተናገረው። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።                 

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለዐቢይ_ጾም_ለመጀመርያ_ሳምንት #ለዘወረደ (ለጾመ ሕርቃል)ና #ለቅበላ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዚህ_ሳምንት_የዘወረደ_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ  "#ተቀነዩ_ለእግዚአብሔር_በፍርሃት_ወተሐሠዩ_ሎቱ በረዓድ እስመ ለዓለም ምሕረቱ ለትውልደ ትውልድ ጽድቁ ንሕነሰ ሕዝቡ ባኡ ቅድሜሁ በተጋንዮ ወውስተ አዕፃዲሁ በስብሐት እመንዎ፤ እ፣ #ንጹም_ጾም_ወናፍቅር_ቢጸነ_ወንትፋቀር_በበይናቲነ፤ እ፣ አክብሩ ሰንበተ ተገበሩ ጽድቀ እስመ ሰንበትሰ በእንተ ሰብእ ተፈጥረት፤ እ፣ ምሕረተ ወፍትሐ አሐሊ ለከ እዜምር ወእሌቡ ፍኖተ ንጹሐ እስመ ለዓለም ምሕረቱ ለትውልደ ትውልድ ጽድቁ ንሕነሰ ሕዝቡ አባግዐ መርዔቱ። ትርጉም፦ #ለእግዚአብሔር_በፍርሃት_ተገዙ፣ ለእርሱም መገዛት ደስ ይበላችሁ። #እግዚአብሔር ቸር ምሕረቱም ለዘላለም፣ እውነቱም ለልጅ  ልጅ ነውና። እኛስ ሕዝቡ የማሰማሪያው በጎች  ነን፤ ወደ ደጁ በመገዛት፣ ወደ አደባባዮችም በምስጋና ግቡ፤ #ጾምን _እንጹም፤ #ጓደኞቻችንን_እናፍቅር_እርስ_በርሳችንም_እንፋቀር። ሰንበት ስለሰው ተሠርታለችና ሰንበትን እናክብር። እውነትንም እንሥራ፤ አቤቱ ምሕረትንና ፍርድን እቀኝልሃለሁ፤ እዘምራለሁ፤ ንጹሕ መንገድንም አስተውላለሁ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በጾመ_ድጓው ላይ።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ዘወረደ፦ የ0ቢይ ጾም የመጀመሪያው እሁድ (ሳምንት) ዘወረደ ይባላል። ❤ ጌታችን እኛን ለማዳን ከሰማይ መውረዱን የሚነገርበት ሳምንት በመሆኑ ዘወረደ ተብሏል። ❤ ከሰማይ ወረደ ማለት እርሱ የሌለበት ኖሮ ካለበት ወደዚህ መጣ ማለት አይደለም እርሱስ ጽርሐ አርያም ምጥቀቱ በርባኖስ ጥልቀቱ ፥ አድማስ ናጌብ ስፋቱ ተብሎ የማይነገርበት በዓለም ሙሉዕ ነውና ዓለማትን ቢወስን እንጂ ዓለማት እርሱን አይወስኑትም ።   ❤ የፀሐይ ብርሃን ከክበቡ ሳይለይ ከ0ይናችን ብሌን ጋር እንደሚዋሓድ ወልደም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ በምልዓቱ መወሰን ሳይኖርበት በሥጋ ማርያም መገለጹን ሰው መሆኑን ያስረዳል :: ❤ ከሰማይ ወረደ ሲባል ስንሰማ "ሰማይ" ያለው ዕበዩን፣ ክብሩን ፣ ልዕልናውን ፣ ጌትነቱን፣ መንግሥቱን ፣ ርቀቱን .... ነው :: ስለዚህ ከሰማይ ወረደ ማለት የባሪያውን መልክ ይዞ ሰው መሆኑን ለመግለጽ ነው። ፊል 2፥6-8 ❤  ሰው ሆኖ መፈጠር ታላቅ ክብር ነው ለአምላክ ግን ሰው መሆኑ ተዋርዶ ነውና ይልቁንም እኛን ለማዳን በለበሰው ሥጋ መራብ መጠማቱ ፣ መገረፍ መታመሙ ... እንኳን ከአብ እና ከመንፈስ ቅዱስ ይቅርና ከመላእክት እንኳን ያነሰበት ነው መላእክት በባህሪያቸው መራብ መጠማት፣ መታመም የለባቸውምና " ከመላእክት እንኳን አሳነስከው" ያለውም ስለዚህ ነው ። መዝ 8፥5፣ ዕብ 2፥7 ❤ ይህ ማለት ግን ወልድ ሰው መሆኑ አምላክነቱን አጥቶ በዚህም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ አነሰ ማለት አይደለም ጌታችንም "አብ ይበልጠኛል" ያለው በለበሰው ሥጋ ባገኘው መራብ መጠማት አነሰ ለማለት ነው አብ እና መንፈስ ቅዱስ ሰው ሆነው መራብ መጠማት ... ያላገኛቸው መሆኑን ለመግለጽ ነው። ዮሐ.14፥28 ❤ ቅዱስ ያሬድ ጾመ ድጓውን ሲጀምር  ሃሌ ሃሌ ሉያ "ዘወረደ እም ላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሃዩ በቃሉ"። ትርጉም፦ ከሰማየ ሰማያት የወረደ አይሁድ የሰቀሉት ሁሉን በቃሉ እንደሚያድን አይሁድ ያላወቁት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።  በማለት ሰው ሆኖ በአይሁድ ተዋርዶ ያገኘው መሆኑን የዚህን ሳምንት ጠቅላላ ሀሣብ ይገልጻል። ምንጭ፦ ከአምኃ ሥላሴ (መኩሪያ ተስፋዬ) ፔጅ የተወሰደ።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዐቢይ_ጾም የመጀመሪያው ሌላ ስሙ #ጾመ_ሕርቃል፦ ሕርቃል ማን ነው? ለምንስ በስሙ ተሰየመ? በ614 ዓ.ም ኪርዮስ የተባለ የፋርስ ንጉሥ ኢየሩሳሌምን በመውረር ጥቃት አደረሰ፡፡ በዚህ ወቅት በኢየሩሳሌም ንግሥት ዕሌኒ በሠራችው ቤተመቅደስ ውስጥ ሲገባ ንግሥቷ በክብር አስቀምጣው የነበረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል እንደ ፀሐይ ሲያበራ አገኘው፡፡ ❤ ቢነካው አቃጠለው ዲያቆናቱን አሸክሞ ሌላውን ንዋየ ቅድሳት ዘርፎ 60ሺ የሚደርሱትን አቁስሎ ገድሎ 3ሺ የሚሆኑትን ማርኮ ከተማዋንም አቃጥሎ ወደ ፋርስ ባቢሎን ይመለሳል፡፡ በዚህ ጊዜ ከጦርነቱ ያመለጡ በየዋሻው በየጉራንጉሩ ገብተው የተሸሸጉ ተሰብስበው ከ14 ዓመት በኋላ በ628 ጩኸታቸውንና የደረሰባቸውን በደል ለክርስቲየኑ የሮም ንጉሥ ሕርቃል ይነግሩታል፡፡ ❤ እርሱም "ሐዋርያት ሰውን የገደለ  ዕድሜውን በሙሉ ይጹም ስላሉ እንዴት ላድርገው?" አላቸው እኛ "የአንተን ዕድሜ ተከፋፍለን እንጾማለን" ብለው አንድ አንድ ሳምንት ደርሷቸው ጾሙን በሚገባ ጾመውታል፡፡ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀልና የተማረኩ ክርስቲያኖችን ለመመለስ ሕርቃል ጦር መዝዞ በኪርዮስ ላይ ተነሳበት ድል ለሕርቃል ሆነና መስቀሉን ያለበትን አጥቶ ሲቸገር መስቀሉን ሲቀብርና ዲያቆናቱን ሲያስገድል በመስኮት ሆና ያየችው ከኢየሩሳሌም የተማረከች አንዲት ብላቴና አሳይታው አውጥቶ በልብሰ መንግሥቱ ጠቅልሎ ወደ ቊስጥንጥንያ ተመለሰ፡፡ ❤ የተማረኩት በሙሉ ነጻ ወጡ ይህን ለማሰብ ለማስታወስ በተጨማሪም በኃጢአት ላይ ድል እንድናገኝ መንፈሳዊ ጦር በውስጣችን እንዲበዛልን መስቀልህ ከምርኮ እንደተመለሰ እኛንም ከኃጢአት ምርኮ መልሰን ለሕርቃል ድል መንሳትንና በጠላቶቹ ላይ ኃይልን እንደሰጠኸው ለእኛም በኃጢአት ላይ ድል መንሳት መንፈሳዊ ኃይልን ስጠን እያልን እንጾመዋለን፡፡ ❤ በጌታ ጾም ላይ እንዲጾም የሆነበት ምክንያት ጾሙ የጌታ ጾም በሚጾምበት ወቅት ላይ ስለተጾመ ቤተክርስቲያናችን አብራ ደንግጋዋለች፡፡ እዚህ ላይ በዚያን ጊዜ ለሕርቃል ሕዝቡ ሱባኤ ይዞለታል፡፡ ❤ ዛሬም እኛ ለቤተክርስቲያን ያደረግነውን በማሰብ እግዚአብሔር አምላክ ለሕርቃል የሰጠውን በጠላቶቹ ላይ ድል መንሳትን ለእኛም እንዲሰጠን የምንጠይቅበት ስለሆነ የመጀመሪያውን ሳምንት በሕርቃል ሰይመን ጾሙን እንጾማለን፡፡ ❤ የእኛ ጠላት የጨለማ ገዥ የሆነው ዲያቢሎስ ነውና እሱን ደግሞ በጾም እንደምናሸንፈው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮናል፡፡ ምንጭ፦ የመጋቢት 10 ስንክሳር እና ከፌስቡክ ከማኅበረ ጎዶልያስ ዘ ዑራኤል የተወሰደ።                                 ✝ ✝ ✝ ❤ #የዘወረደ_አራራይ_ዜማ፦ ሃሌሉያ "#መሐረነ ንጉሠ ስብሐት #ተሣሀለነ_እግዚአ_ለሰንበት አቡሃ ለምሕረት #ወሀበነ_ጾመ ለንስሐ በዘይሰረይ ኃጢአት። ትርጉም፦ #የምስጋና_አምላክ ማረን የምሕረት አባት #የሰንበት_ጌታ_ይቅር_በለን #ጾምን_ለንስሐ_ስጠን  ኃጢአታችን ይሰረይ ዘንድ፡፡ #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በጾመ_ድጓው_ላይ።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ተቀነዩ ለእግዚአብሔር በፍርሃት። ወተኀሠዩ ሎቱ በረዓድ። አጽንዕዋ ለጥበብ ከመ ኢይትመዐዕ እግዚአብሔር"። መዝ 2፥11-12። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 13፥7-16፣ ያዕ 4፥6-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 25፥13-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 3፥10-25። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም የቅበላ በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።                 

                            ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ቴዎድሮስ፦ የእስክድርያ ሊቀ ጳጳሳት ቁጥሩም እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ አምስተኛ ነው። ይህ አባት መርዩጥ በሚባል አገር በአንድ ገዳም ውስጥ መነኰሰ የዚያም ገዳም ስም ጠንቡራ ነው። ለአንድ ፍጹም ጻድቅ የሆነ ሽማግሌ ሰው ደቀ መዝሙሩ ሆነ። እርሱም ልጁ ቴዎድሮስ በእስክድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና እንደሚሾም በመንፈስ ቅዱስ አይቶ ይህንን ለመነኰሳቱ ነገራቸው። ❤ ይህም አባት ቴዎድሮስ በገድል የተጠመደ ሆነ መልኩም የሚያምር ነው በሰውነቱም ላይ ከውስጥ ማቅ በመልበስ በላዩ የብረት ልብስ መንቈር ይለብስ ነበር በቅንነቱና በትሕትናው ፍጹም ሆነ። በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ተመርጦ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ የክርስቶስንም መንጋዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቀ ሁልጊዜ መጻሕፍትን በማንበብ ያስተምራቸው ነበር ይልቁንም በሰንበትና በበዓላት ቀን። የሹመቱም ዘመን ጸጥታና ሰላም ነበር ቤተ ክርስቲያንም በሰላም ኖረች በወንጌላዊው ማርቆስ ወንበር ላይ ዐሥራ አንድ ዓመት ተኩል ከኖረ በኋላ፡ በሰላም ዐረፈ። ምንጭ፦ የየካቲት 7 ስንክሳር።                                ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_እብል_ለገዳማዊ_ብሑት። ዘኢርእዮ እምሰብእ መጠነ ሰብዓ ዓመት። ከመ አዘዞ አሐዱ እምላእክት። ድኅረ ወሀባ፡ ኑዛዜ ለነፍሰ ዕብሎይ ኃጥእት። ዘአዕረፈ ዮም በሠሉስ ዕለት"። #ሊቀ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_7።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦"ብከ ንወግዖሙ ለኵሎሙ ፀርነ። ወበስምከ ናኀሥሮሙ ለዕለ ቆሙ ላዕሌነ። ዘአኮ በቀስትየ እትአመን"።መዝ 43፥5-6። የሚነበብት መልዕክታ ኤፌ 6፥10-19፣ ራዕ 13፥11-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 20፥28-31። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 19፥11-28። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።                                  

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ  አሜን"። ❤              ❤ #የካቲት ፯ (7) ቀን። ❤ እንኳን #ለእስክንድርያ_አገር አርባ ሦስተኛ ሊቀ ጳጳስ በአገሩ የነገሡ የተለያዩ አሕዛብ ነገሥታት በጽኑ ሥቃይ ላሠቃዩት ለከበረ አባት #ለአባ_እለስክድሮስና ለአርባ አምስተኛ ሊቀ ጳጳስ ለከበረ አባት #ለአባ_ቴዎድሮስ ለዕረፍታቸው በዓል፣ የሰውን ፊት ሳያይ በበረሀ ለሰባ ዓመት ለኖረ አባ ዕብሎይን ላረጋጋ ለገዳማዊው አባት #ለአባ_አብዱልማስ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ #ከአብራቅያ_ከአባዲር፣ #ከአባርያኖስና ከዕረፍታቸው መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የእስክንድርያ_ሀገር_ሊቀ_ጳጳሳት #አባ_እለእስክንድሮስ፦ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ ሦስተኛ ነው። ይህም አባት "ታሮን" በሚባል ገዳም መነኰሰ ትርጓሜውም "የአባቶች ገዳም" ማለት ነው በጌታችንም ፈቃድ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ እርሱ የተማረ አዋቂ ጻድቅ ሰው ነበረና። ❤ በሹመቱ ወራትም ብዙ መከራ ደረሰበት የግብጽ ንጉሥ ልጁን ሹሞ በመንግሥቱ ላይ አሠለጠነው እርሱም በአስቄጥስ በረሀ ያለውን የመነኰሳቱን ገዳማት አፈረሳቸው። ከክፋቱና ከክህደቱ ብዛት የተነሣ ከምስር በስተሰሜን ወዳለች ገዳም ገብቶ በዚያ አምላክን የወለደች የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ሥዕሏን አየና "ይች ምንድን ናት" አለ እርሷም በሽልማት ሁሉ የተሸለመችና ያጌጠች ናት በልብሶቿም ላይ ያማረ የሐር ልብስ ነበረ ሰዎችም "የክርስቶስ እናት የሆነች የእመቤታችን የድንግል ማርያም ሥዕል ናት" አሉት እርሱም ተሳድቦ የረከሰ ምራቁን በፊቷ ላይ ተፍቶ "ደኅና ከሆንኩ ክርስቲያኖችን ፈጽሜ አጠፋቸዋለሁ" አለ ዳግመኛም በክብር ባለቤት በጌታችን ክርስቶስ ላይ የስድብ ቃልን ተናገረ። ❤ ሌሊትም በሆነ ጊዜ የሚያስፈራና የሚያስደነግጥ ታላቅ ራእይን አየ በነጋም ጊዜ ለአባቱ እንዲህ ብሎ ነገረው "ዛሬ በዚች ሌሊት ታላቅ መከራና ብዙ ቅጣት ደረሰብኝ ታላቅ ዙፋንንም አየሁ በላዩ የተቀመጠበት ሰው እጅግ የሚያስፈራ የሚያስደነግጥ ነው ፊቱም ከፀሐይ ይበራል የብዙ ብዙ የሆኑ ሠራዊት የጦር መሣሪያ ይዘው በዙሪያው ቁመው ነበር እኔና አንተም እሥረኞች ሁነን በኋላው ቁመን ነበር እኔም "በዙፋን ላይ የተቀመጠው ማነው?" ብዬ ጠየቅሁ "ትላንት አንተ የዘበትክበት የክርስቲያን ንጉሥ ክርስቶስ ይህ ነው" አሉኝ ከዚህም በኋላ የጦር መሣሪያ ከተሸከሙት አንዱ ወደ እኔ መጥቶ ጐኔን በጦር ወጋኝ ጦሩንም ከጐኔ ውስጥ አላወጣውም"። ❤ አባቱም ሰምቶ ደነገጠ እጅግም አዘነ ያ ልጁም ወዲያውኑ ታመመ አንደበቱም ተዘግቶ በክፉ አሟሟት ሞተ። ዳግመኛም ከአርባ ቀን በኋላ አባቱ ሞተ። በርሱም ፈንታ ሌላ ንጉሥ ተሾመ እርሱም ክርስቲያኖችን እጅግ አሠቃያቸው ይህንንም አባት ሊቀ ጳጳሳት እለእስክንድሮስን አብዝቶ አሠቃየው ከሕዝቡ ሦስት ሺህ የወርቅ ዲናር ለምኖ እስከ ሰጠው ድረስ ጌታችንም ይህን ንጉሥ ፈጥኖ አጠፋው። ❤ ከዚህም በኋላ አሁንም ሌላ ንጉሥ ተሾመ እርሱም ሊቀ ጳጳሳቱን ይዞ እንደ ቀድሞው ሦስት ሺህ የወርቅ ዲናር እንዲሰጠው ፈለገ እርሱም ከወገኖቼ እስከምለምን ታገሠኝ ብሎ ማለደው ንጉሡም ቀጠሮ ሰጠውና ይለምን ዘንድ ወደ ላይኛው ግብጽ ወጣ። በተራራ ላይ አንድ ገዳማዊ ሰው ነበር ከእርሱም ጋር ሁለት ደቀ መዛሙርት አሉ በተራራውም በአንድ ቦታ እንዲቆፍሩና እንዲጠርጉ አዘዛቸው ወርቅን የተመላ አምስት ማሰሮ አገኙ አንዱን ሸሽገው አራቱን ወደ ገዳማዊ መምህራቸው አመጡ እርሱም ይረዳበት ዘንድ እንዲስጡት ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ ላካቸው። እነርሱ ግን እነዚያን የወርቅ ማሰሮዎች ይዘው ተመልሰው ወደ ዓለም ገቡ የምንኵስና ልብሳቸውንም ጥለው ሚስት አገቡ በዚያም ወርቅ ወንዶችና ሴቶች ባሮችን እንስሳትንም ገዙ። ❤ የዚያችም አገር አስተዳዳሪ ያዛቸው ገንዘብንም ከወዴት እንዳገኙ በመግረፍ መረመራቸው እነርሱም አምስት የወርቅ ማሰሮዎችን እንዳገኙ አመኑ መኰንኑም ለንጉሥ የጭፍራ አለቃ አሳልፎ ሰጣቸው እርሱም ወደ ንጉሥ አቀረባቸውና አምስት የወርቅ ማሰሮ እንዳገኙ አስረዳው ንጉሡም ጭፍሮቹን ልኮ የሊቀ ጳጳሳቱን ቤት በረበረ የአብያተ ክርስቲያናት ከሆነ ከንዋየ ቅድሳት ያገኘውን ሁሉ ወሰደ ሊቀ ጳጳሳቱንም አሠረውና ወርቅን የተመሉ አራቱን ማሰሮዎች ደግሞም ሦስቱን ሽህ የወርቅ ዲናር አምጣልኝ አለው እርሱም ከዚህ ከኃላፊው ዓለም ገንዘብ ምንም ምን የለኝም አለው ወደ ሕዝቡ ልኮ ሦስቱን ሽህ የወርቅ ዲናር አምጥተውለት እስከ ሰጠው ድረስ አልተወውም ይህንንም ክፉ ንጉሥ ጌታችን አጠፉው። ❤ ከዚህም በኋላ ከእርሱ የከፋ ሌላ ንጉሥ ተሾመ እርሱም የሐሰተኛውንና የርኵሱን ነቢይ ስም በከበረ መስቀል ፈንታ በእጆቻቸው ውስጥ እንዲአትሙ የክርስቲያንን ወገኖች አስገደዳቸው። ይችም ምልክት የመለኮትን ነገር የሚናገር ወንጌላዊ ዮሐንስ የተናገራት ትንቢት ናት ይህም ክፋ ንጉሥ ወደ ሀገሮች ሁሉ ይህን እንዲአደርጉ አዘዛቸው ሊቀ ጳጳሳቱንም እንዲሁ ያደርግ ዘንድ አዘዘው። ሊቀ ጳጳሳትም ይተወው ዘንድ ብዙ ለመነው አልተቀበለውም ዳግመኛም እስከ ሦስት ቀን ይታገሠው ዘንድ ለመነው። ❤ ከዚህም በኋላ ደግሞ እንዳይጥለውና ወደዚህ ወደረከሰ ሥራ እንዳያስገባው ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ማለደ ጌታችንም ልመናውን ተቀብሎ በጥቂት ደዌ ጐበኘው ወደ ቤቱ እስክንድርያ ይሔድ ዘንድ እንዲአዝዝለት ንጉሡን ለመነው። ንጉሡም ከለከለው ሰለ እጅ ኀትመት ምክንያት ለመፍጠር ሰለ መሰለው የእግዚአብሔርም መልአክ ተገለጠለትና ነገ ታርፋለህ አለው እርሱም አርድእቱን እግዚአብሔር ነገ ስለሚጐበኘኝ አርፋለሁና መርከብን አዘጋጁ አላቸው። አንዳለውም በማግሥቱ አረፈ ሥጋውንም በመርከብ ተሸክመው ወስደው ከአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሥጋ ጋር ቀበሩት። በዚህም አባት አለእስክንድሮስ ዘመን በግብጽ አገር ለሚኖሩ መለካውያን ስሙ አንስጣስዮስ የሚባል ሊቀ ጳጳሳት ነበራቸው ያዕቆባውያን ምእመናንን ይወዳቸዋል ስለዚህም ወገኖቹ መለካውያን ተጣሉት። እርሱም ነፍሱን ያድን ዘንድ አስቦ ወደዚህ አባት አለእስክንድሮስ መጥቶ ከሥልጣኑ በታች በመሆን የሚታዘዝ ሆነ እለእስክንድሮስም አንስጣስዮስን በእርሱ ፈንታ የሊቀ ጵጵስናውን ሥልጣን ይዞ መንጋውን ይመራ ዘንድ እርሱ ግን ከመነኰሳት እንዳንዱ ሁኖ በገዳም ይኖር ዘንድ እንዲተወው ለመነው። ❤ አባ አንስጣስዮስም አልወደደም እንዲህም አለ "ይህን የምሻ ከሆነ አኔ እስከ ዛሬ ሊቀ ጳጳሳት አልነበርኩምን ላንተ ደቀ መዝሙርህ ሁኜ ላገለግልህ ወደድኩ እንጂ" አለ። በመካከላቸው ከተደረገው ከብዙ ልመና ከብዙ ምልልስም በኋላ ኤጲስቆጶስ ይሆን ዘንድ አንስጣስዮስ ፈቀደ በአንዲትም ሀገር ላይ ኤጲስቆጶስነትን ሾመው። መንጋውንም እንደሚገባ በጎ አጠባበቅን ጠበቀ፡፡ አባት እለእስክንድሮስም በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር የኖረው ሃያ አራት ዓመት ከስድስት ወር ነው እግዚአብሔርንም አገለገለው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ እለእስክንድሮስ ጸሎት ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

❤ ይህም የከበረ አባት ስለ ቀናች ሃይማኖት ብዙ ድርሳናትን ደርሶል ከእርሳቸውም ስለ አካላዊ ቃል ሰው መሆንና ከኃጢአት በቀር በሥራው ሁሉ አንድ ባሕርይ ስለ መሆኑ የደረሰው አለ። ዳግመኛም እግዚአብሔር የሚወደውን ስለ መሥራት የደረሳቸው ተግሣጻትና ትምህርቶች አሉ ስለ ቤተ ክርስቲያንም ሕግ ሠላሳ ስምንት መመሪያዎችን ሠርቷል እሊህም በሁሉ አብያተ ክርስቲያን ይገኛሉ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አቡሊዲስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የየካቲት6 ስንክሳር።                                                        ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_እብል_ዕርገተ_ሥጋሁ_እምባሕር። እንዘ ዕብን ክቡድ ውስተ እገሪሁ እሡር። #አቡሊዲስ_ሊቅ ዘበትውልዱ ማእምር። ያምጽእ ሊተ በረከተ እምነ ገሪዛን ደብር። ከመ ንዋየ ክቡር ወብዕል ያመጽእ ሐመር"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_6።                                ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦"ከርቤ ወቀንዓት ወሰሊሆት አእምነ አልባሲከ። እምክቡዳነ አቅርንት ዘእምኔሆሙ አስተፌሥሐከ። አዋልደ ንሥት ለክብር"። መዝ 44፥8-9። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 1፥15-18፣ ያዕ 4፥1-10 እና የሐዋ ሥራ 27፥39-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 26፥6-17። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የማርያም እንተ ዕፍረት የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።                  

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤              ❤ #የካቲት ፮ (6) ቀን። ❤ እንኳን #ጌታችንን_ሽቱ_ለቀባችው_ለማርያም_እንተ ዕፍረት ለዕለፍቷ መታሰቢያ በዓል፣ ለዓለሙ ሁሉ መምህር ለሆነ ለሮሜ አገር ሊቀ ጳጳሳት ለከበረ አባት #ለአባ_አቡሊዲስ ሥጋው ከባሕር ለወጣበት በዓልና #ለከበሩ_ቅዱሳን_አቡቂርና_ዮሐንስ ለሦስቱ ደናግላን #ለቅድሳት_ቴዎድራ_ቴዎፍና_ቴዎዶክስያና ለእናታቸው #ለቅድስት_አትናስያ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። ከእነዚህ  ቅዱሳን እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                                  ✝ ✝ ✝ ❤ #ማርያም እንተ ዕፍረት፦ ይችም ቅድስት አስቀድማ ኑሮዋን በዝሙት ያሳለፈች ኃጢኣተኛ ነበረች። እርሷም ጐልማሶችን ወደርሷ ትማርካቸው ዘንድ በየራሱ በሆነ ሽልማትና ጌጥ ትሸለም ነበር። በአንዲትም ዕለት እንደ ልማድዋ ተሸልማ አጊጣ ሽቱም ተቀብታ ፊቷን በመስታዋት ተመለከተች የጉንጯ ቅላትና ደም ግባቷ፡የዓይኗም ወገግታና ጥራት ማማሩን አይታ እያደነቀች አንድ ሰዓት ያህል ቆየች ከዚህም በኋላ በጎ ኀሳብ በላይዋ መጣ ሞትንና የዚህን ዓለም ማለፍ አሰበች። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስም ኃጢኣተኞችን እንደ ሚቀበልና ኃጢአትንም እንደሚያአስተሰርይ ሰምታ በዝሙት የሰበሰበችውን ሦስት መቶ ወቄት ወርቅ አላት ያን ይዛ ኼዳለች። ❤ ዲያብሎስም ታመልጠኛለች ይኽነን ጊዜ ላስታት ብሎ ቀድሞ ከምታውቀው አንዱን መስሎ፡በመልከ፡መልካም ወጣት አምሳል ከመንገድ ላይ ቆይቷት "ወዴት ትኼጃለሽ" አላት፤ ዝም አለችው፤ "አንቺ ባትነግሪኝ እኔ እነግርሽ የለም፤ እንግዳ ወንድ መጥቶብሽ ለርሱ የምትቀቢው ሽቶ ልትገዢ ትኼጃለሽ" አላት፤ "አዎን" አለችው፤ ይኽም አይደለም "ፍቅሩ ያላለቀበት ወንድ መጥቶብሽ ለርሱ የምትቀቢው ሽቱ ልትገዢ ትኼጃለሽ" አላት፤ "አዎን" አለችው። ይኽም አይደለም "በጥቂት ገንዘብ ብዙ ገንዘብ የሚሸጥ ነጋዴ መጥቶብሽ ለርሱ የምትቀቢው ሽቱ ልትገዢ ትኼጃለሽ" አላት፤ "አዎን" አለችው። ኹሉንም "አዎን አዎን ትያለሽ ማናቸው ነው ትክክል" አላት፤ ርሷም ተገልጾላት "እንግዳ ወንድ መጥቶብሽ አልከኝ፤ ከዚኽ ዓለም ልዩ የሚኾን ጌታ መጥቷል፤ ፍቅሩ ያላለቀበት ወንድ መጥቶብሽ ላልከኝ የሰው ፍቅር አገብሮት ሊሞት መጥቷል፤ በጥቂት ገንዘብ ብዙ ገንዘብ የሚሸጥ ነጋዴ መጥቶብሽ ላልከኝ "አዎን በጥቂት ትሩፋት ብዙ ክብር የሚሰጥ ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቷልና ለርሱ የምቀባው ሽቱ ልገዛ እኼዳለኊ"ብላ ስሙን ብትጠራበት እንደ ትቢያ በኖ እንደ ጢስ ተንኖ ጠፍቶላታል፤ ከዚኽ በኋላ ሃድኖክ የሚባል ባለጸጋ ነጋዴ አለ፤ ኼዳ "ለነገሥታት የሚገባ ሽቱ አምጣ" ብላ ሦስት መቶ ወቄት ወርቅ ሰጠችው፤ በአገራቸው "ሐሰት የለምና ይኽን ያኽልስ የሚያወጣ የለለኝም" አላት፤ ርሱ የማያውቀው እናቱ የምታውቀው ዳዊት ሰሎሞን ተቀብተውለት የተረፈ ነበርና ከእንዲኽ ያለ ቦታ አለና ሽጥላት ብላው ሽጦላት አምጥታ ቀብታዋለች፤ ይኽም ብቻም አይደለም ጌታ ከእናቱ ጋር ግብጽ በተሰደደበት ጊዜ ሰሎሜም ፈያታዊ ዘየማንም ይዘውት ሳለ ከልብሱ ላይ ወዛ ቢያጥቡት ሰፈፈ ይኽም በዕቃ አኑረውት ነበርና ያም ተጨምሮበታል፤ በቢታንያ በለምጻሙ በስምዖን ቤት ሳለ ዋጋው እጅግ የበዛውን ይኽነን ሽቱ የመላው የአልባስጥሮስ ብልቃጥ ይዛ ወደ ርሱ ቀርባ በማዕድም ተቀምጦ ሳለ በራሱ ላይ አፍስሳዋለች፤ ጌታችንም ለደቀ መዛሙርቱ "ይኽነን ሽቱ በሰውነቴ ላይ አፍስሳ ለመቃብሬ አደረገች፤ እውነት እላችኋለኊ ይኽ ወንጌል በዓለም ኹሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት ርሷ ያደረገችው ደግሞ ለርሷ መታሰቢያ እንዲኾን ይነገራል" ብሏታልና። ምንጭ፦ የየካቲት6 ስንክሳርና መጽሐፈ ተአምኆ ቅዱሳን ንባብና ትርጓሜው መጋቢ ሐዲስ ሮዳስ ከጻፈው።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱስ_ዮሐንስ_ቅዱስ_አቡቂር #ሦስቱ_ደናግልም_ልጆቿና_እናታቸው_ቅድስት_አትናስያና፡- የእሊህም ስማቸው ቴዎድራ ትርጓሜው "የእግዚአብሔር ስጦታ" ነው ሁለተኛወ ቴዎፍና ትርጓሜውም "የእግዚአብሔር ሃይማኖት" ሦስተኛይቱም ቴዎዶክስያ ትርጓሜውም "የእግዚአብሔር ምስጋና" የእናታቸውም የአትናስያ ትርጓሜው "ሕይወት የሆነ" ነው፡፡ ይህም የከበረ ቅዱስ አቡቂር ከታናሽነቱ ጀምሮ በገድል ተጠምዶ የሚኖር መነኰስ ነው፡፡ የከበረ ቅዱስ ዮሐንስ ግን በንጉሥ ሠራዊት ውስጥ ወታደር ነበር፡፡ የእነርሱም አገራቸው እስክንድርያ ሲሆን የሚኖሩት ግን አንጾኪያ ነው፡፡በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም ፊት ቁመው ከእሊህ ደናግል ከእናታቸው ከአትናስያም ጋር በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ። እርሱም ከወዴት እንደሆኑ ጠየቀ ከእስክንድርያ አገር እንደሆኑ በተረዳ ጊዜ ወደዚያ ይወስዷቸው ዘንድ አዘዘ፡፡ ❤ ወደ እስክንድርያ በደረሱ ጊዜ ዳግመኛ በመኰንኑ ፊት ቁመው በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ መኰንኑም ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃያቸው ማሠቃየትንም በደከመው ጊዜ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፡፡ አትናስያም ደናግል ልጆቿን በከበረ ስሙ ምስክር ሁነው ከሞቱ ለሰማያዊው ሙሽራ ለክርስቶስ እነርሱም ሙሽሮቹ እንደሚሆኑ በማስረዳት ታጽናናቸው ታስታግሣቸው ነበር፡፡ እንዲሁም ቅዱስ አቡቂር በከበረች ሐዋርያዊት በቅድስት ቴክላ ላይ የደረሰውን መከራና ያገኘችውን ክብር ይገልጥላቸውና ያጽናናቸው ነበር፡፡ ወታደሮችም ባለ ሰይፍ በማከታተል አንዲቱን ከአንዲቱ በኋላ የሚያቀርቡ ሆኑ ከዚህም እናታቸውን የከበሩ፣ ቅዱስ አቡቂርንና ቅዱስ ዮሐንስን ቆረጡ። መኰንኑም ሥጋቸውን ለአራዊትና ለአዕዋፍ ይጥሉ ዘንድ አዘዘ፡፡ ምእመናንም ሥጋቸውን በሥውር ወሰዱ በክብር ገነዙአቸው የመከራው ዘመን እስቲያልፍ በሣጥን አድርገው ሠወሩአቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶላቸው ቅዱስ ሥጋቸውን በውስጧ አኖሩ፡፡ ከእርሳቸውም ታላላቅ ድንቆች ተአምራቶች ተገለጠ። በረከታቸው ከእኛ ጋራ ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_አቡሊዲስ፦ ይህም የከበረ በእውቀቱም ፍጹም የሆነ ሰው ነው ከአባት አውክዮስም በኋላ ለሮሜ አገር ሊቀ ጳጳሳት ይሆን ዘንድ መንፈስ ቅዱስ መረጠው ይህም የእስክንድር ሊቀ ጳጳሳት አባ ከላድያኑ በተሾመባት በመጀመሪያ ዓመት ነው ሕዝቡንም ከአረማውያን ጠባይ የሚጠብቃቸው የምያስተምራቸውና በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖት የሚያጸናቸው ሆነ። ❤ በከሀዲውም ንጉሥ በከላድያኖስ ዘንድ ዜናው ተሰማ ይህንንም የከበረ አቡሊዲስን ይዞ በብዙ ግርፋትና ድብደባ አሠቃየው ማሠቃየቱንም በሰለቸው ጊዜ በእግሮቹ ውስጥ ታላቅ ድንጊያ አሥሮ ከጥልቅ ባሕር የካቲት አምስት ቀን አሰጠመው። ማግሥትም ሲሆን የካቲት ስድስት በዛሬዋ ቀን የዚህ አባት ሥጋው በውኃ ላይ ተንሳፎ ተገኘ ደንጊያውም በእግሮቹ ውስጥ እንደታሠረ ነበር አንድ ምእመን ሰው ወስዶ በርሱ ዘንድ አኖረው በከበሩ ልብሶችም ገንዞ ሠወረው ወሬውም በሮሜ አገሮች ሁሉ ተሰማ ንጉሡም ሊአቃጥለው ፈልጎት ነበር ግን አላገኘውም ያ ሰው ሠውሮታልና።