uk
Feedback
🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

Відкрити в Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

Показати більше
2 212
Підписники
-124 години
-67 днів
-3230 день
Архів дописів
አህባሾችና አላህን ከ‘ጂሀ’ እና ከ“መካን” የማጥራት እሳቤ ክፍል 2/2 የአላህ ከፍጥረታት በላይ መሆን አላህ በተፈጥሮ በልባችን ያኖረው ግልጽ እምነት ነው። አላህ በቁርአን እንደገለፀው የአላህን ከፍጥረታት በላይ መሆን "ዑሉው" መግልጽ ብቻ ለአህሉሱና በቂ ነው።  በቁርአንም ላይ የምናገኘው አካሄድ ይኸው ነው። ‘አላህን ከጉድለትና ከመመሳሰል ማጥራት’ ጥቅል በሆነ መልኩ ሲቀርብ ፤ የአላህን ባህሪያት ማጽደቅ ግን በዝርዝር ሲቀርብ እናገኛለን። ለአብነት ያክል ተከታዩን መልእክት እናስተውል፤ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ} الشور : 11  ‹‹የሚመስለው ምንም ነገር የለም፡፡እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው» አል ሹራ 11  ይህ አንቀፅ በየትኛውም ሁኔታ በፍጡራንና በፈጣሪ መካከል መመሳሰል እንደሌለና አላህ ሰሚና ተመልካች መሆኑን ያሳያል፡፡ መስሚያና መመልከቻ የብዙ ፍጡራን መገለጫዎች ቢሆኑም ነገር ግን የአላህ መስሚያና መመልከቻ ከፍጡራኑ ጋር አይመሳሰልም። በመስሚያና በመመልከቻ አምሳያ እንዳሌለው ሁሉ በሌሎችም ባህሪያቱ አምሳያ የለውም፡፡  ይህ አንቀጽ ሙስሊሞች ለአላህ የማይገቡ ባህሪያትን ከመረዳት አንጻር ሊኖራቸው ለሚገባው ትክክለኛ አካሄድ በመርህ መልክ ይቀርጻል።  አንቀጹ የጉድለት ባህሪዎችን ጥቅል በሆነ መልኩ ዉድቅ ሲያደርግ ምሉዕ ባህሪዎችን ግን በዝርዝር ያጸድቃል። አቅጣጫዎች ህዋሳዊ ማነጻጸሪያ reference point በመጠቀም ብቻ የሚታወቁ ናቸው። ማንኛውም ሰው የቂብላን አቅጣጫ ለማወቅ ጸሀይን ማነጻጸሪያ እንደሚያደርገው ማለት ነው። ሰዎች በአዕምሮአቸው የሚቀርጿቸው ማነጻጸሪያዎች ሁሉ በፍጥረተ አለሙ የተገደቡ በመሆናቸው ስለአላህ ለመናገር እነዚህን ፍጡራዊ ማነጻጸሪያዎችን መጠቀም አይገባም!አህሉሱና ፍልስፍዎችን በቁርአን እና በሱና ላይ አይሾሙም! አላህ ለራሱ ያጸደቃቸውን ባህሪዎች ያጸድቃሉ፤ ለአላህ ተገቢዉን ክብር ስለሚሰጡ ስለባህሪዎቹ የተነገሩ መረጃዎችን የፍጡራንን ባህሪ በሚረዱበት ሁኔታ አይረዱም። ሁልጊዜ መነሻቸው አላህን ከጉድለትና ከመመሳሰል ማጽዳት ስለሆነም እነዚህና መሰል የአስተሳሰብ ግድፈቶች አይገጥሟቸውም ። አዎን! አላህን በጉድለትም ይሁን ከፍጡራን ጋር በመመሳሰል ከመግለፅ የፀዱ ናቸው!! በአንፃሩ አህባሾችና አርአያዎቻቸው ጀህሚዮች፤ ሁሌም መነሻቸው ስለ አላህ የተነገሩ መረጃዎችን ልክ ፍጡራን ላይ በሚያውቋቸው ባህሪያት መልኩ መረዳት ስለሆነ አላህን ከፍጡራን መለየት ያልቻሉ "ሙመሲላህ" አመሳሳዮች እነሱው ናቸው። የሰማያትና የምድር ፈጣሪ አምላክ ሰለሆነው አላህ ሲነገር እንዴት ፍጡራዊ የሆኑ ባህሪዎች ይታወሳሉ?? አላህ ከጥመት ይጠብቀን! አቡጁነይድ ዙልቂእዳ 17/1436 ዓ.ሂ @abujunaidposts

አህባሾችና አላህን ከ‘ጂሀ’ እና ከ“መካን” የማጥራት እሳቤ ክፍል 1/2 ምስጋና ለአላህ የተገባ ነው። የአላህ ሰላምና እዝነት በመልእከተኛው ላይ የሁን። በመቀጠል፤ አላህ እንዲህ ብሏል፤ {الرَّحْمَٰنُ عَلَى الْعَرْشِ اسْتَوَىٰ} [طه : 5] «አል ረህማን ከዓርሽ በላይ ከፍ አለ» ጣሀ 5 ማንኛውንም ጤናማ ሙስሊም ይህንን አንቀፅ ስትሰማ፤ ‘ሰማያት አላህን ተሸክመዋል፣ ፍጥረራቱ ያካብቡታል’፣ ‘አላህ ከዓርሽ ፈላጊ ነው’ ወይም ‘አላህ በፍጥረታቱ ውስጥ ሰርጿል’ የሚሉ መጥፎ መልዕክቶችን ተረድተሀልን? ብለህ ብንጠይቀው፤ “ፈጽሞ አዕምሮዬ አላሰበዉም” እንደሚለን ግልጽ ነው። በፍልስፍና ልቡ ያልታወረ ማንኛውም ሙስሊም ይህንን እና መሰል መልእክቶችን ከጥመት በራቀ መልኩ እንደሚረዳው ይታወቃል። በርግጥም ከዚህ ግልጽ ቁርአናዊ መልእክት ጥመትን የሚረዳ ልቡ ውስጥ በሽታ ያለበት ብቻ ነው! አህሉሱና ግን አላህ ከእርሱ ክብርና ግርማ ሞገስ ጋር በሚሄድ መልኩ ከሰማያትና ከዓርሽም በላይ መሆኑን እና ከፍጥረታቱ የተለየ “ባኢን’ መሆኑን ያምናሉ። በዚህ መልኩ ንፁህ ምልከታ ኖሮህ አላህ የተናገረውን አፅድቀህ ስትመሰክር ሰላም ነህ። ሆኖም አህባሾችና ይህንን ጥመት ያወረሷቸው ቀደምት አንጃዎች «አላህ ከአርሽ በላይ ነው» ስትል በአላህ ክደሀል ይሉሀል። ለምን ብትላቸው ለአላህ ቦታ እና አቅጣጫን ስለሰጠህ ካፊር ይሉሀል። ስለዚህም ዘወትር "አላሁ መውጁዱን ቢላ መካን" የሚል ባዶ መፈክር ሀዲስ በማስመሰል ይደሰኩራሉ። ለመሆኑ አህባሾች... የዚህን አንቀፅ ቀጥተኛ መልእክት በሰው አእምሮ የማይመጣን የጉድለት ባህሪ የሚያስገነዝብ የኩፍር መልእክት አድርገው ለምን ይረዱታል? ሰሀቦችና ታቢዒዮች ከአላህ የመጣውን መልእክት ተቀብለው ሳይፈላሰፉ እንዳፀዱቀት እነርሱም አፅድቀው በማመን ፈንታ መካን እና ጂሀ የሚል ፀጉር ስንጠቃስ ለምን አስፈለጋቸው? መነሻዎቻቸውንና ትክክለኛውን የአህሉሱና አቋም ማወቅ ጠቃሚ ነውና ልብ ብለህ ተከታተለኝ። በመሰረቱ "ጂሀ" (አቅጣጫ) እና "መካን" (ቦታ) የሚሉት ቃላት ሸሪዓዊ መሰረት የላቸውም። ከዚህ ርዕስ ጋር በተያያዘ በቁርዓንም ይሁን በሀዲስ አናገኛቸዉም። በተመሳሳይ መልኩ ‘ሀድ’ እና ‘ጂስም’ የመሳሰሉ "ሙጅመል" ጥቅል ቃላት ሸሪዓዊ መሰረት የላቸውም። አህሉሱና በዚህም ይሁን በሌሎች ርዕሶች ላይ መረጃን መሰረት ያደረገ አካሄድ ስላላቸው እንዲህ አይነቶቹን ጥቅል ቃላት “አል አልፋዝ አል ሙጅመላህ” መነሻ አድርገው አይናገሩም መፈተኛም አያደርጓቸውም። ነገር ግን ከቢድዓ አራማጆች በኩል ሲመጡ ለማጽደቅም ይሁን ውድቅ ለማድረግ ሳይሽቀዳደሙ ቃሉን ባለበት በመተው የሚፈለግበት መልዕክት ምን እንደሆነ ይጠይቃሉ። ከምላሹም በመነሳትም መልዕክቱ ሀቅ ከሆነ ያጸድቁታል፤ ሀቅ ካልሆነም ውድቅ ያደርጉታል። ለምሳሌ፤ አንድ አህባሽ «ለአላህ ጂሀ ‘አቅጣጫ’ አታድርጉለት ይህ ኩፍር ነው» ቢልህ፤ ከዚህ ርዕስ ጋር በተያያዘ ‘ጂሀ’ የሚለውን ቃል በቁርአን እና በሀዲስ እንደማታውቀው በመንገር በዚህ ቃል ምን እንደተፈለገበት ጠይቀው። ሀሳቡ አላህ ከፍጡራኑ ሁሉ በላይ መሆኑን ማስተባበል ከሆነ ከቁርአንና ከሱና እንዲሁም ከተፈጥሯዊ እምነት ጋር የሚጋጭ ተራ ወሬ ስለሆነ ሀሳቡን እንደማትቀበል ትነግረዋለህ። ነገር ግን የፍጥረተ ዓለሙ አካል የሆኑትን ስድስት አቅጣጫዎች ለአላህ መገለጫ ማድረግ የለብንም ለማለት ከሆነ ይህ የታወቀ እንደሆነ እና ይህ አይነት ትርጓሜ ያለዉን ‘ጂሀ’ ለአላህ እንደማናጸድቅ፤ ቀደወሞውንም ስለአላህ ስናወራ በዙሪያችን ያሉ አቅጣጫዎች ፍፁም እንደማይታሰቡን ታስረዳዋለህ። {أَأَمِنتُم مَّن فِي السَّمَاء} [الملك : 16] «ከሰማይ በላይ ያለውን ‘አላህ’ ትተማመናላችሁን?» አልሙልክ 16 ልብ በል ወንድሜ፤ ይህንን እና መሰል አንቀፆችን ሲሰሙ የቁርአንን መልእክት በቀጥታ በመጠምዘዝ ‘አላህ ከሰማይ በላይ’ መሆኑን ሲያስተባብሉ ታይና ተገርመህ ይህ ሁሉ ልፋት እና መወራጨት ምን አመጣው ብለህ ችግራቸውን ስታጠና፤ አሁንም ለአላህ ቦታ “መካን” መስጠት አይገባም የሚሉት የፍጡራን መኖሪያ የሆኑትን ሰባቱን የቅርብ ሰማያት በማሰብ እንደሆነ ትረዳለህ። እንደዚሁ ‘አላህ ከፍጡራን በላይ ነው’ ሲባሉ በዙርያቸው የሚያውቋቸውን ስድስት አቅጣጫዎች በማሰብ አላህ ከጂሀ “አቅጣጫ” የጸዳ ነዉና ከፍጡራን በላይ ነው አይባልም እንደሚሉ ትረዳለህ። የስህተታቸው ሁሉ መሰረት ይህ ነው። ☞ ጀህሚያ፣ ሙዕተዚላ እንዲሁም አሻዒራ የአላህን የበላይ መሆን የሚያስተባብሉባቸው ፍልስፍናዊ መረጃዎች ሁሉ የሚያጠነጥኑት በዚህ ብዥታ ላይ ነው። መካን(ቦታ) እና ጂሀ(አቅጣጫ) ለአላህ አይገቡም በማለት የአላህን ከፍጡራኑ የበላይ መሆን ያስተባብላሉ። እውነታው ግን፤ እነሱ ለዚህ ስለ አላህ ባህሪያት ለማወቅ መነሻ ያደረጉት ከፍጥረተዓለሙ ጋር የተያያዙትን «ዉጁዲይ» ቦታ እና አቅጣጫን ነው። ስለ አላህ የሚነገሩ እውነታዎችን ሁሉ ፍጡራን ላይ በሚያያቸው ግንዛቤዎች ከሚተረጉም እውር አስተሳሰብ መጠንቀቅ ያስፈልጋል። ☞ አህሉሱና አላህ ከፍጡራን ሁሉ በላይ መሆኑን ያምናሉ፤ ‘ከሰማይ በላይ ነው’ ወይም ‘ከዓርሽ በላይ ነው’ የሚለዉን ሁሉ አላህ በነገራቸው መሰረት ሳይጨምሩና ሳይቀንሱ ይቀበሉታል። ስላልተነገራቸው የባህሪ ምንነት ‘ከይፊያ’ ግን ምንም አይናገሩም። አህሉሱና ከአላህ ባህሪያት ጋር በተያዘ ፍጡራዊ የሆኑትን ጂሀ እና መካን ለአላህ አያጸድቁም። ቁርአናዊውን የ‘ዑሉው’ አስተምህሮ ተቀብለው ሲያፀድቁም፤ ሙዓጢላዎች እንደሚያስቡት... ✘ አላህ አንደኛ ሁለተኛ ተብሎ በሚቆጠረው የመላዕክት መኖሪያ ሰማይ ላይ ይኖራል እያሉ አይደለም። መላዕክትም በሰማይ ሰዎች በመሬት በሚኖሩበት መልኩ አላህም በሰማይ ይኖራል የሚል እምነት ያለው ሰው በእርግጥም በአላህ ክዷል። ✘ እንደዚሁ ሰማይ አላህን ይሸከመዋል ወይም ያካብበዋል ከሚልም አስተሳሰብ የጸዱ ናቸው። ይህ የአላህን ከፍጥረታቱ ጋር መቀላቀልን “ሁሉል” የሚያምኑ የቢድዓ አራማጆች እምነት ነው። ✘ አላህ በፍጥረተዓለሙ ዉስጥ በሚገኙት ስድስት አቅጣጫዎች ይገለጻል፤ ፍጥረተአለሙም ያካብበዋል ማለትን ፈፅሞ አያመላክትም። ይህንን ያለ ሰውም በአላህ ላይ ውሸትን ተናግሯል፣ መንገድንም ስቷል። አህሉሱና ይህ ሁሉ ጥመት ስለመሆኑ አይወዛገቡም። ይቀጥላል... @abujunaidposts

🔊 አል ፉቲሓ እና አል ሐቃህ #ኸሊል_ረህመቶ 🍂||• #تلاوات_تعجبني •||🍂 የመስጂድ ሀምዛ (አደም በዳኔ) የ1432ሒ የተራዊሕ ቲላዋ تلاوة الأخ خليل رحمتوا من ذكريات التراويح والقيام بمسجد حمزة في أديس أبابا https://t.me/abujunaidposts/148

🔖 የቁርአን ወዳጆች 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ የ 50 ደቂቃ ሙሀደራ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/147 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

የ ‘አል–ኡሱሉ ሠላሣህ’ ኪታብ ጭብጦች እና የተደራጀው የማጠልሸት ፕሮፓጋንዳ! """""""""""""""""""""""""""""" ✍ አቡ ጁነይድ ሳላሕ አሕመድ አል ኡሱሉ ሠላሣህ (ሦስቱ መሰረተሰዊ መርሆዎ ኪታብ) ወሳኝ የአኼራ ጥያቄዎችን በማስታወስ ቁርአንና ሐዲሥን መሰረት አድርጎ ለጀማሪ ተማሪዎች የተዘጋጀ ምርጥ ትምህርት ነው። ቁርአንና ሱናን መሰረት አድርጎ የተከተበው ይህ መፅሐፍ፤ ከቅርብ ግዜ ወዲህ ዘርፈ ብዙ የማጠልሸት ፕሮፓጋንዳዎች ኢላማ አድርገውታል። በበርካታ ሀዲሶች የተብራሩ ግልፅ መሰረቶችን የሚያብራራውን ድንቅ መልእክት ሲያጠለሹ፤ የኩፍር መፅሐፍ፣ መፅሀፈ ስላሴ፣ የወሓቢያ ካሪኩለም ወዘተ... በማለት ተማሪዎችን ለማሸማቀቅ ይሞክራሉ። በተለይ አንዳንድ አደብ ያጡ ኹራፊዮች የነጃሳ መሰረቶች "ኡሱሉ ነጃሳ" ይሉታል። ለመሆኑ ተውሂድ የማይመቻቸውን ወገኖች እንቅልፍ ያሳጣው አል ኡሱል አሰላሳህ የሚዳስሳቸው ቁምነገሮች ምን ምን ናቸው? በሸይኽ ሙሐመድ ኢብኑ አብድልወሀብ የተዘጋጀው ይህ መፅሀፍ አንድ ሰው ጌታውን ነብዩን እና ዲኑን መገንዘብ እንዳለበት ይመክራል። መፅሀፉ አንድን ቁምነገር ለማስተላለፍ መረጃን ብቻ በመጥቀስ ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ከፍተኛ ተቀባይነትን አትርፏል። በመፅሀፉ በዋናነት የተዳሰሱት ሶስቱ መሰረታዊ ጉዳዮች በሐዲሥ ላይ በቀጥታ የቀብር ጥያቄ መሆናቸው ተዘክሯል። ሁለቱ መላእክቶች እነዚህን ጥያቄዎች እንደሚጠይቁ የሚገልፀው ሐዲሥ በኢማሙ አህመድ የተዘገበ ሐዲሥ የታወቀ ሲሆን፤ ሌላም ሀዲሶች እነዚህን መሰረታዊ አጀንዳዎች አንስተዋቸዋል። ከአል ዓባስ ኢብኑ አብደልሙጠሊብ የተዘገበው ሐዲሥ እንዲህ ይነበባል። عن العباس بن عبد المطلب في صحيح مسلم أنَّه سمع رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول:" ذاق طعم الإيمان مَن رضي بالله ربًّا، وبالإسلام ديناً، وبمحمد رسولاً" رواه مسلم «አላህን በጌትነት፣ ኢስላምን በሀይማኖትነት ሙሐመድን በመልእክተኝነት ወዶ የተቀበለ የኢማንን ጣዕም አጊኝቷል» ሙስሊም ዘግበውታል ተመሳሳይ መልእክት ያለውን የአቡ ሰዒድ አልኹድሪይ ሐዲሥም ኢማሙ ሙስሊም ዘግበውታል። በማጠልሸት ፕሮፓጋንዳ ተጠቅተው ሳያውቁት ሀሰትን ለሚያራግቡ ሁሉ መፅሀፉን እንዲማሩት እየመከርን ለተዛላፊዎቹ አላህ ልብ የሰጣቸው ዘንድ ፀሀፊውንም አላህ ይምራቸው ዘንድ እንለምነዋለን። ባለፉት አመታት የተውሂድ ተጣሪዎች ላይ ወሓቢያ የሚል ስያሜ በመለጠፍ ከፍተኛ የማጥላላት ዘመቻዎች መካሄዳቸው ግልፅ ነው። ለመሆኑ ሰዎች ወሓቢያ ተብለው የሚፈረጁበት መስፈርት ምን ይሆን? ሸህ ሙሐመድ ቢን አብድልወሀብ ከኖሩባቸው አካባቢዎች በራቁት እንደ ህንድ ባሉ አገሮች ከቁርአን እና ከሱና እንዲሁም ከቀደምት አበዎች የተወረሱ አስተምህሮቶች ከእሳቸው ዳእዋ በብዙ ምእተአመታት ቀድመው የተስፋፉ የአህሉልሐዲሥ ዳእዋዎች ይታወቃሉ። በሰሜናዊው አፍሪካ በየመን እና በብዙ አረብ አገራትም ሸይኹን ሳያውቁ ነገር ግን ተመሳሳይ ግንዛቤና ጥሪ የነበራቸው ብዙ ናቸው። ከተላላቅ የአልጄሪያ ኡለማዎች መካከል እ.ኤ.አ 1960 ያለፉት ሸይኽ ጠይብ አል–ዑቅቢ "እንዲህ ቢሉኝ እንዲህ አልኳቸው" በሚል ርእስ ባሰፈሩት ወግ ላይ ይህንን ብለዋል፤ «ሰዎች ‘ያንተ እምነት የወሓብዮች አይነት ነው’ ሲሉኝ፤ "ይህ ከሆነማ ወሀብዮች ማለት የአላህን አንድነት የሚያረጋግጡ (ሙወሂዶች) ናቸው ማለት ነው" በማለት እመልስ ነበር» ሲሉ ፅፈዋል።» ምንጭ፦ ሺሀብ ጋዜጣ ኦክቶበር 27/1927 በሌላም ፅሁፋቸውም፤ «በዳእዋ ስራ ህዝባችንን ግንዛቤ ማስጨበጥና በትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ ማነፅ እንፈልጋለን። ይህንንም በሁለት ነጥቦች ማስቀመጥ ይቻላል። 1) ከአላህ በስተቀር ማንንም አለማምለክ፤ 2) አላህን የምናመልከው እርሱ በደነገገውና ከሱ ዘንድ በመጣው መመሪያ መሆን አለበት። ወሃብያ ማለት፤ አላህ ለባሮቹ በደነገገው መልኩ እርሱን በብቸኝነት ማምለክ ከሆነ፤ ይህ አላህን የምናመልክበት ዲናችን፣ መዝሃባችንም ነው። ገር የሆነው መንገዳችን እሱ ነው። በዚህ ላይ ኖረን በዚሁ አቋም ላይ እንሞታለን። በአላህ ፍቃድም ከሚድኑት ሆነን እንቀሰቀሳለን» ምንጭ፦ ሱና ጋዜጣ አፕሪል 22 1933 እትም ካቀረበው ጽሁፋቸው እውነት ነው! ባሁኑ ጊዜ፤ የኢስላምን ብርሐን ከጃሂሊያ ፅልመት የለየ፤ አላህን በብቸኝነት አምልኩ፤ ከቀብር አምልኮ፣ ቅዱሳንን ከመማፀን እንዲሁም ከማንኛውም የባእድ አምልኮ ተግባር እንራቅ... ያለ ሁሉ ወሀብይ ይባላል። በተለይም ባሁኑ ዘመን የጃሂሊያን ሽርክ ለማንገስ የሚሯሯጡ አካላት ዘንድ ወሀቢያ የሚለው ታፔላ የጧት ማታ መዝሙር ሆኗል። ሀቁ ግን፤ ከሸይኽ ሙሐመድ አብዱልወሀብ ዳእዋ በፊትም ይሁን በኃላ፤ እራሱን ከተፅእኖ አላቆ ላስተዋለ ሁሉ፤ ቅዱሳንን ማምለክ ከኢስላማዊ አስተምህሮ ጋር ፍፁም የሚጋጭ የሽርክ ተግባርና የጃሂሊያ ቅሪት መሆኑን አያጣውም! ኢስላም ማለት የአላህን አንድነት በማረጋገጥ ለርሱ ትእዛዛት ማደር መሆኑ ያጠራጥራልን? አላህ ሆይ! ከኛ መካከል በጃሂሊያ የሽርክ ጥሪ የተሸነገሉን ሁሉ የተውሒድን ብርሃን አሳያቸው! ባጢል ልቦናቸውን ሰውሮታልና በጥበብህ ወደ ተፈጥሯዊ ምልከታቸው መልሳቸው! አሚን! ከነሲሓ መጽሔት ቅጽ Vol1 ቁጥር 1 |๏ መደብ | ነሲሓ ብዕር http://nesiha.com/blog/Vol1/01/index.php?Article=24

🔗 የሙስሊም ወጣቶች ሚና እና ሃላፊነት 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 👌 ወጣቶች አድምጡ... አስተውሉ! 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/143 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🍂||• #تلاوات_تعجبني •||🍂 📖 [ أَفَمَن یَعۡلَمُ أَنَّمَاۤ أُنزِلَ إِلَیۡكَ مِن رَّبِّكَ ٱلۡحَقُّ كَمَنۡ هُوَ أَعۡمَىٰۤۚ إِنَّمَا یَتَذَكَّرُ أُو۟لُوا۟ ٱلۡأَلۡبَـٰبِ] الرعد ١٩ إبراهيم عسيري #ኢብራሂም_ዓሲሪይ https://t.me/abujunaidposts/142

በካፊሮች በዓል እንኳን አደረሳችሁ ማለት ይፈቀዳልን? በበአላት ሰሞን በተደጋጋሚ እገሌና እገሌ ላይክ አድርገውታል ከሚለን ፖስቶች መካከል ከፊሎቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክቶች ናቸው። ለጌታ መወለድ፣ ለጌታ መሰቀል፣ ለጌታ ሞቶ መነሳት (ትንሳኤና) መሰል ክስተቶች እንኳን አደረሳችሁ ሲባል ሼር ወይም ላይክ የሚያደርጉ ብዙ እህትና ወንድሞችን አስተውያለው። አንዳንዴ በስህተት ሌላ ግዜም ነገሩን እንደቀላል በመውሰድ የሚፈፀም ሊሆን ይችላል። ሆኖም እጅግ ከባድና በአኼራ ዋጋ የሚያስከፍል መዘናጋት ነው!! በካፊሮች በአል፤ እንኳን አደረሳችሁ... እንኳን ደስ አላችሁ... እንኳን አብሮ አደረሰን ማለት እነሱን ለማስደሰትም ይሁን ለመመሳሰል ከአላህ ዲን መንሸራተት እና የካፊሮችን ኩፍር የመናገር ስነልቦና መካብ ስለሆነ ክልክል ነው። መከባበር እና አብሮነትን ለማሳየት ከእምነታችን መንሸራተት አይጠበቅብንም። ዲን ከምንም በላይ ነውና ሸሪዓን መተላለፍ ፍፁም ጥፋት ነው!! ፈጣሪ ወለደ ተወለደ የሚለው አስተምህሮ የጥፋትነቱ ክብደት ሰማያትንና ምድርን ሊሰነጥቅ እንደሚቀርብ ቁርአን ይነግረናል። አላህን የሚያስቆጣ ተግባር በመፈፀማቸው እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት ከሙስሊም አይጠበቅም!! (وَقَالُوا۟ ٱتَّخَذَ ٱلرَّحۡمَـٰنُ وَلَدࣰا * لَّقَدۡ جِئۡتُمۡ شَیۡـًٔا إِدࣰّا * تَكَادُ ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تُ یَتَفَطَّرۡنَ مِنۡهُ وَتَنشَقُّ ٱلۡأَرۡضُ وَتَخِرُّ ٱلۡجِبَالُ هَدًّا * أَن دَعَوۡا۟ لِلرَّحۡمَـٰنِ وَلَدࣰا * وَمَا یَنۢبَغِی لِلرَّحۡمَـٰنِ أَن یَتَّخِذَ وَلَدًا * إِن كُلُّ مَن فِی ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تِ وَٱلۡأَرۡضِ إِلَّاۤ ءَاتِی ٱلرَّحۡمَـٰنِ عَبۡدࣰا * لَّقَدۡ أَحۡصَىٰهُمۡ وَعَدَّهُمۡ عَدࣰّا * وَكُلُّهُمۡ ءَاتِیهِ یَوۡمَ ٱلۡقِیَـٰمَةِ فَرۡدًا) [«አልረሕማንም ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡ ከባድ መጥፎን ነገር በእርግጥ አመጣችሁ፡፡ በእርሱ (በንግግራቸው ምክንያት) ሰማያት ሊቀደዱ፣ ምድርም ልትሰነጠቅ፣ ጋራዎችም ተንደው ሊወድቁ ይቃረባሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅ አለው ስለአሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅን መያዝ አይገባውም!! በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ (በትንሣኤ ቀን) ለአልራሕማን ባሪያ ኾነው የሚመጡ እንጂ ሌላ አይደሉም] Surah Maryam 88 - 95 ለመሆኑ አንድን ካፊር ለሀይማኖታዊ በአል እንኳን አደረሰህ ስትለው፤ ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ አይደለምን? እንኳን አደረሰህ... ጌታ ተወልዶ ተሰቅሎ ሞቷል ብለህ ለማወጅ፣ ለመስቀል ለመስገድና የፈጣሪን ክብር የሚነኩ ንግግሮችን ለመናገር እንኳን በቃህ! እንኳን አደረሰህ... ማርያም ፈጣሪዋን ወለደችው፤ በመጠቅለያም ጠቀለለችው እያልክ ለመዘመር እንኳን በቃህ! የኩፍር ተግባርን ለመከወን ከሆነ የደረሰው ለምንስ እንኳን አብሮ አደረሰን እንላለን? እውቁ አሊም ኢብኑል ቀይም ረሂመሁላህ ይህ ተግባር የተከለከለ ስለመሆኑ የኡለማዎች የጋራ አቋም መሆኑን በመጠቆም እንዲህ ብለዋል፤ «ኩፍርን ብቻ በሚያንፀባርቁ የሀይማኖታቸው መገለጫዎች እንኳን አደረሳችሁ...እንኳን ደስ ያለችሁ ማለት ሀራም መሆኑ የሁሉም ሊቃውንት ስምምነት ያለበት ነው። ለምሳሌ አንድ ሙስሊም በነሱ በዓላትና ፆም ጊዜ፤ «በአሉን የተባረከ ያድርግልህ» ወይም «መልካም የደስታ በአል ያድርግልህ» እና መሰል የደስታ መግለጫዎችን ቢያስተላልፍ፤ ተናጋሪው ከኩፍር ቢድን እንኳ ከባድ ወንጀል ነው የፈፀመው። ይህም፤ ልክ «እንኳን ለመስቀል ሰገድክ» ብሎ ደስታን እንደመግለፅ ነው! ይህ እንደውም፤ አንድ ሰው ነብስ በማጥፋቱ፣ አልኮል በመጠጣቱ፣ ዝሙት በመፈፀሙና በመሰል ተግባራት እንኳን ደስ ያለህ ከማለት በወንጀልነት የከበደ እና አስቀያሚ ነው። ለኢስላማዊ ድንጋጌዎች ተገቢዉን ክብር የማይሰጡ ብዙ ሰዎች ይህንን ይፈፅማሉ። ምን ያክል የሚያስጠላ የግባር እንደፈፀሙም አያስተውሉም። ቢድአ፣ ኩፍር እና ወንጀሎች በመፈፀማቸው እንኳን አደረሰህ፣ እንኳን ደስ ያለህ እና መሰል የደስታ መግለጫዎችን ያስተላለፈ፤ እራሱን ለአላህ ቁጣና ጥላቻ የተገባ እንዲሆን የሚያደርግ ምክኒያት ፈፅሟል» አህካም አህሉዚማህ የዘመናችን ፈቂህ ሸይኽ ኡሰይሚን ረሂመሁላህ እንዲህ አሉ «ካፊሮችን እንኳን አደረሳችሁ ማለት ኢብኑል ቀይም እንዳለው የዚህን ያክል ከባድ የሆነበት ምክኒያት እነርሱ የሚፈፅሟቸውን የኩፍር መገለጫዎች ማፅደቅ ስለሆነ ነው። ምንም እንኳን ለራሱ ይህንን ኩፍር መፈፀምን ባይወድም እነሱ መፈፀማቸውን ወዷልና። ሙስሊም ደግሞ የኩፍር መገለጫዎችን መውደድም ይሁን ሌሎችን እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት አይፈቀድለትም።» መጅሙዑ ፈታዋ ወረሳኢል አሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን 3/44 በተመሳሳይ መልኩ፤ ክሪስማስም ሆነ ሌሎች በአላት ላይ ስጦታ ወይም ፓስት ካርዶችን መለዋወጥ፤ እንዲሁም ማንኛውም ደስታን መግለጫ የሆኑ ነገሮችን መፈፀም በአሉን መካፈል ስለሆነ የተከለከለ ነው!! በዚህ ፅሁፍ መጠቆም የፈለኩት ምንም አይነት ማህበራዊ ግንኙነት ሀራም ነው የሚል መልእክት አይደለም። በተለይም ከክርስቲያን እና አይሁዶች ጋር ባለን ማህበራዊ ግንኙነቶች ላይ የተፈቀዱ ብዙ በመልካም የመኗኗር እሴቶች አሉን። ሆኖም ሀይማኖታዊ ወሰኖች የሉም ማለት አይደለም። የተፈቀደውን ስንተገብር እንደ ያልተፈቀደ ጋብቻ፣ በአላት ላይ መሳተፍ፣ ለሞቱት የአላህን ማርታ መለመንና ባጠቃላይ በዲን መመሳሰልን ግን በፍፁም አንፈፅምም። ይህንን የእምነትና የሀይማኖት ወሰን መናድ አይቻልም። ማንነታችንን ማክበር፣ ግንኙነታችንን በዲናዊ ገደቦች ማጠር ብሎም አለመሟሟት ለሌሎች ሞራል ዲንና ማንነት ከመጨነቅ ይቀድማል። ዲን ከምንም በላይ ነውና ከመሸማቀቅ እንውጣ። ይህ የዲናችን መገለጫ እንጂ እንደ ማክረርና ፅንፈኝነት የሚታይ አይደለም። በነገራችን ላይ የአንድ እምነት ተከታይ ከሌሎች ለመቀራረብ ብሎ ከራሱ እምነት ጋር የሚጣላበት ሁኔታ ድሮ ቀርቷል። ሌሎቹም ቢሆኑ ይህ በኛ ሀይማኖት አልፈቀድም እና ይቅርታ ይሉሀል። (فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِّبِینَ * وَدُّوا۟ لَوۡ تُدۡهِنُ فَیُدۡهِنُونَ * وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافࣲ مَّهِینٍ) አስተባባዮችንም አትታዝዙ፡፡ ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡ [Surah Al-Qalam 8 - 10] ወላሁ አዕለም አላህ ከጥፋት ሁሉ ይጠብቀን! ____ አቡጁነይድ ረጀብ 24/1437 ዓ.ሒ / ሜይ 1/ 2016 ከጥቂት ማሻሻያዎች ጋር https://t.me/abujunaidposts/141

ጥንቃቄ! قال الحافظ الذهبي رحمه الله : 👈🏼 فكَمْ مِن رجل نطق بالحق، وأمر بالمعروف .. فيُسلِّط الله عليه مَن يؤذيه ! ▪ لِسوءِ قصده ▪ وحُبّهِ للرئاسة الدينية ! 📒 [ السّير : (١٩٢/١٨) ] አል ሐፊዝ አዝ ዘሐቢይ ረሂመሁላህ እንዲህ ብለዋል፦ (ሐቅን የሚናገር እና በመልካም የሚያዝ... ሆኖ ሳለ በመጥፎ አላማውና የዲን ስልጣንን በመውደዱ ምክንያት አላህ አዛ የሚያደርገውን አካል የሚያዝበት ስንት ሰው አለ!) ሲየሩ አዕላሚ’ኑበላዕ ቅፅ 18 ገፅ 192 ________________ @abujunaidposts

يَعِزُّ غَنِيُّ النَفسِ إِن قَلَّ مالُهُ ويَغنى غَنِيُّ المالِ وَهوَ ذَليلُ وَلا خَيرَ في وِدِّ اِمرِئٍ مُتَلَّونٍ إِذا الريحُ مالَت مالَ حَيثُ تَميلُ جَوادٌ إِذا اِستَغنَيتَ عَن أَخذِ مالِهِ وَعِندَ اِحتِمالِ الفَقرِ عَنكَ بَخيلُ فَما أَكثَرَ الإِخوان حينَ تَعدّهُم وَلَكِنَهُم في النائِباتِ قَليلُ @abujunaidposts

🔗 ንፁሕ ልብ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/137 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔗 ተውሒድ በሱረቱል ከሕፍ ታሪኮች 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ የ 41 ደቂቃ መልዕክት 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/136 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

ዱዓ ወደ ፈጣሪ ወይስ ፍጡራን? አላህ እንጂ ሌላ ማንም በማይችለው ጉዳይ ላይ ከአላህ ሌላ የሆነን አካል መለመን፣ እርዳታን እና ጥበቃን መጠየቅ እንዲሁም ድረሱልን ማለት … እነዚህ የተለያዩ የዱዓእ ወይም የፀሎት ክፍሎች ናቸዉ። ኑዕማን ኢብኑ በሺር በአስተላለፉት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዱዓእ ለአላህ ብቻ የሚገባ አምልኮ መሆኑን እንዲህ በማለት ይገልፁልናል፤ “ዱዓእ እርሱ እራሱ አምልኮ ነው” ኢማሙ አህመድ፣ ቲርሚዚይ እና ሌሎችም ዘግበውታል ሽርክ ማለት ለአላህ ብቻ የሚገባን ዒባዳ (አምልኮ) ለሌላ አሳልፎ መስጠት ነው፡፡ ስለሆነም ከላይ የጠቀስናቸዉን የተለያዩ የዱዓእ ክፍሎች ለነብያት፣ ለመላኢኮች (መላእክት) ፣ ለጂኖች (ለአጋንንት)፣ ለሞቱም ሆነ በህይወት ሳሉ ደጋግ የአላህ ባሮች፣ ለአላህ ወዳጆች (ወልዮች) … ወዘተ ማዋል ከትልቁ ሽርክ ውስጥ የሚመደብ ተግባር ነው፡፡ ፍጡራንን “ያ ረሱለላህ፣ ያ ዐሊይ፣ ያ ሰይዳ ፋጡማ፣ ያ ሁሰይን፣ ያ አብዱልቃድር ጀይላኒ፣ ያ ሰይዳ ዘይነብ፣ ያ ነጃሺ፣ ያ ኑርሁሰይን፣ ያ አብሬት፣ ያ ቃጥባሪ፣ ያ አልከሰዬ፣ ያ ሐጂ አሊዬ … ወዘተ እያሉ አላህ እንጂ ሌላ ማንም ሊፈፅመው በደይችለው ጉዳይ ላይ ለምሳሌ፡- ልጅ የለኝምና ልጅ ስጡኝ ፣ ታምሜያለሁና ፈውሱኝ፣ ተርቤያለሁና ሲሳይን ለግሱኝ፣ ፣ ተጨንቂያሁና ከጭንቅ አውጡኝ፣ ፈርቼያለሁ እና ከአደጋ ጠብቁኝ፣ ከጀሀነም እሳት ጠብቁኝ፣ ለጀነት አብቁኝ፣ አማላጅ ጠበቃ ሁኑኝ… በማለት እነሱን መጠራትና መማፀን እና ድረሱልኝ ማለት በጥብቅ የተከለከለ ግልፅ የሽርክ ተግባር ነው፡፡ ይህ አይነቱ ጥሪ ሽርክ መሆኑን ከሚያመላክቱ እጅግ በጣም በርካታ የቁርአን እና የሐዲስ መረጃዎች መካከል ጥቂቶቹን ብቻ ለመጠቆም እምክራለሁ፡፡ አላህ እርሱ እንጅ ሌላ ማንም በማይችለው ጉዳይ ላይ ሌላን እርዳታ እንዳንጠይቅ ቃል ሲያስገባን እንዲህ ይላል፡- (ﺇِﻳَّﺎﻙَ ﻧَﻌْﺒُﺪُ ﻭﺇِﻳَّﺎﻙَ ﻧَﺴْﺘَﻌِﻴﻦُ) ﺍﻟﻔﺎﺗﺤﺔ : ٥ "አንተን ብቻ እናመልካለን አንተንም ብቻ እርዳታ እንለምናለን፡፡" አልፋቲሀ:5 እንዲሁም አላህ የሰው ልጆች ከደጋሚ፣ ከመተተኛ እና ከጠንቋይ፣ ከአጋንንት እና ከሌሎች እርኩሳን አካላት ክፋት እና ሴራ በእርሱ ብቻ አንዲጠበቁ ያዛል፡፡ አላህ መልዕክተኛውን ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ እንዲሉ አዟቸዋል፦ ﻗُﻞْ ﺃَﻋُﻮﺫُ ﺑِﺮَﺏِّ ﺍﻟْﻔَﻠَﻖِ ‏( 1 ‏) ﻣِﻦْ ﺷَﺮِّ ﻣَﺎ ﺧَﻠَﻖَ ‏( 2 ‏) ﻭَﻣِﻦْ ﺷَﺮِّ ﻏَﺎﺳِﻖٍ ﺇِﺫَﺍ ﻭَﻗَﺐَ ‏( 3 ‏) ﻭَﻣِﻦْ ﺷَﺮِّ ﺍﻟﻨَّﻔَّﺎﺛَﺎﺕِ ﻓِﻲ ﺍﻟْﻌُﻘَﺪِ ‏( 4 ‏) ﻭَﻣِﻦْ ﺷَﺮِّ ﺣَﺎﺳِﺪٍ ﺇِﺫَﺍ ﺣَﺴَﺪَ ‏( 5 ) "በል «በተፈልቃቂው ጎህ ጌታ እጠበቃለሁ፡፡ ከፈጠረው ፍጡር ሁሉ ክፋት፡፡ ከሌሊትም ክፋት ባጨለመ ጊዜ፤ በተቋጠሩ (ክሮች) ላይ ተፊዎች ከኾኑት (ደጋሚ) ሴቶችም ክፋት" (አል ፈለቅ 1-5) አላህ ብቻ እንጂ ሌላ ማንም በማይችለው ጉዳይ ላይ አንድ ሰው ከችግር እንዲያወጣውም ይሁን ጥቅምን እንዲያስገኝለት ሌላን አካል ድረሱልኝ ብሎ መማፀኑ ችግሩን እንደማያስወግዱለት ወይም ጉዳቱን እንደማይመክትለት ከመግለፁም ባሻገር ይህ ተግባርና እምነት ክህደት እንደሆነ ተናገሯል፡፡ ﻗﺎﻝ ﺗﻌﺎﻟﻰ : ‏(ﻭَﻣَﻦْ ﺃَﺿَﻞُّ ﻣِﻤَّﻦ ﻳَﺪْﻋُﻮ ﻣِﻦ ﺩُﻭﻥِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻣَﻦ ﻻ ﻳَﺴْﺘَﺠِﻴﺐُ ﻟَﻪُ ﺇِﻟَﻰ ﻳَﻮﻡِ ﺍﻟْﻘِﻴَﺎﻣَﺔِ ﻭَﻫُﻢْ ﻋَﻦ ﺩُﻋَﺎﺋِﻬِﻢْ ﻏَﺎﻓِﻠُﻮﻥَ) ﺍﻷﺣﻘﺎﻑ : ٥ – ٦ "እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስም ለእርሱ የማይመልስለትን (ጣዖት) ከአላህ ሌላ ከሚጠራ ሰው ይበልጥ የተሳሳተ ማነው? እነርሱም ከጥሪያቸው ዘንጊዎች ናቸው፡፡ ሰዎችም በተሰበሰቡ ጊዜ (ጣዖቶቹ) ለእነርሱ ጠላቶች ይኾናሉ፡፡ (እነሱን) መገዛታቸውንም ከሓዲዎች ይኾናሉ" (አል አህቃፍ 5-6) ﻋﻦ ﺍﺑﻦ ﻣﺴﻌﻮﺩ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﺃﻥ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﻗﺎﻝ : ‏( ﻣﻦ ﻣﺎﺕ ﻭﻫﻮ ﻳﺪﻋﻮ ﻣﻨﺪﻭﻥ ﺍﻟﻠﻪ ﻧﺪﺍً ﺩﺧﻞ ﺍﻟﻨﺎﺭ ‏) ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﺒﺨﺎﺭﻱ ዓብድላህ ኢብኑ መስዑድ በአስተላለፉት ሐዲስ የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ ፦ “ከአላህ ውጭ ሌላን አካል ለአላህ አጋር አድርጎ መለመንን ሳይተው (ተውበት ሳያደርግ) የሞተ ሰው እሳት ገባ” (ቡኻሪ ዘግበውታል።) ﻓﻔﻲ ﺍﻟﺤﺪﻳﺚ ﺍﻟﺼﺤﻴﺢ ﻗﺎﻝ ﺍﻟﻨﺒﻲ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﻻﺑﻦ ﻋﺒﺎﺱ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻬﻤﺎ : ‏( ... ﺇﺫﺍ ﺳﺄﻟﺖ ﻓﺎﺳﺄﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺇﺫﺍ ﺍﺳﺘﻌﻨﺖ ﻓﺎﺳﺘﻌﻦ ﺑﺎﻟﻠﻪ ‏) ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﺘﺮﻣﺬﻱ ﻭﻗﺎﻝ ﺣﺪﻳﺚ ﺣﺴﻦ ﺻﺤﻴﺢ በሌላ ሐዲስም የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦ “መለመንን ስትፈልግ አላህን ብቻ ለምን፣ እርዳታንም ብትፈልግ በአላህ ብቻ ተረዳ” (ቲርሚዚይ ዘግበውታል) አላህ ሁላችንንም እርሱን በብቸኝነት ለማምለክ ይወፍቀን። በተውሒድ ኖረን የምንሞት ያድርገን። ወቢላሂተውፊቅ T.me/abujunaidposts

እንደ ተውሒድ አይነት ፀጋ የለም! እንደ ሙወሒድ ሰው ሐብታም የለም!! አልሐምዱሊላህ!! @abujunaidposts

የሙስሊሞች አንድነት 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ የ 44 ደቂቃ መልዕክት 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/132 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

ወቅታዊ ብስራትና እና ወሳኝ ማሳሰቢያ ኮሮና ብዙ የምንሳሳላቸውን ውድ ሰዎች እያሳጣን ነው። ባለፉት ሁለት ወራት ኡማውን ብዙ የሚጠቅሙ ታላላቅ መሻይኾች ሳይቀር በኮሮና ምክንያት ተለይተውናል። ሁሉም የአላህ ውሳኔ ስለሆነ ወደን እንቀበላለን እንጂ አናማርርም። አልሐምዱሊላህ ችግሩና ተጋላጭነቱ እየሰፋ መዘናጋታችንም እየጨመረ መምጣቱን እናስተውላለን። ምክንያቱ ደግሞ የበሽታው ስፋትና ፍጥነት በአብዛኞቻችን ዘንድ በጥንቃቄ የሚዘለቅ አይደለም ከሚል ተስፋ የመቁረጥ ስሜት የመነጨ ይመስለኛል። በአላህ ከመመካት ጋር ሞራላችንን አድሰን ጥንቃቄያችንን ጨምረን እንድንቆይ ከሚያበረታቱን መልካም ዜናዎች መካከል በከፍተኛ ደረጃ ስኬታማ የሆኑ ክትባቶች መገኘታቸው ነው። በቅርቡ 90% ውጤታማ የሆነ ከትባት ተገኝቶ እንደነበር ይታወሳል። አሁን ደግሞ በ43,000 ሰዎች ላይ ተሞክሮ 94.5% ስኬታማ የሆነ ክትባት ይፋ ተደርጓል። ክትባቱ ታህሳስ መጨረሻ ተጀምሮ እስከ ሚያዝያ ድረስ በአለማችን ሁሉም አካባቢዎች ተደራሽ እንደሚሆን የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት በትላንትናው ምሽት ይፋ አድርጓል። ሀገራችንም በቀዳሚነት እድሉን ከሚያገኘቱት ሀገራት እንደምትሆን ከዚህ ቀደም ተገልጿል። ይህ መልካም ዜና በቀረው ግዜ እንደቀድሞው ሁሉ ለማስክ እና ሳኖታይዘር ትኩረት ለመስጠት የመስጂዶችንም የጥንቃቄ መመሪያዎች ተቀብሎ ለመተግበር ያበረታታል። ስለሆነም የክትባቱን መልካም ዜና አብስረን ሰዎች ተስፋ ከመቁረጥ እንዲወጡ እናድርግ። ከሰላምታና ርቀትን ከመጠበቅ አንፃር የምናስተውላቸውን ስህተቶች ለመቅረፍ እንደግብአት እንጠቀምበት። አላህን በመለመን እና በሱ ከመመካት ጋር የተቻለንን ጥንቃቄ በማድረግ ሁላችንም እንበረታ ዘንድ አደራ እላለው። አላህ ከውጫዊም ይሁን ከውስጣዊ በሽታዎች ሁሉ ሁላችንንም ይጠብቀን! አኹኩም አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ህዳር 9/2013 T.me/abujunaidposts