uk
Feedback
የአማራ ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል

የአማራ ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል

Відкрити в Telegram

የአማራ ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል ሁሉንም የአማራ ምሁራን በአንድ ጣራ ስር አሰባስቦ በህዝባችን የኢኮኖሚያ ሽግግር አጀንዳዎች ላይ እንዲወያዩ ለማድረግ የተቀረፀ ማእከል ነው:: ምሁራን አዳዲስ ሃሳቦችን በማንሳት የሚወያዩበት የሚከራከሩበት መፍትሄዎችንም ለህዝቡ፣ ለመንግስትና ለሁሉም የኢኮኖሚው ተዋናዮች የሚያበረክቱበት የሃሳብ ገበታ ነው:: Contact us @AmharaCETABot

Показати більше
Країна не вказанаКатегорія не вказана
2 432
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 день
Архів дописів
በቀን 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ሊትር የምግብ ዘይት የማምረት አቅም ያለው ፊቤላ የዘይት ፋብሪካ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተመረቀ። የሀገሪቱን የምግብ ዘይት አቅርቦት 60 በመቶ የመሸፈን አቅም እ
+3
በቀን 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ሊትር የምግብ ዘይት የማምረት አቅም ያለው ፊቤላ የዘይት ፋብሪካ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተመረቀ። የሀገሪቱን የምግብ ዘይት አቅርቦት 60 በመቶ የመሸፈን አቅም እንዳለው የተነገረለት ፊቤላ ኀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ከምግብ ዘይት ምርት በተጨማሪ የሰሊጥ ማቀነባበሪያ፣ ሳሙና እና የእንስሳት መኖ ያመርታልም ነው የተባለው። በባለሃብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ የተገነባው ፋብሪካው 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጭ ተደርጎበታል። ለ3 ሺህ ዜጎች የሥራ እድል ይፈጥራል ተብሏል። ምርቱን ከነገ ጀምሮ ለገበያ ያቀርባል። ዘጋቢ፡- ዘገባው የአብመድ ነው

የቡሬ የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመረቀ ************************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የቡሬ የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክን መርቀው ከፍተዋል። በምረቃ ስነ ስር
+4
የቡሬ የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመረቀ ************************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የቡሬ የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክን መርቀው ከፍተዋል። በምረቃ ስነ ስርአት ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር እና ሌሎችም ከፍተኛ የፌደራል የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ኢንዱስትሪ ፓርኩ በተለይም የግብርና ምርቶችን በፋብሪካ በማቀነባበርና እሴት ጨምሮ ለውጭ ገበያ በማቅረብ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እገዛው የጎላ መሆኑም በምረቃው ላይ ተገልጿል። ዘጋው፦ የEBC ነው

Debre Berhan International Investment, Trade and Finance Expo to be held from January 10_18 2013 Debre Berhan City Administration Industry and Investment Office Head, Berhan Gebrehiwot, said preparations are underway to hold the first international investment, trade and finance expo at the Emperor Zera Ya'aqob Stadium in Debre Berhan from January 2 to 9, 2021. He said the international expo is organized in collaboration with North Shoa Zone, Debre Berhan City Administration and Debre Berhan City Industry and Investment Office in collaboration with Puma Media and Promotion as well as Nablis Communication. The purpose of the expo is to strengthen the growing investment flow in Debre Berhan and Shoa woredas and city administrations in general, attract local and foreign investors, create linkages between investment and financial institutions and provide a good opportunity for producers and distributors to promote their products, Berhan said. Debre Berhan is an economic and commercial center of East Amhara, a city that is on the path of development and growth. He called on local and foreign investors, traders, manufacturers and distributors to participate in this international expo. Source: Invest Amhara Telegram Page

የአማራ ክልል ኢንደስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በክልሉ የመጀመሪያ የሆነውን አግሮ ኢንደስትሪ ፓርክ ግንባታ ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡ *** የኢንደስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ
የአማራ ክልል ኢንደስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በክልሉ የመጀመሪያ የሆነውን አግሮ ኢንደስትሪ ፓርክ ግንባታ ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡ *** የኢንደስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደሴ አስሜ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በሀገሪቱም ሆነ በክልሉ የመጀመሪያ የሆነው የቡሬ የተቀናጀ አግሮ ኢንደስትሪ ፓርክ ግንባታ መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ ግንባታው በ2010 ዓ.ም ተጀምሮ በዚህ ዓመት መጠናቀቁን የተናገሩት ኃላፊው ጥር 30/2013 ዓ.ም ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል ብለዋል፡፡ ኤስ ዲ ጂ በተባል የመንግስት የልማት ድርጅት የበጀት ድጋፍ እስካሁን 4 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ወጭ መደረጉን የተናገሩት አቶ ደሴ 26 ሄክታር መሬት ለባለሃብቶች መሰጠቱን ገልፀው ቀጣይ ወደ ስራ ለሚገቡ ባለሃብቶች 46 ሄክታር መሬት ለመስጠት ታስቧል ሲሉ አቶ ደሴ ተናግረዋል፡፡ ኮርፖሬሽኑ የተለያዩ አገልግሎት ሰጭ ግንባታዎችን አጠናቆ ለስራ ያዘጋጀ ሲሆን የተለያዩ መሰረተ ልማቶችም ተሟልተውለት በውስጡም 13 ኪሎ ሜትር የመሰረተ ልማት መንገድ እንደተሰራም አቶ ደሴ አስረድተዋል፡፡ ኢንደስትሪ ፓርኩ በዋናነት እንደግብዓት የሚጠቀማቸው የግብርና ውጤቶች ማለትም ጥራጥሬ እና የቅባት እህሎች፣ የጓሮ አትክልቶች ፣ እንስሳትና የእንስሳት ተዋፅኦ ብቻ መሆኑን የተናገሩት ዋና ስራ አስፈፃሚው የግብዓት እጥረት እንዳይኖር ግብርናውን በእጅጉ ማዘመን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ግብርናውን ማዘመን አርሶ አደሩ በግብርና ስራው ተጠቃሚ እንደሚያደርግና በምግብ እራሱን እንዲችል እንደሚያግዝ የገለጹት ወና ስራ አስፈጻሚው አግሮ ፓርኩም ለ25 ሺህ ስራ አጥ ወጣቶች የስራ እድል እንደሚፈጥርም ገልፀዋል፡፡ ዘጋባው የአማራ ኮሙኒኬሽን ነው

የአክሲዮን ገበያ ማቋቋም ጥያቄ ...? ‹‹የአክሲዮን ገበያ ማቋቋም ጥያቄ የማይነሳበትና ወቅቱ የሚጠይቀው ወሳኝ አገራዊ ጉዳይ ነው›› አቶ ኤርሚያስ አመልጋ፣ የፋይናንስና የኢኮኖሚ ባለሙያ ‹‹ኢትዮጵ
የአክሲዮን ገበያ ማቋቋም ጥያቄ ...? ‹‹የአክሲዮን ገበያ ማቋቋም ጥያቄ የማይነሳበትና ወቅቱ የሚጠይቀው ወሳኝ አገራዊ ጉዳይ ነው›› አቶ ኤርሚያስ አመልጋ፣ የፋይናንስና የኢኮኖሚ ባለሙያ ‹‹ኢትዮጵያ የአክሲዮን ገበያ ቢኖራት ኖሮ፣ በአኅጉረ አፍሪካ ቁጥር አንድ ሳቢ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ትሆን ነበር፡፡ የአክሲዮን ገበያው መኖሩ የበለጠ ግልጽነት እንዲሰፍንና የኢትዮጵን የተፋጠነ ዕድገት የበለጠ ለማቀጣጠል የሚያስችል ተጨማሪ ካፒታል እንዲመደብ ያስችል ነበር፡፡ ኢትዮጵያ መደበኛ የአክሲዮን ገበያ ሳይኖራት እንኳን፣ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ከአፍሪካ አገራት በአንደኛ ደረጃ ላይ ናት፤›› ፣ የኒውዮርክ ስቶክ ብሮከር ማኔጂንግ ዳይሬክተር ኤውር ባች ግሬይሰን። ሪፖርተርን ጠቅሶ የዘገበው ጌጡ ተመስገን - Getu Temesgen ነው።

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ ! እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ ! እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

ከ3 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በጎንደር ከተማ ኢንቨስት ለማድረግ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ በጎንደር ከተማ ከ3 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በኢንቨስትመንት ለመሰማራት ጥያቄ ማቅረባቸውን ከተማ አስተዳደሩ ገልጿል፡፡ የከተማዋ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ባዩ አቡሃይ ከፍተኛ የቱሪስት ፍስት ያላት የጎንደር ከተማ በኢንቨስትመንት ዘርፍ ተጠቃሚ አልነበረችም፡፡ በተለይም በአካባቢው ከዓመታት በፊት የነበረው አለመረጋጋት በኢንቨስትመንት ፍሰቱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሮ እንደነበረ አስታውሰዋል፡፡ ይሁንና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የከተማ አስተዳደሩ ከኅብረተሰቡ ጋር ተቀናጅቶ ችግሩን ለመፍታት በሰራው ሥራ ሠላም በመረጋገጡ የኢንቨስትመንት ፍሰቱ መጨመሩን ተናግረዋል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ ባለሀብቶችን ለመሳብና የኢንቨስትመንት ፍሰቱን ለማሳደግ ሠላሙን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን የአካባቢውን እምቅ ሀብት በማስተዋወቅ በኩል ከፍተኛ ሥራ መሥራቱን ገልፀዋል፡፡ በአካባቢው ለኢንዱስትሪ ጥሬ እቃ የሚሆን ግብዓት መገኘቱና በቂ የሰለጠነ የሰው ኃይል አቅርቦት መኖሩ ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ባለፉት ሁለት ዓመታት የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ባለሀብቶች በአካባቢው በተለያዩ የልማት መስኮች ለመሰማራት ያሳዩት ተነሳሽነት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በከተማ አስተዳደሩ 33 ኢንዱስትሪዎች ማምረት መጀመራቸውንና 60 ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ግንባታቸውን በማጠናቀቅ ማሽነሪ በማስገባት ሂደት ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ በከተማዋ በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አምስት ወራት ከ3 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 75 ባለሀብቶች በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ለመሰማራት ጥያቄ ማቅረባቸውንም ተናግረዋል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ ጎንደርን የኢንዱስትሪ መዳረሻ ለማድረግ የበለጠ እንደሚሠራ የተናገሩት አቶ ባዩ በተለይም በአግሮ ኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎት፣ በማኑፋክቸሪንግና ሌሎች ዘርፎች መሠማራት የሚሹ አካላትን ለማስተናገድ ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታውቀዋል፡፡ “ለዚህ ስኬቱ ከተማ አስተዳደሩ ከፌዴራልና ከክልሉ መንግሥት ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው” ብለዋል፡፡ በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሠማሩ ባለሀብቶች በበኩላቸው አካባቢው ሠላም መሆን በኢንቨስትመንት ሥራቸው ተጠቃሚ ከመሆናቸው ባሻገር ለወጣቶች የሥራ ዕድል እንደፈጠሩ መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡ ጎንደር በተለይ ለጋርመንትና ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ምቹ መሆኗን ጠቅሰው ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች ቢሰማሩ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል። ዘገባው የአብመድ ነው

በቡሬ ከተማ የተገነባ የዘይት ፋብሪካ የሙከራ ምርት ጀመረ። ንብረትነቱ የአቶ በላይነህ ክንዴ የሆነው ፌቤላ ኃላፊነቱ የተ.የ.ማ በሙሉ አቅሙ ማምረት ሲጀምር 22 ሚሊዮን 500 ሺ ሊትር ዘይት ለአገር
+2
በቡሬ ከተማ የተገነባ የዘይት ፋብሪካ የሙከራ ምርት ጀመረ። ንብረትነቱ የአቶ በላይነህ ክንዴ የሆነው ፌቤላ ኃላፊነቱ የተ.የ.ማ በሙሉ አቅሙ ማምረት ሲጀምር 22 ሚሊዮን 500 ሺ ሊትር ዘይት ለአገር ውስጥ ገበያ ያቀርባል። ለውጭ ገበያ ከሚያቀርበው የምግብ ዘይት 61 ሚሊዮን 680 ሺ ዶላር የውጭ ምንዛሬ ያስገኛል። ዘገባው የአብመድ ነው

በ2.8 ቢሊዮን ብር የተገነባው የቦርት ማልት ብቅል ፋብሪካ በደብረብርሃን ከተማ ስራ ጀመረ። ፋብሪካው በሃገሪቱ ያሉ የቢራ ፋብሪካዎችን የብቅል ፍላጎትን ያሟላል ተብሎ ይጠበቃል ዘገባው የአብመድ ነው
በ2.8 ቢሊዮን ብር የተገነባው የቦርት ማልት ብቅል ፋብሪካ በደብረብርሃን ከተማ ስራ ጀመረ። ፋብሪካው በሃገሪቱ ያሉ የቢራ ፋብሪካዎችን የብቅል ፍላጎትን ያሟላል ተብሎ ይጠበቃል ዘገባው የአብመድ ነው

በራሳችሁ ተነሳሽነት ለተቋማችን አባል ጋዜጠኛ ወንዳጥር መኮነን አቀባበልና ሽልማት ላደረጋችሁ አባሎቻችን ሁሉ የከበረ ምስጋና እናቀርባለን። በዚህ አጋጣሚ ሁላችንም በየተሰማራንበት መደበኛ የስራ መስክ ጀግንነታችንን በማሳየት ለህዝባችን አለኝታ መሆን ይጠበቅብናል።

የአማራ ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል አባላት ለአባላቸውና ጓደኛቸው ጋዜጠኛ ወንዳጥር መኮነን የጀግና አቀባበል አደረጉ !! ከማዕከሉ አባላት መካከል 33 የሚሆኑት በግላቸው 70 ሺ ብር በማዋጣት ለአባላቸውና ጓደኛቸው በጋዜጠኛው መኖሪያ ቤት በመገኘት አቀባበል በማድረግ ለእሱና ለባለቤቱ የክብር ስጦታ አበርክተዋል።

የአማራ ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል አባላት ለተማሪዎች የዩኒፎርም ድጋፍ አደረጉ። የአማራ ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል (አኢሽማ) አባላት "አንድ የአኢሽማ አባል ለአንድ ዩኒፎርም" በሚል መሪ ቃል ባሰባሰቡት
+2
የአማራ ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል አባላት ለተማሪዎች የዩኒፎርም ድጋፍ አደረጉ። የአማራ ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል (አኢሽማ) አባላት "አንድ የአኢሽማ አባል ለአንድ ዩኒፎርም" በሚል መሪ ቃል ባሰባሰቡት ገንዘብ ለ 156 የባህር ከተማ ተማሪዎች በ 62,400 ብር ወጭ ለተማሪዎች ዩኒፎርም አሰፍተዋል። የተሰፋውን ዩኒፎርም ዛሬ በፈለገ-አባይ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ባካሄደው ዝግጅት ላይ ርክክብ አድርጓል። በዝግጅቱ ላይም የባህር ዳር ከተማ ትምህርት መምሪያ ም/ኃላፊ አቶ መላክ ጀመረ፣ የአኢሽማ አመራሮችና አባላትና ሌሎችም የከተማዋ አመራሮች ተገኝተዋል። አኢሽማ ከነደፋቸው አስር አላማዎች ውስጥ አንዱ የኢኮኖሚ ሽግግር መሰረት የሆነው ትምህርት ላይ የመስራት ዕቅድን በገንዘብ አቅም ማነስ ለመማር የተቸገሩ ተማሪዎችን በማገዝ ተጀምሯል። ድጋፍ የተደረገላቸው የፈለግ-አባይ፣ ጠይማ፣ ሽምብጥ፣ አፄ ሠርፀ-ድንግልና ቁልቋል ትምህርት ቤት ተማሪዎች ናቸው። በተጨማሪም አኢሽማ በቀጣይ በትምህርት ላይ ሊሰራቸው ያቀዳቸው ዕቅዶች ብሎም ወደ ትግበራ የገባባቸው ስራዎች ይፋ ተደርጓል። መቀመጫውን በቤልጂየም ሀገር ባደረገው የአኢሽማ የትምህርት ፕሮጀክት በሆነው አደይ የበጎ አድራጎት ድርጅት አስተባባሪነት በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች የሚተገበር የቤተ-መፅሐፍት ግንባታ ፕሮጀክት እየተቀረፀ መሆኑ ይፋ ተደርጓል። በሌላ በኩል በቤልጅየም አገር የተሰበሰበ ከ1000 በላይ መፅሐፍትን ጨምሮ ልዩ ልዩ የትምህርት መርጃ መሳሪያዎች ወደ ሀገር ውስጥ የገባ ሲሆን በቅርቡ ለትምህርት ቤቶች እንደሚከፋፈል በፕሮግራሙ ላይ ተገልጿል።

አማራ ባንክ ለሚያካሂደው የምስረታ ጠቅላላ ጉባኤ እያንዳንዱ ባለ ባለአክሲዮን ከሚከተሉት አደራጆች አንዱን እንዲወክል ይጠበቃል። ለመረጃ ያክል፦ ውክልናው የሚያገለግለው ለአንድ ጊዜ ብቻ ነው።
አማራ ባንክ ለሚያካሂደው የምስረታ ጠቅላላ ጉባኤ እያንዳንዱ ባለ ባለአክሲዮን ከሚከተሉት አደራጆች አንዱን እንዲወክል ይጠበቃል። ለመረጃ ያክል፦ ውክልናው የሚያገለግለው ለአንድ ጊዜ ብቻ ነው።

የአማራ ባንክ ውክልናን በተመለከተ አጭር ማብራሪያ ፤ በዶ/ር ለጤናህ እጅጉ (የአደራጅ ኮሚቴው ም/ሰብሳቢ) 1. ማን ነው የሚወከል ? ከኮቪድ አንፃር እና የባንኩ ባለአክሲዮኖች ቁጥር ከ150,000 በላይ በመሆናቸው በባለ አክሲዮኖች እንዲወከሉ የሚፈለገው የባንኩ አደራጆች ናቸው ። ነገር ግን ተመራጭ አማራጭ ባይሆኑም ባለአክሲዮኖች የሚከተሉት ሁለት መብቶች አሏቸው ። አንደኛ ከአደራጆች ውጭ ያለ ሌላ ማንኛውም ሰው የመወከል መብት አላቸው ። ሁለተኛ ማንንም ሰው አልወክልም እኔ በቀጥታ ነው ስብሰባ የምሳተፈው ካሉም መብታቸው ነው ። ነገር ግን እነዚህን ሁለት አማራጮች በስፋት ጥቅም ላይ ከዋሉ በስብሰባው የሚገኘውን ሰው ቁጥር ያበዛብናል ። ይህ ሲሆን ደግሞ በኮቪድ እና ሎጂስቲክ ጉዳዮች ስብሰባው ማካሄድ ያስቸግረናል ። በዚህም የባንኩ ምስረታ ይጓተታል ። ስለዚህ ባለአክሲዮኖች ከላይ የተጠቀሱት ሁለት መብቶች ቢኖራቸውም የባንኩን ምስረታ ለማፍጠን ሲባል አደራጆችን እንድትወክሉና እና ምስረታውን እንድናፈጥነው ስንል በአክብሮት እንጠይቃለን ። ይህን ስንል ግን ባንኩ በአደራጆች ጉባኤ ብቻ ይመሰረታል ማለት አይደለም ። ሌላ ሰው በሚወክሉ ባለአክሲዮኖች ፤ በቀጥታ መገኘት በሚፈልጉ ባለአክሲዮኖች ፤ ከፍተኛ ድርሻ ባላቸው ባለአክሲኖች ፤ ብዙ ህዝብ በሚወክሉ ድርጅቶች ፤ ማህበራት ፤ እድሮች ወዘተ የሚካሄድ ይሆናል ። አደራጆችን ወክሉ ስንል የተሳታፊውን ቁጥር ለመቀነስ እንጂ አደራጆች ብቻ ስብሰባውን ያካሂዱታል ብላችሁ ያልተገባ ግንዛቤ እንዳትይዙ ለማሳሰብ እንወዳለን ። የባንኩ አደራጆች በቁጥር 34 ናቸው ። የአደራጆቹ ኘሮፋይል ውልክና በምትሰጡበት ጣቢያ በፖስተር የሚተዋወቅ ይሆናል ። ከእነዚህ አደራጆች ውስጥ ይወክለኛል የምትሉትን አንዱን አደራጅ ወክሉት ። የተጠናል ወይም የቡድን ውክልና መስጠት ይቻላል ። የተናጠል ውክልና ማለት አንድ ባለአክሲዮን አንድ አደራጅ ሲወክል ነው ። የቡድን ውክልና ማለት ደግሞ ለምሳሌ 10 የሚሆኑ ባለአክሲዮኖች ሰብሰብ ብለው በአንድ የውክልና ፎርም አንድ አደራጅ እንዲወክል ሲያደርጉ ነው ። የቡድን ውክልና በሌላ መልኩም ሊፈፀም ይችላል ። አስር ባለአክሲዮኖች በአንድ የውክልና ፎርም ላይ የየራሳቸውን የተለያየ ተወካይ መወከል ሁሉ ይችላሉ ። የውክልና እና የመላኪያ (ፖስታ) ወጭዎችን ከመቀነስ አንፃር እኛ የምንመርጠው የቡድን ውክልናን ነው ። በውክልናው ለአደራጁ የምትሰጡት መብት ሁለት ነው ። አንደኛው በጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተገኝቶ ውሳኔዎችን የማስተላለፍ ነው ። ሁለተኛ የባንኩን መመስረቻ ፅሁፍና መተዳደሪያ ደንብ እንዲፈርም ናቸው ። 2. ውክልና የሚሰጠው መቸና የት ነው ? ከህዳር 1-15 ፤ 2013 👉 በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ እና ድሬዳዋ የምትገኙ ባለአክሲዮኖች የምትወክሉት በየአካባቢያችሁ የሚገኝ የፌደራሉ ውልና ማስረጃ ፅ/ቤት እየቀረባችሁ ነው ። አዲስ አበባ ላይ በየክፍለ ከተማው ባለ የፌደራሉ ውልና ማስረጃ ፅ/ቤት ለአማራ ባንክ ብቻ የተመደበ መስኮት ስላለ እየቀረባችሁ ውክልና መስጠት ትችላላችሁ ። ከህዳር 16-30 ፤ 2013 👉 በአማራ ክልል የዞን ከተሞች ያላችሁ ባለአክሲዮኖች የምትወክሉት በምናመቻቸው የፌደራሉ ውልና ማስረጃ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ይሆናል ። ይህንን ወደፊት የምነግራችሁ ይሆናል ። ከህዳር 1-30 ፤ 2013 👉 በአማራ ክልል የወረዳ ከተሞች እና በሌሎች ክልሎች ያላችሁ ባለአክሲዮኖች የምትወክሉት በየአካባቢያችሁ የሚገኙ የወረዳ የውልና ማስረጃ አገልግሎት የሚሰጡ የፍትህ ተቋማት ነው ። ውክልናውን ከሰጣችሁ በኋላ በተራ ቁጥር 3 ከታች ከተጠቀሱ ዶክመንቶች ጋር በአማራ ባንክ የአዲስ አበባ የፖስታ ሳጥን ቁጥር 149 አድራሻ መላክ አለባችሁ ። 👉 በውጭ አገር የምትኖሩ ዳያስፖራ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የምትወክሉት ደግሞ በምትኖሩበት አገር ኤምባሲ በመቅረብ ይሆናል ። እናንተም ከላይ የተጠቀሱ ሙሉ ዶክመንቶችን በአማራ ባንክ ፖስታ ሳጥን መላክ አለባችሁ ። 3. ውክልናውን ለመስጠት የሚያስፈልግ ዶክመንት ፤ ለመወከል ስትመጡ የሚከተሉትን ዶክመንቶችን መያዝ አለባችሁ 👉 የታደሰ መታወቂያ ፤ የቀበሌ ፤ መንጃ ፈቃድ ፤ ፓስፖርት ወዘተ እንደ መታወቂያነት ያገለግላል ። 👉 አክሲዮን ስትገዙ የሞላችሁት የአማራ ባንክ ፎርም እና ገንዘቡን ገቢ ያደረጋችሁበት የባንክ ደረሰኝ ። 👉 ለህፃናት አክሲዮን ከገዛችሁ የልደት ሰርተፊኬታቸው ። ግልፅ ያልሆነ ነገር ካለ ብትጠይቁን ለመመለስ ዝግጁ ነን ።

የአማራ ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል የስራ አስፈፃሚ ስብሰባ በነገው ዕለት በባ/ዳር ከተማ ይካሄዳል !! ሰባት አባላት ያለው ስራ አስፈፃሚው ከአውሮፓ፣ ከአዲስ አበባና ከባ/ዳር በመምጣት በአካል ተገናኝቶ
የአማራ ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል የስራ አስፈፃሚ ስብሰባ በነገው ዕለት በባ/ዳር ከተማ ይካሄዳል !! ሰባት አባላት ያለው ስራ አስፈፃሚው ከአውሮፓ፣ ከአዲስ አበባና ከባ/ዳር በመምጣት በአካል ተገናኝቶ ይወያያል። የስብሰባው ዋናው አጀንዳ ያለፉት ሶስት ወራት አፈፃፀምን መገምገምና የቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ ይሆናል። በመሆኑም አኢሽማ በውይይቱ ውስጣዊ ጥንካሬውንና ድክመቱን ይለያል። ውጫዊ መልካም አጋጣሚዎችን እና ፈተናዎች ላይም ይመክራል። በመጨረሻም ድክመቶችን ቀርፎ ጥንካሬዎችን የሚያጎላ፤ እንዲሁም ፈተናዎችን ተቋቁሞ መልካም አጋጣሚዎችን ለመጠቀም የሚያግዝ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል።