uk
Feedback
NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)

NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)

Закритий канал

NISIR International Broadcasting Co. is an impartial and independent media agency operates as social media & multimedia production. Voice of voices ንሥር ኢንተርናሽናል ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የማያዳላ እና ገለልተኛ የመገናኛ ተቋም ነዉ። ማህበራዊ ሚዲያ እና መልታይሚዲያ እምራች ሁኖ ይሰራል። አማራ ድምፅ!

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)

Канал NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 28 384 підписників, посідаючи 8 809 місце в категорії Новини і ЗМІ та 1 162 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 28 384 підписників.

За останніми даними від 10 березня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -552, а за останні 24 години на 0, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 0%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає N/A% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 0 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 0 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 0.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
NISIR International Broadcasting Co. is an impartial and independent media agency operates as social media & multimedia production. Voice of voices ንሥር ኢንተርናሽናል ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የማያዳላ እና ገለልተኛ የመገናኛ ተቋም ነዉ። ማህበራዊ ሚዲያ እና መልታይሚዲያ እምራች ሁኖ ይሰራል። አማራ ድምፅ...

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 11 березня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Новини і ЗМІ.

28 384
Підписники
Немає даних24 години
-1017 днів
-55230 днів
Архів дописів
የተከበራችሁ በውጭው ዓለም የምትኖሩ የኅልውና ትግላችን ደጋፊ ወገኖቻችን፣ የተከበራችሁ በሞት፣ በመፈናቀል፣ በሰቆቃ ላይ የምትገኙ ግፉአን አማራዎች፣ የተከበራችሁ የአማራውን ሥርዓታዊ ግፍ በሃሳብም በግብርም የምትቃወሙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፣ ክቡራትና ክቡራን!!! ከሁሉ አስቀድሜ ከሠላማዊ ትግል እስከ ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግላችን ውድ ሕይወታቸውን ለከፈሉ የትግሉ ሰማዕታት ያለኝን ታላቅ አክብሮት መግለጽ እፈልጋለሁ። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በጽኑ አለት ላይ የተመሠረተ የአማራ ሕዝብን በአራቱም አቅጣጫ አቅፎ የሚያታግል ተቋም መሆኑን እየገለጽኩ ተቋማችን አፋብኃ መሠረቱ የትግሉ ሰማዕታት ደምና አጥንት ባይሆን ኖሮ ከውስጥም ከውጭም በተሰማሩ የጠላት አንጃዎች ፈርሰን፣ ተበትነን ነበር። ቅሉ የያዝነው ትግል መሠረቱ የትግሉ ሰማዕታት የተሰውለትን እውነት፣ የታገሉበትን ዕውቀት፣ የመከሩበትን ሐቀኛ አመክንዮ ያነገበ በመሆኑ ወደፊት ከመወንጨፍ ውጭ አማራጭ ስለሌለው በጽናት ከዛሬ ደርሰናል። የአፋብኃ ሠራዊት የጽናት ምንጩ አንዲት የማትተካ ሕይወታቸውን ለሕዝባቸው፣ ለታሪካቸው፣ ለባሕላቸው፣ ለእምነታቸው በጥቅሉ ለአማራዊ ማንነታቸው አሳልፈው የሰጡት የእነ ሜጀር ጄኔራል ውባንተ አባተ፣ የእነ አርበኛ ዮሐንስ ዓለማየሁ፣ የእነ አርበኛ ሳጅን አደም አሊ (አባ ናደው)፣ የእነ አርበኛ ሃምሳ አለቃ አባይ እንዲሁም የግፍ ግዞተኛው የአርበኛ አሰግድ መኮንንም የአደራ ቃል ነው። ስለሆነም መራብን፣ መቁሰልን፣ ብርድና ሙቀቱን ሁሉ ሕይወትን ከመስጠት በታች ነውና በጽናት ታግሰን፣ ሐቀኛ የመርኅ ተቋም እንድንፈጥር በሕይወት የተለዩን አርበኞች ምኞት ነበራቸውና ለምኞታቸው ማሳኪያ፣ ለዓላማቸው ማስፈጸሚያ እንዲሆን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይልን (አፋብኃ)ን መሠርተን በመታገል ላይ እንገኛለን። ክቡራትና ክቡራን ወገኖቻችን፦ • አፋብኃ የተሰው የትግሉ ሰማዕታት በደማቸው ቀለምነት ከትበው የሰጡን የአደራ ቤታችን ነው። አፋብኃ በየማጎሪያ ቤቱ በአማራዊ ማንነታቸው በግዞት የሚማቅቁ ምሁራን፣ ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞች ነጻ መውጫ ተቋም ነው። አፋብኃ በዘር ተኮር ጭፍጨፋ መዋቅራዊ አዋጅ የተጨፈጨፉ ሕጻናት፣ ሴቶች፣ አረጋውያን የሰቆቃ ድምጽ እረፍት የሚነሳው የትግል ተቋም ነው። o አፋብኃ ውስጥ ሕጻን አይሻ መሃመድ አለች፣ o አፋብኃ ውስጥ ሃምሳ አለቃ አባይ አለ፣ o አፋብኃ ውስጥ ሜ/ጄ ውባንተ አባተ አለ፣ o አፋብኃ ውስጥ ሳጅን አደም አሊ አለ፣ o አፋብኃ ውስጥ ዮሐንስ ዓለማየሁ አለ። በመሆኑም አፋብኃ በአርበኝነት የተሰው ጓዶቻችን አደራ፣ ምኞት እንዲሁም በሕይወት የሚገኙ አደራ ተቀባይ ታማኝ አርበኞች የነፍስ ትስስር፣ አማራዊ ተጋምዶ የተሸመኑበት ተቋም መሆኑን አውቃችሁ ለዓላማችን መሳካት የሕይወት ዘመን ባለቤቶች ጭምር እንድትሆኑ ነው ይህ ሲምፖዚዬም የተዘጋጀው። • አፋብኃ በእውነት፣ ለእውነት፣ ስለእውነት የጀመርነውን ትግል ቅርጽ ፈጥሮ፣ መርኅ ሕግ እና አሠራር አበጅቶ የተገባደደውን ትግላችንን መቋጫ ተቋማችን በመሆኑ በአንድ ጎን እንተኩሳለን፣ በአንድ ጎን እናሰለጥናለን እናደራጃለን፣ በአንድ በኩል ዲፕሎማሲ፣ አድቮኬሲና ፕሮፓጋንዳ እንሠራለን። እነዚህን ሁሉ ሥራዎች ለማከናወን ብዙ የሙያ ስብጥር፣ በርካታ የሰው ኃይል አስፈላጊ ስለሆነ አፋብኃን ከመደገፍ አፋብኃ ወደ መሆን ትሸጋገሩም ዘንድ ጥብቅ ጥሪ ማስተላለፍ እፈልጋለሁ። ክቡራትና ክቡራን ወገኖቻችን፦ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ድርጅታዊ መርኅን አክብሮ፣ የሕዝባችንን ኅልውና በዘላቂነት ለማረጋገጥ አስቻይ የአንድነት መደላድሎችን በሰከነ ውይይት ፈትቶ እንደሚታገል በተደጋጋሚ ገልጸናል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በመላው ዓለም የምትገግኙ ወገኖቻችን • የሙያ ተደጋግፎት፣ • የዓላማ ተደጋግፎት፣ • የአማራዊነት ተደጋግፎት ፈጥራችሁ በምትኖሩባቸው ከተሞች ሁሉ አንድ እንድትሆኑ፣ ምን እናድርግ በሚል ሁለትም፣ ሦስትም፣ በርካታም ሆናችሁ በጋራ እንድትመክሩ፣ ስለአንድነት እንድትመክሩና በማኅበራዊ ሚዲያ፣ በፎክ ሚዲያ፣ በሜንስትሪም ሚዲያ የሚደረጉ መነቃቀፎችን፣ የሚቀርቡ ዘለፋዎችንና ፍረጃዎችን አስወግዳችሁ • አንድ ዓይነት ጩኸት፣ • አንድ ዓይነት ቋንቋ፣ • አንድ ዓይነት ትንፋሽ፣ • አንድ ዓይነት እርምጃዎችን ልንራመድ የምንችለው ስንቀራረብ፣ ስንነጋገር፣ አንድ ስንሆን ብቻ መሆኑን አውቃችሁ አንድ ሁኑ፣ አደራ አደራ አደራ አንድ ሁኑ። ያኔ በሁሉም ዘርፍ ተጽእኖ ፈጣሪዎች መሆን እንችላለን። • ዓለም የተጽእኖ ፈጣሪዎች፣ • ድል አድራጊነትም የተጽእኖ ፈጣሪዎች ስለሆነች ድል አድራጊነታችንን በአጭር ጊዜ እንድናደርገው አንድ እንሁን፣ ዓለም አቀፋዊ ተጽእኖም እንፍጠር። ያኔ በቀናት ውስጥ አይደለም በሰአታት ውስጥ እናሸንፋለን ማለት እፈልጋለሁ። ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) አርበኛ ኢንጂኒዬር ደሳለኝ ሲያስብሸዋ አመሠግናለሁ። ጳግሜ 2/2017/ዓ.ም

➾አርበኛ ዘመነ ካሴ በአፋብኃ ሲምፖዚየም ያስተላለፈው ታሪካዊ መልዕክት እና ድንቅ ንግግር‼ የተከበራችሁ የዚህ ውይይት ተሳታፊዎችና ተከታታዮች ክቡራን የማሕበራት ተወካዮች የተወደዳችሁ የመገናኛ ብዙሃን ሙያያተኞችና ድርጅቶች ውድ የድርጅታችን አፋብኃ አመራሮችና የሠራዊታችን አባላት ሁላችሁም በመላው ዓለም ያላችሁ አማራዎችና የአማራ ወዳጆች፤ በቅድሚያ የአክብሮት ሠላምታዬ ይድረሳችሁ!! ከትናንት ጀምሮ እየተካሔደ ያለው ውይይትና እየቀረበ ያለው መልዕክት የአማራ ወገናችን ራሱን ከፈፅሞ ጥፋት ለመታደግ የሚያደርገው የሕልውና እና የፍትሕ ርትዕ ትግል አንድ ሁነኛ መገለጫ ነው። ዛሬ በዚህ መድረክ ተሰባስበን ስንመክር በአማራነታችን ላይ የታወጀውን ጥፋት ለመመከት፡ ከምንግዜውም በላይ ንቃት ፈጥረን፡ አደረጃጀት አበጅተን፡ የትናንትን ጉድለት በዛሬ ጥረት አሟልተን ፡ነጋችንን የተሻለ የማድረግ ቁርጠኝነታችንን የምናድስበት ነው። ባለፉት ሁለት ዓመታት የአማራነት ንቃትና መሰባሰብ ከእነውስንነቶቹ  አመርቂ የሚባል እድገት አሳይቷል። ግዙፍ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅም በመፍጠር የመደራጀት ያደረ የቤት ስራችንን መመለስና ማረም ጀምረናል!! በአማራነት ላይ የተፈጠረው ንቃትና መሰባሰብ የዘመናት የጥቃት አዙሪትን ለመስበር በሚያስችል ግለት ውስጥ ይገኛል። ባለፉት ሁለት ዓመታት ራሳችንን አጠናክረናል !! ለሕልውናው የሚሰለፍ ሕዝባዊ ኃይል ፈጥረናል!! ሊያጠፋን የተነሳውን ጠላት በመመከት ማሸነፍ እንደምንችል አረጋግጠናል !! የዕጣፈንታችን ወሳኞች እኛ ነን ብለን ስንነሳ የመናጆነት፣ የተከታይነት፣ የአጃቢነት ልማዶችን ሰብረን የአማራዊ ማንነታችን እና ፍላጎቶቻችን በአማራ ልጆች የሚወሰንበት ምዕራፍ ለመክፈት ነውና ጀምረነው ብዙ ርቀት ሔደናል። የተከበራችሁ የዚህ መድረክ ተሳታፊዎች፤ አማራዎች ራሳችንን ብሎም አገራችንን ለማዳን አብዛኛውን የትግል መንገድ ሞክረነዋል። በዜግነት ፖለቲካና በአገር አንድነት ትግል አልፈናል። ሆኖም በአማራነታችን ላይ የታወጀውን ጥፋት አልመከትነውም። በዚያ መንገድ ኢትዮጵያን ከመስቀለኛ መንገድ መታደግ አልተቻለም። አሁን ለረጅም ጊዜ ያልሔድንበት በአማራነት ተደራጅቶ ራስን የመታደግ ትግል የጊዜው ቁልፍ ተልዕኮ ነው። አማራና አማራነት የዚህ ዘመን ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡ በአማራነት ላይ በተከፈቱ ጥቃቶች ውስጥ ገና ከማለዳው እነደጃዝማች ፀሐዩ እንቁስላሴ የገለጡት የወል ጥቃት መረዳት ተዳፍኖ የቀረ ነበር። ኋላም እነፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ያነሳሱት የአማራ ንቃት ቅስቀሳ ብዙም ሳይሻገር ቀርቷል። በረጅሙ ታሪካችን ውስጥ አማራነታችን ላይ ጥቃቶች በቀጠሉበት፥ በአማራነት መሰባሰብ እና የጋራ ተቋም መፍጠር ሳንችል ቀርተን አማራን የሚያሕል ሕዝብ የሕልውና አደጋ ውስጥ ይገኛል። ተቃርኖው ይገርማል !! አገር የመሠረተ ሕዝብ ፣ ይብዛም ይነስም የአገሪቱን ተቋማት የመሠረተና የመራ ሕዝብ፣ ለሺህ ዘመን ፀንተው የቆሙ መንፈሳዊ ተቋማትን ያደራጀ ሕዝብ ፣ ለዘመናት አገር የጠበቀ አርበኝነት ያለው ሕዝብ ፥ ራሱን ከሕልውና ጥቃት የሚመክትባቸው ተቋማት አጥቶ ዛሬ ላይ ደረሰ። አማራዎች ራሳችንን የምንጠብቅበት ሥርዓት፣ ፍላጎታችንን የምንገልጥባቸው አማራዊ ተቋማትን መፍጠር ዳገት ሆኖብን መኖራችን መገታት አለበት። ይህ ትግል "የአማራን ሕዝብ ሁለንተናዊ ሕልውና በዘላቂነት የማረጋገጥ ነው" ስንል የሕልውና መሠረቶቻችንን የሚሸከሙ ተቋማትን የመትከል መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም። የፋኖ አንድነት ተቋማዊ ጉዞ የዚያ ምሰሶ ይሆናል!! በአማራነት ተለይቶ መጠቃት በታወጀበት ዘመን እንኳ አባቶቻችንና እናቶቻችን ስለአገር እንጂ ስለአማራነታቸው አልመከሩም ፡ አልተሰባሰቡም፡  አልተደራጁም። ስለአገር ዋጋ መክፈላቸው ባልከፋ ፥ ሲከፍሉት የኖሩት ዋጋ ግን በአማራነታቸው ላይ የተከፈተውን የጥፋት ጦርነት ሊያስቆመው አልቻለም። የትናንት አለመደራጀት ለዛሬ ያወረሰን ምን እንደሆነ በውል ተገንዝበን ተነስተናል !! ትናንት ያልሠራነው ሥራ ቁጭት ካወረሰንና ለዛሬ ብርቱ ትግል ስንቅ ከሆነን በቂ ነው። ነጋችንን የምናሳምረው ግን በዛሬ የተባበረ ጥረታችን ነው!! ይሕ ትውልድ ለነገ የሚያሻግረው የጥቃት ውርስ ሊኖር አይገባም !! ይሕ የእኛ ትውልድ  የቤት ሥራውን ሳይሠራ ቀርቶ የነገው ትውልድ ጥፋትን እና ፈፅሞ መገፋትን ሊወርስ አይገባም!! ስለዚህ እንሰባሰብ !! በአማራነታችን እንደራጅ !! በአማራነት የመደራጀትና የመታገል ጉዳይ ግለሰባዊ እና ጠባብ ቡድናዊ ፍላጎትን መተው ይፈልጋል። በመካከለችን ያለ ትናንሽና መለስተኛ ቅራኔና ፀብን፥ ኩርፊያና ልዩነትን በመተውና በማቆየት ለወል ፍላጎታችን መሰለፍን ይጠይቃል። ብሔርተኝነት እንደዚያ ነው !! ከትናንትም ሆነ ከዛሬ ነገሮቻችን መካከል መርጦ መዘንጋት እና ለይቶ ማንሳትን ይፈልጋል !! ስለጋራ አማራዊ ፍላጎታችን የመሰለፍ ጥሪ ነው !! ያን ስናደርግ እንኳን ለአማራ ትውልድ፥ ለኢትዮጵያ እና ለሰው ልጆች ሁሉ የሚተርፍ ቁምነገር እንሠራለን!! የጋራ ጥቃት አንገሽግሾን የወጣን ታጋዮች ሁሉ እንደአማራ ስንመክር፣ እንደፋኖ ስንነጋገር  ከባድ የመሠለን ቀላል እንደሚሆን አይተናል። የራሳችንን ጉዳዮች በራሳችን ለመወሰን "የእብድ ገላጋይ..." አያሻንም።   እናም የጀመርነው የአንድነት ጉዞ የተማከለ አማራዊ አታጋይ ተቋም በመመስረት የሚቋጭ ይሆናል። ይሕ የአዲሱ አመት ድላችን ሆኖ ይመዘገባል!! የተወደዳችሁ የሕልውና ትግሉ ተሰላፊ ምሑራንና ማሕበራት፤ ያለነው እንቅልፍ አልባ ዘመን ነው። እኛን ለማጥፋት ፍፁም ጭካኔ እና ሙሉ ቆራጥነት ያለው ገዢ ጠላት ነው የገጠመን። የምናሸንፈው ከአጥፊው ጠላታችን በላይ ስንጨክን፣ ከገጠመን ደመኛ በላይ ስንተጋ፣ ከእነሱ በላይ ስንደራጅና አንድ ስንሆን፣ ከጠላቶቻችን በላይ ቆራጦች ስንሆን ነው። ከእነሱ በላይ ስንሠራ እንጂ በእነሱ ልክ እየተራመድንም አይደለም። ስለሆነም በዓለም ዙሪያ ያላችሁ የአማራ ምሑራን፣ የዲያስፖራ ማሕበራት፣ ሰፊው በወጭ አገር ያለህ ወገናችን እንድትሰባሰቡ በአንድ እንድትቆሙ ጥሪ ማቅረብ እፈልጋለሁ። ስለወገናችን የምንቻቻልበት፣ ስለራሳችን የምንመክርበት፣ የምንተሳሰብበት ፣ በእያንዳንዳችን ላይ ልዩ ተልዕኮ የወደቀብን ወቅት አሁን ነው። ከዚህ ወቅት በቀር ስለአማራና አማራነት የምንሰለፍበት የምንሠራበት የተለየ ጊዜ የለም። ዛሬ ነው !! እናም የአማራ ማሕበራት ከተበታተነ ጉዞ ውጡና ተሰባሰቡ!! በየአሕጉሩ አንድ ጠንካራ ሕብረት አቁሙ!! ምሳሌ ሁኑ!!  የአንድነት ፤ የዲፕሎማሲ ፣ የአድቮኬሲና ትብብር ምሳሌ ሁኑ!! በመጨረሻ ግን በዋነኛነት ፥ በመላው ዓለም የምትገኙ ማሕበራት፣ ምሑራንና መገናኛ ብዙሃን ሁሉንአቀፍ አማራዊ ጉዳዮቻችን የሚመከሩበት "የአማራ የምክክር ጉባኤ" በፍጥነት እንዲዘጋጅ ጥሪ አቀርባለሁ። አርበኛ ዘመነ ካሴ የአፋብኃ ሴንትራል ኮማንድና የምዕራብ አማራ ቀጠና ቴወድሮስ ዕዝ ሰብሳቢ አዲስ ትውልድ፣ አዲስ ተሰፋ፣ አዲስ አስተሳሰብ

ሰበር መረጃ!! ምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ ሀሮ አዲስ አለም ከተማ ፋኖ ቤተሰብ አላቹህ የተባሉ ንፁሀን አማራዎች በሙሉ ከቤታቸው እንዲወጡ እዬተደረገ ቤታቸው እዬታሸገባቸው ይገኛል። እንደምንጮች ገለፃ አማራ ላይ የተከፈተው የተቀናጀ ጥቃት በሁሉም ወለጋ ዞኖች ተባብሶ ቀጥሏል። በወለጋ አሁን የተያዘው አማራን ከወለጋ ማፅዳት የሚል ፕሮጀክት ነው ሲሉም ነው ምንጮች የገለፁ። ጳግሜ 2/2017/

የአፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ የሐዲስ ዓለማየሁ 7ኛ ክ/ጦር የየቦቅላ አባይ ብርጌድ በቀን 02/13/2017 ዓ.ም ደብረ ማርቆስ ላይ ልዩ ኦፕሬሽን ሰርቷል። ከተማ በመግባት አብማ ቀበሌ 04 ሙሉ ሆቴል ጀርባ ጎጆ መሿለኪያ አካባቢ የአረመኔው አገዛዝ ሰራዊት መመሸጊያ ላይ መብረቃዊ ጥቃት በመፈፀም በቦታው የነበሩ ምሊሻዎችን ሙትና ቁስለኛ አድርገዋል።በባንዳ ላይ የሚደረጉ ጥቃቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ። ከጉንደ ወይን ወደ ደብረ -ወርቅ ኮፖይ አድርሶ ሲመለስ ከቀኑ 8:30 ሠዓት ሽፋሬ በምትባል ንዑስ ከተማ ላይ 9ኛ ሳሙኤል አወቀ ክ/ጦር የሶማ ብርጌድ ጥቂት ሀይሎች ደፈጣ በመያዝ  አድማ ብተና በጫነ ካሶኒ ላይ የቦንብና የጥይት በረዶ በማዝነብ  ከፋተኛ ጀብ መፈፀም ተችሏል። በጠላት ላይ የደረሰ ኪሳራ፦6 የአድማ ብተና አባላት በቦንብ ተጨፍልቀው እሰከወዳኘው ሲሸኙ አራት የሚሆኑት የአድማ ብተና አባላት ደግሞ ከባድ ቁስለኛ ሁነው በፈለገ-ብርሀን ጤና ጣቢያ ውስጥ ይገኛሉ።የበተመሳሳይ አባኮስትር ብርጌድ የደፈጣ ጥቃት ሲፈፅም አብራጅት ብርጌድ ደግሞ የላምጌጅ ከተማን ተቆጣጥሮ ውሏል።ይህ በየቦታው በሚደረገው ጥቃት የደከመው አረመኔ ሰራዊት በገፍ እጁን ለፋኖ እየሰጠ ይገኛል። 1ኛ. አዲሱ ሞላ ከአድማ ብተና ተቀም ወደ አፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴወድሮስ ዕዝ 1ኛክ/ጦር ባህርዳር ብርጌድ ጊወንሻለቃ የተቀላቀለ ። 2ኛ.ናትናኤል አበበ የሬጅመንት ሶስት ሞርተር ምድብተኛ ከጠላት ካንፕ በመክዳት ወደ አፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ ጎጃም አገዉ ምድር ፫ኛ ክ/ጦር፣ የቢትወደድ አያሌዉ መኮነንን ብርጌድን የተቀላቀለ። 3ኛ.ሀብታም መለሰ የሚባል የአረመኔው አገዛዝ አሽከር የነበረ ሚሊሻ የአፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ የሐዲስ ዓለማየሁ 7ኛ ክ/ጦር አብራጂት ብርጌድን ተቀላቅሏል። 4ኛ.አበረ ገበረጌታ የተባለ የአረመኔው አሽከር ሚሊሻ ከየጁቤ ከተማ በመውጣት የአብራጂት ብርጌድን የተላቅሏል። 5ኛ. እውነቱ ምትኩ የተባ  የሚኒሻ አባል ከደብረ -ወርቅ ከተማ በመክዳት  9ኛ ሳሙኤል አወቀ ክ/ጦር ሶማ ብርጌድ ተቀላቅሏል። ሕዝባዊ ውይይቶችና ምክክሮች በአንደኛ ክፍለጦር እና 7ኛ ክፍለጦር  ነፃ ቀጠና ቀበሌዎች ተደርገዋል። በውይይቱም ሌቦችን በጥቆማ መያዝ እና የማያዳግም እርምጃ መውሰድ ተችሏል። አፋብኃ|ቴዎድሮስ ዕዝ ጳጒሜን 02/2017ዓ.ም

ሦስት የፖሊስ አመረራሮች ተገደሉ የፋኖ ቤተሰብ ናችሁ በሚል የሦስትና የአራት ዓመት ህፃናትን ጨምሮ በርካታ እናቶችንና አረጋውያንን ለእስር በመዳረግ ግፍና መከራ ሲፈፅሙ ነበር የተባሉ ሦስት የፖሊስ አመራሮች ከነ አጃቢዎቻቸው ተገደሉ።የፖሊስ አመራሮቹ የተገደሉት በተፈፀመባቸው የደፈጣ ጥቃት ሲሆን፡ ተሳፍረው ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀሱበት የነበረው ወታደራዊ ፓትሮልም ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተሰምቷል። ሕሊናቸውን በሆድ ቀይረው፡ አገዛዙ በወገናቸው ላይ ለሚፈፀመው የዘር ጭፍጨፋ ተባባሪ በሆኑ የፖሊስና የሚሊሻ እንዲሁም የአድማ ብተና አባላት ላይ የሚወሰደው ጥብቅና ከባድ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ፋኖ አስታውቋል። በደቡብ አማራ ቀጠና ኤፍራታና ግድም ወረዳ በቆሪ ሜዳ ቀበሌ ልዩ ስሙ ቀርሣ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ላይ ትናንት ጳጉሜ 01/2017 ዓ/ም አመሻሹን በተፈፀመ ደፈጣ ጥቃት ሦስት የፖሊስ አመራሮችና አምስት የአመራሮቹ አጃቢዎች መገደላቸውን የአሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ካወጣው መረጃ ለማወቅ ተችሏል። የፖሊስ አመራሮቹ፡ "ፋኖ ናችሁ፣ የፋኖ ቤተሰብ ናችሁ፣ የፋኖ ደጋፊ ናችሁ" በሚል የሦስትና አራት ዓመት ህፃናትን ጨምሮ በርካታ የወረዳው ነዋሪዎችን ለእስር በመዳረግ ሲያሰቃዩና አንዳንዶቹንም ከእስር እንዲለቀቁ ከ50ሺ ብር ጀምሮ እስከ አንድ መቶ ሺ ብር ድረስ እንዲከፍሉ በመጠየቅ ግፍና መከራ ሲፈፅሙ የነበሩ ናቸው ተብሏል። በእነዚህ የፖሊስ አመራሮች ትዕዛዝ ሰጭነት ታስረው የጠተየቀባቸውን ገንዘብ መክፈል ካልቻሉ ንፁኋኖት መካከል፡ "ለፋኖ ሲሰልሉ የተገኙ" ተብለው እንዲረሸኑና አንዳንዶቹም ከድብደባ ብዛት ከባድ የአካል ጉዳት እንዲደርስባቸው የተደረጉ ስለመኖራቸውም ተነግሯል። በእነዚህ ፀረ ሕዝብና የነፃነት አሜካላ እሾዎች ላይ የተጠናና ስኬታማ የሆነ ደፈጣ ጥቃትን በማካሄድ ግድያውን የፈፀሙት በአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና ብርጋዲየር ጄነራል አሳምነው ፅጌ ዕዝ ዓፄ ይኩኖአምላክ ክ/ጦር ስር የሚገኙት "ፀያይሞቹ አናብስት" የሚል ቅፅል ስም ያላቸው የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ብርጌድ የቃኝ አባላት መሆናቸውን ነው ከዕዙ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ለማረጋገጥ የተቻለው። ትናንት ጳጉሜ 01/2017 ዓ/ም አመሻሹን ደፈጣ ጥቃቱ የተፈፀመው በኤፍራታና ግድም ወረዳ ቆሪ ሜዳ ቀበሌ ልዩ ስሙ ቀርሣ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ ሲሆን፡ በዚህም ፋኖ የሕዝቡን እምባ  ያበሰ እጅግ ትልቅ ድል መቀዳጀቱ ነው የተነገረው።አመራሮቹ ደፈጣ ጥቃቱ የተፈፀመባቸው በልዩ ዞኑ ስር በምትገኘው ከጨፋ ሮቢት ከተማ ወደ አጣየ ከተማ እየተጓዙ ባሉበት ሁኔታ ነው የተባለ ሲሆን፡ ደቂቃዎችን ባልፈጀ ኦፕሬሽን በግፈኞች ላይ የመጨረሻውና ከባዱ እርምጃ ተወስዶቸዋል ተብሏል። በዚህ ደፈጣ ጥቃት ሦስቱ የፖሊስ አመራሮችን ጨምሮ አምስት አጃቢዎች በድምሩ ስምንት ፀረ ሰላምና ፀረ ሕዝብ ኃይሎች መገደላቸው ታውቋል።በጥቃቱ ከተገደሉት አመራሮችና የአመራሮቹ አጃቢዎች በተጨማሪ፡ ተሳፍረው ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀሱበት የነበረው ወታደራዊ ፓትሮልም ሙሉ በሙሉ መውደሙን ዕዙ አስታውቋል። ሕሊናቸውን በሆድ ቀይረው፡ አገዛዙ በወገናቸው ላይ በሚፈፀመው የዘር ጭፍጨፋ እንዲሁም ግፍና በደል ተባባሪ በሆኑ የፖሊስና የሚሊሻ እንዲሁም የአድማ ብተና አባላት ላይ የሚወሰደው ጥብቅና ከባድ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ፋኖ አስታውቋል።

ደ/ኤልያስና አካባቢው ላይ የመሸገው የብልፅግና ስርዓት ሀይል ንፁሀንን እየዘረፈና ንብረቶቹን እያወደመበት ይገኛል። በቀጠናው የዘረፋና የውንብድና ስራዎች በአገዛዙ ዘራፊና አሸባሪ ቡድን ተጠናክሮ ቀጥ
ደ/ኤልያስና አካባቢው ላይ የመሸገው የብልፅግና ስርዓት ሀይል ንፁሀንን እየዘረፈና ንብረቶቹን እያወደመበት ይገኛል። በቀጠናው የዘረፋና የውንብድና ስራዎች በአገዛዙ ዘራፊና አሸባሪ ቡድን ተጠናክሮ ቀጥሏል።የቀጋት ቀበሌ ልዮ ቦታ ጋርማ በምትባል ቦታ አቶ አንማው ተመስገን ከተባሉ ሽማግሌ ቤት በቀን 27ለ28/12/2017 ዓ.ም ሌሊት ፊታቸውን ጭንብል በመልበስ በወረዳዋ የተሰባሰቡ ሰላም አስከባሪ ነን የሚሉ የመንግስት ዘራፊና አሸባሪ ቡድኖች 1ኩንታል ስንዴ አንድ ኩንታል ዱቄት አንድ የአንገት ክታብ ከነሁለት ብር ቅጥል 1ድፍን ብር ቅጥል (ውድ ጌጣጌጦችን) በመዝረፍ ተሰውረዋል። ለዘረፋና ለውንብድና የተሰማሩት የአሸባርሪው አገዛዝ ቡድኖች ይህን እኩይ ድርጊት የፈጸሙት ፋኖ ነን በሚል ስም ሲሆን ፋኖን ከማህበረሰቡ ለመነጠል በማሰብ ነውና ማህበረሰባችን ይህን ሴራ መረዳት እና ፋኖ ይህን እኩይ ድርጊት እንደማያደርግ ማወቅ ይገባል። ሌላው የአማራውን ማህበረሰብ በኢኮኖሚ ለማዳከም በቀረጹት አጀንዳ መሰረት የማህበረሰብ ንብረቶችን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ እያቃጠሉ ይገኛል ሲል ቀስተ ደመና ብርጌድ አስታውቋል። ጷጉሜን 2/2017 ዓ.ም

ከደብረታቦር ከተማ በቅርብ ርቀት አቄቶ አከባቢ በአገዛዙ ኃይሎች ላይ በተፈፀመ ደፈጣ ጥቃት 20 ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ መደረጋቸው ታወቀ። መነሻቸውን የደቡብ ጎንደር ዞን መቀመጫ ከሆነችው ደብረ ታቦ
ከደብረታቦር ከተማ በቅርብ ርቀት አቄቶ አከባቢ በአገዛዙ ኃይሎች ላይ በተፈፀመ ደፈጣ ጥቃት 20 ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ መደረጋቸው ታወቀ። መነሻቸውን የደቡብ ጎንደር ዞን መቀመጫ ከሆነችው ደብረ ታቦር ከተማ አድርገው ወደ እስቴ መካነየሱስ ከተማ ሲጓዙ የነበሩ የፀረ አማራው አገዛዝ ስልጣን አስጠባቂ ወታደሮች፡ ልዩ ስሙ አቄቶ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ላይ ሲደርሱ በተፈፀመባቸው ደፈጣ ጥቃት 13 ወታደሮች ሲገደሉ፡ ሰባት ወታደሮች ደግሞ በከባድ ሁኔታ መቁሰላቸውን መረብ ሚዲያ በአፋብኃ በላይ ዘለቀ ዕዝ ከሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ 1ኛ ኮር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ለማመጋገጥ ችሏል።በዚህ ደፈጣ ጥቃት ከተገደሉ የአገዛዙ ወታደሮች መካከል የሕዝብን አደራ በምስር ወጥ ለውጠው እጃቸውን ለአገዛዙ ሰጥተው የነበሩ ከሃዲ ባንዳዎች ይገኙበታል ተብሏል። ጥቃቱ የተፈፀመው ትናንት ጳጉሜ 01/2017 ዓ/ም ሲሆን፡ ጥቃቱን በመፈፀም ድል የተቀዳጁት ደግሞ አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ 1ኛ ኮር በጉና ክፍለ ጦር መቅደላ አምባ ብርጌድ ስር የሚገኙት የናደው ሻለቃ አባላት መሆናቸውን መረብ ሚዲያ ከኮሩ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ጳግሜ 2/2017/ዓ.ም

የላምጌጅ በፋኖ ቁጥጥር ስር ገባች በዘመቻ ሰመአታት በርካታ ተጋድሎወችን ሲያደርግ የሰነበተው አፋብሀ ምእራብ አማራ ቀጠና ቴወድሮስ እዝ ሀዲስ ዓለማየሁ 7ኛ ክፍለጦር በባሶ ሊበን ወረዳ የምትገኘውን
የላምጌጅ በፋኖ ቁጥጥር ስር ገባች በዘመቻ ሰመአታት በርካታ ተጋድሎወችን ሲያደርግ የሰነበተው አፋብሀ ምእራብ አማራ ቀጠና ቴወድሮስ እዝ ሀዲስ ዓለማየሁ 7ኛ ክፍለጦር በባሶ ሊበን ወረዳ የምትገኘውን ታዳጊ ከተማ #የላምጌጅን ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥሯል። ጠላትም ወደ ወረዳው ዋና ከተማ የጁቤ ጓዙን እያንጠባጠበ ፈርጥጧል። ህዝቡም በአደባባይ ደስታውን እየገለጸ ነው። በዘመቻ ሰማእታት ሀዲስ ዓለማየሁ 7ኛ ክፍለጦር ከዚህ በፊት ኮርክ ከተማን በቋሚነት መቆጣጠሩ የሚታወስ ነው። ጳግሜ 2/2017/

የአ.ፋ.ብ.ኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር አባ ኮስትር ብርጌድ በቢቸና ከተማ፣የትመን ከተማ፣ወይራ ጠልማ ቀበሌ እንዲሁም ደባይ ጮቄ ብርጌድ እና የክፍለ ጦሩ ጥምር ኃይል በጋራ በመሆን በማህበረ ብርሃን ቀበሌ የሚገኜውን የአረመኔው ሰራዊት ላይ ሙትና ቁስለኛ አድርገዋል። በየትመን ከተማ ጠላት ይጠቀምበት የነበረው ካንፕ በቦንብ እና RPG መሳሪያዎች በኮስትር ልጆች ወድሟል ተቃጥሎል። ጳጉሜ 02/2017 ዓ.ም

የአስቴጉማ ተራራ ክፍለጦር በጠላት ወንበር አስጠባቂ ሚሊሻ ሀይል ላይ ርምጃ ወሰደ ‎ ‎በትላንትናው ዕለት የአስቴጉማ ተራራ ክፍለጦር በከሚሴ ልዩ ዞን ዳዋ ጨፌ ወረዳ ሰረት ቀበሌ የክፍለጦሩ አራተኛ ሻለቃ ሰርጎ በመግባት በብልፅግና ወንበር ጠባቂ የሚሊሻ ሀይል ላይ በተሰራው ኦፕሬሽን የጠላትን በርካታ ሀይል ሙት እና ቁስለኛ ተደርጓል።‎የአስቴጉማ ተራራ ክፍለጦር በተቆጣጠረችበት በሶስቱም ወረዳዎች ዳዋ ጨፌ ወረዳን ጨምሮ ጀግኖቹ ለህዝባቸው ከሚያደርጉት የልማት ስራዎች እንዳሉ ሆነው ‎ከበላይ አመራሮች የተሰጣቸውን መደበኛ ግዳጅ በሶስቱም ወረዳዎች ጠላትን ረፍት በመንሳት በጠላት ላይ ከፍተኛ የሆነ የሰብዓዊ ጉዳት እና የቁሳዊ ኪሳራ አድርሰውበታል። ‎ እንዲሁም በወረዳው መሽጎ ያለው የፋሽስቱ ወንበር ጠባቂ ወረዳ ካድሬ እና ሚሊሻ  በከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ በመግባት በመከላከያ ካምፕ ውስጥ እንዲሁም ከሚሴ ከተማ ድረስ በመሔድ እንደሚያድሩ እና ፋኖ መጣ አልመጣ በሚል ከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ እንደወደቁ የውስጥ ምንጮች ገልፀዋል ። ‎ ‎በሌላ መልኩ የአስቴጉማ ተራራ ክፍለጦር በተቆጣጠሩበት ቀጠና ርዕሰ መምህራንን እና መምህራንን በመሰብሰብ እና በማወያየት የተማሪዎችን የምዝገባ ቀን በተመለከተ ክፍለጦሩ መድረክ በመፍጠር እና በማወያየት የተማሪዎች የምዝገባ ቀን ከመስከረም 8 እና 9 እንጂመር በመድረኩ ተወስኗል።‎የተማሪዎች የምዝገባ ቀን ትንሽ ዘግየት ያለበትም ምክንያት በቀጠናው ከዚህ ቀደም 8 ንፁህ በአገዛዙ ሰራዊት በግፍ በመረሸናቸው የአርባ ቀን መታሰቢያቸው ይለፍ በማለት እና የህዝባችንን ስነልቦና እና ሞራል ለመጠበቅ ሲባል የመመዝገቢያ ጊዜ በዚህ ምክንያት የተራዘመ ቢሆንም ትምህርት ለትውልዱ አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት ተማሪዎች ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ እና ምዝገባው እንዲጀመር ከሚመለከታቸው የትምህርት ቤቱ መምህራን እና ርዕሰ መምህራን ጋር በመነጋገር ምዝገባው እዲጀመር ተወስኗል ሲል ክፍለጦሩ አሳውቋል። ጳግሜ 2/2017/

ከ43_በላይ_የጥምር_ሰራዊት_ፋኖን_ተቀላቀለ። የብልፅግና ስርዓት  ዙፋን አስጠባቂ የመከላከያ እና የሚሊሻ አባላት በስቦ ማስከዳት እየተበታተነ ነው።የዐማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 5ኛ ክፍለ ጦር የነበልባሉ ገረመው ወንዳውክ ብርጌድ ስቦ በማስከዳት የብልፅግናን ዙፋን አስጠባቂ የሚሊሻ እና የመከላከያ አባለትን እየበታተነ ይገኛል። የመከላከያ ሰራዊት አባል የነበረ መ/ወታደር ታደሰ ሞላ ለሚዲያችን እንደገለፁት ወደ ቋሪት ስንገባ ገነት አቦ ከተማ ላይ 28 ጌዜ ሞርተር ተኩሰናል፤  ፋኖ ላይ አንድም ጉዳት አልደረሰም ንፁሀን ነው የጎዳው፤ በዚህ ምክንያት ህዝብን ከሚወጋ  ኃይል ጋር አልዋጋም ብየ ስርዓቱን ክጄ ከእነሙሉ ትጥቄ ፋኖን ተቀላቅያለሁ ብሏል። እየፈራርሰ የመጣው የቋሪት ወረዳ የሚሊሻ አባል የነበረው ጌታሰው ተሰራ እንዳለው ነሐሴ 3/2017 ዓ.ም ነበልባሉ የገረመው ወንዳውክ ብርጌድ በገ/ማርያም ከተማ ባደረገው ውጊያ  በርካታ የሚሊሻ አባል መበተኑን ገልፆ፤ መጀመሪያም ስገባ ከወንድሞቸ ጋር ልዋጋ ሳይሆን ትጥቅ ከጠላት ታጥቄ ወይም ነጥቄ ለመውጣት ነበር፤ አላማየና ሀሳቤ ተሳክቶ ከሚሊሻ መሳሪያ ነጥቄ ከፍኖ ወንድሞቼ ጋር ተቀላቅያለሁ ብሏል። ሌላው የአገዛዙ ዙፋን አስጠባቂ የሚሊሻ አባል የነበረ ወጣት ይከበር ጫኔ እንዳለው ወደ ሚሊሻ የገባሁ መሳሪያ ለመታጠቅ ነበር ነገር ግን ፋኖ በነሃሴ 3/2017 ዓ.ም ባደረገው ውጊያ ሚሊሻ ላይ ብቻ ትኩርቱን በማድረጉ በርካታ የሚሊሻ አባላት ላይ ከፍተኛ እርምጃ በመወሰዱ ሀሳቤ ሳይሳካ ህይወቴን ለማቆየት በጀሌ ወጥቻለሁ ብሏል። አፋባኃ ምዕራብ አማራ ቴዎድሮስ ዕዝ 5ኛ ክ/ጦር ነበልባሉን የገረመው ወንዳውክ ብርጌድን ጳጉሜ 02/5017 ዓ.ም የተቀላቀሉ የአገዛዙ ዙፋን አስጠባቂ የነበሩ የመከላከያና የሚሊሻ አባላት:- 1.መ/ወታደር ዘሪሁን መና 403 ኮር  71ኛ ክ/ጦር 5ኛ ሻለቃ የነበረ 2. መ/ ወታደር ታደሰ ሞላ 403 ኮር 71ኛ ክ/ጦር  5ኛ ሻለቃ የነበረ 3. የሻምበል ንብርት ቀበሌ ግራርማ የሽል ሚሊሻ   ቲም መሪ  4. ሀይማኖት በለጠ ቀበሌ ጎምት ድዋሮ ሚሊሻ 5. የቻለ አልፈር  ቀበሌ ወይበይኝ ሚሊሻ 6. ጌታሁን በቀለ ቀበሌ አ/ሌ ገደል ሚሊሻ 7. ይርጋ አዕምሮ ቀበሌ አ/ሌባ ገደል ሚሊሻ 8.ይከበር ጫኔ ቀበሌ አ/ሌባ ገደል ሚሊሻ 9. በላይ ደረበው ቀበሌ ወይበይኝ ሚሊሻ 10 ካሳሁን ይታይህ ቀበሌ አ/ይበርት ሚሊሻ 11. ዘመኑ አየለ ቀበሌ ወይበይኝ ሚሊሻ 12. ይናገር ዋለ ቀበሌ ወይበይኝ ሚሊሻ 13. ይገርማል ዘርያቆብ ቀበሌ ጎምት ድዋሮ ሚሊሻ 14. አያና ደርበው ቀበሌ  ወይበይኝ ሚሊሻ 15. ጌታሰው ተሰራ ቀበሌ ጎምት ድዋሮ ሚሊሻ 16. ደጀኔ ወርቄ ቀበሌ ወይበይኝ ሚሊሻ 17. ይልቃል ወረቄ ቀበሌ ወይበይኝ ሚሊሻ 18. መኳንንት አንማው ቀበሌ ወይበይኝ ሚሊሻ 19. ፋኖስ ጫኔ ቀበሌ ወይበይኝ ሚሊሻ 20. አትንኩት አለምነህ ቀበሌ ቦረዝ በስኮስ ሚሊሻ 22. አብርሃም ጉልማ ቀበሌ አየን ይበርት ሚሊሻ 23. ተስፋሁን ጫኔ ቀበሌ ወይበይኝ ሚሊሻ 24. ሀብታሙ ጌታነህ ቀበሌ ወይበይኝ ሚሊሻ  ሻምበል መሪ 25. ደጉ የኔነህ ቀበሌ ጎሞት ድዋሮ ሚሊሻ 26. ካሳሁን ይታይህ ቀበሌ  አ/ይበረት ሚሊሻ 27. ገደፋው አሸብር ቀበሌ ወይበዬኝ ሚሊሻ ጋንታ መሪ 28. መላክ አያሌው ቀበሌ ወይበይኝ ሚሊሻ ቲም መሪ 29. ይከበር ጠብቄ ቀበሌ ወይበይኝ  የወረዳው ሰላምና ደህንነት ኃላፊ (ዋሌ ቢተው) አጃቢ የነበረ 30. መልሰው አወቀ ቀበሌ ቦረዝ በስኮስ ሚሊሻ 31. እንየው የደሜ ቀበሌ ቦረዝ በስኮስ ሚሊሻ 32.ካሳሁን እንግዳ ቀበሌ አየን ይበርት ሚሊሻ #ነሐሴ 04/2017 ዓ.ም ይፋ ያደረግናቸው 33ኛ. እንደግ ጋሻው __  ጀሌ 34ኛ. ይከበር ንጋቱ __ አንድ እግር ክላሽ 35ኛ. አዳነ ውባለም __ ጂንፎ ኤስኬኤስ 35ኛ. መኳንንት ተስፌ __ እንየው ከተባለ ሚኒሻ ክላሽ ነጥቆ የወጣ 36ኛ. እሱባለው መኮነን __ ጀሌ 37ኛ. አጠቃ አልፈር __ ጀሌ 38ኛ. ይግረም አንዷለም __ ጀሌ 39ኛ. በለው ገነት __ ጅንፎ ኤስኬኤስ 40ኛ. ግርማው መሰሉ __  ጀሌ 41ኛ. ጊዜው እውነቱ __ ጀሌ 42ኛ. ሚኪያሰ እንዳሌ __ ጀሌ 43ኛ. ዳንኤል አሁንም የዘገያችሁ ፍጠኑ፣ እንቀበላለን። ©ነበልባሉ ገረመው ወንዳውክ ብርጌድ ሕዝብ ግንኙነት ጳግሜ 02/2017 ዓ.ም

በጎንደር ከተማ አፈሳ ተጀመረ ትላንት ማምሻውን ጀምሮ ዛሬም የነቁ ወጣቶች ላይ እና የፋኖ ቤተሰቦች ላይ ያነጣጠረ አፈሳ መጀመሩን ምንጮች ገልፀዋል። ከፌደራል በመጡ ደህንነቶች አፈሳው እንደሚመራ የተገለፀ ሲሆን ፌደራል ፖሊስ፣ መከላከያ ፣ ምሊሻ ሌሎችም የአገዛዙ የፀጥታ ሀይሎች እየተሳተፉበት እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። እንደ መረጃ ምንጮቻችን ገለጻ፣ በተለይ ባለፉት ወራት አገዛዙ ጎንደር ከተማ ላይ በርካታ የፌደራልና የክልል የፀጥታ ሀይሎችን እንዳስገባና  እንዳሰማራ ምንጮች የገለፁ ሲሆን ጎንደር ከተማ ላይ የሚፈፀሙ እገታዎች ግን እንደተስፋፉ ገልፀዋል። እገታዎቹ የአገዛዙ የፀጥታ ኃይሎች እንደሚሳተፉባቸው ለማወቅ ተችሏል። ነሐሴ 29 ቀን 2017 ዓ.ም በጎንደር ከተማ ቀበሌ 04 የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቷ ተወስዳ የተገደለችው ቤተሰብ አስተዳዳሪና የሁለት ልጆች እናት የሆነችው ወ/ሮ ራሔል አፈና እና ግድያ ጀርባ በአገዛዙ የፀጥታ ኃይሎች እንደተመራ በስፋት እየተገለፀ ነው። የዛሬ አመት ማለትም ነሐሴ 27 2016 ዓ.ም በጎንደር ከተማ ኖላዊት ዘገየ የተባለች የሁለት አመት ልጅ ታግታ ተገድላ በወላጆቿ መኖሪያ ቤት አስክሬኗ ተጥሎ መገኘቱ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሶ እንደነበር የሚታወስ ነው። የክልሉ መንግስት በወቅቱ የመንግስት የፀጥታ አካላት በህፃኗ ግድያ መሳተፋቸውን አምነው መግለፃቸው በወቅቱ አናጋጋሪ ሆኖ ነበር። አሁንም በክልሉ ላይ የሚደረጉ አፈና፣ ግድያ ሌሎች ወንጀሎች በአገዛዙ የፀጥታ ኃይሎች እንደሚመሩ ምንጮች ገልፀዋል። አገዛዙ ከተለያዩ አካባቢዎች ምርጥ 10 ብሎ የሰበሰባቸው ሚሊሻዎች በበርካታ ወንጀሎች የተጨማለቁ እና አብዛኛዎቹ በደም ምክንያት ወደ ትውልድ አካባቢያቸው መመለስ የማይችሉ እንደሆኑ የመረጃ ምንጮች የገለፁ ሲሆን፤ በአገዛዙ በኩልም ነፃ የዘረፋና የእገታ ስልጣን እንደተሰጣቸው ታውቋል። በጎንደር ከተማ ከፌደራል የፀጥታ ኃይሎች ጋር በመሆን በናቃቸው የሚመራው ምርጥ 10 ተብሎ የሚጠራው የአገዛዙ ሚሊሻ  ከደፈጫ እስከ አንቦ በር ፈንጠርን ይዞ  ማህበረሰቡ ላይ ከፍተኛ አፈናና በደል እያደረሰ እንደሆነ ምንጮች ገልፀዋል። ትላንት ነሐሴ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት የተጀመረው አፈሳም መቀመጫውን ጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 ያደረገ የፌደራል ደህንነቶች እንደሚመራ እና ከሌሎች የአገዛዙ ፀጥታ አካላት ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዳለው ለማወቅ ተችሏል።የጎንደር ከተማ ወጣት ጥንቃቄ እንዲያደርግና ራሱን እንዲከላከል የመረጃ ምንጮች አክለው ገልጸውናል። ጳግሜ 2/2017/

ዘመቻ_ሰማዕታት_እንደቀጠለ_ነው የአ.ፋ.ብ.ሃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር አባ ኮስትር ብርጌድ በቢቸና ከተማ፣የትመን ከተማ፣ወይራ ጠልማ ቀበሌ እንዲሁም ደባይ ጮቄ ብርጌድ እና የክፍለ ጦሩ ጥምር ኃይል በጋራ በመሆን በማህበረ ብርሃን ቀበሌ የሚገኜውን የአረመኔው ሰራዊት ላይ ሙትና ቁስለኛ አድርገዋል።በየትመን ከተማ ጠላት ይጠቀምበት የነበረው ካንፕ #በቦንብ እና #RPG መሳሪያዎች በኮስትር ልጆች #ወድሟል_ተቃጥሎልጳጒሜን 02/2017 ዓ.ም

የጥንቃቄ መልዕክት ! በጎጃም ቀጠና ሰሜን አቸፈርና አካባቢው ላይ የድሮን አሰሳ እየተደረገ ሲሆን ሌሎች የአገዛዙ የእግረኛ ጦር እንቅስቃሴዎችም ከሌሊቱ 6:00 ጀምሮ ቀጥለዋል። በተለይም ከበለን እስ
የጥንቃቄ መልዕክት ! በጎጃም ቀጠና ሰሜን አቸፈርና አካባቢው ላይ የድሮን አሰሳ እየተደረገ ሲሆን ሌሎች የአገዛዙ የእግረኛ ጦር እንቅስቃሴዎችም ከሌሊቱ 6:00 ጀምሮ ቀጥለዋል። በተለይም ከበለን እስከ አለፋ ባለው ቀጠና ጥንቃቄ ይደረግ ተብሏል። አገዛዙ አሁን ላይ በሁሉም የክልሉ አካባቢ እንደ አዲስ የድሮን ጥቃት ለመፈፀም ዝግጅት ማድረጉም እየተነገረ ሲሆን ምንጮች ሁሉም የፋኖ ሀይሎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል።