GESEM ACADEMY📢Kg to Primary
Відкрити в Telegram
879
Підписники
+124 години
+57 днів
+2730 день
Архів дописів
ውድ ወላጆች: በቅድሚያ እንኳን ለ2018ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመዝጊያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያልን የዚህ ዓመት የመዝጊያ ፕሮግራም የሚሆነው አስቀድመን በወላጅ እና በመምህር የመልእክት መላላኪያ ደብተር (Communication book) ላይ ባሳወቅነው መሰረት ነገ ሐምሌ5/2018ዓ.ም አየር ጤና ባለው በተስፋ ድርጅት አዳራሽ ይሆናል።
ፕሮግራማችን ጠዋት 2:00 ሰዓት ይጀምራል። ስለሆነም በሰዓቱ መተው ልጆን ለክፍል መምህራኖቻቸው አስረክበው እርሶም ለፕሮግራም በተዘጋጀው አዳራሽ ውስጥ ቦታ እዲይዙ በአክብሮት ተጠርተዋል።
ማሳሰቢያ:
1. በተለይ ፕሮግራም የሚያቀርቡ ተማሪዎች ቀድመው ይገኙ።
2. የኬጂም የአንደኛ ደረጃም ተማሪዎች የውጤት መግለጫ ካርድ (Report card) የሚሰጠው ሰኞ እና ማክሰኞ ከ3:00-6:00 ሰዓት በየጊቢያቸው ይሆናል።
3. የተመራቂ ተማሪዎች ጋወን ሀሙስ እና አርብ ማለትም ሐምሌ9 እና 10 ይመለሳል። እናመሰግናለን!!!
#MoE
ትምህርት ሚኒስቴር በ2019 ዓ.ም በዘጠኝ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን በኦንላይን መዝግቦ በማወዳደር ለማስተማር ይፈልጋል።
ሚኒስቴሩ ለ2019 የትምህርት ዘመን በ2018 ዓ.ም ትምህርት በጀመረባቸው አምስት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በአራት አዲስ በሚጀምሩ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለማስተማር ይፈልጋል።
በመሆኑም በእነዚህ ዘጠኝ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ተመዝግባችሁ ለመማር የምትፈልጉ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ስለሚኖር ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
የምዝገባ ጊዜው በቀጣይ የሚገለፅ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
@tikvahuniversity
CONGRATULATIONS!🏆🏆🏆
እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን 🏆🏆🏆
የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ የሚኒስትሪ ተፈታኝ ተማሪዎቻችን በከፍተኛ ውጤት 100%(ሁሉም) አልፈዋል።
የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት መመልከቻ ሊንክ
👇👇👇👇👇👇👇
https://aa.ministry.et/#/result
CONGRATULATIONS!🏆🏆🏆
እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን 🏆🏆🏆
የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ የሚኒስትሪ ተፈታኝ ተማሪዎቻችን በከፍተኛ ውጤት 100%(ሁሉም) አልፈዋል።
ሰላም ውድ የ 6ኛ ክፍል ተማሪዎች
የአፋን ኦሮሞ የትምህርት ዓይነት የመልስ መስጫ ሙሉ መረጃ የሚፃፈው በአፋን ኦሮሞ ስለሆነ ፆታ፣ የት/ቤታችሁ ስም፣ ክ/ከተማ ከታች በፃፍንላችሁ ተለማመዱ።
👉 የት/ቤቱ ስም:- Geeseem Akkaadaami
👉 ክ/ከተማ: Kolfee Qaraaniyoo
👉ፆታ :- Du ማለት ሴት ፣ ።Dhi ማለት ወንድ።
ሰላም ውድ የ 6ኛ ክፍል ተማሪዎች
የአፋን ኦሮሞ የትምህርት ዓይነት የመልስ መስጫ ሙሉ መረጃ የሚፃፈው በአፋን ኦሮሞ ስለሆነ ሙሉ ስማችሁ፣ ፆታ፣ የት/ቤታችሁ ስም፣ ክ/ከተማ ከታች በፃፍንላችሁ ተለማመዱ።
👉 የት/ቤቱ ስም:- Jooyinti Viizyiini Seksees Akkadaamii
👉 ክ/ከተማ: Kolfee Qaraaniyoo
👉ፆታ :- Du ማለት ሴት ፣ ።Dhi ማለት ወንድ።
ለመላው የጌሴም አካዳሚ የ6ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች!
በመጀመሪያ ደረጃ፣ የዚህን ታላቅ የትምህርት ምዕራፍ ማጠቃለያ የሆነውን የክልላዊ (ሚኒስትሪ) ፈተና ለመውሰድ በመብቃታችሁ መላው የትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ታላቅ ኩራት ይሰማዋል። ላለፉት ዓመታት በትምህርታችሁ ስታሳዩት የነበረው ጥረት፣ ትጋትና የዲሲፕሊን ውጤት እዚህ ደረጃ አድርሷችኋል።
ይህ ፈተና ያጠናችሁትንና ያወቃችሁትን የምታሳዩበት ዕድል እንጂ የምትሰጉበት መድረክ አይደለም። ስለዚህ ሙሉ በራስ-መተማመን፣ በተረጋጋ መንፈስና በትኩረት ፈተናችሁን እንድትሰሩና የደከማችሁበትን አመርቂ ውጤት እንድታስመዘግቡ እንመኛለን።
ት/ቤቱ
📚 የተፈታኞች መብትና ግዴታ ✅
📚 ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብና ሥርዓት አከባበር እንዲሁም የመልስ ወረቀት አጠቋቆርና ተዛማጅ ሁኔታዎችን አስመልክቶ በሚሰጡ ገለፃዎች ላይ የመሣተፍ ግዴታ አለበት።
📚 ተፈታኙ በገለፃው ላይ ባለመሳተፉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል።
📚 ተፈታኙ/ኟ የሰራበትን የመልስ ወረቀት ለፈታኙ በመስጠት የጥያቄ ወረቀቱን ይዞ መውጣት ይችላል
📚 ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ጥያቄዎቹን መስራት ከመጀመሩ በፊት በፈተና የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ የግል መለያ መረጃዎችን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ በቅደም ተከተል ጽፎ ማጥቆር ይኖርበታል (በተለይ የመለያ ቁጥር እና የትምህርት አይነት ኮድ)።
📚 ማንኛውም ተፈታኝ የራሱን ችሎታና ዕውቀት ተጠቅሞ መስራት ይጠበቅበታል፡፡
📚 የሚሠራባቸው የጥያቄና የመልስ መስጫ ወረቀቶች ለሌሎች ተፈታኞች ዕይታ የተጋለጡ እንዳይሆኑ ሸፍኖ መስራት ይኖርበታል
📚 ማንኛውም ተፈታኝ ሞባይል፣ ካልኩሌተርና የመሳሰሉ ማንኛውንም ዓይነት የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው ።
📚 እያንዳንዱ ተፈታኝ ይህንን አውቆ በቅድሚያ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ።
📚 ይህንን ባለማድረጉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ተፈታኙ ራሱ ኃላፊነቱን ይወስዳል።
📚 ማንኛውም ተፈታኝ በመፈተን ላይ እያለ ፈተናውን እንዳይሠራ የሚያውኩ ሁኔታዎች ቢያጋጥመው በፈታኙ ሲፈቀደለት ችግሩን በመግለጽ አስፈላጊውን እርዳታ ማግኘት ይችላል ይሁንና በማንኛውም ምክንያት ለባከነ ጊዜ ተጨማሪ ሰዓት አይፈቀድም
📚 ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከሚጀመርበት ጊዜ ተኩል ሰዓት /30 ደቂቃ/ ቀደም ብለው ከመፈታኛው ቦታ በመገኘት መቀመጫቸውን መያዝ አለባቸው።
📚 ፈተናው ከተጀመረ ከ15 ደቂቃ በኋላ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተናው አዳራሽ መግባት አይፈቀድለትም።
📚 ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ፈተናውን ሠርቶ ቢያጠናቅቅም እንዲወጣ አይፈቀድለትም።
📚 ይሁን እንጂ ፈተናው ከተጀመረ ከ45 ደቂቃ በኋላ ከፈተና አዳራሹ ለመውጣት እንዲፈቀድለት ሲጠይቅ የመልስ ወረቀቱን ለፈታኙ አስረክቦ በጸጥታ እንዲወጣ ይፈቀድለታል።
📚 ፈተናው ሊጠናቀቅ ከ10 ደቂቃ ያነሰ ጊዜ ሲቀረው የሚጨርስ ተፈታኝ የሁሉም ተፈታኞች የመልስ ወረቀቶች እስኪሰበሰቡና ለፈተናው የተፈቀደው የጊዜ ገደብ አብቅቶ እስኪደወል ድረስ በቦታው ተቀምጦ እንዲቆይ ይደረጋል።
📚 ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ ማንኛውም ተፈታኝ ትክክለኛ ያልሆነ የተቀደደ ወይም የተበላሸ የፈተና ጥያቄ ጥራዝ ከገጠመው ወይም የተሰጠው የመልስ ወረቀት የተበላሸ ከሆነ ወይም በራሱ እጅ ቢበላሽበት እጁን አንስቶ በመጠየቅ ሲፈቀድለት ሊያስቀይር ይችላል።
ለተፈታኞች የተፈቀዱ
✅ እርሳስ
✅ የተማሪዎች የደንብ ልብስ (UNIFORM)
✅ ADMISSION CARD
✅ ላጲስ፣ መቅረጫና ማስመሪያ
ለተፈታኞች የተከለከሉ
❌ ስልክ ይዞ መግባት አይቻልም
❌ ካልኩሌተር
❌ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን
❌ ሰዓት
❌ በሀኪም ከታዘዘ ውጪ የሆኑ መነጽሮች
❌ የሚነበቡ ጽሁፎች በሙሉ
የፈተና ኦረንቴሽን ቀን
√ ለ6ኛ እና 8ኛ ክፍል በ05/10/2018 ዓ.ም በፈተና ጣቢያችሁ።
#ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ
√ 6ኛ ክፍል ከሰኔ 8- 10 /2018 ዓ/ም
√ 8ኛ ክፍል ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ/ም ይሆናል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡
(ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና እና የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡
በዚህ መሰረትም ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ሰኔ 8 ፣ 9 እና 10/2018 ዓ.ም እንዲሁም የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሰጠው በዚህ ከተማ አቀፍ ፈተና በ6ኛ ከፍል 84,882 ተማሪዎች 199 የመፈተኛ ጣቢያዎች እንዲሁም በ8ኛ ከፍል 86,808 ተማሪዎች 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች ፈተናዉን ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
ውድ ወላጆች ከመንግስት በመጣ አቅጣጫ መሠረት ከሰኞ ግንቦት 24-ረቡዕ ግንቦት 26 ድረስ ትምህርት የማይኖር ሲሆን ሐሙስ ግንቦት 27 የአራተኛው ሩብ ዓመት አጋማሽ ፈተና (Mid exam)የሚሰጥ ይሆናል።
ስለሆነም ከወዲሁ ዝግጅት እያደረጉ እንዲቆዩ ያድርጉልን።
ለሁሉም የመንግስት እና የግል ት/ቤቶች
ከቀን 24___26/09/2018 ዓ.ም ድረስ ትምህርት ባለመኖሩ ለተማሪዎች እንዲታሳውቁ።
