uk
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Відкрити в Telegram
805
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
-130 днів
Архів дописів
የኢትዮጵያ ካቶሊክ ካርዝማቲክ እንቅስቀሴ የአባላት የአንድነት ፕሮግራም ትላንት ማክሰኞ በልዩ ሁኔታ ተደረገ።

እምነት እምነትና ስራ ያዕቆብ መልዕክት 2:17 17-እንደዚሁም ስራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው። ➮ቃሉ እንደሚለን እመኑ ይላል እምነትን ደግሞ በመስራት እንገልፀዋለን እናፀናዋለን እናፀናዋለን። ያመነው ሰው የሚለንን ነገር እናደርጋለን እንሰራለን አይደል። እግዚአብሔርንም ስናምንም ቅዱስ ቃሉ የሚለንን እንሰራለን እንፈፅማለን። ቃሉ ሰውን ውደድ ይለናል መውደድ አለብን የተቸገሩን እርዱ በጎ ነገር ስሩ ይላል መስራት አለብን ይቅር ባይ ሁኑ ይላል ይቅር ማለት አለብን ጌታን በፍፁም ልባችሁ ውደዱ ይላል መውደድ አለብን ከቃል ባለፈ እነዚህን ነገሮች በተግባር የሚገለፁ ናቸውና በተግባር መኖር አለብን።እኛ በማመናችን ተፈውሰን ሌሎችን መፈወስ መቀየር እንችላለን ይህን ማረግ የምንችለው ደግሞ በፀሎትና በድርጊት ነው። ከቃል በላይ ተግባር ሀይል አለው።ያመነው የሚለንን መስማትና መፈፀም አለብን። ያዕቆብ መልዕክት 1:22 22-ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ። በመጨረሻም እንደ አለማዊው አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድንም በመንፈሳዊውም ህይወት አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድነንም። አለማወቃችንን ለማጥፋት መጣር አለብን።ቃሉን በማንበብና ከቃላት ባለፈ በተግባር መኖር አለብን።ባለማወቃችን ከእግዚአብሔር የተሰጠንን የፀጋ ስጦታዎች አንጠቀምም። ነገር ግን ቃሉን በማንበብ በማወቅና በማመን ይህን የተሰጠንን ፀጋ መጠቀም እንችላለን። #የጌታ ቃል የታመነ ነውና እንዴት ለምን ሳንል በእምነት አሜን ብለን እንቀበል ጌታ ይሰራል።ጌታ ይባረክ መልካም የተባረከ ቀን ይሁንላችሁ

እምነት ያመነ ሰው መገለጫዎች ምን ምን ናቸው? ማር 16:16-20 16-ያመነ የተጠመቀ ይድናል ያላመነ ግን ይፈረድበታል። 17-ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ። እባቦችን ይይዛሉ። 18-የሚገድልም ነገር ቢጠጡ አይጎዳቸውም እጃቸውን በድውያኖች ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይድናሉ። 19-ጌታ ኢየሱስ ከእነርሱ ጋር ከተናገረ በኃላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ። 20-እነርሱም ወጥተው በየስፍራው ሁሉ ስበኩ ጌታም ከእነርሱ ጋር ይሰራ ነበር በሚከተሉትም ምልክቶች ቃሉን ያፀና ነበር። #በጌታ ያመነ ሰው ➮ይድናል ➮ ምልክቶች ይከተሉታል እንጂ ምልክትን አይከተልም። ➮በቆመበት ባለበት ቦታ አጋንንት አይቆምም። ➮በአዲስ ቋንቋ በመላዕክት ቋንቋ ይናገራል። ➮ከባድ የሆነ ነገር ሁሉ መቋቋም ማለፍ ይችላል። ➮የሚጎዳ ነገር እንኳን ቢኖር አይጎዳቸውም። ➮እጃቸውን በድውያኖች ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይድናሉ። ➮ለሌሎች መዳን ምክንያት ይሆናሉ። ➮ከእግዚአብሔር የተሰጣቸውን የፀጋ ስጦታዎች ይጠቀማሉ። ⨳ይህ ሁሉ የተሰጠው በጌታ በሙሉ ልብ ለሚያምኑት ሁሉ ነው እንጂ ለተወሰኑ ሰዎች አይደለም። #አለማመን ➮ፍርሀትን ያመጣል ➮ከመዳን ይገድባል ➮የእግዚአብሔር ስራ በእኛ ውስጥ እንዳይሰራ እንዳይገለጥ ያረጋል። ➮ከእግዚአብሔር የተሰጡንን የፀጋ ስጦታዎች እንዳንጠቀም ያደርጋል። ➮ከልጅነት ስልጣን ይገድበናል። ➮መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን እንዳይሰራ ያደርገናል። ➮የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች እና ፍሬዎች እንዳይገለጥ ያረጋል። ➮የድግግሞሽ ፀሎት እንዲኖር ያደርጋል። *ምክንያቱም የፀለይነው ነገር ሚሆን ስለማይመስለን በየለዕቱ እሱን በመደጋገም እንፀልየዋለን ካልተሳካ ለመፀለይ እንሰለቻለን። ➮ጥርጣሬ ይመጣብናል። ⨳እግዚአብሔር ጋር ደግሞ በጥርጣሬ የሚሆን ነገር የለም። #ስለዚህ በማመን ለእግዚአብሔር ስራዎች መንገድ እንሁን። ይቀጥላል.... መልካም የተባረከ ቀን ይሁንላችሁ

እምነት እምነት ለምን ይጠቅማል? ➮የእግዚአብሔር ስራ ለማወቅ ለማየት ➮የእግዚአብሔር ስራ በእኛ እንዲገለጥ ➮ለመዳን ለመፈወስ ሌሎችንም ለማዳን ማቴ 9:27-30 27-ኢየሱስም ከዚያ ሲያልፍ ሁለት ዕውሮች።የዳዊት ልጅ ሆይ ማረን ብለው እየጮሁ ተከተሉት። 28-ወደ ቤትም በገባ ጊዜ ዕውሮቹ ወደ እርሱ ቀረቡ ኢየሱስም። ይህን ማድረግ እንድችል ታምናላችሁን? አላቸው። አዎን ጌታ ሆይ አሉት። 29-በዚያን ጊዜ።እንደ እምነታችሁ ይሁንላችሁ ብሎ ዓይኖቻቸውን ዳሰሰ። 30-ዓይኖቻቸውም ተከፈቱ። ➮ለመፈወሳቸው ዋናው ምክንያት ሲሄዱ እንደ ሚያድናቸው ያለቸው ዕምነት ነው። ➮ዛሬም እኛ በጌታ ፊት ስንቀርብ የሚጠይቀን አምነሻል አምነሀል ነው ሚለን ከዚያም እንደ እምነትህ(ሽ) ይሁንልህ(ሽ) ነው ሚለን እና አምነን እንደሄድነው ይሆንልናል። ዝም ብሎ የእግር መመላለስ ምንም ጥቅም የለውም ዋናው እግዚአብሔር የሚያየው ልባችንን ነው። ለምሳሌ:-ሰዎች ፈውስን ፍለጋ በአለማዊ ከሆስፒታል ሆስፒታል በመንፈሳዊ ከፀበል ፀበል , ከቤተክርስቲያን ቤተክርስቲያን ሲመላለሱ እናያለን ። ሰዎችም ሲመክሩ ሃሳብ ሲሰጡ ብዙ ጊዜ ይሄ ፀበል ፈዋሽ ነው እሲቲ እዛ ሂጂ ወይ ጎበዝ የሚፀልይ ፓስተር ቄስ አለ እዛ ሞክር(ሪ) ይላሉ። ሞክሪ ነው እንጂ ሄደሽ ተፈወሺ(ስ) አይሉም። ነገር ግን ፀበል ብንቀያይር ቤተክርስቲያን ብንቀያይር ልባችን ለመዳን ካላመነ ሁሌ ስንዞር እንኖራለን። እግራችን መሄዱ ሳይሆን ልባችን መለወጡ አምነን መሄዳችን ነው።እና እኛም ስንመክር ንግግራችን መሆን ያለበት ዋናው ነገር በእምነት መሄድ ነውና አምነህ(ሽ) ሂጂ(ድ) ነው ማለት ያለብን። ⨳በእምነት ከሄድን ጌታ ይፈውሳል። በእምነት ከሄድን መዞር አይጠበቅብንም ባለንበት ሆነን እንድናለን። ይቀጥላል..... መልካም የተባረከ ቀን ይሁንላችሁ

እምነት እምነታችን በማን መሆን አለበት? ➮እምነታችን መሆን ያለበት ባለን ነገር ማለትም ( በቤተሰብ በጎደኛ በባል በሚስት በልጆች ወይም በጊዜያዊና ጠፊ በሆነ ነገር መሆን የለበትም። እምነታችን መሆን ያለበት ዘላለማዊ በሆነው በእግዚአብሔር ነው። እግዚአብሔርን ስናምን ሁሌ አመስጋኝ ነው ምንሆነው ቢሳካም ባይሳካም ቢሞላም ቢጎልም ምክንያቱም እግዚአብሔር ሁሌ ቢሆን በእኛ ላይ ያለው ሀሳቡ መልካም በጎ እንደሆነ ስለምናቅ የማማረር ህይወት ይበቃል ያቆማል። ⨳የሱናማዊቷን ሴት ታሪክ ስናይ እግዚአብሔር ልጅ ከሰጣት በኋላ ሲሞትባት የሞተ ልጅዋን እቤትዎ አስተኝታ ሰላም ነው ያስባላት በእግዚአብሔር ላይ ያላት እምነቷ ነው። የያዘችውን ያመነችውን አምላክ ስለምታውቅ ነው። እንጂ አንድ በእምነቱ ደካማ የሆነ ሰው ወይም እምነት የሌለው ሰው የሞተ ልጅ እቤቱ አስተኝቶ ሰላም ነው ሊል አይችልም። ⨳ጌታን የያዘ ያመነ ሰው በነገር ሁሉ ሰላም መልካም ነው ይላል። # የእኛስ እምነት የቱ ጋር ነው? ማቴ 9:20-22 20-እነሆም ከአስራ ሁለት አመት ጀምሮ ደም የሚፈስሳት ሴት በኋላው ቀርባ የልብሱን ጫፍ ዳሰሰች። 21-በልብዋ። ልብሱን ብቻ የዳሰስሁ እንደ ሆነ እድናለሁ ትል ነበረችና። 22-ኢየሱስም ዘወር ብሎ አያትና። ልጄ ሆይ አይዞሽ እምነትሽ አድኖሻል አላት። ሴቲቱም ከዚያች ሰአት ጀምራ ዳነች። ➮እምነቷ በግርግር ውስጥ አልፋ በእምነት ሰውነቱን አይደለም ያለችው የልብሱን ጫፍ ብነካ እድናለሁ ብላ በልቧ አስባ ነው የነካችው ጌታም እንደ እምነትሽ አላት ያመነችው ሆነላት። ➮ዛሬም በአለም ግርግር ተከበን ቢሆንም ነገር ግን የሚሻለውን መርጠን ወደ ጌታ በእምነት መሄድ አለብን። ጌታም ነገሮቻችንን ያከናውንልናል ይሰራል ይፈውሰናል ይቀይረናል ከጌታ ሀይል ይወጣል።እኛ ብቻ ጌታን በማመን ወደ እርሱ እንቅረብ ጌታ ይሰራል። ይቀጥላል..... መልካም የተባረከ ቀን ይሁንላችሁ

እምነት እምነት ምን ማለት ነው? ➮እምነት ማለት እራስን አሳልፎ መስጠት ነው። ➮እምነት በሞኝነት ይገኛል።እምነት በሳይንሳዊ መንገድ አይገኝም። ⨳ራሳችንን አሳልፈን መስጠት ስንል ራሳችንን ለማን ነው አሳልፈን ምንሰጠው? ➮አኛነታችንን አሳልፈን ለእግዚአብሔር መስጠት ያስፈልጋል።ልክ እንደ እናታችን ማርያም። እናታችን ማርያም በትህትና እሷነቷን ለእግዚአብሔር አሳልፋ በመስጠቷ ነው ክርስቶስን ለመውለድ የበቃችችው። የእግዚአብሔር ስራ በእሷ የተከናወነው። ➮ እምነት ያለ ጥርጥር እራስን አሳልፎ መስጠት ለምን እንዴት ሳንል የጌታን ቃል በሞኝነት መቀበል ነው። ሉቃ 1:38 ማርያምም።እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ አለች። መልአኩም ከእርሷ ሄደ። ➮አንድን ሰው ስንወደው እናምነዋለን ስናምነው ደግሞ ሁሉ ነገራችንን እንነግረዋለን ሚስጠረኛችን እናረገዋለን እራሳችንን እንሰጠዋለን ምክንያቱም ምንም መጥፎ ነገር አያረገንም ብለን ስለምናስብ ለነገሮቻችን መፍትሄ ይኖረዋል ስለምንል። የወደድነው ሰው ምንም ቢል እናምነዋለን።ምክንያቱም እንደማይዋሸን እንደማይጎዳን ስለምናስብ። #እግዚአብሔር በአወቅነው መጠን እንወደዋለን በወደድነው መጠን እናምነዋለን።እኛነታችንን በእምነት ለሱ አሳልፈን እሰጠዋለን።እኛነታችንን ስንሰጠው እግዚአብሔር መልካም አባት ስለሆነ በመልካም ነገር ያሳድገናል ከሚጎዳን ነገር ያርቀናል ለነገሮቻችን መፍትሄ ይሰጠናል የእራሱ የክብር ዕቃ ያደርገናል በብዙ ይጠቀምብናል። ለቤተሰብ ለጎደኛ ለቤተክርስቲያን ለትውልድ ለሀገር ለአለም መለወጥ መዳን ምክንያት ያረገናል። ➮ለዚህ ሁሉ ነገር በሙሉ እምነት ተጠቀምብን ያንተ አድርገን ብለን ለእግዚአብሔር እኛነታችንን መስጠት አለብን። ይቀጥላል..... መልካም የተባረከ ቀን ይሁንላችሁ