cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Ye Orthodox tewahido mezmuroch

ሰላም ውድ የቅድስት ድንግል ማርያም ልጆች የዚህ ቻናል ዋና አላማ አሪፍ አሪፍ የኦርቶዶክሳዊት መዝሙሮችን መልቀቅ ሰለሆነ እባካችሁን ስለ እመአምላክ ብላችሁ ሼር በማድረግ ተባብሩን ለትብብራችሁ ሁሉ እናመሰግናለን 😊😘

Більше
Країна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
Рекламні дописи
488
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Enkuan le hosana beal be selam be tena be fkr aderessachu Le ametu yadrssen amen ❤️
Показати все...
#እናት_አለኝ እናት አለኝ የምታብስ እንባ አያታለሁ ስወጣ ስገባ ኪዳነምረት/3/ አምባ መጠጊያ ናት ሔዋን ሰጥታኝ ከበለሱ ፍሬ ራቁቴን ብቆምም አፍሬ ልብሴን ይዘሽ ወደኔ መጥተሻል ደጏ እናቴ ቤቴን አድምቀሻል ኪዳነምረት/3/ አምባ መጠጊያ ናት #አዝ ለዘላለም ንፅሕት በመሆኗ ከእኔ ጋር ነው ሕያው ቃልኪዳኗ ደስተኛ ነኝ ሐዘኔን አልፌ አፅናኝ ሆናኝ የመስቀል ስር ትርፌ ኪዳነምረት/3/ አምባ መጠጊያ ናት #አዝ ከጥፋት ውሃ ማረፊያዬ መርከቤ ነሽ ከሞት ማምለጫዬ የአምላክ እናት ምልጃሽ ሆኖኝ ክብሬ በሕይወት አለሁ ጥልቁን ተሻግሬ ኪዳነምረት/3/ አምባ መጠጊያ ናት #አዝ በእናትነት ሕይወቴን ጎብኝታ ልቤ አረፈ ተነቅሎ በሽታ ሰንሰለቴ ከእግሬ ተቆረጠ መራራዬ በልጅሽ ጣፈጠ ኪዳነምረት/3/ አምባ መጠጊያ ናት #አዝ ሔዋን ሰጥታኝ ከበለሱ ፍሬ ራቁቴን ብቆምም አፍሬ ልብሴን ይዘሽ ወደኔ መጥተሻል ደጏ እናቴ ቤቴን አድምቀሻል ኪዳነምረት/3/ አምባ መጠጊያ ናት 💚 @methmur💚 💛 @methmur 💛 ❤️ @methmur ❤️
Показати все...
ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ 🔺
Share share adrgu ye tewahido ljoch hagerachnin lay mideregewn haymanotachnin minekfu ngrochn bmkawm ke abatocgachin gon bmkom enasay✊✊ EGZIABHER ETHIOPIAN ENA LJOCHWAN YBARK🙏🙏🙏 @methmur @methmur @methmur
Показати все...
02:05
Відео недоступнеДивитись в Telegram
የስግደት አይነት ስንት አይነት ስግደት አለ?   1.    የአምልኮት ስግደት ለአምላክ ሁሌ የሚሰገድ   በሚሰገድበት ጊዜ ከታች ንጹህ ቦታ ላይ መጽሐፍ ቅዱስ መስቀል ወይም የቅዱሳን መጻሕፍት መቀመጥ አለበት ሰጋጁ አይኑን ገልጦ ሲሆን የሚሰግዳው ግንባሩ መጽሐፍ ቅዱሱን መስቀሉን ወይም የቅዱሳን መጻሕፍትን ማስነካት አለበት:: ለአብ እሰግዳለሁ፣ ለወልድ እሰግዳለሁ፣ ለመንፈስ ቅዱስ እሰግዳለሁ፣ ምስጋና ይሁን ለአብ፣ ምስጋና ይሁን ለወልድ፣ ምስጋና ይሁን ለመንፈስ ቅዱስ፣ በረከቱን ለሰጠን፣ ሀይሉን ላበዛልን፣ በዚህ ሰአት ላቆመን፣ በቸርነቱ መንገድ ለመራን፣ በዚህ ሰእት በጸጋ ለጠበቀን፣ በብርሀኑ ሐይል ለመራኸን፣ ላንተ ክብር ምስጋና ይግባው፣ ሐሌሉያ ለአብ፣ ሐሌሉያ ለወልድ፣ ሐሌሉያ ለመንፈስ ቅዱስ፣ ቅዱስ እግዚአብሔር፣ ቅዱስ ሐያል፣ ቅዱስ ሕያው፣ ቅዱስ ኤልሻዳይ፣ ቅዱስ አዶናይ፣ ቅዱስ ያህዌ፣ ቅዱስ ፀባኦት፣ ቅዱስ ኢየሱስ፣ ቅዱስ ክርስቶስ፣ ቅዱስ አማኑኤል፣ የድንግል ማርያም ልጅ፣ ክብር ምስጋና ይግባው:: እያልን እንሰግዳለን::   2.    የፀጋ ስግደት ቅዱስ ገብርኤል ፀጋን የተሞላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ እንዳላት እኛም እንዲሁ እያልን ለእመቤታችን የፀጋ ስግደት እንሰግዳለን:: ስንሰግድ ድንግል ማርያም ክብር ምስጋና ይገባሻል እያልን (21 ጊዜ) እንሰግዳለን::   3.    የንስሐ ስግደት ኪሪያላይሶን ኢየሱስ፣ ኪሪያላይሶን ክርስቶስ፣ ኪሪያላይሶን አማኑኤል፣ እቤቱ ክርስቶስ ሆይ ማረን፣ አቤቱ አምላክ ሆይ ማረን፣ አቤቱ መድሀኒአለም ሆይ ማረን፣ አቤቱ የድንግል ማርያም ልጅ ሆይ ማረን:: እያልን እንሰግዳለን::   4.    የክብር ስግደት ለቅዱሳን መላእክት ለቅዱሳን ጻድቃን ለሰማእታተ የሚሰገድ:: ለምሳሌ 12 Noon (6 ሰአት) በ ቅዱስ ሚካኤል እሰግዳለሁ እና ለ ቅዱስ ሚካኤል እሰግዳለሁ እንዲሁም በ ወርኃዊ በአል ጊዜ:: ኦ: ቅዱስ ገብርኤል…. እያልን የአክብሮት ስግደት እንሰግዳለን::   ክብረ በአል ከሆነ (ለምሳሌ በ12 የቅዱስ ሚካኤል ቀን ፣ በ19 የቅዱስ ገብርኤል ቀን ፣ የ21 የማርያም ቀን) ስብአት ለአብ፣ ስብአት ለወልድ፣ ስብአት ለመንፈስ ቅዱስ፣ ቅዱስ እግዚአብሔር፣ ቅዱስ ሀያል፣ ቅዱስ ህያው፣ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ:: እያልን እጣን እያጨስን እንሰግዳለን::      ሌሎች ምእመናን Add በማድረግ አንድ ላይ ለፀሎት እንበረታታ ሌሎችም ሼር 👇👇👇👇 https://t.me/joinchat/G6VEPJ3q5dgTfQx1
Показати все...
Ere share adergu😘😘 @methmur @methmur @methmur
Показати все...
መካነ-ነገስት ግምጃ ቤት ማርያም ዘጎንደር ማን ናት? በ1650 ዓ/ም በአፄ ፋሲል የታነፀችዉ መካነ-ነገስት ግምጃ ቤት ማርያም ዘጎንደር ማን ናት? መካነ ነገስት ግምጃ ቤት ማርያም ቤ/ክ የምsትገኘዉ በጥንታዊቷ መዲና:የነገስታት መናገሻ ፤የሊቃውንት መፍለቂያ እና የባህል ጎተራ በሆነችዉ ጎንደር በአፄ ፋሲል ቤተ መንግስት ቅጽር ዉስጥ ነዉ፡፡ምንም አንኳን አሁን በአጥር ብትከለልም ደብሯ በአፄ ፋሲል በጎንደር ከተተከሉት ከሰባቱ ቀደምት አብያተ ክርስቲያናት ማለትም v ከፊት አቦ፣ፊት ሚካኤል፣ v አደባባይ ኢየሱስ፣ v እልፍኝ ጊዮርጊስ፣ v መ/መ/መድኃኔዓለም፣ v አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል አንዷ ናት፡፡ መካነ ነገስት ግምጃ ቤት ማርያም ብለዉ የሰየሟትም አፄ ፋሲል እንደሆኑ ታሪክ ያስረዳል፡፡ግምጃ ቤት የሚለዉን ስም ልታገኝ የቻለችዉም ንጉሱ ቤተ ክርስቲያነኗን ከማፃነሳቸዉ በፊት አሁን ቤተ ክርስቲያኗ ባለችበት ቦታ ወንበር በር በሚባለዉ በኩል በእንቁላል ግንብ ወደዋናዉ ቤተ መንግስት በሚወስደዉ የንጉሱ የዕቃ ግምጃ ቤት ነበር፡፡በዚህም ሳቢያ ይኼንን ስም ልታገኝ ችላለች፡፡ ቤተ ክርስቲያኗ በአፄ ፋሲል ጊዜ የሚያገለግሏት 5-ልዑካን የሚባሉት ሲሆኑ በአፄ ኢያሱ ጊዜ ግን እንደማንኛዉም ደብር የሚያገለግሏት ለቤተ መቅደሱ ቄስ፣ዲያቆን፣ ገበዝ፣ ለቅኔ ማኅሌቱ ደግሞ አለቃ፣ መርጌታ፣ቀኝ ጌታ፣ ግራ ጌታ ፣ከመኳንንቱና ወይዛዝርቱ ጋር በአጠቃላይ 199 አገልጋዮች ተወስኖ ተሰጥቷትም ነበር፡፡ ይኸች ጥናታዊት ደብር የመጀመሪያዉ አራቱ ጉባኤ የተተከለባት ስትሆን( በነገራችን ላይ አራቱ ጉባኤ ስንል መጽሐፈ ሊቃዉንት፣መጽሐፈ መነኮሳት፣መጽሐፈ ብሉያት፣መጽሐፈ ሐዲሳት ማለታችን ነዉ፡፡) አራቱ ጉባኤ ትምህርት በተለያዩ አባቶች ሲሰጥ ቆይቶ በአፄ ኃ/ስላሴ ዘመነ መንግስት አፄዉ እራሳቸዉ እንዲህ አይነቱ ትምህርት በአንድ ቦታ ብቻ መሰጠት የለበትም በማለት መጽሐፈ ብሉያት በአብየ እግዚእ ኪዳነ ምህረት፣መጽሐፈ ሐዲሳት በመካነ ነገስትግምጃ ቤት ማርያም፣ መጽሐፈ ሊቃዉንት በመ/መ/መድኃኔዓለም፣ መጽሐፈ መነኮሳት በሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምህረት(በለሳቱ ምኢት)ትምህርቱ እንዲሰጥ አዘዉ ለጉባኤዉ በጀት በጅተዉ ደልደለዉታል፡፡እናም አሁን እርሳቸዉ በደለደሉት መሰረት በቤተ ክርስቲያኗ ያሉት መምህር መጋቤ ወልደ ሰንበት ባይነሳኝ( ብቸኛዉ የአራቱ ጉባኤ መምህር) ምንም እንኳን በአራቱ ጉባኤ የተካኑ ቢሆኑም በንጉሱ እንደተመደበዉ ከመጽሐፈ ሐዲሳት በተጨማሪም የፍትሐ ነገስት ትምህርት በዚሁ ቦታ እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያኗ በድርቡሽ መቃጠሏና በተአምር ከቃጠሎ የተረፈችዉ ስዕለ አድህኖ በአፄ ዮሐንስ ዘመነ መንግስት በ1881ዓ/ም ድርቡሽ/መሀዲስቶች/ወደ ጎንደር ዘልቀዉ በመግባት አብያተ ክርስቲያንንና የታሪክ መዘክሮችን ባቃጠሉ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኗ በዉስጧ ከሚገኙ ንዋያተ ቅድሳት ጋር ተቃጥላለች፡፡ ጽላቱን ግን አባቶች አስቀድመዉ ወደ ሌላ ቦታ አሸሽተዉት ነበርና መትረፍ ችሏል፡፡መካነ ነገስት ግምጃ ቤት ማርያም ቤ/ክ በተቃተለች ጊዜ ጻድቁ ዮሐንስ ያሳሏት የእመቤታችን ማርያም ስዕል ግን በታምር ሳትቃጠል ቀርታለች ስዕለ ማርያሟ አሁንም ድረስ ያለች ሲሆን የምትገኘዉም ቤተ መቅደሷ ዉስጥ ነዉ፡፡ይኸችን ተአምረኛ ስዕል በማየትና በመሳለምም የበረከቷ ተቋዳሽ ይሁኑ፡ ቤተ ክርስቲያኗ በድርቡሽ በተቃጠለች ጊዜ አፄ ፋሲል የተከሏት ቤተ ክርስቲያን ፈርሳ ስለ ነበር፡፡ አባቶች ጽላቱን ይዘዉ በተመለሱ ጊዜ የሳር ሰቀላ ቤት ሰርተዉ ጽላቱን አስቀመጡት፡፡ከዚኽም በኋላ ከዚህ ቤት እንደቆየች አሁን ያለዉን ህንፃ ቤ/ክ በ1936-1939ዓ/ም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድና በህዝበ ክርስቲያኑ ንቁ ተሳትፎ ቅድስቱና መቅደሱ ተሰራ ቅኔ ማኅሌቱን ደግሞ እቴጌ መነን እንዳሰሩት አባቶች ይናገራሉ፡፡ቤተ ክርስቲያኗ የታነፀችዉ በድንጋይና ጭቃ ስለነበር በ1985 ዓ/ም በጊዜዉ የነበሩ የሰበካ ጉባኤ አባላትና ካህናት ምዕመናኑን በማስተባበር የአሁኑን ህንፃ ቤ/ክ መልክ እንድትይዝ አድርገዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያኗ በነገስታት ዘመን መቀደሻና ማስቀደሻዉ ግብር በነገስታቱ እየተሰጣት የምትተዳደር ሲሆን ነገስታቱም ለመምህራኑ ቀረጥ እየቀረጡ ከሚያገኙት ሁለት እጅ ይሰጧቸዋል፡፡ይኽም ማር፣ቅቤ፣ቅመማቅመም ሲሆን በዓበይት በዓላት ደግሞ እንደ ልደት፣ትንሣኤ፣ቅ/ዮሐንስ፣ነገስታቱ ፍሪዳ፣ጉንደ-ማር ያበረክቱላቸዉም ነበር፡፡ በአሁን ጊዜ ግን ቤተ ክርስቲያኗ በወርሃዊ ገቢዋ ማለትም ምዕመናን በሚሰጡት ገንዘብ ብቻ መምህራኑን፣ካህናቱን፣ዲያቆናቱን፣መዘምራኑን፣በማስተዳደር ቃለ እግዚአብሔርን ሳታጓድል ማስተማሩዋን ቀጥላለች፡፡ በደብሯ በሰማዕትነት የተሰዉ መምህራን አባቶች አፄ ፋሲል በጎንደር ቤተ መንግስት ከመሰረቱበትና መካነ ነገስት ግምጃ ቤት ማርያም ብለዉ ሰይመዉ ቤተ ክርስቲያኗን ከተከሉበት ዘመን ጀምሮ በቤተ ክርስቲያኗ ያስተማሩ መምህራን ምንም ብዙ ቢሆኑም በቃል ጎልቶ ሲነገር እንደሰማነዉ በጽሁፍም ሰፍሮ እንዳገኝነዉ በመ/ነ/ግምጃ ቤት ማርያም በቅርብ ዘመን ተገኝተዉ የሐዲስ ጉባኤ አስፋፍተዉ ያስተማሩ መምህራን 1. መምህር ወ/ሚካኤል ወልደ አብ 2 መምህር ተ/ማርያም ቢሠወር 3 መምህር ክፍሌ ይመር እና ሌሎችም ናቸዉ፡፡ * መምህር ወ/ሚካኤል፤-በቀና በኃይማኖታቸዉ በመልካም ምግባራቸዉና በትሩፋታቸዉ ለደቀ መዛሙርቶቻቸዉ መልካም አብነት የሆኑ መንፈሳዊ መምህር ነበሩ፡፡በ1881 ድርቡሽ የጎንደርን አብያተ ክርስቲያናት በሚያጠፋበት ጊዜ መምህር ወ/ሚካኤል በዚሁ ቤተ ክርስቲያን ጉባኤ ዘርግተዉ ያስተምሩ ነበር፡፡ከደቀ መዛሙርታቸዉ ዉስጥ አንዱ ከዚህ ሰቆቃ እንዲሸሹ አጥብቆ ሲወተዉታቸዉ መምህር ወ/ሚካኤል ግን ለደቀ መዛሙራቶቻቸዉ‹‹ ልጆቸ ስጋችሁን የወደዳቹ ሂዱ ሽሹ ነፍሳችሁን የወደዳቹ ግን ከእኔ ጋር ቆዩ አሏቸዉ፡፡››ደቀ መዛሙርቶቻቸዉም ‹‹አባታችን እርሰዎን ትተን የትም አንሄድም›› ብለዉ መለሱላቸዉ፡፡ ሁሉም በአንድ ሀሳብ ተስማምተዉ ቤተ-ክርስቲያኗ ወስጥ ፀንተዉ ቆዩ ድንገት ግን ጠላት ድርቡሽ ቤተ ክርስቲያኗ ቅጽር ዉስጥ ዘልቆ ገባ መ/ወ/ሚካኤል ከደቀ መዛሙርቶቻቸዉ ጋር ወንጌላቸዉን እንደያዙ ጠላትም ሰይፉን እንደያዘ ‹‹በእምነትህን ለዉጥ ››አለዉጥም ተፋጠጡ በዚህ ፍጥጫ መሃል ከጠላት ወገን አንድ ድምጽ ተሰማ‹‹ፊሳ ቢላ››የሚል.. እኒህ ታላቅ አባት ግን ወንጌላቸዉን ከፍ በማድረግ ‹‹ነአምን በአሐዱ አምላክ ››ሲሉ ተናገሩ ደቀ መዛሙረቱም ይኼንን ቃል አስተጋቡ በዚህ ጊዜ የጠላት ሰይፍ በእነዚህ ቅዱሳን አባቶች ላይ አረፈ ደማቸዉም እንደጎርፍ ፈሰሰ እምነታቸዉንም ጠብቀዉ በሰማዕትነት አረፉ፡፡ መምህር ወ/ሚካኤል ከደቀ መዛሙርቶቻቸዉ ጋር እንደ በግ በታረዱ ጊዜ ለጊዜዉ ቀባሪ ሊያገኙ አልቻሉም፡፡ምክንያቱም የሽብርና የመከራ ጊዜ በመሆኑ የከተማዋ ሰዉ ከፊሉ ተገድሎ ከፊሉ ሸሽቶና ተማርኮ ከተማዋ ባዶዋን ስለቀረች እንደወደቁ ሰንብተዋል፡፡ አሞራም ሆነ አዉሬ እንዳይነካቸዉ እግዚአብሔር በጥበቡ ሲጠብቃቸዉ ሰንብቶ ድርቡሽ ከተማዋን ለቆ ሲወጣ ከሽሽት የተመለሱ አንድ ሰዉ ከተማዋን ለማየት ሲዘዋወሩ በመ/ነ/ግምጃ ቤት ማርያም የእነዚህን ቅዱሳን ሬሳ ተጋድሞ አገኙት በአካባቢዉ የነበረዉ ሽታም እንደ መልካም ጽጌረዳ ሽታ ሆኖ ያዉድ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ሰዉየዉ እጅግ ደንግጠዉና አዝነዉ ተጨማሪ ሰዉ ጠርተዉ አንስተዉ በክብር ቀብረዋቸዉል፡፡የእነዚህ ቅዱሳን አባቶች መቃብራቸዉ በቤ
Показати все...