uk
Feedback
ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan)

ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan)

Відкрити в Telegram

🌷ይህ ቻናል የተከፈተው ለመላው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትና እምነት ተከታይ ሲሆን ዋና አላማውም ምዕመናን በንስሐ ህይወት ተመላልሰው የእግዚአብሔርን መንግሥት እንድወርሱ የሚያስችል ትምህርት መስጠት ነው፡፡ 🌷💚የቅዱሳን ገድላት 🌷💛ስንክሳር 🌷♥ ቅዱሳን ስዕላት መንፈሳዊ ትምህርቶችና ጽሑፎች 🎤 ስብከቶች ............ይቀርቡበታል፡፡🌎

Показати більше
2 415
Підписники
-124 години
+117 днів
+2930 день
Архів дописів
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ዘለዓለም ሥላሴ አሜን። #​​እንኳን_ለታላቁ_ቅዱስ ለአቡነ ተክለ ኃይማኖት ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።🙏 #ልደት በልቡናው መልካም መልካም መዝገበ ያስቀመጠ ሰው ከልቡናው መዝገብ አውጥቶ ዛፍ የሚናገረው ከዚያው ነውና የጻድቁ ወላጆችም በደግነት፣ በጸሎት ከልባቸው የተመኙትን ወደ እግዚአብሔር አመልክተው ተደርጎላቸዋለ። መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው። እርሱ በክህነቱ እርሷ በደግነቷ በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል። በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ ሚካኤል ጸጋ ዘአብን ከሞት እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል። በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል። ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተጸነሱት መጋቢት 24 ቀን በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታሕሳስ 24 ቀን በ1207 ዓ/ም ነው። በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል። ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል። #ዕድገት/አስተዳደጋቸው የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል። ይሕንን ስም ይዘው አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል። በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል። በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል። ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል። #መጠራት_ወደ ቅድስና ህይወት አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮስ ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ። የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ። "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን። ከዚህ በሁዋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ። ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ። ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ ሰዓትን አላጠፉም። ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ። #አገልግሎት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ። በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ። ያን ጊዜ ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት። 1ኛ. ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል። 2ኛው. ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር። ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ። ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: #ገዳማዊ_ሕይወታቸው ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል። እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል። እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል። በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል። በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል። #ስድስት_ክንፍ ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል። ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር:: የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል። ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በሁዋላ ነው ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም። በገሃድ:- -በቤተ መቅደስ ብስራቱን -በቤተ ልሔም ልደቱን -በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን -በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን -በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር። የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ። በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው። #በዚያም :- -የብርሃን ዐይን ተቀብለው -6 ክንፍ አብቅለው -የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው -ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው -ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው -ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው -"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል። #ያደረጓቸው_ተአምራት የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው። ሙት አንስተዋል ድውያንን ፈውሰዋል አጋንንትን አሳደዋል እሳትን ጨብጠዋል በክንፍ በረዋል ደመናን ዙፋን አድርገዋል። ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል። በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል። በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: #ዕረፍት ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል። ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል። 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል። የጻድቁ በረከት ምልጃና ጸሎት ይደረግልን። በቃል ኪዳናቸው ለሀገራችን ሰላምን ይስጥልን። #ለእግዚአብሔር_ምስጋና ይሁን💚💛❤️ 💚 @mahiberekidusan 💚 💛 @mahiberekidusan 💛 ❤️ @mahiberekidusan ❤️

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ዘለዓለም ሥላሴ አሜን። #​​እንኳን_ለታላቁ_ቅዱስ ለአቡነ ተክለ ኃይማኖት ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።🙏 #ልደት በልቡናው መልካም መልካም መዝገበ ያስቀመጠ ሰው ከልቡናው መዝገብ አውጥቶ ዛፍ የሚናገረው ከዚያው ነውና የጻድቁ ወላጆችም በደግነት፣ በጸሎት ከልባቸው የተመኙትን ወደ እግዚአብሔር አመልክተው ተደርጎላቸዋለ። መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው። እርሱ በክህነቱ እርሷ በደግነቷ በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል። በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ ሚካኤል ጸጋ ዘአብን ከሞት እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል። በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል። ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተጸነሱት መጋቢት 24 ቀን በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታሕሳስ 24 ቀን በ1207 ዓ/ም ነው። በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል። ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል። #ዕድገት/አስተዳደጋቸው የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል። ይሕንን ስም ይዘው አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል። በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል። በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል። ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል። #መጠራት_ወደ ቅድስና ህይወት አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮስ ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ። የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ። "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን። ከዚህ በሁዋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ። ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ። ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ ሰዓትን አላጠፉም። ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ። #አገልግሎት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ። በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ። ያን ጊዜ ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት። 1ኛ. ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል። 2ኛው. ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር። ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ። ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: #ገዳማዊ_ሕይወታቸው ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል። እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል። እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል። በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል። በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል። #ስድስት_ክንፍ ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል። ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር:: የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል። ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በሁዋላ ነው ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም። በገሃድ:- -በቤተ መቅደስ ብስራቱን -በቤተ ልሔም ልደቱን -በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን -በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን -በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር። የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ። በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው። #በዚያም :- -የብርሃን ዐይን ተቀብለው -6 ክንፍ አብቅለው -የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው -ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው -ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው -ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው -"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል። #ያደረጓቸው_ተአምራት የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው። ሙት አንስተዋል ድውያንን ፈውሰዋል አጋንንትን አሳደዋል እሳትን ጨብጠዋል በክንፍ በረዋል ደመናን ዙፋን አድርገዋል። ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል። በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል። በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: #ዕረፍት ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል። ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል። 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል። የጻድቁ በረከት ምልጃና ጸሎት ይደረግልን። በቃል ኪዳናቸው ለሀገራችን ሰላምን ይስጥልን። #ለእግዚአብሔር_ምስጋና ይሁን💚💛❤️ 💚 @mahiberekidusan 💚 💛 @mahiberekidusan 💛 ❤️ @mahiberekidusan ❤️

"…በዚህ ዓለም 64 ዓመት ኑራ ጥር 21 ቀን ያረፈችው የእመቤታችን የእረፍቷስ ነገር እንደምን ነው ቢሉ… "…ቅዱስ ዮሐንስን እንደምን ሆነች አሉት ከገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አለች አላቸው። ቅዱስ ዮ
+2
"…በዚህ ዓለም 64 ዓመት ኑራ ጥር 21 ቀን ያረፈችው የእመቤታችን የእረፍቷስ ነገር እንደምን ነው ቢሉ… "…ቅዱስ ዮሐንስን እንደምን ሆነች አሉት ከገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አለች አላቸው። ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ ብለው በነሐሴ መባቻ ጾም ጀመሩ 2ሱባዔ ሲፈጸምም እሑድ አምጥቶ ሰጥቷቸው ቀብረዋታል። በ3ኛ ቀን ማክሰኞ “ከመ ትንሳኤ ወልዳ” እንደ ልጇ ተነሥታለች። ቅዱስ ቶማስ አልነበረም ደመና ጠቅሶ ከሀገረ ስብከቱ ሲመጣ ስታርግ አገኛት። ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ ዛሬም ደግሞ ያንችን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁን ብሎ “ወፈቀደ ይደቅ እምደመናሁ” ከኀዘኑ የተነሳ ሊወድቅ ወደደ። እመቤታችንም አይዞህ አትዘን እሊያ ትንሣኤዬን ዕርገቴን አላዩም አንተ አይተሃል ተነሣች ዐረገች ብለህ ንገራቸው ብላ የያዘችውን ሰበን ሰጥታ ሰደደችው። ከዚህ በኋላ ሂዶ የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ? አላቸው። አግኝተን ቀበርናት አሉት። ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር ተዉ ይህ ነገር አይመስለኝም አላቸው። ቅዱስ ጴጥሮስም መልሶ አንተ እንጅ ልማድህ ነው አንተ ብቻ ተጠራጥረህ አትቀርም ሰውን ሁሉ ስታጠራጥር ትኖራልህ ብሎ ተቆጥቶ ወደ መቃብሩ ሂዶ ቢከፍተው አጣት። ደንግጦ ቆመ ሐዋርያው ቶማስም አታምኑኝም ብየ እንጅ እመቤታችንስ ተነሣች ዐረገች አላቸው። የያዘውንም ሰበን ሰጣቸው። ለበረከትም ተካፍለውታል። "…በዓመቱ ሐዋርያት ቅዱስ ቶማስ ትንሣኤሽን ዕርገትሽን ዓይቶ እኛ ሳናይ ብለው ጾም ጀመሩ በ16ኛው ቀን እመቤታችንን መንበር፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ካህን፣ ቅዱስ እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ በዚያው ላይ ቀድሶ አቁርቧቸዋል። ቤተክርስቲያንም ይህንን መታሰቢያ አድርጋ በየዓመቱ ታከብረዋለች። ወስብሐት ለእግዚአብሔር @mahiberekidusan

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_ዘለዓለም_ሥላሴ_አሜን። #እንኳን_ለእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም_ጾመ_ፍልሰታ የፍቺ በዓል ና ለእመቤታችን የትንሳኤና የዕርገት በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ! በአጽናፈ  ዓለም የምትኖሩ/የምትገኙ ውድ  የክርስትና እምነት ተከታዮች የተዋህዶ ልጆች ክርስቲያናዊ ሰላምታችን በቅዱስ እግዚአብሔር ስም ይድረሳችሁ፡፡ #የእመቤታችን_ትንሣኤና_ዕርገት_ ነሐሴ 16 ቀን የእመቤታችን ድንግል ማርያም ሥጋዋ ያረገበት ዕለት ነው። #እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም በዚህ ምድር የኖረችው ስልሳ_አራት ዓመት ነው፡፡ እነዚህ ዓመታት ሲተነተኑ ሦስት ዓመት በወላጆቿ ሐናና ኢያቄም ቤት፣ ዐሥራ ሁለት ዓመት በቤተ መቅደስ፣ ሠላሣ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አሥራ አምስት ዓመት ከሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ጋር ነው፡፡ እመቤታችን እመ አምላክ በስዕለት የተወለደች ፣ በጸጋ የተሞላች፣ ባለሟልነትን የተጎናጸፈች፣አምላክን በአጭር ቁመት ፣በጠባብ ደረት የወሰነች፣የመለኮቱ እሳትነት ስጋዋን ሳያቃጥላት አምላክ ፈጣሪዋን ጸንሳ የወለደች ፣ በግብፅ በርሃ በስደት የተንከራተተች፣ በእውነቱ የህይወትን ምግብ አዝላ ስለእኛ የተራበች ፣የተጠማች፣ ከመዓር ከስኳር የሚጥም ጡቶቿን ያጠባችው ልጇ በቀራኒዮ ኮረብታ ተሰቅሎ ሲሞት መሪር እንባን ያለቀሰች፣ ለቅዱሳን ስደትን ለመባረክ ምሳሌ በመሆን የተጓዘች የተንገላታች ... ድንቅ ዘለዓለማዊ እናት ነች። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በቅዳሜ አርጋኖን ሶስቱ ያልተከፈቱ ደጆች ይልና ። ያብራራል ። አንድም በድንግልና መጽነሷን፦ ድንግልናዋን ሳይለውጠው እግዚአብሔር ወልድ በግብረ መንፈስ ቅዱስ የመጸነሱ፤ በሁለተኛ ደረጃ ክርስቶስን በምትወልድበት ጊዜ የሴቶች ልማድ ሳያገኛት በጥበበ እግዚአብሔር መውለዷ፤ በሶስተኛ ደረጃ ደግሞ ከወለደችው በኋላ ማህተመ ድንግልናዋ አልተፈታም። እመቤታችን ዘላለማዊ ድንግል ናት። የስጋ ብቻ ያይደለ የሀሳብም ድንግል ናት። አጠር ባለ አገላለጽ አምላክን ከመውለዷ በፊት፣ አምላክን በምትወልድበት ጊዜ እና አምላክን ከወለደች በኋላ ፍጹም ዘላለማዊ ድንግል መሆኗን ሊቁ ያስረዳል ።  እመቤታችን ጥር 21 ቀን በ50 ዓ.ም ከዚህ አለም ድካም አርፋ ወደ ልጇ ተጠርታ ሄዳለች። ወላድተ አምላክ ባረፈችበት ወቅት ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡር ሥጋዋን ለማሳረፍ ወደ ጌቴ ሴማኒ ሲሔዱ አይሁድ "ቀድሞ ልጇ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ፤ በአርባኛውም ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ፤ ተመልሶም ይህን ዓለምን ለማሳለፍ ይመጣል እያሉ በማስተማር ሕዝባችንን ወስደውብናል፡፡ አሁን ደግሞ ዝም ብለን ብንተዋት እርሷም እንደ ልጇ ተነሳች እያሉ በማስተማር ሊያውኩን አይደለምን? ኑ! ተሰብስበን በእሳት እናቃጥላት" ብለው ክፉ ምክር ተማከሩ፡፡ አይሁድም ከተማከሩ በኋላ ከመካከላቸውም ብርቱ ጉልበተኛ ሰው የሆነው #ታውፋንያ የተባለ ቅድስት ሥጋዋን ከሐዋርያት ነጥቆ ለማስቀረት ክቡር ሥጋዋ ያለበትን የአልጋ ሸንኮር ሲይዝ በመልአከ እግዚአብሔር እጁ ተቆርጣ ከአልጋው ላይ ተንጠልጥላ ቀረች፤ ከዚህ የጥፋቱ ሥራው ተምሮ እመቤታችንን በመለመኑ እመቤታችን የተቆረጠች እጁን መልሳለታለች፡፡ ከዚህ በኋላ መልአከ እግዚአብሔር የእመቤታችንን የተቀደሰ ሥጋዋን ጌታችን ይወደው የነበረ ተብሎ የተነገረለት ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስን ይዞ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር አስቀመጠው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም የሆነውን ሁሉ ለወንድሞቹ ቅዱሳን ሐዋርያት ነገራቸው፡፡ እነሱም የእመቤታችን ሥጋ በክብር ለማሳረፍ ካላቸው ጉጉት የተነሣ ከነሐሴ 1 ቀን ጀምሮ ሱባኤ ገቡ፡፡ ከሁለተኛ ሱባኤ ቆይታቸው በኋላ በአሥራ አራተኛ ቀናቸው ጌታችን የእመቤታችንን ትኩስ ሥጋ ሰጣቸው፡፡ ሐዋርያትም በዝማሬና በታላቅ ምስጋና በጌቴ ሴማኔ ቀበሯት፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ‹‹አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት› › ተብሎ ትንቢት የተናገረውን ሲተረጉሙት ‹‹ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ሆይ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምታሳርፈው የመቅደስህ ታቦት የሆነችውን ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነሥ›› ብለው ያመሰጥሩታል፡፡ /መዝ. 131፥8/፡፡ የእመቤታችንን ቅድስት ሥጋዋን ሐዋርያት ሲቀብሯት በሀገረ ስብከቱ ሕንድ የነበረው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመናሰረገላ ተጭኖ ሲመለስ እመቤታችን ስታርግ አገኛት። ለማረጓ ምልክት ይሆን ዘንድ ለምልክት እንዲሆነው ሰበኗን (የመግነዟን ጨርቅ) ተቀብሏት ይለያያሉ፡፡ ለወንድሞቹ ለቅዱሳን ሐዋርያት ያየውን ምስጢር/የተመለከተውን ድንቅ ተዓምር/የወላድተ አምላክን ዕርገት ነገራቸው፡፡ እመቤታችን ለበረከት የሰጠችውንም ሰበን አሳያቸውና አካፈላቸው ፤ ሐዋርያት ‹ ‹ዕርገቷን እንዴት እሱ ብቻ ተመልክቶ ለምን እኛ ይቀርብናል› › ብለው በዓመቱ ነሐሴ አንድ ቀን ሱባኤ ገቡ፡፡ ነሐሴ 16 ቀን የልባቸው መሻት ተፈጸመላቸው፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችንን መንበር፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ንፍቀ (ረዳት) ቄስ፣ ቀዳሚ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን ገባሬ ሰናይ (ዋና ዲያቆን) አድርጎ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው፡፡ በንጽህና፣ በፍጹም እምነት ፣በትኅትና የያዙት በተስፋ የጠበቁት በአንድነት ወደ እግዚአብሔር ያቀረቡት ሱባኤም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዕርገቷን ለማየት አበቃቸው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ይህን መሠረት አድርጋ ከነሐሴ 1-16 ጾመ ፍልሰታ በማለት ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ አድርገን እንድንጠቀምበት ሥርዐት ሠራችልን፡፡ በቅዱሳን አበው በነቢያትና በሐዋርያት በቅዱሳን ሁሉ መሠረት ላይ የታነጽን ኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች በየዓመቱ ይህን ጾም በሱባኤ በማሳለፍ ከእመቤታችን ጸጋና በረከት ተሳታፊዎች እንሆናለን፤ ሆነናልም፡፡ ለቅዱሳን ሐዋርያት ትንሳኤዋን ፣ ዕርገቷን እንደገለጸችላቸው ለእኛም ምስጢርን ፣ እውቀትን ታድለን ። ትግለጽልን ። የአመት ሰው ይበለን። መልካም በዓል ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከወላድተ አምላክ በረከት፣ረድኤት ፍቅር፣ምልጃና ጸሎት ተካፋዮች ያድርገን፡፡                      አሜን! ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን🙏🙏🙏 #ለወዳጅዎ_ዘመድ_ ፣_ለተዋህዶ_ልጆች #ሼር_ያድርጉ! 💚 @mahiberekidusan 💚 💛 @mahiberekidusan 💛 ❤️ @mahiberekidusan

የሐሙስ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan

#በስመ-አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን            መንፈሳዊ  ግጥም             #ደብረ_ታቦር ከደብሮች ሁሉ ልቀሽ   እውነት ብርሃንን አጥልቀሽ ተንቀሽ የነበርሽ ተራራ አንቺ የምሥጢር ሥፍራ የመለኮት ብርሃን በር የሥሉስ ቅዱስ ምሥጢር ልቆ የታየብሽ መንደር ደብረ ታቦር!!! ከአድማሳት ከፍ ከፍ ብሎ የስምሽ ተረፈ ውሉ የተዘከረው በዓለሙ ምን ይሆን ወርቅ ሰሙ? ምን አገኘሽ ያኔ ታቦር እንዲያ ተከፍቶ የብርሃንሽ በር የክብሩ ግርማ የዋጠሽ እኮ ማን ነው የረገጠሽ? ጌታሽ ነው አሉ ስሰማ ከተራራሽ አናት ማማ የብርሃን ጉንጉን ሸማ ያጎናፀፈሽ በግርማ ግሩም እኮ ነው! ከተራሮች አንቺን መርጦ ከነአባቱ ተገልጦ ደጅሽን ሳይንቅ ማክበሩ እንዴት እንዴት ይሆን ምሥጢሩ?   ይህንንም ደግሞ ዳዊት ተናግሯል አሉ በትንቢት ታቦር ወአርሞንኤም በሚል ቅኔ በስሙ ተደሰቱ ያኔ እያለ ዘመረ በክብር የዚህችን ተራራ ምሥጢር ያ ልበ አምላክ ዳዊት የተናገረው ትንቢት ለካ ይህ ኖሯል ግቡ ደጅሽ በብርሃን ማበቡ ኧረግ! አንቺስ ታድለሻል የማይቻለውን ችለሻል እሳተ መለኮትን ይዘሻል ለመሆኑ እንዴት ቻልሽው ታቦር ያን እውነተኛ ፍቅር? ከመንበሩ የሳበው ንጉሥ በብርሃን ሠረገላው ሲፈስ መሠረትሽ ሳይናጋ ባለበት ቆሞ የረጋ ምን ይሆን ምሥጢሩ የፅናትሽ በፊቱ ቆመሽ መታየትሽ? ልብሱ ነጭ ሆኖ በረድ አብም ከሰማይ ሲወርድ ዙሪያው በክብር ደመና ተመልቶ በብርሃን ፋና ሙሴ ከመቃብሩ ተጠርቶ ኤልያስ ከብሄረ ሕያዋን መጥቶ     በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው ሲወያዩ ላስተዋለው ምን ይመስል ይሆን ገጹ? የብርሃን መለኮት መገለጹ ደግሞ የሐዋርያቱ የእነዚያ የሦስቱ ሲጋልቡ ርደው እንደ ቄጤማ ወርደው ከሰሩ የተነጠፉቱ ምንድን ይሆን ምክንያቱ? ጴጥሮሰማ ተሽብሮ ናላው በድንጋጤ ዞሮ ለእያንዳንዳችሁ በጋራ ሦስት ዳሶችን እንስራ ብሎ በዚያች የብርሃን እልፍኝ የዘለዓለም ደስታን ሊያገኝ አስቦ በቅጽበት መመኘቱ ገርሞትም አይደል ክስተቱ የብርሃን ፀዳል ድምቀቱ? እኮ እንደምን አይገርመው ሙሴና ኤልያስ ቆመው ክብሩን ሲያውጁ እያዩ ማነው የሙሴን አምላክ ሙሴ ባዩ? ሲል ሙሴ ባሕር ከፋዩ የኤልያስንስ ክብር ጌታ አውርደውት ከሰው ተርታ ኤልያስ ባዮቹ እነማን ናቸው? ሲል ኤልያስ ገርሟቸው ይህን ሲሰሙ ሐዋርያቱ በድንጋጤ ሲመቱ ደግሞ ወርዶ አባቱ ልጄን ስሙት በማለቱ በፍርሃት ማዕበል ሲንገላቱ ይህ ሁሉ ምስጢር መታየቱ በአንቺም አይደል ታቦር መገለጹ የሦስትነት ምስጢር ጥንትስ ታሪክሽ ተዘክሮ መቼ ያልቅና ተነግሮ እንዲያው ድንቅ እንበል እንጂ ድንቅ ድንቅ! የብርሃንሽ ሰንደቅ ከአድማሳት ልቆ ሲደምቅ ክብር እንበልሽ ክብር!ክብር!   አንቺ እውነተኛ የምስጢር በር የሥሉስ ቅዱስ ነገር የተገለጸብሽ መንደር ደብረ ታቦር!!! ያበራሽ ይብራ ስሙ ይግነን ዛሬም ለእኛ ብርሃን ይሁነን ገኖ ያግነን በፈቃዱ በራ ይሁንልን መንገዱ ክብሩም ከፍ ከፍ ወደ ላይ ከሰማየ ሰማያት በላይ እንዲሁም በምድር በቀላይ የአምላካችን አዶናይ ክብርሽ ዛሬም ነገ ይነገር መሆንሽ እውነተኛ የብርሃን በር የሥሉስ ቅዱስ ምስጢር የተገለጠብሽ መንደር ደብረ ታቦር!!! ልዑል አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር በብርሃነ መለኮቱ ዘመናችንን ፣ ህይወታችንን ያብራልን። መልካም በዓል 🙏🙏🙏 ወስበሐት ለእግዚአብሔር። @mahiberekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan

የረቡዕ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekiduaan

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ዘለዓለም ሥላሴ አሜን፡፡ #እንኳን_ለደብረ_ታቦር_በዓል_በሰላም_አደረሰን፡፡        ደብረ ታቦር/ቡሔ ነሐሴ 13 ቀን ጌታችን መድኃኒታችን  ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሀነ መለኮቱን የገለፀበት ዕለት ነው፡፡ በዚች ዕለት አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሶስቱን ደቀ መዛሙርቱን ጴጥሮስን፣ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ወደ ተራራ ላይ ወጡ መልኩም በፊታቸው ተለወጠና ብርሃነ መለኮቱን ገለጸባቸው ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሆነ ሉቃ 9፥28 ማቴ 17 ፥1 እነሆ ሙሴን ከመቃብር ኤልያስን ከብሔረ ህያዋን ጠቅሶ አምጥቶ አሳያቸው፡፡ ጴጥሮስም ይህንን አይቶ ጌታችንን እንድህ አለው፡፡አቤቱ ጌታ ሆይ በዚህ መኖር መልካም ነው ሶስት ሰቀላዎችንም እንስራ አንዱን ለአንተ አንዱን ለሙሴ አንዱን ለኤልያስ አለው፡፡ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሰው እጅ የተሰራ ማደሪያ የማይሻ መሆኑን ለጴጥሮስ ያሳየው ዘንድ እነሆ ደመና ጋረዳቸው የጌታችንን ጌትነቱን የሚገልፅ በሐዋርያትም ልቡና እምነትን የሚያጸና እንድህ የሚል ቃል ከደመና ውስጥ መጣ ይህ የምወደው በእርሱ ደስ የሚለኝ     ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት ሙሴና ኤልያስም ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩት ትንቢታቸውንም በቸርነቱ አረጋግጦ ወደ ተራራ ላይ በመውጣቱ ነቢያት እና ሐዋርያት ደስ አላቸው፡፡ በአጠቃላይ ይህ ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ሙሴና ኤልያስን ለሶስቱ ምስጢረ ሐዋርያት ያሳየበት እርሱም ሁለመናው ነጭ ልብስ መልኩ እንደመብረቅ ሆኖ የታየበት ዕለት ነው ፡፡ በቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ይህ በዓል ከጌታችን አበይት በዓላት አንዱ እንደሆነ ታስተምራለች፡፡ ምዕመናንም በዓሉን በድምቀት ያከብሩታል፡፡ ዳቦ በመጋገር ምሳሌውም እረኞች በተራራው ላይ ብርሀኑን እያዩ በወጡበት አልተመለሱም ነበረና ቤተሰቦቻቸው ዳቦ ይዘው የመሄዳቸው ምሳሌ ነው ጅራፉ የነጎድጓድ ችቦ የሚበራው ወይም ደመራው የብርሃነ መለኮቱ ምሳሌ ነው፡፡ #እናት_ቤተ ክርስቲያን ሁሉንም በምሳሌ ሰንዳ አስቀምጣለች፡፡ ለአባቶቻችን ምስጢሩን የገለጸ ለእኛም ይግለጽል፡፡ ስለ ሁሉም ነገር የቸርነቱን ስራ ይስራልን፡፡ ከበዓሉ በረከት ከቅዱሳን ምልጃና ጸሎት ከመላዕክት ጠባቂነት ከቅድስት ድንግል ማርያም እናትነትና ምልጃ ይክፈለን፡፡ "አድህነኒ እግዚኦ እስመ ኃልቀ ኄር ወውህዴ ኃይማኖት እመእጓለ እመህያው" መዝ 11፥1 ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላድቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን፡፡ @mahiberekidusan

የማክሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan

+1
የእሁድ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan

👉 የቅዳሜ ውዳሴ ማርያም አንድምታ 🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን #ለወዳጅዎ-ለተዋህዶ ልጆች_ሼር ያድርጉ! 💚 @mahiberekidusan💚 💛 @mahiberekidusan💛 ❤️ @mahiberekidusan

+3
የአርብ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-በማድረግ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታዎን ይወጡ። @mahibetekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan

የሐሙስ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan

የረቡዕ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekiduaan

👉 ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ በሁለተኛው ክፍል ለክርስቶስ ምሳሌ ሁኖ የቀረበውን ወፍ ታሪክ ላጋራችሁ ስለ ከራድዮን ወፍ ምን ያክል እናውቃለን "ከራድዮን ወፍ ምንድነው ከራድዮን ነጭ ወፍ ሲሆን በሊቃውንት ዘንድ የታወቀ ነው። ጠቢባን በድካም ፈልገው አድነው ይይዙታል፣ የታመመ ሰው ቢኖር ያቀርቡታል ፤ እሱም በሽተኛውን ትኩር ብሎ ያየዋል የማይድን ለሞት የቀረበ ከሆነ ፊቱን ይመለሳል፣ የሚድን ከሆነ ግን አፉን ከፍቶ ከበሽተኛው አፍ አድርጎ እስትንፋሱን ይወስዳል፣ የሰውየው ደዌ ሙሉ ለሙሉ ወደ ወፉ በእስትንፋሱ ይተላለፋል። ሰውየው ይድናል ወፉ ይታመማል። 👉ነጭ የነበረው እንደ ክሰል ይጠቁራል፣ ህመም ሲሰማው ወደ አየር ይነጠቃል ሲብስበት ወደ ባሕር ራሱን ይወረውራል። በባሕር 3 መዓልት 3 ሌሊት ቆይቶ ጽጉሩን መልጦ አዲስ ጸጉር ተክቶ ፣ድኖ፣ታድሶ፣ኃያል ሆኖ ይወጣል። ይህን ወፍ ሊቃውንቱ የክርስቶስ ምሳሌ ወይም የምስጢረ ትንሣኤ ሙታን ምሳሌ አድርገውታል ከራድዮን ወፍ ---- የክርስቶስ ምሳሌ የታመመው ሰው --- የአዳም ዘር ምሳሌ ሲሆን ወፉ በዐይኑ መመልከቱ --- በክርስቶስ ላመነ ሁሉ ድኅነት ምህረት ማግኘቱ ምሳሌ ወፉ መታመሙ---- ክርስቶስ ስለ እኛ በደል መታመሙ ምሳሌ። መጥቆሩ ---- ስለእኛ ቤዛ ከኀጢአተኛ የመቆጠሩ ምሳሌ ወፉ ወደ ላይ መውጣቱ---- ክርስቶስ ከፍ ብሎ መሰቀሉ ምሳሌ ወፉ በባህር 3ቀን 3ሌሊት መኖሩ ----ክርስቶስ በከርሰ መቃብር 3ቀን 3 ሌሊት መቆየቱ ምሳሌ 👉ከራድዮን ወፍ ታድሶ ኃያል ሆኖ ከባህር መውጣቱ -ክርስቶስ በሲዖል የነበሩ ነፍሳትን አድሶ አንጽቶ ገነት አስገብቶ፤ እርሱም ከቅድስት ድንግል ማርያም በነሣው በለበሰው ሥጋ ወደ ቀደሞ መለኮታዊ ሥልጣኑ ኃይሉ መቀመጡ ምሳሌ ነው። የታደለው ወፍ የክርስቶስ ምሳሌ ሲሆን ያልታደለው የሰው ልጅ የክርስቶስ ምሳሌ መሆን ሲገባው የዲያብሎስ ምሳሌ ሆነ 🤔🤔🤔 በኦሪቱ ፈርዖን እና ሠራዊቱ በዲያብሎስ በአጋንንት ተመስለዋል ግብጽ የገሃነም ወይም የሲዖል ምሳሌ ሁናለች። @mahibrrekidusan

የማክሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan

+3
የአርብ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-በማድረግ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታዎን ይወጡ። @mahibetekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan

ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan): የአርብ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-በማድረግ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታዎን ይወጡ። @mahibetekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan 👉 የቅዳሜ ውዳሴ ማርያም አንድምታ 🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን #ለወዳጅዎ-ለተዋህዶ ልጆች_ሼር ያድርጉ! 💚 @mahiberekidusan💚 💛 @mahiberekidusan💛 ❤️ @mahiberekidusan❤ የእሁድ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan የሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር ያድርጉ @mahiberekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan

ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan): በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ዘለዓለም ሥላሴ አሜን። #ጾመ_ፍልሰታ ፍልሰታ የግእዝ ቃል ነው፤ #ፈለሰ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጕሙም ተለየ፣ ሄደ፣ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ መሄድን ያመለክታል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያትን አብነት አድርገን፤ ሐዋርያት የተቀበሉትን በረከት ለማግኘት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን የምንጾመው ታላቅ ጾም ነው። እመቤታችን እንደ ሰው ልማድ ሞትን ትቀምስ ዘንድ ግድ ስለኾነ፤ ጻዕርና ሕማም በሌለበት አሟሟት፤ ዕዝራ በመሰንቆ፥ ዳዊት በበገና እያጫወቷት፤ በተወለደች በ64 ዓመቷ ጥር 21 ቀን #በ48 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ አርፋለች። ሐዋርያትም እንደምታርፍ በመንፈስ ቅዱስ ስለተገለጸላቸው ከያሉበት (ከየሀገረ ስብከታቸው) ወደ መኖሪያ ቤቷ (የሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ቤት) ተሰባስበው ነበር። ነፍሷ ከሥጋዋ እንደተለየች ሥጋዋን ገንዘውና ሸፍነው ወስደው ለመቅበር ወደ #ጌቴሴማኒ ሲሄዱ አይሁድ ሰምተው መጡና ሐዋርያትን ከበቧቸው። የአይሁድ ተንኮል አስከሬኗን ከሐዋርያት እጅ ቀምተው በእሳት ለማቃጠል ነበር፤  ይህንንም ማድረግ የፈለጉበት ምክንያት፤ የሐዋርያት ትምህርት (የጌታችን ከሞት መነሳትና ለፍርድ ተመልሶ መምጣት)ከአይሁድ አልፎ ዓለም ሁሉ እያመነበት ስለመጣ እመቤታችንም ተነሥታ ዐርጋለች እያሉ ሐዋርያት ያስተምራሉ በሚል ስጋት ነበር። ‹‹የፈሩት ይነግሣል፥ የጠሉት ይወርሳል›› እንዲሉ አበው፤ የእመቤታችን ትንሣኤም ሆነ ዕርገት አይቀሬ ሁኗል። አይሁድ የእመቤታችንን ሥጋ ለመንጠቅ በሞከሩበት ጊዜም #ታውፋኒያ የተባለ ጎልማሳ ሰው በጉልበቱና በድፍረቱ በአይሁድ ዘንድ ተመርጦ የእመቤታችንን ሥጋዋ ያረፈበትን ቃሬዛ ከሐዋርያት ነጥቆ መሬት ላይ ለመጣል ሲሞክር፤ የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሰይፍ ሁሉቱንም እጆቹን ቀንጥሶ (ቆርጦ) ጥሏቸዋል። ነገር ግን ጥፋቱን አውቆ ወዲያው ስለተፀፀተና ይቅርታ ስለጠየቀ በአምላክ ፈቃድ በእመቤታችን አማላጅነት በቅዱስ ጴጥሮስ አማካኝነት እጆቹ እንደገና ተመልሰውለት የእመቤታችንን እመ አምላክነት (የአምላክ እናት መሆኗ)ና ክብርን ለመመስከር በቅቷል። የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ በመላእክት ተነጥቆ ከተወሰደ በኋላ በገነት ውስጥ #በዕፀ ሕይወት ሥር መቀመጡ ከዮሐንስ በስተቀር ለሌሎች ሐዋርያት ለጊዜው ምሥጢር ሆኖባቸው ቆይቶ ነበር። ቆየት ብሎ ግን ሐዋርያው ዮሐንስ ስለ እመቤታችን ሥጋ ነገራቸው። ቅዱሳን ሐዋርያትም ለእመቤታችን ካላቸው ክብርና ፍቅር የተነሳ ለምን አልቀበርናትም? ለምንስ የሥጋዋ ምሥጢር ለዮሐንስ ተገልጾ ለኛ ይደበቅብናል? በማለት እያዘኑና እየለመኑ ከጥር 21 አንስተው ለስድስት ወራት ከዐሥር ቀናት ቆይተዋል። ከዚህም በኋላ ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ሱባዔ ይዘው ለ14 ቀናት እግዚአብሔርን በጾምና በጸሎት ጠየቁት። በመጨረሻም የነገሩትን የማይረሳ፥ የለመኑትን የማይነሳ ልጇ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነሐሴ 14 ቀን ሥጋዋን አምጥቶ ስለሰጣቸው፤ ሳይውሉ ሳያድሩ በዕለቱ በጌቴሴማኒ በታላቅ ክብርና ዝማሬ ቀበሯት። በተቀበረችም በ3ኛው ቀን በነሐሴ 16 ከተቀበረችበት መቃብር ተነሥታ ወዲያውኑ በታላቅ ክብር በመላእክት አጃቢነት ወደ ሰማይ ዐርጋለች። ጥበበኛው ሰሎሞንም “ውዴ  እንዲህ ይለኛል ሙሽራዬ ውዴ ሆይ! ተነሺ የእኔ ውብ ሆይ ነዪ አብረን እንሂድ” በማለት አመሣጥሮ የተናገረው በጥበበ እግዚአብሔር ተመርቶ እንደ ክርስቶስ ሆኖ ውዴ ያላት እመቤታችን መሆኗንና ልጇ ተነሥቶ እንደ ዐረገ እሷም መነሣቷንና ማረጓን እንረዳለን። /መሓ.፪፥፲/። እመቤታችን ባረገችበት ጊዜ ሐዋርያው #ቶማስ በመንፈስ ቅዱስ ጥበብ በደመና ተጭኖ  ከሀገረ ስብከቱ  (ሕንድ) ወደ   ኢየሩሳሌም ሲመለስ እመቤታችን በመላእክት ታጅባ ወደ ሰማይ ስታርግ ተገናኙ። በዚህ ጊዜ ቶማስ ቀድሞ የልጇን ትንሣኤ ሳላይ አሁንም ደግሞ እርሷን ሳልቀብራት ከትንሣኤዋም ሳልደርስ ቀረሁ ብሎ አዘነ ከደመናው ላይ ሊወድቅም ፈለገ፤ ሆኖም እመቤታችን ዕርገቷን ከእርሱ በቀር ሌሎች አለማየታቸውን ገልጻ አረጋጋችው፤ ዕርገቷንም ለሐዋርያት እንዲነግርና ምልክትና ማስረጃ እንዲሆነው ተገንዛበት የነበረውን ሰበኗን/የከፈን ጨርቅ/ ሰጥታ አሰናበተችው።     ቶማስም መሬት ለይ ወርዶ መቀበሯን፣ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ያላወቀ መስሎ ሐዋርያትን ስለ እመቤታችን ሥጋ ጉዳይ ጠየቃቸው፤ እነርሱም ሱባዔ ገብተው እግዚአብሔርን በጸሎት መጠየቃቸውን፣ ከሱባዔያቸው በኋላ የእግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኖ ሥጋዋን መላእክት አምጥተው እንደሰጧቸውና እንደቀበሯት አስረዱት። እርሱ ግን ‹‹ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር›› እንዴት ሊሆን ይችላል? ሲል ተከራከራቸው። ሐዋርያትም ቶማስን ለማሳመንና ለማሳየት ወደ መቃብሯ ወሰዱት፤ ሆኖም መቃብሯ ባዶ ሆኖ አገኙትና ተደናገጡ፤ በዚህ ጊዜ ቶማስ የሆነውን ሁሉ ገልጾ ለምልክትና ለማረጋገጫ የሰጠችውን ሰበኗን /ተገንዛበት የነበረውን ጨርቅ/ አሳያቸው፤ የራሱን ድርሻም አስቀርቶ አከፋፍሎ ሰጣቸው፤ #ዛሬም_ካህናት ከእጅ መስቀላቸው ጋር የሚይዙት እራፊ ጨርቅ የሚይዙበት ምክንያት ሐዋርያት የተከፋፈሉት የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ ነው።        ሐዋርያትም የዕርገቷን ምሥጢር ካመኑ በኋላ ዕርገቷን ለማየት በዓመቱ በተመሳሳይ ሁኔታ እንደገና ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ለ፪ኛ ጊዜ ሁለት ሱባዔ ገቡ፣ እግዚአብሔርም ልመናቸውን ሰምቶ በነሐሴ ወር በ16ኛው ቀን ጌታችን ሐዋርያትን ወደ ሰማይ አውጥቷቸው እመቤታችንን አግኝተዋት ከሷ ተባርከው በታላቅ ደስታ ወደ ደብረዘይት ተመልሰዋል። በአጠቃላይ #የእመቤታችን ለሐዋርያት በተለያዩ ጊዜያት መታየት፣ የሥጋዋና የነፍሷ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ፍልሰት ሲባል ከዚህ የተነሣ #የነሐሴ ጾም በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዐት መሠረት ሐዋርያት ያገኙትን በረከት ለማግኘት ጾመ ፍልሰታን እንጾማለን።  የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃና ጸሎት አይለየን :: ኦርቶዶክሳዊ ወንድሞች እና እህቶች ሆይ ለኦርቶዶክሳዊ ወንድምዎ እህትዎ ሼር በማድረግ የቤተክርስቲያናችንን ቀጥተኛ ትምህርት ያሳውቁ ይመስክሩ ። 👇👇👇👇👇👇👇👇 👇@mahiberekidusan 👇@mahiberekidusan      @mahiberekidusan 👆👆👆👆👆👆👆👆 የአርብ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ #ሼር-በማድረግ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታዎን ይወጡ። @mahibetekidusan @mahiberekidusan @mahiberekidusan