cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Getem becha

Hey their🖐🖐 how r u ? In this channel we will listen and see Music 🎵🎶🎶 Videos📽📽 Poems 📝📝 Stories📖📖 Quotes 📑 💫💫 feel likes ur home😘😘😘 Ask whatever u want @kidukud Ebakachehun qexeta weda gudayachu gebu 😇😇 @kidukid

Більше
Країна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
Рекламні дописи
348
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

​​🙇🙇🙇ስህተቴ🙇🙇🙇 🌺🌺ክፍል አምስት (5)🌺🌺 🌼🌼 ቅን ልቦች 🌼🌼 አረብ ሀገር ካሉ ሴቶች ብር መቀበል ከጀመርን በኋላ ሱስ ላይ ሳንወድቅ አንዳንዴ ለሙድ ብለን እንቃም ተባብለን መቃም ጀመርን። እኔናሚኪ ሄለንን እና ፌቨንን አብረዉን እንዲተኙ ለማድረግ ጉትጎታዉን ጀምረናል። . አርብ ቀን ከፌቪ ጋር እንደተገናኘን ኦፊሳችንን እንድትጎበኘዉ ወደተከራየነዉ ቤት ይዣት ሄድኩ። ቀድሜ ከነአብነት ጋር አዉርቼበት ስለነበር ቤቱን አስተካክለዉ ወደ ፑል ቤት ሄደዋል። በነገራችን ላይ ኦፊሳችን ዉስጥ ያሉት ነገሮች ከሪም ከቤቱ ያመጣዉ አንሶላ ፣የገዛናቸዉ ፍራሽ ፣ ትራስ እና ትናንሽዬ የፕላስቲክ ወንበሮች ናቸዉ። ገና እንደገባን ፌቪ "ዋዉ ፍራሻችሁ ደስ ትላለች።" አለችና ጫማዋን አዉልቃ ፍራሹ ላይ ተቀመጠች። እኔ በሩ ጋር ቆሜ አያታለሁ። የዛሬዉ እቅዴ ከተሳካልኝ አብሪያት መተኛት ካልሆነም መንገዱን ማመቻቸት ነዉ። ሄጄ ከአጠገቧ ተቀመጥኩኝ። ፌቪ ዩኒፎርሟን አዉልቃ ቦርሳዋ ዉስጥ አድርጋዋለች። ከዉስጥ ሱሪ ለብሳ ስለነበር በሱሪ ናት። ከላይ ደግሞ የሚያምር ሰማያዊ ሹራብ ለብሳለች። በቦርሳዋ ይዛዉ የመጣችዉ ነዉ። ቲቸር እያሱ ካስደነገጣት በኋላ ሁሌም እንዲህ ነዉ የምታደርገዉ። . ከአጠገቧ እንደተቀመጥኩ "ፌቪዬ ምን ያህል ትወጂኛለሽ?" አልኳት። የሚካኤልን "ዉዴ እወድሻለሁ" የሚለዉን ዘፈን በወንድ አድርጋ ዘፈነችልኝ። ለጥያቄዬ በቂ ምላሽ ነበረዉ። በደንብ ወደሷ እየተጠጋሁ "ማለቴ ራስሽን አሳልፈሽ ትሰጪኛለሽ?" አልኳት። ደረቴ ላይ እየተኛች "ህይወቴ እኮ አንተ ነህ ምን ህይወት አለኝና ራሴን ካንተ እከለክላለሁ?" አለችኝ። "እወድሻለሁ!" አልኳት። ፌቪ እወድሻለሁ ስላት ደስ ይላታል። ከደረቴ ላይ ተነስታ ወደ ከንፈሮቼ ሄደች። ለኔናለሷ መሳሳም ቀልድ ነዉ። እንኳን እንደዚህ ባዶ ቤት አግኝተን ይቅርና መንገድ ላይ ጭር ሲልልን ራሱ እድሉን ከመጠቀም ወደኋላ ብለን አናዉቅም። . እየተሳሳምን እጆቼ አጉል ወደ ሆነ ቦታ ሲቃብዙ ፌቪ ያዘቻቸዉ። ትንፋሿን ሰበሰበችና አይኖቿን እየገለጠች ሹክሹክታ በሚመስል ድምፅ "ሀቢቤ አብረን እንድንተኛ ፈልገሀል እንዴ?" አለችኝ። እጆቼ እየተርመሰመሱ የነበረበት ቦታ ለመተኛት የሚገፋፋ በመሆኑ የገመተች ይመስለኛል። "አዎን ፌቪ! እኔ ሁሉም ነገር ካንቺ ተሟልቶልኝ ወደ ሌላ ሴት የማይበት ምክንያት ማጣት እፈልጋለሁ።" አልኳት። ድሀ ሆንኩ እንጂ ንግግርማ ታድሎኛል። ለመዉለቅ ምንም ያልቀረዉን ሹራቧን እየለበሰች "ሀቢቤ ትንሽ አትታገስም?" አለችኝ። ሙከራዬ እንዳይከሽፍ እየተመኘሁ "ፌቪ ምን እስኪፈጠር ድረስ ልታገስ?" አልኳት። "በቃ እሺ ላስብበት እና እነግርሀለሁ።" አለችኝ። እየሳቅኩ "እና እስከዛ መሳሙንም ተከለከልኩ ማለት ነዉ?" አልኩ። ፌቪ እንዳልነካት እጆቼን ወደ ኋላ ጠፍራ ይዛ ሳመችኝ። . ፌቪን ሸኝቼያት ሚኪያስ ጋር ደወልኩ። ከፑል ቤት መጥቶ ወደ እማዬ ምግብ ቤት ሄድን። "አብነትናከሪሜ ይመሽብናል ብለዉ ወደ ሰፈራቸዉ ሄዱ!" አለኝ። ከፌቪ ጋር እንዳልተኛን ስነግረዉ የሌለ ተናደደ። እንደዉም እንድዘጋት መከረኝ። እኔ ግን አስባበት የምትለዉን ከሰማሁ በኋላ ለመወሰን ነዉ ያሰብኩት። እማዬ ምግብ ቤቷን መዝጊያ ሰዓቷ ሲደርስ እንደተለመደዉ ሰፌዶቹን ይዤ ወደ ቤት ተመለስን። ሚኪ ወደ ቤቱ ተቀነጠሰ። . ሰፈር ስንደርስ አምሪያ ሰላሳ ሊትር ጀሪካን የግቢዉ በር ጋር አስቀምጣ በጆግ ዉሀ እየቀዳች የተከልናቸዉን ችግኞች ታጠጣለች። እማዬ እንደተለመደዉ የያዝኳቸዉን ሰፌዶች ተቀብላ "ሂድ ቢያንስ ሰላሳ ሊትር ጀሪካን ሴት ስትነቀንቅ ይሰማህ! ዉሀዉን በጆግ እየቀዳህ ስጣት!" አለችኝ። የእዉነት ተናድጃለሁ። ምናባቷ የማትችለዉን ስራ ያሰራታል? ብሽቅ! እየደበረኝም ቢሆን የእናቴን ትዕዛዝ ተቀብዬ አምሪያን ለማገዝ ወደ በራቸዉ ሄድኩኝ። በጆግ ዉሀ ቀድቼ እያቀበልኳት "አምሪ ቧንቧ የላችሁም እንዴ?" አልኳት። "እሱማ አለን ግን ሀይል ስለሚኖረዉ በጎማ ስቤ ባጠጣቸዉ ስላልጠነከሩ ይሰብራቸዋል ብዬ ነዉ።" አለችኝ። በልቤ ምናባቷ ሀይል መቀነሻ የሌለዉ ቧንቧ ነዉ እንዴ ያላቸዉ? እያልኩ እበሽቃለሁ። አበባዎቹን ዉሀ አጠጥታ ስትጨርስ ጥርሶቿን ያጠረዉን ሽቦ እያየሁ "ቆይ ይሄን ነገር ምን እያደረግሽ ስታስቸግሪ ነዉ ዙሪያዉን ያጠሩት?" አልኳት። ሳቀችና "እንዳሰብከዉ እንኳ አይደለም ጥርሴን ለማስተካከል ነዉ።" አለችኝ። "ኦኬ ገጣጣ ነበርሽ ማለት ነዉ?" አልኳት። አምሪያ የምጠቀማቸዉ ቃላት እና ድፍረቴ የሌለ እያሳቃት "እንደዛ ነገር ፣ የሆንክ አመዳም!" አለችኝ። ጀሪካኑን ወደቤታቸዉ አስገብቼላት ልሄድ ስል አምሪ እየሳቀች "ጥጋበኛ ነገር ነህ!" አለችኝ። እየሳቅኩ "የምግብ ቤት ባለቤት ልጅ ስለሆንኩ ይሆናል!" አልኳት። እናቴ ከአምሪያ ቤተሰቦች ጋር የሌለ ተመቻችታለች። የአምሪያ እናት ሲጀመርም ሙድ አላቸዉ። ከእማዬ ጋር ተጠፋፍተዉ የተገናኙ እህትማማቾች ነዉ የሚመስሉት። ባይሆን ያልመሰጠኝ ሙዳቸዉ መስጂድ ለምን አትሄድም እያሉ የሚያዝጉኝ ነገር ነዉ። . እሁድ ዕለት አንድ የፌቨን ጓደኛ ደዉላ ልታገኘኝ እንደምትፈልግ ነገረችኝና አገኘኋት። አንድ ካፌ ገብተን እንደተቀመጥን ራሷን ማስተዋወቅ ጀመረች። "ፍቅር እባላለሁ የፌቪ የልብ ጓደኛዋ ነኝ። ሜይቢ ትምህርት ቤት ልትወስዳት ስትመጣ አይተኸኝ ሊሆን ይችላል።" አለችኝ። በርግጥ ልጅቷን ብዙ ጊዜ ፌቪን ከትምህርት ቤቷ ልወስዳት ስሄድ አይቻታለሁ። ግን አልተቀራረብንም። ቀጠለችና "ዛሬ የፈለግኩህ ያዉ አርብ እለት ከፌቪ ጋር ያወራችሁትን ፌቪ አጫዉታኝ ነበር እና የምትወዳት ከሆነ ልጅቷ ቨርጅን ስለሆነች ባለፈዉ የጠየቅካትን ነገር አሪፍ ቦታ ላይ ብታደርጉት ብዬ ላማክርህ ነዉ!" አለችኝ። ያለችዉ ስላልገባኝ "አሪፍ ስትይ?" አልኳት። "አሪፍ ስልህ ያዉ ለሴት ልጅ የማይረሳት ትዝታዋ ድንግልናዋን ያጣችበት ቅፅበት ነዉ። እና አሪፍ ሆቴል ኦር ሪዞርት ዉስጥ ብታደርጉት አሪፍ ትዝታ ይሆናታል። እሷ ልትነግርህ ሼም ስለያዛት ነዉ እኔ የነገርኩህ። እንደማገኝህ አታዉቅም!" አለችኝ። እየሳቅኩኝ "ስለዚህ በድርጊቱ ላይ ተስማምታለች አደራረጉ ላይ ነዋ ድርድሩ?" አልኳት። የዛ ቀን ኦፊሳችን ዉስጥ ማድረጉ ደብሯት ነዉ ማለት ነዉ። ይቀጥላል @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid
Показати все...
​​🙇🙇🙇ስህተቴ🙇🙇🙇 🌺🌺ክፍል ስድስት (6)🌺🌺 🌼አቅራቢ ቅን ልቦች🌼 እሷም እየሳቀች "አሁን በደንብ ገብቶሀል!" አለችኝ። ልጅቷን አተኩሬ አየኋት! ሙሉ ለሙሉ ጥቁር ናት። የሆነ ናይጄሪያዊ ነዉ የምትመስለዉ። ግን ደስ የሚል ነገር አላት። የፌቪ ጓደኛ ባትሆን አሰምጣት ነበር። እዉነት ለመናገር እኔ ከፌቪ ጋር ለመተኛት ብዬ ሆቴል በሉት ወላ ሪዞርት መሄድ አልፈልግም ነበር። የተስማማሁት ጓደኛዋ ስለገንዘቡ አትጨነቅ እሷ ጋር አለ ስላለችኝ ነዉ። . ማታ ማታ አምስት ሰዓት ድረስ ፌቪንናየአረብ ሀገሮቹን ሴቶች በአንድነት እያዋራሁ አመሻለሁ። እናቴ እንዳትሰማኝ በፅሁፍ ብቻ ነዉ የማስተናግዳቸዉ። ሰሞኑን ከሪሜ የሚያወራት ልጅ ደሞዜን ባንክ አስቀምጥልኝ ብላ ስለላከችለት ብር በብር ሆነናል። ወር ሙሉ የለፉበትን እንዲህ ለኛ ሲያስረክቡ በጣም ነዉ የሚገርሙኝ! እንዴት ለማንም አንስተዉ የለፉበትን ይልካሉ? የሚያስቅ የዋህነት! ማታዉን እየተጀናጀንኩ እማዬ ስታቃስት ሰማሁ። እየሮጥኩ ወደሷ ክፍል ሄድኩኝ። "ምነዉ እማ?" አልኳት። ጉበቷን አንዳንዴ ያማት ነበር። አሁንም እሱ እንደሆነ በእጇ ጠቆመችኝ። ሀኪም ቤት እንዳንሄድ በጣም መሽቷል። እማዬን ሳያት ግን በጣም ያመማት ስለመሰለኝ የአምሪያን አባት መኪና ለማስቸገር አሰብኩ። ወዲያዉ ግን እማዬ እንደመሻል አላት። እስክትተኛ ድረስ አጠገቧ ተቀምጬ ጠበቅ ኳት። እንቅልፍ ሲወስዳት ወደ ምተኛበት ክፍል ሄጄ መጀናጀኔን ቀጠልኩ። . ጠዋቱን እማዬ እንደተለመደዉ ጉድ ጉድ ስትል ሰማሁ። ማታ የታመመች ሴትዮ አሁን ጤነኛ ሆናለች። ይገርማል! እንጀራዉን ይሀ የፈረደበት የላስቲክ ምግብ ቤት አድርሼላት ከሚኪ ጋር ወደ ትምህርት ለመሄድ ተገናኘን። ሚኪ ፈገግ ብሎ "ዛሬ ኦፊሱ የኔናየሄለን ግዛት ነዉ ድርሽ እንዳትሉ!" አለኝ። ከኔ ቀድሞ ማስማማቱ ገረመኝ። ያዉ ሄለንን ዛሬ ሊተኛት መሆኑ ነዉ። ስለኔዋ ስነግረዉ "በሷ ወጪ ከሆነ ለምን ሆቴል አይደለም ቤተ መንግስት አትልህም ምን ቸገረህ?!" አለኝ። . ጠዋቱን ከከሪም እና አብነት ጋር ሆነን ባወጣነዉ እቅድ መሰረት ክላስ ቀጥተን ሚኪናሄለን እስኪመጡ የተከራየናትን ኦፊስ አፀዳድተን ጠበቅናቸዉ። አምስት ሰዓት አካባቢ ሚኪ ሄለንን የሆነ ቦታ ደህና ምግብ ጋብዟት ይመስለኛል መጡ። ሄለን የኛ ትምህርት ቤት ልጅ ስለሆነች ሁላችንም በደንብ እናዉቃታለን። አጠር ያለች ጠይም ልጅ ናት። እንደመጡ ሰላም ብለናቸዉ ቤቱን ለቀን ወጣን። ስወጣ እየሳቅኩ ሚኪን በጆሮዉ "በል እንግዲህ ያላየኸዉን አዲስ ሀገር እየዉ!" አልኩት። እየሳቀ ገፍትሮ አስወጥቶኝ በሩን ዘጋዉ። እኛ እንዳማረብን ወደ ፑል ቤት ሄደን ስንጫወት ቆየን። . በግምት ከነሚኪ ጋር ከተለያየን ከአራት ሰዓታት በኋላ ይመስለኛል ሚኪ ደወለልኝ። እየሳቅኩኝ "ወዬ ክቡርነትዎ!" አልኩት። "የት ናችሁ? ተከሰቱ!" አለኝ። ከአብነት እና ከሪሜ ጋር ሆነን ወደ ኦፊስ ሄድን። ስንገባ ሄለን የሚኪያስን ሹራብ ለብሳ ተቀምጣለች። እሱ በቦዲ ነዉ። ቤቱ የሆነ የሞት ሽረት ትግል እንደነበረበት ያስታዉቃል። ከሪሜ ከቤት ያመጣት አንሶላ በደንብ ተንገላታለች። ትንሽ ተቀምጠን ካወራን በኋላ የኔዋ ጉድ ፌቨን ከትምህርት የምትለቀቅበት ሰዓት ስለደረሰ ለመሄድ ተነሳሁ። ሚኪም ሄለንን ሊሸኛት ልብሷን ቀያይራ አብረን ወጣን። ሄለንን ሸኝቶ ፑል ቤት እንደሚጠብቀኝ ነግሮኝ ተለያየን። የሚገርመዉ ግን ሄለን ድንግል አልነበረችም። ከሚኪ በፊት ከሌላ ወንድ ጋር ፍቅቅሮሽ ዉስጥ ገብታ ነበር። . ፌቪን እንዳገኘኋት በጣም ከማፈሯ የተነሳ ቀና ብላ እንኳ አላየችኝም። ሲመስለኝ ጓደኛዋ እንዳናገረችኝ ነግራታለች። እየተሽኮረመመች "እኔ አልነበርኩም የላኳት! ራሷ ነች።" አለችኝ። ፈገግ ብዬ "እቅድሽን ንገሪኝ!" አልኳት። በጓደኛዋ ልደት አሳበን ሶደሬ ለመዝናናት እንድንሄድ ቤተሰቧን አስፈቅዳ ቅዳሜ ሄደን እሁድ ማታ እንድንመለስ ነዉ ያቀደችዉ። ለገንዘቡ አታስብ ጓደኞቼም አብረዉን ስለሚመጡ ችግር የለዉም ስላለች እቅዷን ሙሉ ለሙሉ ተቀበልኩት። እኔ ከሴት ጋር ለመተኛት ብዙ ብር አወጣ ብለዉ እነሚኪ እንዳይፎግሩኝ ብዬ ነዉ እንጂ ከአረብ ሀገር ሚስኪን ታላቢዎቻችን የተላከ ገንዘብ ነበረኝ። 🌼 ይ ቀ ጥ ላ ል 🌼 ለአስተያየት @bakiny @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid
Показати все...
​​🙇🙇🙇ስህተቴ🙇🙇🙇 🌺🌺ክፍል አራት (4)🌺🌺 ቀረበ በ 🌼ቅን ልቦች🌼 ❣❣❣❣❣❣❣❣❣❣❣ ኧረ የለኝም ነገሩን ነዉ እንጂ!" አልኳት። አምሪያ በግርምት እያየችኝ "ግን በጣም ደፋር ነህ!" አለች። ቀጠለችና "ማለቴ በህይወትህ ለሁለተኛ ቀን ያገኘኸዉን ሰዉ ስለፍቅረኛዉ መጠየቅ አይከብድም?" አለችኝ። እየሳቅኩ "ባክሽ የፍቅር ጥያቄ መጠየቅ ራሱ አይከብድም!" አልኳት። አምሪ ራሷን መቆጣጠር እስኪከብዳት ድረስ ሳቀች። አባቷ ከቤት ሲወጡ እኛ አበባ እየተከልን ነዉ። አዩንና ፈገግ ብለዉ "ጎበዞች! ዛሬ መልካም ነገር ከዘራችሁ ፣ ነገ የምታጭዱትም መልካም ነገርን ነዉ። መጥፎ ከሆነም በተመሳሳዩ!" አሉና በሩ ላይ ቆሞ የነበረዉ መኪናቸዉ ዉስጥ ገቡ። እሳቸዉ እንደሄዱ ጨርሰን ስለነበር ከአምሪያ ጋር ቦታዉን አፀዳድተን ተሰነባበትን። ስንለያይ አምሪያ የቤታቸዉን በር ከዉስጥ ሆና ይዛ "ስማ ሀቢቤ!" አለችኝ። እየዞርኩ "ወዬ" አልኳት። "ትንሽ መሬት ያዝ! ተረጋጋ እሺ!" ብላኝ እየሳቀች በሩን ዘጋችዉ። . ቅዳሜን ከእናቴ ጋር ስንደፋደፍ አሳለፍኩት። ምግብ ስሰራ በጣም ጎበዝ ነኝ። ሴት አስንቃለሁ። እሁድን ከሚኪ ጋር አሳለፍን። አምሪያን ቅዳሜም ሆነ እሁድ አላየኋትም። ሰኞ በጣም ብዙ የምስራቾችን የምንሰማበት ቀ ን እንደሚሆን ተስፋ አድርጌያለሁ። ገና እንደተገናኘን ሚኪ ለሻይ ቤቷ አስተናጋጅ ስምረት ጮርናቄ እና ሻያችንን ካዘዘልን በኋላ "ኧረ ይሄን ሁለት ቀን ጉድ ነዉ ያየሁት!" አለ። አብነት እንደ እብድ ዝም ብሎ ብቻዉን ይስቃል። "ምን አየሽ ሚኪ?" አልኩት ወደሱ እየዞርኩ። በፌስቡክ አረብ ሀገር ያሉ ሴቶችን ተዋዉቆ ሁለቱ ስልኩን ጠይቀዉት በዋትሳፕ ደዉለዉ እንዳወሩት ነገረን። ሚኪያስ "ኧረ ሙቀቱ ይሁን እኔንጃ ብቻ የሌለ ነዉ ፍልት ያለባቸዉ። የአዳም ዘር ከሆንክ የሚምሩህ አይመስለኝም። አንዷ የሌለ ነዉ በአንዴ ጠብ ያለችልኝ። በስሜት ሁሉ አቃሰተች።" አለ። እኔም መስመር ስለያዙልኝ ሶስት ሴቶች ነገርኳቸዉ። ከሪሜ አልቀናዉም። አብነት ግን አሁንም ብቻዉን እንደእብድ እየሳቀ ነዉ። ሚኪ እያፈጠጠበት "ምናባህ ያንተከትክሀል?" አለዉ። አብነት ስልኩን ከፈተና ራቁቷን ያለች ሴት ምስል አሳየን። ሁላችንም ተቀባብለን አየነዉ። "እናላችሁ በአንድ ሳምንት ዉስጥ ብር እልክልሀለሁ ብላለች!" አለን። በሶስት ቀን ራቁት ፎቶ ማስላክ የሚደንቅ ነዉ። . ከአስራአምስት ቀን በኋላ ለሶስታችን አረብ ሀገር ከሚኖሩ ሴቶች ገንዘብ ተላከልን። የመጀመሪያዉ እቅዳችን አንድ የምንደበርበት ቤት መከራየት ነበር። ከሰፈር ራቅ ብለን ተከራየን። ኦፊስ እንለዋለን። ቤቱን ተከራይተን አንዳንድ ወሳኝ ነገሮችን እንዳሟላን ሚኪ ፌቨንናሄለንን እዚህ አምጥተን አብረናቸዉ እንድንተኛ ሀሳብ አቀረበ። የሰሞኑ እቅዶቹ ደስ የሚሉ ናቸዉ። ሄለንና ፌቨንን ለማሳመን ተነጋግረን ተለያየን። ከሪሜ ምንም የአረብ ሀገር ሀበሻዎችን ባያሰምጥም አንዷን እየጀነጀናት 'በቪዲዮ ኮል' ሲያወሩ የዋህ የሚመስል ፊቱን አይታ ደሞዟን ባንክ እንዲያስገባላት በየወሩ ልትልክለት ተስማሙ። የገልፍ ሀገራትን የተቆጣጠርን ያህል ደስ አለን። አሁን ወሳኙ ነገር ፌቨንን አብረን እንድንተኛ ማሳመኑ ነዉ። ይቀጥላል @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid
Показати все...
​​🙇🙇🙇ስህተቴ🙇🙇🙇 ክፍል ሁለት (2) አቅራቢ ኢትዮፒካ Tube 👼👼👼👼👼👼👼👼👼👼👼 ከካፌዉ እንደወጣን ቦርሳዋን ይዤላት እያወራንና በየመሀሉ እየዘፈነችልኝ ወደ ቤቷ ሸኘኋት። ከሷ ጋር ስጨርስ ሚኪ ጋር ደወልኩለት። ፑል ቤት እየተጫወተ እየጠበቀኝ ነበር። ተገናኝተን ወደ እማዬ ምግብ ቤት ሄድን። እማዬ ምግብ ካቀረበችልን በኋላ "ከኛ ቤት ጎን የተሰራዉ ትልቁ ቤት እኮ ተሸጠ። ዛሬ ሰዎቹ ገቡበት።" አለችን። እኔና ሚኪ ትምህርት በመሄዳችን እቃ አዉርደን የምናገኘዉን ብር ስላጣን ተበሳጨን። ለነገሩ ጎረቤት መቦጨቅ ደሞ አይነፋም። እማዬ ለሌላ ተስተናጋጅ ምግብ እያቀረበች "ደሞ ጥሩ ሰዎች ይመስላሉ። ሰዉየዉ ቁልፉን እንድሰጣቸዉ ደዉለዉ ሄጄ አይቻቸዉ ነበር።" አለች። እማዬ ቤቱ እስኪሸጥ ደላላ ሲመጣ እንድታሳይ አደራ ተብላ ቁልፉ እሷ ጋር ነበር። . ማታዉን እናቴ ቡና አፍልታ አዲሶቹ ጎረቤቶቻችን ጋር ሄድን። እኔ እንኳ ጀበናዉን እና ሽንብራዉን አድርሼላት ለመዉጣትና ከፌቪ ጋር ፌስቡክ ላይ ለመጀናጀን አስቤ ነበር። ሰዎቹ ጋር ስናንኳኳ አንድ ጠይም የሆነች፣ ረዥም ቀሚስ የለበሰች፣ ሂጃብ የጠመጠመችና ጥርሷ በብሬስ የታሰረ ወዛም ልጅ በሩን ከፈተችልን። እቃ አድርሶ የመመለሱን ሀሳብ ሰረዝኩት። ይህቺን የመሰለች ልጅ ያለችበት ቤት መቀመጡ ራሱ ደስ ይላል። እኔ ሴት ላይ ችግር አለብኝ። ያየሁት ሁሉ ያምረኛል። ለነገሩ ይህቺ እንኳ ትገባኛለች። የሰፈሬን ሴትማ ማንንም አላስበላም። እማዬ ሴቶቹ ጋር ገባች። እኔን ልጅቷ ወደ ሳሎን ወሰደችኝ። ሳሎን ስገባ ምግብ ቀርቦ ነበር። አንድ ሸምገል ያሉ ሰዉዬ ስገምት አባቷ ይመስሉኛል "አምሪያ እጅ መታጠቢያዉን አሳይዉ ይቀላቀለን!" አሉ። አሀ ስሟ አምሪያ ነዉ ማለት ነዉ አልኩ በልቤ። ምናለ ስልኳንም በዛዉ ቢጠሩት። ፈገግ ብላ መታጠቢያ ቤት ወሰደችኝ። እየታጠብኩ "ስንተኛ ክፍል ነሽ?" አልኳት። ድፍረቴ ሳይገርማት አይቀርም። "ከወር በኋላ ኢንትራንስ እፈተናለሁ። አስራሁለተኛ ክፍል ነኝ።" አለችኝ በትህትና። ስለራሴ ትንሽ ነገርኳትና የአባቷን ስም ጠየቅኳት። "ራህመቶ" አለችኝ ፈገግ ብላ። ልጅቷ ፈገግታ ታበዛለች። እኔ የአባቷን ስም የጠየቅኳት አባቷን መተዋወቅ ፈልጌ ሳ ይሆን ፌስቡክ ላይ ልፈልጋት ስላሰብኩ ነዉ። ታጥቤ እየተመለስኩ ቆም አልኩና "ወንድም ምናምን የለሽም?" አልኳት። "ሶስት አሉኝ። ሳሎን ያሉት ሁለቱ ወንድሞቼ ናቸዉ። አንደኛዉ ልጁ ታማ ሄዷል። ሶስቱም አግብተዉ ወጥተዋል።" አለችኝ። የቤቱ ታናሽ መሆኗ ነዉ እንግዲህ! ለዛሬ ከበቂ በላይ መረጃ እንደሰበሰብኩ አሰብኩ። ነገ ለነሚኪ ይተረካል። ሳሎን ገብቼ በልተን ከጨረስን በኋላ አባቷ የጥያቄ መዓት አወረዱብኝ። ብዙዉ የሀይማኖት ትምህርት ለምን እንዳልተማርኩ ምናምን ነዉ። ሲጠይቁኝ ስወዛገብ አለመማሬ ገባቸዉ መሰለኝ። ሰዉየዉ ሀይማኖተኛ ነገር ናቸዉ። ፌቪ አስሬ ትደዉላለች። ስልኬን ዘጋሁት። ደሞ በመጀመሪያ ቀን ልጠቆር እንዴ? . ሰዉየዉ አንድ በአንድ ሳሎን የነበሩትን ልጆች ካስተዋወቁኝ በኋላ አምሪያን ጠርተዉ ሰፈሩን እንዳላምዳት አደራ አሉኝ። ተመስገን! እንኳን አደራ ተብዬ ወትሮዉንም እንዲሁ ነኝ። አንገቴን ስደፋ ምንም የማላዉቅ መስያቸዋለሁ። . ከነአምሪያ ቤት እንደወጣሁ ፌቨን ጋር ደወልኩ። ፌቪ በጣም ተጨንቃ ነበር። ሁሌም ከሶስት ሰዓት በኋላ ስለምናወራ ስልክ አላነሳ ስላት ደንግጣለች። ድንጋጤዋ ሲበርድላት "አንድ አንድ እንዝፈን!" አለችኝ። ፌቪ ስዘፍን ድምፄን ትወደዋለች። አንድ አንድ ተዘፋፍነን ስልኩን ዘጋሁት። ቤት ከገባሁ በኋላ አምሪያን ፌስቡክ ላይ አሰስኳት። መጨረሻ ላይ አንድ ፎቶ የሌለዉ አካዉንት የሷ ይሆናል ብዬ ገመትኩና ሪኳየስት ላኩኝ። ወዲያዉ ተቀበለችኝ። ትንሽ እንዳወራኋት እሷ አለመሆኗን አወቅኩ። ተበሳጨሁ። . ልተኛ ስል ሚኪ ደወለ "ኧ ሚኪ" አልኩ ስልኩን አንስቼ "ሀቢቤ ያበደ እቅድ አለ ቸከሶቹን በተመለከተ! አሁን አያቴ ሰዉ ሲመክር ሰምቼ ነዉ። ጠዋት በሰፊዉ እተነትንልሀለሁ።" አለኝ። ሚኪ የሌለ ጓጉቷል። እኔም እስኪ ይንጋና ለነሚኪ ስለ አምሪያ ልተርተርላቸዉ። @kidukid @kidukid 💌 share 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺 ይቀጥላል ክፍል 3 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid
Показати все...
​​🙇🙇🙇ስህተቴ🙇🙇🙇 🌼🌼ክፍል ሶስት (3)🌼🌼 ❣ተዘጋጀ በ ቅን ልቦች❣ . ከሚኪያስ ባህሪዎች በጣሙን የሚገርመኝ ሙድ የሚፈበርከዉ ሲከለከሉ ከሰማቸዉ ነገሮች ዉስጥ መሆኑ ነዉ። ገና እንደተገናኘን "እስከአሁን በቺኮች ጉዳይ ላይ የሌለ ተበልተናል! ጥቅም የሌለዉ ስራ ነበር የሰራነዉ!" አለኝ። ደሞ ማናባቱ ፍቅረኛ መያዝ መጥፎ ነዉ ብሎት ይሆን? በግርምት እያየሁት "እና ሄለንን ልትተዋት ነዉ?" አልኩት። ሄለን የሚኪ ፍቅረኛ ነች። "ለምንድነዉ የምተዋት?" አለኝ። ግራ እየተጋባሁ "እና ምንድነዉ የምታወራዉ?" አልኩት። ሚኪ ተረጋግቶ ማስረዳት ጀመረ። "ይኸዉልህ ሀቢቤ እኛ እዚህ የትምሮ ቤት ሴቶችን ስናሯሩጥ በጣም ብዙ ገንዘብ አምልጦናል። ማታ እኮ ነዉ የገባኝ። የጎረቤታችን የጋሽ አክሊሉ ልጅ አረብ ሀገር ልትሄድ አያቴ ሲመክሯት ሰማሁ። ምን አሉ መሰለህ 'እዛ አረብ ሀገር ያሉ ሴቶችን እዚህ ቁጭ ብለዉ እያባበሉ የሚበሉ አመዳም ልጆች አሉ። እና ብርሽን ለማታዉቂዉ ሰዉ በወደድኩት ሰበብ አትላኪ!' አሏት። አያቴ አሁን ጎረቤት ከሚመክርበት ምናለ እኔን ነግሮኝ እያባበልኩ በበላሁ!? ለማንኛዉም ከዚህ በኋላ ሄለን እና ፌቪ ላይ እየተደበርን እነዛን ደሞ በፌስቡክ አሳደን ብናሰምጥና መላ ብናገኝስ?" አለኝ። ምንም የማይወጣለት ቆንጆ ሀሳብ ነበር ያመጣዉ። ፈገግ ብዬ "ይኼማ አብነት እና ከሪሜን እራሱ ያሳትፋል። እንደዉም የቺክ ፎቢያቸዉን ይገፍላቸዋል።" አልኩት። ትምሮ ቤት እንደሄድን ከአብነትናከሪሜ ጋር ጮርናቄ የምንበላበት ሻይ ቤት ተገናኘን። ጮርናቄ በሻያችንን አዘን በደንብ ሚኪ ያመጣዉን ሀሳብ አስረዳናቸዉ። የመጀመሪያዉ ስራ አረብ ሀገር ያሉ ሴቶችን ለይቶ ፌስቡክ ላይ ጓደኛ ማድረግ ነዉ። በሀሳቡ ላይ ከተስማማን በኋላ በመሀል ሚኪ ወደኔ እየዞረ "አዲሶቹ ጎረቤቶቻችሁ ሙድ አላቸዉ?" አለኝ። ሚኪ ሌላ ሀሳብ አምጥቶ አስረሳኝ እንጂ እኮ ስለ አምሪያ መተርተር የመጀመሪያዉ እቅዴ ነበር። ወዲያዉ ማታ ስለነበረዉ ነገር እና ስለ አምሪያ በዝርዝር ነገርኳቸዉ። አብነት ኮስተር ብሎ "ይህቺን ልጅ ፎንቃ ካስጨመደድካት የዛኔ አንተን የፍቅር መምህር እንልሀለን!" አለኝ። እኔ የሚገርመኝ አብነት አንድ ቺክ እንኳ ሳይጠብስ እኔ አራተኛዬን ይዤ እልህ ሊያስይዘኝ መሞከሩ። ከሪሜን እያየሁ "ፌቪ ስትሰለቸኝ ወደ እሷ እዞራለሁ።" አልኩ። ከሪም ዝም ብሎ ያየናል። ሚኪ ሀሳባችንን እየተቃወመ "ጎረቤት መጀንጀን እንኳ አይነፋም!" አለ። "እሱን ለኔ ተውት!" አልኳቸዉና ስልካችን ላይ ተተክለን አረብ ሀገር የሚኖሩ የሀገራችን ሴቶችን ማሰስ ጀመርን። . ከአራታችን በእድሜ የሚያንሰዉ ከሪሜ ነዉ። አስራሰባት አመቴ ነዉ ይላል። እዉነቱን ፈጣሪ ነዉ የሚያዉቀዉ! እኛ አስራ ዘጠኝ ላይ ነን። የክፍላችን የእድሜ ባለፀጋዎች እኛ ነን። እኔ በአባቴ ሞት ምክንያት ለሁለት አመት ትምህርት አቋርጬ ነበር። ሚኪ ከመሸ ነዉ ትምህርት የጀመረዉ። አብነት ከክፍለሀገር ሲመጣ ተከልሶ ነዉ ወደ ኋላ የቀረዉ። . በቻልነዉ መጠን ለብዙ ሴቶች ፍሬንድሪኳየስት ላክን። እዛዉ ተጥደዉ ነዉ መሰለኝ የሚዉሉት ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ወዲያዉ ተቀበሉን። እኔ የኔዎቹን በስማቸዉ ቅደም ተከተል እየሄድኩ መፃፃፍ ጀመርኩ። አንዳንዶቹ አይመልሱም ብዙዎቹ ግን መለሱልኝ። ተመቸኝ ፣ በደንብ መፃፃፍ ጀመርኩኝ። ክፍል ገብተን አስተማሪዉ እያስተማረ እኛ ከኋላ ቁጭ ብለን በፌስቡክ እንጀናጀናለን። . ዘጠኝ ሰዓት ላይ ከትምሮ እንደወጣን እኔ ፌቨንን እንደተለመደዉ ላገኛት ወደ ትምህርትቤቷ ሄድኩኝ። ደግሞ አርብ ነዉ። ቅዳሜ እሷ ትምህርት ቢኖራትም እኔ የለኝም። እሷን ብዬ እንዳልሄድ ደግሞ እናቴን ሳግዝ ነዉ የምዉለዉ። እሁድ እሷ ከቤት ስለማትወጣ አንገናኝም። ስለዚህ አርባችንን ያማረ አርብ ለማድረግ ብዙጊዜ እስከአስራሁለት ሰዓት እናመሻለን። ማምሻዉን ስንመለስ በሰፈራችን ዉስጥ ለዉስጥ እየተሽሎኮለክን ፣ጭር ያለ ቦታ ስናገኝ ደግሞ እየተሳሳምን እናብዳለን። ፌቪ ለቤተሰቦቿ ከጓደኞቼ ጋር ነበርኩ ትላለች። እኔ እንኳ ሲጀመርም ሀይለኛ ቁጥጥር የለብኝም። ከጠየቀችኝም ያዉ ከነሚኪ ጋር ነበርኩ እላለሁ። ዛሬ ፌቪን ገና ሳገኛት ተንሰቅስቃ ማልቀስ ጀመረች። ቦርሳዋን እያወለቅኩላት "ኧረ ፌቪ እኔ የማስለቅስሽ ነዉ የሚመስለዉ አረጋጊዉ እንጂ!" አልኳት። ፌቪ አሁንም ለቅሶዋን አላቆመችም። አቅፌ እያባበልኳት እዛዉ ትምህርት ቤቱ አቅራቢያ ወዳለ ካፌ ሄድን። እንደተቀመጥን እንባዋን እየጠረግኩላት "በቃ ፌቪዬ አታልቅሺ! ምን ተፈጥሮ ነዉ?" አልኳት። ሳግ እየተናነቃት "ቲቸር እያሱ ዩኒፎርም ለብሰሽ ከወንድ ጋር ስትዞሪ ታይተሻል። ለወላጆችሽ እናገራለሁ አለኝ።" አለች። ቲቸር እያሱ የነፌቪ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ነዉ። በእጆቼ ፀጉሯን እያስተካከልኩላት "ግን ቤት አልደወለም አይደል?" አልኳት። "አዎ እግሩ ላይ ወድቄ ስለምነዉ ሁለተኛ እንዳላገኝሽ ብሎ ማረኝ። ግን ከአስራአንደኛ ክፍል ተማሪ አይጠበቅም ምናምን ብሎ ቀወጠዉ።" አለችኝ። "በቃ አትጨነቂ ከዚህ በኋላ ሌላ ልብስ በቦርሳ ይዘሽ መጥተሽ ስትወጪ ትቀይሪዋለሽ!" አልኳት። ፌቪ ፊቷ በፈገግታ እየተሞላ "አሪፍ ሀሳብ ነዉ።" አለች። በፍጥነቴ ተገርማለች። እሷን ያሰጋት ዳግመኛ የመያዙ ነገር ነበር። አሁን ቀለል አለላት። ቀለል ሲልላት መዝፈን ጀመረች። ፌቪ ስትዘፍን በጣም ደስ ይለኛል። . ማታ ከእማዬ ጋር ምግብ ቤቱን ዘግተን ስንመለስ አምሪያ በራቸዉ ላይ ያለዉ የአበባ መትከያ ላይ ችግኝ ለመትከል ቦታዉን ስታመቻች ደረስን። እማዬ የያዝኳቸዉን ሰፌዶች እየተቀበለችኝ "ሂድ አግዛት በወንድ ያምራል!" አለችኝ። ትዕዛዟን ተቀብዬ አምሪያን ለማገዝ ወደነአምሪያ ቤት አጥር ሄድኩ። እናቴ ወደ ቤት ገባች። መሬቱን እያለሰለስኩ አምሪያን ቀና ብዬ አየኋትና "ሰዉ በሚገባበት ሰዓት የምትንደፋደፊዉ ጎበዝ ናት እንድትባይ ነዋ?" አልኳት። አምሪ ሳቋን ለቀቀችዉ። ትስቅና ጥርሶቿን የከለለዉን ሽቦ በከንፈሮቿ ትሸፍነዋለች። ስቃ ስትጨርስ "ነገረኛ ነገር ነህ!" አለችኝ። የሆነ አነጋገሯ ለዛ ነገር አለዉ። "ምን ያስደስትሻል?" አልኳት። "መንፈሳዊ ህይወት!" አለችኝ። የሆነች የአባቷ ቢጤ ናት። ለማስመጥ ማገዶ እንደምትፈጅ አሰብኩ። "እና ፍቅረኛ የለሽማ!" አልኳት። ፊቷን እየጨመደደችዉ "የለኝም ምነዉ አንተ አለህ እንዴ?" አለችኝ። 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺 ይቀጥላል ... 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺 @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid
Показати все...
Yetemchachu ena kefel 2 yeketel yemtelu
Показати все...
👍 4
@like #d51a2a6b1ba590c59
Показати все...
​​ስህተቴ ክፍል አንድ (1) 🙇🙇🙇🙇🙇🙇🙇🙇🙇🙇 የጠዋቷ ፀሀይ በየት በኩልም እንደወጣች እንጃ! ተፈጥሮን የማድነቅ ልምድ የለኝም። ብቻ ዋናዉ ነገር መዉጣቷ ነዉ። እኔም ሰዉነቴ ላይ የተለጠፈ የሚመስለዉን ስኪኒ ዩኒፎርሜን ለብሼ ፣ፀጉሬን ፈርዤና አንድ ደብተር አንጠልጥዬ ወደ ትምህርት ቤት እሄዳለሁ። እንደሌላዉ ተማሪ ቦርሳ ሙሉ ደብተርና መፅሀፍ ተሸክሞ መሄድ በጣም ነዉ የሚሸክከኝ። ቦርሳ የያዙ ልጆችን ሳይ ፋራ ነዉ የሚመስሉኝ። እነሱ ቦርሳ እየተሸከሙ እኔ በወጉ እንኳ ሳልፅፍ ይኸዉ ኩረጃ ዕድሜዉ ይርዘምና አስራአንደኛ ክፍል ደርሻለሁ። ጓደኞቼ አብነት ፣ ሚኪያስ እና ከሪም ይባላሉ። የትምህርት ቤታችን ጭሶች እኛ ነን። እኔ ፍቅረኛ ሳይኖረኝ አንድ ለሊት ካለፈ በጣም ነዉ የሚደብረኝ። ከአንዷ ጋር ስደባበር ሌላኛዋን ወዲያዉ ጠብ አደርጋታለሁ። ሚኪያስም የኔ ቢጤ ነዉ። ከሪም እና አብነት ግን የኛን ወሬ ከመስማት እና በአለባበስ ከመመሳሰል በዘለለ ብዙም ቺክ ማዉረድ አይቀናቸዉም። "ያለሙያችን አንገባም!" ይላሉ። እኛም የቺኮቻችንን ጓደኞች ልናስበላቸዉ እንሞክራለን። ግን እስካሁን አልቀናቸዉም። . ጠዋት አስራሁለት ሰዓት እንደደረሰ የማዉቀዉ እናቴ ቤት ዉስጥ መንጎዳጎድ ስትጀምር ነዉ። "ሀቢቤ ተነስ መቼስ ገና እስክትኳኳል መከራ ነዉ!" አለች። እኔ አልጋ ላይ ተጋድሜ በፌስቡክ ከፌቨን ጋር እጀናጀናለሁ። ፌቪ አዲሷ ፍቅረኛዬ ናት። ሁሌም ጠዋት ጠዋት እናቴ ለሊት የጋገረችዉን እንጀራ ከቤታችን ትንሽ ራቅ ብሎ ያለዉ የላስቲክ ምግብ ቤቷ ሳላደርስላት ወደ ትምህርት ቤት አልሄድም። አባቴ ከሞተ በኋላ በቻለችዉ ሁሉ እኔን ለማኖር ትለፋለች። ቤታችን ቢሸጥ ብዙ ብር የሚያወጣ ቢሆንም እማዬ "የከማሌን ማስታወሻ አልሸጥም!" ብላ ግግም አለች። ከማል የአባቴ ስም ነዉ። ያለኋት ልጅ እኔዉ ብቻ ስለሆንኩ በቻለችዉ መጠን ከማንም እንዳላንስባት ትጥራለች። የምይዘዉ ስልክ ፣ ልብሶቼ እና ኪሴ ዉስጥ የሚገኘዉ ብር የላስቲክ ምግብ ቤት ያላት እናት ያለችኝ አይመስልም። ለኔ ያላትን ከመስጠት ወደ ኋላ ብላ አታዉቅም። እናቴ ሁሌም "ሱስ የሚባል ላይ ትወድቅና አይኔን አታያትም!" ብላ ስለምታስፈራራኝ ሱስን በሩቁ ነዉ የምሸሸዉ። ጓደኞቼም እኔን ስለሚከተሉ ሱስ ሰፈር የሉበትም። ምድር ላይ ሁሉ ነገሬ እናቴ ናት። በጣም እወዳታለሁ። አዛኝ እምቢ ማለት ይከብደኛል። እየተነጫነጭኩም ቢሆን ያለችኝን እፈፅማለሁ። . ከአልጋ ላይ ተነስቼ ከተጣጠብኩና ፀጉሬን ከፈረዝኩ በኋላ ደብተሬን እናቴ ይዛልኝ፣ እንጀራዉን ፍሪዜ እንዳይበላሽ በእጆቼ አየር ላይ ተሸክሜ ወደ ምግብ ቤት አድርሼ ፤በዛዉ ሚኪያስን ጠርቼዉ ወደ ትምህርት ቤት ሄድኩ። አብነት እና ከሪሜ እኛ ሰፈር ስላልሆኑ ትምህርት ቤት ነዉ የምንገናኘዉ። ከክፍላችን ተማሪዎች በእድሜ ትንሽ ከፍ የምንለዉ እኛ ነን። ሰልፍ እስኪያልቅ ድረስ ዉጪ ላይ ያለዉ ሻይ ቤት ጮርናቄ በሻይ እየበላን እናረፍዳለን። ሰልፍ ሲያልቅ እንገባለን። ሚኪ ከቺኩ ጋር ሲዛዛግ ይቆይና ካሰናበታት በኋላ አብረን እናሳልፋለን። ከትምሮ ስንለቀቅ የኔዋ ፌቨን ከኛ ትምህርት ቤት አቅራቢያ ያለ የግል ትምህርት ቤት ስለምትማር አብሬያት እስከ አስራአንድ ሰዓት ቆይቼ ሸኝቼያት ወደ ቤት እመለሳለሁ። እኛ የምንማረዉ የመንግስት ትምህርት ቤት ነዉ። . ፌቨን እዉነት ካወራን ቆንጆ አትባልም። ግን የሆነ የደስ ደስ አላት። ቅብጥብጥ ትላለች። ከሷ ጋር ፍቅረኛ ከሆንን ወር አልፎናል። ጓደኞቼ ፌቨንን ጠብ ሳደርጋት የሌለ ነዉ የኮሩብኝ። ምዕራባዊያንን ያንበረከክኩ ያህል! እሷ ትንሽ የሀብታም ልጅ ነገር ስለሆነች ጓደኞቼን ሳይቀር ትጋብዛቸዋለች። እዉነቱን ለመናገር ግን ከሶስት ወር በላይ ከአንድ ሴት ጋር መቆየት አይሆንልኝም። ከዚህ በፊት ሶስት ሴቶች ፍቅረኛዎቼ ሆነዉ ነበር። ሰላማዊት ፣ ሜሮን እና ሰሚራ ይባላሉ። ከሰላም እና ከሰሚራ ጋር ተኝቻለሁ። ከተዉኳቸዉ በኋላ ሁለቱም በጣም ተጎድተዋል። ሜሮን ስትገግምብኝ ነዉ የጫርኳት። ከዛ በኋላ ምን ትሁን ምን አላዉቅም። ብቻ ግን ከፍቅር ግንኙነቶች መቋረጥ በኋላ በጣም የሚጎዱት ሴቶቹ ናቸዉ። ሁለ ነገራቸዉ ብልሽትሽት ነዉ የሚለዉ። . ከፌቨን ጋር ዛሬ ከተገናኘን በኋላ አንድ ሰፈራችን ዉስጥ ደፍሬ ገብቼ ወደማላዉቅበት ካፌ ወሰደችኝ። ካፌዉ ግርማ ሞገስ አለዉ። ገብተን አንዱ ጥግ እንደተቀመጥን ፌቪ አይን አይኔን እያየች "የእዉነት ትወደኛለህ?" አለችኝ። ወዲያዉ ፈገግ ብዬ "አንቺን አለመዉደድ እንዴት ይቻላል?" አልኳት። ምላሴ እኮ ጤፍ ይቆላል። "ግን እኮ እኛ ትምህርት ቤት ስላንተ ደስ የማይል ነገር ይወራል።" አለችኝ። "ምን?" አልኳት ትኩር ብዬ እያየኋት ፍርሀት አይኖቿን እኔን ከመመልከት እየሰበራቸዉ "ሴት አሯሯጭ ነዉ ፣ ብዙ ሴት ያተራምሳል! ምናምን" አለችኝ። እንደመቆጣት እያልኩኝ "እሱ ትናንት ነዉ። ዛሬ አንቺ መጥተሽ ህይወቴን ሙሉ ለዉጠሽዋል። ተስተካክያለሁ። አታምኚኝም እንዴ?" አልኳት። ፈጥና እጆቼን በእጆቿ ጭምቅ እያደረገች "ኧረ አምንሀለሁ። ተዋቸዉ በቃ!" አለችኝ። የፌቪ ፍቅር ሁሉ ነገሯ ዉስጥ ይታያል። ጀንጅኜ ያሰመጥኳት እኔዉ ነኝ ግን እሷ ፎንቃዬ የሌለ ገብቶላታል። ፌቪ ስትዘፍን ድምጿ በጣም ያምራል። ብዙ ጊዜ ደዉላ ትዘፍንልኛለች። የልቧን የምትነግረኝ በዘፈን ነዉ። ዛሬም ዘፈነችልኝ። ድምጿ ዉስጥ የሆነ ለቅሶ አለ። እንዳታጣኝ ሰግታለች። 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺 💓💓💓ይቀጥላል💓💓💓 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺 @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid
Показати все...
🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰 💔ስለፍቅር የተከፈተ ቻናል 💔ፍቅር ምንድን ነው 💔ሰው እንዴት ልንወድ እንችላለን? 💔የወደድነውን ሰው እንዴት መርሳት እንችላለን? 💔ለነዚህ ጥያቄዎች መልስ ከፈለጉ ይቀላቀሉ Join join join join join join 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid @kidukid
Показати все...
😍😍👏👏 ❤️በውስጤ የታመቁ መግለፅ ያልቻልኳቸው ቃላቶች፤ የደበቅኳቸው ስሜቶች፣ ያላነበብሻቸው መስመሮች ሞልተዋል።።። ፅህፈት....semir @kidukid
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.