የግጥም ረመጥ✍️
የግጥም ረመጥ አንዴ join ካሉ ሱስ የሚያስይዙ ግጥሞች የሚያገኙበት ስለፍቅር ስለሀገር ስለቤተሰብ ስለሁሉም ጉዳዮች የተገጠሙ ግጥሞችን የሚያገኙበት ምርጥ ቻናል ከግጥም ቻናሉ ያልተስሞሟት ነገር ካለ እንዲስተካከል አስተያየት ይስጡን እናስተካክላለን። ለአስተያየቶች @SUNMAN111 👈👈 ይህን ይጠቀሙ። @Abelaaaaam @Abelaaaaam @Abelaaaaam
Більше531
Підписники
-124 години
-47 днів
-1130 днів
- Підписники
- Перегляди допису
- ER - коефіцієнт залучення
Триває завантаження даних...
Приріст підписників
Триває завантаження даних...
በ 40 ዓመቷ በጨጓራ ካንሰር
ከመሞቷ በፊት በዓለም ታዋቂዋ
ዲዛነር እና ደራሲ " ክሪስዳ
ሮድሪጌዝ " እንዲ ስትል ፅፋለች ።
1⃣ ጋራዥ ዉስጥ የአለማችን ዉድ
መኪና ነበረኝ ፣ አሁን ግን በዊልቸር
መቀሳቀስ አለብኝ ።
2⃣ ቤቴ ሁሉንም አይነት ብራንድ
ያላቸዉ ልብሶች ፣ ጫማዎች እና
ዉድ እቃዎች ይሸጣል ፣ አሁን ግን
ሰዉነቴ በሆስፒታሉ በተዘጋጀ ትንሽ
ጨርቅ ተጠቅልሏል ።
3⃣ በባንክ ዉስጥ ብዙ ገንዘብ
አለኝ ። አሉን ግን ከዚህ መጠን
ምንም አልጠቀመኝም ።
4⃣ ቤቴ እንደ ቤተ መንግስት ነበር
አሁን ግን በሆስፒታል ዉስጥ
በሁለት አልጋዎች ተኝቻለዉ ።
5⃣ ከባለ አምስት ኮከብ ሆቴል ወደ
ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል . አሁን ግን
በሆስፒታል ዉስጥ ከአንድ ላብራቶሪ
ወደ ሌላ በመቀስቀስ ጊዜዬን
አሳልፋለዉ
6⃣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን
ፊርማ ሰጥቻለሁ ነገር ግን በዚህ ጊዜ
የሕክምና መዝገቦች የእኔ ፊርማ
ናቸዉ ።
7⃣ ፀጉሬን ለመስራት ሰባት ፀጉር
አስተካካዮች ነበሩኝ ፣ አሁን ግን
በራሴ ላይ አንድ ፀጉር የለኝም ።
8⃣ በግል ጄት ላይ ፣ የትኛዉም ቦታ
መብረር እችላለሁ ፣ አሁን ግን ወደ
ሆስፒታል በር ለመራመድ ሁለት
እርዳታዋች ያስፈልጉኛል ።
9⃣ ምንም እንኳን ብዙ ምግቦች
ቢኖሩም አሁን የእኔ አመጋገብ በቀን
ሁለት ኪኒን እና ምሽት ላይ ጥቂት
የጨዉ ዉሃ ጠብታዎች ናቸዉ ።
1⃣0⃣ ይህ ቤት ፣ ይህ መኪና ፣ ይህ
አዉሮፕላን ፣ ይህ የቤት ዕቃ ፣ ይህ
ባንክ ፣ ብዙ ዝናና ዝና ፣ አንዳቸዉም
አይመጥኑኝም ነበር ። አሁን ግን
ከእነዚህ ዉስጥ አንዳቸዉም
ሊደርሱልኝ እና ሊጠቅሙኝ
አልቻሉም ።
" የሰዉ ሕይወት በገንዘቡ
ብዛት አይደለም ና ተጠንቀቁ ÷
ከመጐምጀትም ሁሉ
ተጠበቁ ..... ። "
ሉቃስ 12 ÷ 15
❤ 3
ጓደኛ ማለት ዛሬም ሆነ ነገ
የማይለወጥ የደስታም ሆነ
የሐዘን ተካፋይ መሆን የሚችል
ክፋት የማይፈፅም ለተንኮል
የማይሰለፍ ችግር ሲያጋጥም
የማይሸሽ እና አብሮ የሚጋፈጥ
ማለት ነዉ ።
❤ 1
የአንድ ወቶ አደር ሲቃ
እናት ሀገር እናትዬ ፣
ላንቺ መድማት ፡ ላንቺ ብቆስል ይሁን
ብዬ ፣
ካሳደገኝ ከእናቴ እቅፍ ፡ ከአባት ኩራት
ተነጥዬ ፣
ከአያቶቼ የጀብድ ታሪክ ፡
........ ከዚያች ሸጋ ፡ የአፍላ ፍቅሬን
አንጠልጥዬ ፣
ወጣሁልሽ ፡ ስለ ሀገሬ አሜን ብዬ
................. ስለ እምዬ ።
በዱር ባድር ፡ ከ እቶን ስር በበርሃ ፣
ድካም በዝቶ ስንገላታ ፡ እጎነጨዉ አጥቼ
ዉሃ ።
አፈር ምድሩን ፡ ባሩድ ሽታ እያወደ ፣
በዉሽንፍር በጥይቱ ፡ አካላቴ እየራደ ።
ደግሞም ጥሎ ዶፍ መአቱ ፡ የበረዶዉ
ቅዝቃዜ ፣
ከጭቃዉ ጋር ሲመሳሰል ፡ የልጅነት
መልኬ ወዜ ፣
ተጫጭኖኝ ፡ ዐቢይ ድካም ወ ትካዜ ።
ከምሽግ ስር እንደ ወደኩ ፡ ቢያልፉ ቀናት ፣
ሰላም ለኪ ብዬ ፡ አዛኝቱን ስማፀናት ፣
ልቤ ሲርድ ፡ ደም መርጨቱን እንዳቆመ
እያስመሰለ ፣
ያ ጎልያድ ከበፊቴ ፡ እየፎከረ እየሸለለ ።
ፍርሃት ወርሶኝ ፡ አካላቴ እያለቀ ፣
አዳኝ ጌታ እስኪ መስለኝ ፡ ከእኔ የራቀ ።
አበቃለት ሞተ ዛሬ ፡ ሲሉኝ ንቀዉ ፣
እዉነቴን ነዉ ፡ ይህን ሁሉ ታግሻለዉ ፣
በምወደዉ ፡ በሰንደቅሽ እምላለዉ ።
አምኖን ዛሬም ፡ ወንድምነቱን ዘንግቶ ፣
ክብርሽን ሊያጎድፍ ። ወስልቶ ፣
ድንግል አፈር መሬትሽን ፡ ቋምጦ ሽቶ ።
ክፋት ወርሶት ፡ ጎኔን ሲወጋኝ ፣
ሳምነዉ ክዶ ፡ ቃየል ጨካኝ ሲሆንብኝ ።
እስራትሽን ልፈታልሽ ፡ ያንን አዉሬ
ስፋለመዉ ፣
ለካስ ያለዉ ጠላት ፡ ከጎኔ ነዉ ፣
በአላማ እንደ ወንድም ፡ እመኜዉ ፣
ሙሉ ልቤን ክፍት አድርጌ ፡ ባስጎበኘዉ ።
ይሁዳ ነበር ፡ ባንዳነት ያለበት ፣
በደካማዉ ጎኔ ፡ ጥይት ሰደደበት ።
ላንቺ መድማት ፡ ላንቺ ብቆስል ይሁን ብዬ
፣
እናት አለም ፡ እናት ሀገር ፡ እናትዬ ።
ከአያቶቼ የጀብድ ታሪክ ፡
..... ከዚያች ሸጋ ፡ የአፍላ ፍቅሬን
ሳላጣጥም ፣
..... ስለ ክብርሽ ፡ ትግል ስገጥም ።
አለፍኩልሽ ፡ በእስትንፋሴ ፣
እስትንፋስሽን ፡ አስቀጥዬ ።
Yibeltal Belay Zeleke
❤ 2
የቴዲ አፍሮ ወርቃማ አባባሎች
ክፉን በመልካም ማሸነፍ
ታላቅነት ነዉ ።
በየትኛዉም ስፍራ ጥሩ
ሆነህ ተገኝ ። ጥሩ ነገርንም
አድርግ ። በህይወትህ
የጎደለዉን እግዚአብሔር
ይሞላልሃል ።
እግዚአብሔር የምንፈራዉ
በማዉራት ሳይሆን ከዉስጣችን
ባለ ቅንነት እና የዋህነት ነዉ ።
ብልህ ሰዉ ታናሹንም
ያዳምጣል ።
❤ 2
ሁሌም ሰላም ደና ሁኑ በሁሉም ነገሮቻችዉ ላይ እግዚአብሔር ይርዳችዉ ሰላማችዉ ይብዛ እግዚአብሔር ይጠብቃችዉ
❤ 1
እጅ እስካልሰጠህ ድረስ
አልተሸነፍክም
# የሰጠንን _ ብናዉቅ _ የጎደለን
# የለም ።
አትኩሮትህን በሌለህ ነገር
ላይ ሳይሆን ባለህ ነገር ላይ
አድርገዉ ። ደስተኛ ለመሆን
ሁሉም ነገር ሊኖርህ አይገባም ።
በደንብ ካስተዋልከዉ አሁን
ያለህ ነገር ደስተኛ ለመሆን
በቂ ነዉ ። ምክንያቱም አንተ
ያለህን የሚመኙ ምስኪኖች ብዙ
ናቸዉና ።
❤ 1
እናት ኮ አለም ናት ሁሉንም የቻለች
ስንቱን ተሸክማ የምትኖር ሳትሰለች
እናት ለምን ትሙት ትኑር ለዘላለም
እርሷ የሌለችበት መራራ ናት አለም
ስለያት ከጎኗ ካጠገቧ ስርቅ
ሳቋ ብቻ ሳይሆን ቁጣዋ ' ሚናፍቅ
ብበላ ብጠጣ አይደርስም ካንጀቴ
ከጎኔ ከሌለች ገራገሯ እናቴ
ፍቅሯ ወደር አልባ ቢነሳ ቢወደስ
ፈገግተዋ ብቻ ከህመም የሚፈዉስ
nahom
❤ 1
ደካማ መሆንን
አትፍራ
ጠንካራ በመሆንህ
አትኩራ
ማንም ምንም አለም
ያሻዉን ይበል
ዕራስህን ሁን
መንገድህን ተከተል
ዕድልህን ተጠቀምበት
እንጂ አትልቀቀዉ
ወደ ገርነት
መመለስን አትተዉ
❤ 3