6 971
Підписники
Немає даних24 години
-367 днів
-20230 днів
Архів дописів
6 971
እርካታና ሁካታ
ምንጭ የምድር አራዊት ጥማቸውን የሚያረኩበት የእርካታ ስፍራ የሆነውን ያህል ህልውናቸው አደጋ ላይ የሚወድቅበትም ሁከት የሞላበት አደገኛ ቦታ ነው። ምክንያቱም አውሬዎች ሊበሉ የሚቋምጧቸው እንስሶች በጥም ተቃጥለው እያለከለኩ ውሃ ፍለጋ እንደሚመጡ ስለሚያውቁ አድብተው የሚጠብቁበት ቦታ ነው።
የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በዚሁ ተንኮል ይጠቀማል። በምኞት በምንናውዝለትና በምንቋምጠው ጉዳይ ዙሪያ ሰይጣን እኛን እስከወዲያኛው ከእግዚአብሔር ለመለየት የተሳለ ካራ ይዞ ይቀመጣል። እግዚአብሔር ከሰጠው ከ10ቱ ትዕዛዛት አንዱ "አትመኝ" መሆኑም በምክንያት ነው።
ለምሳሌ ገንዘብ በርካታ ፍላጎቶቻችንንና ጉዳዮቻችንን ልንፈጽም የምንችልበት መልካም አገልጋይ ሆኖ ሳለ የገንዘብ ፍቅር ግን ሰይጣን በግልጽ የሚገለገልበት ክፉ መሳሪያ ነው።
"ገንዘብን መውደድ የክፋት ሁሉ ሥር ነውና፥ አንዳንዶች ይህን ሲመኙ፥ ከሃይማኖት/ከእምነት ተሳስተው በብዙ ሥቃይ ራሳቸውን ወጉ።" 1ኛጢሞቴዎስ 6:10 እንደሚል ሊኖረን በተመኘነው ነገር ተወግቶ ከሁለት የወጣ መሆን እጅግ አሳዛኝ ፍፃሜ ነው።
ታዲያ ጥሩ ነገር መመኘት ትክክል አይደለም ማለት ነው? መልሱ ቀላል ነው።
"ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።" ማቴዎስ 6:33
ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን!
Share @Bruh_Tesfa
6 971
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደምናነበው ቅዱሳንን በተለያየ ጊዜና መንገድ የሚፈትነው ፈታኙ የተባለው ጠላት ዲያብሎስ ነው:: ሰይጣን ጌታንም ፈትኖአል ግን አልተሳካለትም (ማቴ 4:3)::
ሰይጣንን በአይኑ ያየ የዳሰሰውም የለም :: መንፈስ ነውና የመፈተን ሥራውን የሚሠራው ሌሎች ኀጢአተኛ ክፉ ወይም ደካማ ሰዎችን በመጠቀም ነው:: ፈተናው ከትንሽ ኅሊናን ከሚያጎድፍ ንግግር ጀምሮ እምነትን እስከማስጣል የሚያደርስ አደጋን ሊያደርስ ይችላል::
እናም የዲያብሎስን ሽንገላ ለመቋቋም የእግዚአብሔርን የጦር እቃን ሁሉ እምነትን በወንጌል በጸሎት በእግዚአብሔር መንፈስና በቃሉ መታጠቅ አለብን (ኤፌ 6)::
እንግዲህ ሰዎች ትእግስታችንን ሲፈታተኑ: ውሸትን ሲናገሩብን: ትእቢት ሲመጣብን እምነት ሲጎድልብን አሳቡን አንስተውም ተብሎ ተፅፏልና እንቃወመው::ወደጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ ምህረት አግኝተን ኀይልን እንሞላለን:: ሰይጣን በጌታ በመስቀሉ የተሸነፈ ቢሆንም እስከመጨረሻው እስኪጣል ድረስ እኛንም ጎትቶ ሊጥለን ዘወትር እንደሚያደባ አንርሳ:: ጌታ ኢየሱስን አምነን የዳንን ይህ አሸንፋችኁዋል የሚለው ቃል አለን::
ተባረኩ
ይህን መዝሙር ልጋብዛችሁ
https://youtu.be/fAvj9ZXhPpY
6 971
የደሙ ሚስጥር
እግዚአብሔርን መታዘዝ በህይወት የመኖር ዋናው ህገደንብ ሲሆን አለመታዘዝ ደግሞ ኃጢአት ይባላል።
አዳም በገነት መኖሩን ወይም መባረሩን የሚወስነው ይህንን ኃጢአት በማድረጉ ወይንም ባለማድረጉ ላይ ነበር።
ከገነት የተባረረው የሰው ልጅ እንደወጣ በዛው እንዳይቀር ከወጣበት እንዲመለስ እግዚአብሔር ያዘጋጃቸው የመመለስ ኪዳን ደግሞ የኃጢያት ስርየት ይባላል። በዚህ የኪዳን ህግ መሠረት ደም ሳይፈስ ስርየት የለም ብሎ እግዚአብሔር ራሱ ደነግጓል።
ስለዚህም የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት ሌሎች ያመጡላቸውንና ነውር የሌለባቸውን እንስሳት ደም ይዘው ወደ መቅደሱ ውስጠኛ ቅድስተ ቅዱሳን ገብተው ደሙን በመርጨት ያስተሰርዩ ነበር።
ዛሬ ያ ስርዓት የለም፣ ነገር ግን ደም ሳይፈስ ስርየት የለም የሚለው ህግ ዛሬም የፀና ስለሆነ የአዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህን ሌሎች ያመጡለትን ሳይሆን ለኃጢአታችን ስርየት የራሱን ደም ይዞ ስለእኛ ሊታይ በእግዚአብሔር ፊት ገባ። ቁ. 24
ታዲያ ከእኛ ምን ይፈለጋል? ጥቂት ነገር ብቻ፡-
1. የፈሰሰው የክርስቶስ ደም ለኔ ኃጢያት ስርየት ነው ብሎ ማመን
2. በደሙ ስርየት ከተቀበልን በኋላ ወደን በኃጢአት እንደገና እንዳንመላለስ
ለሙሉ ሃሳብ ዕብራውያን ምዕ 9ን ያንብቡ።
ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን!
Share @Bruh_Tesfa
6 971
ፈተና
ዓይነታቸው ብዙ ነው። አንዳንዱ የሚገፋ ሌላው የሚጎትት፣ የሚጠልፍ፣ የሚገፍፍ፣ የሚያማልል የሚጎነትል፣ እሳት የሚተፋ፣ ሙቀት የሚያጠፋ፣ የሚያሴር፣ የሚያስር፣ የሚከስ፣ የሚተነኮስ፣ የሚሰርቅ፣ የሚንቅ፣ ምን ቅጡ፤ ልዩ ልዩ ነው።
የዚያኑ ያህል እኛም ለየፈተናው ዓይነት ልንሰጠው የሚገባው ምላሽ የተለያየ ካልሆነ ፈተናውን አናልፈውም። ዋናው ቁም ነገር መፈተናችን ሳይሆን ፈተናውን ማለፋችን ነውና።
ቤትን ለሚገፋ ደራሽ ጎርፍ መላው ጥሩ መሰረት እንጂ የዋና ችሎታ አይደለም። ማቴ 7:24
በሆነ ባልሆነው የቁጣ እሳት ሲዘንብ ትዕግስትን የመሰለ እሳት ማጥፊያ አይገኝም።
ሊያስተኛህ ዳር ዳርህን እየዞረ ልብስን ለሚጎትት መድሃኒቱ ትግል ወይንም ትዕግስት ሳይሆን መሸሽ ብቻ ነው (ዮሴፍ ይጠየቅ ዘፍ 39)።
የሚጠላኝን ብጠላው ጥላቻው ይጨምራል፣ ፍቅር ግን ጥላቻን ያጠፋል።
ስድብን በስድብ፣ ክፋትን በክፋት መመለስ ለቀጣዩ ዙር በርን መክፈት ነው፤ በጎነት ግን የክፋትን በር ይዘጋል።
እናም በዚህች ጽሁፍ ሁሉን መዘርዝር ባይቻልም ከፈተናዎች ጀርባ ያለውን ፈታኝ ማወቅ ግን የፈተናውን ግማሽ መልስ እንደማወቅ ነው፤ ፈተናውን ሙሉ በሙሉ ለማለፍ የኛም የግል ምላሽ ድርሻ አለውና።
የእግዚአብሔር ቃል ሁሉንም ፈተናዎች እንዴት ማሸነፍ እንደምንችል ቁልፉን ይሰጠናል ኤፌሶን 6: 10-18
በወንጌል፣ በእምነት፣ በጸሎትና በእግዚአብሔር ቃል።
አስታውስ! ዋናው መፈተንህ ሳይሆን ፈተናውን በብቃት ማለፍህ ነው።
ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን!
Share @Bruh_Tesfa
6 971
የት ትቀበራለህ ወይስ የት ታርፋለህ
ከሞት በኋላ ቀባሪዎች የሚጠይቁት የተለመደ ጥያቄ ነው። ኦርቶዶክስ፣ ሙስሊም፣ ወንጌላውያን፣ ካቶሊክ ወዘተ በየስማቸው በተዘጋጀ መቃብር በሃይማኖቱ ስርዓት ለመሸኘት ይሯሯጣሉ። ነገር ግን አሸኛኘት ምን ቢለያየም ዘላለም ግን አንድ ነው፤ የዘላለም ህይወት ወይንም ሞት።
ታዲያ ለሰዎች ከዘላለም ርዕሰ ጉዳይ በላይ ምን የከበደ ነገር ሊኖር ይችላል? የምድሩ ቆይታማ ከአንቀልባ እስከ ሽምግልና ዕድሜ እንዴት ባለ ፍጥነት እንደሚንደረደር ትላንት የአራስ መጠየቂያ ይዘን የሄድንበትን ህጻን ዛሬ አንቱ ተብሎ ሲጠራ ማየት በራሱ በቂ ማስረጃ ነው።
ስለዚህም የቀበር ሽኝትህ እንዴትም ያለ ቢሆን ዋናው ጥያቄ ነፍስህ የት ታርፋለች የሚለው ነው። ምክንያቱም ሰው ሁሉ 'የዘላለም አምላክ' ተብሎ በተጠራው አንድ አምላክ ፊት ይቆማል እንጂ ስንሞት እንደየእምነታችን የሚቀበሉን የተለያየ እምነት ያላቸው አምላኮች የሉም።
"ሰው አንድ ጊዜ ሊሞት ከዚያም በኋላ በፍርድ ፊት ሊቆም ተወስኖበታል።" ዕብራውያን 9:27
እናም የእርስዎ ተራ መቼ እንደሚሆን ባይታወቅም በዘመንዎ ፍጻሜ ማወቅ የሚፈልጉት ዋና ጉዳይ የትና እንዴት ባለ ስርዓት እንደሚቀበሩ ሳይሆን ነፍስዎ የትኛው ዘላለም እንደምታርፍ ነው።
"እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።" ዮሐንስ ወን 17:3
ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን!
Share @Bruh_Tesfa
6 971
ያለ አስተማሪ!
"መጽሐፍ ቅዱስ አነባለሁ ግን ብዙም አይገባኝም። ወይንም ደግሞ ማንበብ እጀምርና ስለማልረዳው ጨምሬ ለማንበብ ፍላጎት አጣለሁ" ብለው ያውቃሉ?
ይህ ከሆነ ልክ እንደርሶ ተመሳሳይ ስሜት ስለነበረውና በመጽሐፍ ቅዱስ ሐዋ. ሥራ 8:26 ላይ ታሪኩ ስለተዘገበልን አንድ ኢትዮጵያዊ ልንገርዎ።
ይህ ኢትዮጵያዊ የተማረ፣ በገንዘብ ሚኒስቴር ደረጃ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን ደግሞም ሃይማኖተኛ የነበረ ሰው እንደሆነ ተጽፎለታል (ሙሉ ታሪኩን ያንብቡ)። ኢየሩሳሌም ሊሰግድ ሄዶ ሲመለስ በሠረገላ ውስጥ ሆኖ ነብዩ ኢሳያስ ስለ ኢየሱስ የፃፈውን የትንቢት መጽሐፍ እያነበበ ወደ አገሩ እየተመለሰ ሳለ ፊሊጶስ የተባለ የጌታ ተከታይ ወደ ሰረገላው ቀርቦ የምታነበውን ታስተውላለህ ወይ ብሎ ሲጠይቀው "የሚያስረዳኝ ሳይኖር እንዴት" የሚል ቅንና እውነተኛ መልስ ሰጠ። ይገርማል! ያነባል ነገር ግን አይረዳውም።
ይህ የሆነበት ምክንያት የእግዚአብሔርን ቃል ለመረዳት የቃሉ ባለቤት የሆነው የእግዚአብሔር መንፈስ እርዳታ የግድ ስለሆነ ነው። በዮሐንስ ወንጌል 14:26 "...መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።" ተብለናልና ያለ አስተማሪው መንፈስ ቃሉን ብናነብ፣ ብንማርና ብንመራመር ከቶ አይገባንም ወይንም ህይወት አይሆንልንም።
ስለዚህም ያ ኢትዮጵያዊ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ወደ እርሱ የመጣውን ፊሊጶስን ወደ ሰረገላው ወጥቶ እንዲያስረዳው እንደጋበዘው ሁሉ እኛም ቃሉን ስናነብ እንዲያስተምረን መንፈስ ቅዱስን ወደ ህይወታችን እየጋበዝን ቢሆን እውነቱ ይበራልናል፣ ለእኛም አዲስና ልዩ መገለጥ ይሆንልናል።
መንፈስ ቅዱስን መጋበዝ እንዴት ይቻላል የሚል ጥያቄ ቢኖርዎ ይጻፉልን።
6 971
የእግዜር ቤት
ሰዎች ያለ መጠለያ መኖር አይሆንላቸውም። እናም የሚሰሩትን ቤት ቁመትና ስፋት በሰው ልጆች ልክና ሚዛን ሰፍረው እነርሱን የሚያክል ቤት ይሠራሉ። የዱር እንስሳትና አእዋፋትም እንዲሁ በእነርሱ ቁመት ልክ የሆነውን ቀልሰው ወይንም አፈላልገው በዚያ ይጠለላሉ።
ከዚህ በእጅጉ በተለየ በአንድ ወቅት ሰዎች ለሰማይና ለምድር ዳርቻ ፈጣሪ እግዚአብሔር ቤት እንስራ ብለው ሲያስቡ እግዚአብሔር ቀድሞ አንድ ጥያቄ ጠየቃቸው።
"ለኔ ምን ዓይነት ቤት ትሰራላችሁ?" አላቸው። ምክንያቱንም ሰው በሚገባው ቋንቋ ልኩን ሲያስረዳ፣ እኔ "ሰማይ ዙፋኔ ምድር ደግሞ የእግሬ መረገጫ ናት" አላቸው። ሐዋ 7:48 በእርግጥም ለዚህ ከምድር እስከ ሰማይ ለተዘረጋ እጅግ ታላቅ አምላክ፣ ሰው ምን ዓይነት ቤት ሊሰራለት ይችላል?
ሆኖም እግዚአብሔር ሰውን በመውደዱ በሰዎች መካከል ማደርን ደግሞ ፈልጓል። ስለዚህም እርሱ የሚፈልገውን ዓይነት የማያረጅ እና የማይፈርስ ህያው ቤት እንድንሰራለት የቤቱን ዓይነትና ፕላን በዝርዝር ነግሮናል። ከብዙ በጥቂቱ፡-
1. 1ኛ ዮሐንስ 4:15 "ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በሚታመን ሁሉ እግዚአብሔር በእርሱ ይኖራል እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል።"
2. ዮሐንስ ወንጌል 14:23
"ኢየሱስም መለሰ፡ አለውም፦ “የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል፡ ወደ እርሱም እንመጣለን፡ በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን።"
እግዚአብሔር እንዴት በሰው ውስጥ መኖር ይችላል? እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ሆኖ ይመራናል፣ ይመክረናል፣ ይገስጸናል፣ ያስተምረናል...
ስለዚህም ትልቁ እግዚአብሔር በውስጥህ ሊኖር ወዷልና እባክህ መኖሪያው ቤት ሁንለት።
ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን!
6 971
አይምጣብህ!
ከዓለም ህዝብ 72% ምዕመናንን የያዙት 3ቱም ዋና ዋና ሃይማኖቶች (ክርስትና፣ እስልምናና ሂንዱይዝም) ወደፊት ይመጣል ብለው የሚጠብቁት መሲህ አላቸው። የመሲሁ አመጣጥና ከመጣም በኋላ ያደርጋል በሚሉት ላይ ልዩነት ቢኖራቸውም 3ቱም ሊመጣ ያለው መሲህ ግን ኢየሱስ መሆኑ ላይ ይስማማሉ።
ኢየሱስ ዳግም በሚመጣበት ዓላማ ዙሪያ ሃይማኖቶቹ የሰፋ ልዩነት ስላላቸው የጠራውን እውነት ለማወቅ ኢየሱስ ራሱ ስለ ዳግም መምጣቱ ምን አለ የሚለውን ከራሱ መስማት የግድ ይሆናል።
በመጽ/ቅ ስለ ኢየሱስ ዳግም ምጽአት ከተፃፉት 67 ጥቅሶች ውስጥ ኢየሱስ ራሱ እኔ እያለ የተናገረው ይህ ጥቅስ ይገኝበታል:-
"በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ ይህ ባይሆንማ ኖሮ እነግራችሁ ነበር፤ የምሄደውም ስፍራ ላዘጋጅላችሁ ነው። ሄጄም ስፍራ ካዘጋጀሁላችሁ በኋላ፣ እኔ ባለሁበት እናንተም ከእኔ ጋር እንድትሆኑ ልወስዳችሁ ዳግመኛ እመጣለሁ።" ዮሐንስ 14:2-3
ዋናው ቁምነገር ጌታ የሚመጣላቸው እንዳሉ ሁሉ ሳይዘጋጁ እንደ ሌባ ድንገት የሚመጣባቸውም አሉና ኢየሱስ መጥቶ ከሚወስዳቸው እንጂ ከሚቀሩት አለመሆንዎን እርግጠኛ ይሁኑ።
ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን!
Share @Bruh_Tesfa
6 971
ማወቅ እንጂ ማየት ማመን አይደለም!
በበረሃ ላይ ውሃ የሚመስል ነጸብራቅ (mirage) ስናይ ውሃ ነው ብለን በደስታ የማንፈነጥዘው አሸዋ መሆኑን ስለምናውቅ ነው። ስለዚህም የዕውቀታችን ደረጃ የዕይታችንን ልክ ይወስናል ማለት ነው።
በዕለተ እሁድ በጠዋቱ ወደ መቃብር የሄዱት 3ቱ ሰዎች ስለ ኢየሱስ ሞትና ትንሳዔ በነበራቸው ዕውቀት ማነስ ምክንያት ያዩትን በተሳሳተ መንገድ ነበር የተረዱት።
መግደላዊት ማርያም የመቃብሩ ግጣም ድንጋይ ተንከባሎ ስታይ ሰዎች በሌሊት የጌታን አካል ከመቃብር አውጥተው ለመውሰዳቸው ማሰረጃ ሆኖ ታያት። አብሮአት የነበረው ዮሐንስ ወደ መቃብሩ ሳይገባ ዝቅ ብሎ ሲያይ ከፈን በማየቱ የማርያምን ሀሳብ በግማሽ ተቀበለ። በኋላም ጴጥሮስ ወደ መቃብሩ ገብቶ ከፈኑና የራሱ ጥምጣም ብቻ እንዳለ ሲነግረው እሱም ገብቶ አይቶ መሰረቁን አመነ።
የ3ቱም ዕይታ የተሳሳተበትን ምክንያት መጽ/ቅ ሲነግረን "ከሙታን ይነሣ ዘንድ እንዲገባው የሚለውን የመጽሐፉን ቃል ገና አላወቁም ነበር" ይላል። ቃሉን አለማወቃቸው አሳሳታቸው። ዮሐንስ ወንጌል ምዕ20
ስለዚህም አንተም ስለ ኢየሱስ የሰማኸውን አምነህ ለመቀበል መነሻ ያደረግከው በቃሉ ዕውቀት ላይ ሳይሆን አንተ ከቆምክበት ጠርዝ (ሃይማኖትህ፣ ከልጅነት እስከ ዕውቀት የሰማኸው ወዘተ) ብቻ ከሆነ ሙሉውን እውነት ማየት አትችልም።
እግዚአብሔርን ራሱን ለሰዎች ይገልጣል፣ ቃሉን በግልህ አጥና፣ ፈልገው ይገኝልሃል። "እናንተ ትሹኛላችሁ፥ በፍጹም ልባችሁም ከሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ" ኤርምያስ 13:29
ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን።
Share @Bruh_Tesfa
6 971
ስስ ብልት
ችግር የማይቋቋሙና በቀላሉ ሊጎዱ የሚችሉ የአካላችን ክፍሎች በውስጣችን በብዙ አጀብ ተከልለዋል። ለምሳሌ ልብ ከፊት እና ከኋላ በጎድን አጥንቶች ታጥራ፣ በደረትና ጀርባ ጡንቻዎች ተከልላ፣ ያም ሳያንሳት ከላስላሳው ሳምባ ስር ተሸጉጣ ወሳኝ ስራዋን ያለማቋረጥ ትሰራለች።
ግና ምን ተሰውራ ያለች ቢሆንም ጆሮ በሚሰማው በሚሆንና በማይሆነው ወሬ ደግሞ በቀላሉ የምትናወጥ ነች። በቀላሉ ትናወጣለች እንጂ በቀላሉ አትረጋጋም። ዛሬ ያስጨንቃታል፣ ስለ ነገ ትታወካለች፣ ምኞትና ህልሟ ሲሳካም አታርፍም፣ አስተማማኝና የፀና ተስፋ እስክታገኝ አይዞሽ ብትባልም አትሰማም።
"ልባችሁ አይታወክ" ኢየሱስ ነገአቸው ላስጨነቃቸው ደቀመዛሙርት የነገራቸው ቃል ነበር። ይህ ተራ አይዟችሁ ማጽናኛ ቃል ሳይሆን ልብን ከጭንቀት የሚታደቁ 2 መልህቅ እውነቶችን ቀጥሎ ነገራቸው።
1. በእግዚአብሔር እመኑ፣ በእኔም ደግሞ እመኑ።
2. በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ... ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁ። ዮሐንስ ወንጌል 4: 1-3
ልብን ለዘለቄታ የሚያረጋጋው ዓለም የምትሰጠው ገንዘብና ክብር አይደለም፤ ምክንያቱም ገንዘብና ክብር የራሳቸውን ሌሎች ጭንቀቶችን ይዘው ይመጣሉና።
ለነገ ዋስትና ከሌለ በእርግጥም ነገ ያስጨንቃል። ስለዚህ እርስዎ ዘላቂ የልብ ሰላምና እረፍት ይሻሉ?
ከሆነ የሚያስፈልግዎ:-
1ኛው እምነት፤ ማለትም እግዚአብሔር በላከው በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ ማመን። ሰው ከሰራው ጌታ ጋር ሳይታረቅ ሰላም ሊኖረው አይችልምና።
2ኛው ዕውቀት፤ በልጁ ያመኑ የዘላለም ህይወት እንዳላቸውና የተዘጋጀላቸው መኖሪያ እንዳለ ማወቅ። መንገድ ሲሄዱ ውለው ቀኑ ሲመሽ የትና ማን ቤት እንደሚያርፉ ማወቅ ሰላምን ይሰጣልና የህይወትዎ ቀን ሲመሽ የት ቤት እንደሚያርፉ ያውቃሉ?
ጥያቄ ወይንም አስተያየት ካለዎ ይላኩልን
6 971
እግዚአብሄር መታወቂያ አይጠይቅም።
በኪሳችን ያለው መታወቂያ ፎቶአችንን፣ አድራሻችንንና የትውልድ ቀን መረጃዎችን ይይዛል እንጂ በልባችን የተሰወረውን ማንነታችንን አይገልጽም።
እግዚአብሔር ደግሞ ሰውን የሚያውቀው ወደ ምድር ለላከልን ልጁ በሰጠነው ምላሽ ልክ ነው። በመጽ/ቅ ማርያም ተብለው የሚጠሩ ብዙ ሴቶች ቢኖሩም የአልአዛርን እህት ማርያምን ሲገልጻት "ጌታን ሽቶ የቀባችው፣ እግሩንም በጠጉሩዋ ያበሰችው ማርያም" በማለት ለኢየሱስ በሰጠችው የፍቅር ምላሽ ልክ ያውቃታል።
እንዲሁም በዘመኑ ከነበሩት ብዙ ይሁዳዎች ውስጥ "አሳልፎ የሰጠው አስቆሮቱ ይሁዳ" በማለት ይሁዳ ለኢየሱስ በሰጠው የክህደት ምላሽ ይታወቃል።
ወንድሜ/እህቴ እግዚአብሔር በምን ያውቅህ/ሽ ይሆን? በመስቀል ሞቶ እንዲያድነው የላኩለትን ልጄን መድሃኒት አድርጎ የተቀበለና እርሱንም በዘመኑ ሁሉ ያገለገለ ይላል ወይንስ የልጄን ደም የረገጠ?
ምክንያቱም "ልጅንም አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ የአባቴ ፈቃድ ይህ ነው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።” እንደሚል የእግዚአብሔር አብ ፈቃድ ልጁን አምነን በመቀበል ከዘላለሞት ሞት መዳናችን ነው። ዮሐንስ 6:40
Share @Bruh_Tesfa
6 971
ቻነሉን share እያደረጋችሁ ያላችሁትን እያመሰገንን እስከሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት share አድርጋችሁ subscribe ያደረጉትን ስም ዝርዝር በውስጥ መስመር ላኩልን። ማበረታቻ እንልካለን።
6 971
እነዚህን ጠቃሚ ሰባት ሀሳቦች ስለ እግዚአብሔር ቃል በጥያቄ መልክ አካፈልናችሁ። እናንተ ደግሞ ሌሎች እንዲያውቁ ሊንኩን ለምታውቋቸው በመላክ አካፍሉ። ቻነሉ ብዙ የሚነበብ ስላለው ሊንኩን ቢያንስ ለ10 ሰው ላጋራና ስማቸውን በsubscription ዝርዝር ማየት ከቻልን የማበረታቻ ሽልማት እንልካለን።
@Bruh_Tesfa
6 971
እግዚአብሔር ፍጥረትን በቃሉ "ይሁን" እያለ እንደፈጠረ ሁሉ ዛሬም በቃሉ በኛ ውስጥ የሌለውን ወደ መኖር የማምጣት ኃይል አለው። "ኢየሱስም “እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤ እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል።” ዮሐንስ 8:32
6 971
መጽ/ቅ ዛሬ በህይወት ሳለን ምርጫችንን እንድናስተካክል ይነግረናል እንጂ ከሞትን በኋላ ከፍርድ በቀር ውሳኔአችንን የመቀየር ዕድል እንደሌለን ያስተምረናል። "ለሰዎችም አንድ ጊዜ መሞት ከእርሱ በኋላም ፍርድ እንደ ተመደበባቸው፥..." ዕብራውያን 9:27
