cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

[]ሱና ብቻ ውበት []

ሱና ብቻ ውበት ከሽርክ & ቢድዐ ከመሳሰሉት የጥመት አንጃዎች የጠራ ምርጥ የሰለፍይ ቻናል።

Більше
Країна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
Рекламні дописи
156
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

=_=_=_=_=ገጠርና ተውሂድ=_=_=_=_= =_=_=_=_=_=_=_=\/=_=_=_=_=_=_= በሽርክ አዳራሹ በቢድዓው ሞልቶ ተርፎ እየፈሰሰ የሚያቀና ጠፍቶ ምርቱ ሆኖ ክስረት ሰው እየታረሰ የዳዕዋ ሰዎች ለከተማ ብቻ በሚሰሩበት ዓለም በአሁኑ ሰዓት ሽርክ መስፋፋቱ ከከተማ ገጠር የሚሳት አይደለም =_=_=_=_=_=_=_=\/=_=_=_=_=_=_= በአብላጫው ስናየው የዚሁ ቆሻሻ የተግባር ውዳቂ በዛ ላይ ሞልተዋል ሸይኾች ተብዬ የቢድዓ ንጉስ የሽርክ አለቅላቂ እነሱ ሲመክሩ የገጠሩን ህዝብ ያንን የዋህ ማህበረሰብ ለድን ማወቅ ሳይሆን ለቅሬ ነበረ ሰው ሚሰበሰብ ደግ ይሰብሰቡ እሱ እኛን አልጎዳን ምናለ ቢሰሩ ከሽርክ ከቢድዓ ሰዎችን ለማዳን ይሄ አይታሰብ በእነሱ ዘንዳ ለፋቲሀ ሲባል ትርጉሙ ማይታወቅ ወተቱ ይወጣል ተደብቆ የነበር ከማጀት ከጓዳ =_=_=_=_=_=_=_=\/=_=_=_=_=_=_= ይህን አይነት ኡማ ለሀይማኖቱ ሟች ለድኑ ጠበቃ መስራት የነበረ ከጨለማ ወጥቶ ወደ ብርሀን አለም ሰው እንድነቃ ገጠር ልወድም ነበር በቢድዓ አጀንዳ በሽርክ ገመድ ታንቃ እያለ ሲታረድ አሽርማ ፍየል ወይ ግንባረ ቦቃ የተለማ ዶሮ፣ የሁጁብ፣ የቀብር በሚል ተጨማልቃ ለፋፍም በግ ስቦ ለስላም አምባ ፍየል ለሚሌ ከብት አርዶ ይመለሳል ለፊው የሀገሬ አርሶ አደር ለሽርክ አርግዶ =_=_=_=_=_=_=_=\/=_=_=_=_=_=_= የቁረወጥማን ጎማ የቁስል ዛጎሉ ሰዎች ተሸውደው ወደ ቀብር ጉዞ፣ ወደ ሽርክ መንደሩ ሲያጋሩ ሄደው የሄደ ተካፍሎ ያልሄዱት ደግሞ የሽርክ ፍየል ሰደው ታርዶ እየበሉ አዋቂ ተብለው ሰውን በሽርክ ጎጆ በቢድዓ አንደበት ይሸነግላሉ =_=_=_=_=_=_=_=\/=_=_=_=_=_=_= ይቀጥላል ኢንሻእ አሏህ #አቡ_ዓብዲ_ረህማን_ሀሰን_ኢብኑ_ኢድሪስ https://t.me/hassen_and_his_poemes
Показати все...
🇪🇹ሐሰን እና ግጥሞቹ (Channel)🇸🇦

"وَلَا تَجْعَلُوا مَعَ اللَّهِ إِلَٰهًا آخَرَ ۖ إِنِّي لَكُم مِّنْهُ نَذِيرٌ مُّبِينٌ" "ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አታድርጉ፡፡ እኔ ለእናንተ ከእርሱ (የተላክሁ) ግልጽ አስፈራሪ ነኝና፡፡" #ለአስያየትዎ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 http://t.me/Hassen_And_His_PoemsBot

እራስን መመልከት ~~~~~~ እየውልህ ወንድሜ! ህሊና አልባ በድን ማሽን አትሁን። የምትገባው ከራስህ እንጂ ከኡስታዝህ ቀብር አይደለም። ሲራጥን የምትሻገረው በራስህ ስራ መጠን እንጂ ኡስታዝህ እጅህን ይዞ አያሻግርህም። ያለ አስተርጓሚ ራቁትህን ከጌታህ ፊት ለምርመራ ስትቆምም ኡስታዝህ ከጎንህ አይቆምልህም። ይህንን ሁሉ የምልህ ማንንም በጭፍን እንዳትከተል ነው። በአሁኑ ሰዓት በየሰፈሩ ያሉ ሸይኾችና ኡስታዞች አብይ መታወቂያ ጭፍንነትን ሥራዬ ብለው የሚግቱ፣ ተማሪዎቻቸውን በጭፍንነት የሚኮተኩቱ መሆናቸው ነው። የወደዱትን በጭፍን እንድትወድላቸው፣ የጠሉትን በጭፍን እንድትጠላላቸው እስከ ደም ጠብታ ይታገሉሃል። ቁርኣን፣ ሐዲሥ፣ የዑለማእ ንግግር ተንኮለኛ በሆነ መልኩ ከአውድ ውጭ እያገናኙ የሃሳብ ሽብር ይነዙብሃል። እዚህ ላይ "ለምሳሌ እነ እንትናን ብንወስድ… " ብዬ ባጣቅስ የእነ እንትና ጭፍራ ጦር ሰብቆ ይነሳል። ከነሱ ውጭ ያለው ደግሞ በአመዛኙ ይደግፋል። እውነት ለመናገር ግን ጣት መቀሰሩ ስለሚቀለን እንጂ ይሄ በሽታ ይብዛም ይነስም በየቤቱ ይገኛል። ችግራችን ግን አይናችን ውስጥ ያለውን ግንድ ጥለን ከሌሎች አይን ያለን ጉድፍ ነው የምንመለከተው። የሌሎችን ጥፋት ለማጋለጥ እንረባረባለን። እሺ የራሳችንንስ ማን ያርመው? ለማነው የምንተወው? ኧረ ልባችን ፈቃጅ ተመልካች አጣ!! ድባቡ የተበከለ ሆኖ መገሳሰፅ አልቻልንም። እኛም ለራሳችን ተገቢውን ትኩረት አልሰጠንም። ግን እስከመቼ? እና ወንድሜ ከማንም ጎጠኛ ቡድን ጋር ጭፍን ተሰላፊ አትሁን። ከዑለማእ ንግግር ውስጥ ከስሜቱ ጋር በሚገጥምለት መልኩ እየመረጠ የሚያቀርብ ሰው ስታይ በችኮላ እጅ አትስጥ። የትኛውም ቡድን ጋር የተሰለፈው ሁሉ ይህንን እያደረገ ነውና የሱ ከሌሎች በምን እንደሚለይ ረጋ ብለህ መርምር። የማይነቃነቅ ነባራዊ ሐቅ፣ የአህለ ሱና ዋና መታወቂያ አስመስሎ ያቀረበልህ ጉዳይ አብዛኞቹ ዑለማዎች ዘንድ ያለው አቋም እሱ ካወራህ ተቃራኒ ሆኖ ልታገኘው ትችላለህና ከስሜት ነፃ ሆነህ በሚገባ ፈትሽ። ደግሞ ቆም ብለህ ታዘባቸው። ብዙዎቹ ቡድናዊነት የሰበሰባቸው አካላት:— — "እነ እከሌ ጠርዘኞች ናቸው፣ ድንበር አላፊዎች ናቸው" እያለ ከፍ አድርጎ ያስተጋባል። የሚያስከነዱ ጠርዘኞችን ግን አቅፎ ያሽሞነሙናል። ምክንያቱም እነዚህኞቹ እሱ ሲስል የሚስሉ፣ ሲያነጥስ የሚያነጥሱ የገደል ማሚቶዎች ናቸውና። — "እነ እከሌ ጃሂሎች ናቸው" ይልሃል። በምንም መመዘኛ ከነሱ የማይሻሉ ሰዎችን ግን በትልልቅ መድረክ ላይ ያስተዋውቃል። ምክንያቱ አቋማቸው ከአቋሙ ስለገጠመለት ብቻ ነው። — "እነ እከሌ አቋም የሌላቸው ወላዋዮች ናቸው" ያለህ ስብስብ በየክስተቱ ባደባባይ የሚዋልሉ ሰዎችን ከጎናቸው አሰልፈው ታገኛቸዋለህ። ምክንያቱም መመዘኛው ርካሹ ቡድናዊ ሚዛን እንጂ ኢኽላስ አይደለምና። ወንድሜ ሆይ! አላህን አስበህ ስለምትሰራው ነገር የማንንም ጭብጨባ አትጠብቅ። የማንም ተቃውሞም አይጠፍህ። ይልቅ ውስጥህን አዳምጥ፣ ኢኽላስህን ፈትሽ። ያለ ኢኽላስ ጩኸትህ የቁራ ጩኸት ነው። ልፋትህም ከንቱ ድካም። በደዕዋህ ቀዳሚው ትኩረትህ ሰፊው ህዝብ ይሁን። አትዘንጋ! ዛሬም አብዛኛው ወገናችን ከተውሒድ ግንዛቤ የራቀ ነው። ሺርክ ላይ የሚማቅቀው ብዙ ነው። ከባባድ አጥፊ ወንጀሎች ላይ እስከ አፍንጫው የተነከረው ቀላል አይደለም። ቀዳሚው ጥረትህ የዚህን ወገንህን ሸክም ለመቀነስ ይሁን። ይህንን መሰረታዊ ጉዳይ ገሸሽ በማድረግ ውሃ ቀጠነ፣ ከሰል ጠቆረ ብሎ ለሚነታረክ ጀርባህን ስጠው። የጊዜ ጉዳይ እንጂ ሁሉም አረፋ ነው። በኢኽላስ እስከሰራህ ድረስ የማንም ጫጫታ ቅስምህን አይስበረው። ሰዎች እንቅፋት ሲያበዙ አንተ ፅናትህን ጨምር። ወደፊት እንጂ ወደ ኋላ አትበል። የሌሎችን ጩኸት ሳታጣራ የምታስተጋባ በቀቀን አትሁን። በጭፍን አትደግፍ። በጭፍን አትንቀፍ። እወቅ! እውር ጥላቻና እውር ውዴታ ነገ ከአላህ ፊት ያሳፍርሃል። ማንንም በእውር ድንብር አትከተል። ጭፍን ወገንተኝነት በቃላት ቢያሸበርቅም፣ በሱና፞ ስም ቢቀርብም የተወገዘ ነው። የአሳማ ስጋ በወርቅ ሰሀን ስለቀረበ አሳማነቱ አይቀየርም። አሳማ አሳማ ነው። የመዝሀብ ሰዎች ዘንድ የምናውቀው ጭፍን ወገንተኝነት ተቀባብቶ ተከሽኖ በሱና፞ ዑለማዎች ስም ሲቀርብ ማየት እየተለመደ መጥቷል። ይበልጥ የሚያሳፍረው ደግሞ አንዳንዶች በየሰፈሩ በየመንደሩ እየተቧደኑ ‘ወላእ’ እና ‘በራእ’ የሚቋጥሩባቸው አካላት መመደባቸው ነው። ደግሞም በልክ እንሁን። በሌሎች ሃገራት ወይም አካባቢዎች ያየነውን ወይም የሰማነውን ኺላፍ ሁሉ ሰበብ እየፈለጉ እየጎተቱ ማምጣት ግልብነት ነው። ወላጆችህ ወገኖችህ በሺርክ እየተጨማለቁ አንተ በሸይኽ እንትናና በሸይኽ እከሌ መካከል ስለተፈጠረው ኺላፍ ጧት ማታ እያቦካህ በአካባቢህ ያሉ ዱዓቶችን ለመፈረጅ አድፍጠህ ብትጠባበቅ የፊትና ጥማትህን እንጂ ንቃትህን አያሳይም። በአካባቢህ ይሄ ነው የሚባል የደዕዋ ተሳትፎ ሳይኖርህ እንዳቅማቸው እየደከሙ ያሉ አካላትን ትንሽዬ ጥረት አይኗን ለማጥፋት ጦር ብትሰብቅ ጥሬነትህን ብቻ ነው የሚያሳየው። ወንድሜ ከቻልክ አግዝ። ክፍተት ካየህ አርም። አቅሙ ከሌለህ ባላቸው አስመክር። በምትችለው ከጎናቸው ቁም። ለሰፈርህ ለአካባቢህ የደዕዋ እንቅስቃሴ አጋዥ እንጂ አፍራሽ አትሁን። ለደዕዋ እንቅፋት በመሆን ሌሎች እንዳይለወጡ መሰናክል አትፍጠር። ሰዎች የሚተላለፉበት መንገድ ላይ አስቸጋሪ ነገሮችን መጣል ፀያፍ ጥፋት ነው። ወደ ኣኺራ በሚወስደው የደዕዋ መንገድ ላይ እንቅፋት መጣል ግን እጅግ አደገኛ ወንጀል ነው። እንዲህ አይነቱን የወንጀል ሸክም የምትቋቋምበት ጫንቃው የለህምና ዛሬውኑ ሚናህን ለይ። ዛሬውኑ ለደዕዋ ያለህን አስተዋፅኦ ገምግም። ……………………………………………… Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር) የቴሌግራም ቻናል። ይቀላቀሉ። ሌሎችንም ይጋብዙ። https://t.me/IbnuMunewor
Показати все...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

ቻናሉን ይቀላቀሉ። ለሌሎችም ያሰራጩ።

عيد مبارك تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال
Показати все...
የ_“ተሶውፍ”_ምንነትና_በዲንና_በዒባዳ_መሰረቶች_ላያ_ሱፍያዎች_ያላቸው_አቋም.pdf1.54 MB
#=======ሰውነት ሲጠፋ======= =_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_= ለሰው ማሰብ ቀርቶ በአደባባይ ሲሞት ደሙ እየጎረፈ ይህንን ከማሰብ አልፎም ከመቃወም ማን ነበር ያረፈ እነዚያ ሲቀሩ ከድሀ ጀርባ ላይ ሲያርፍ ብትሩ ቆመው በማጨብጨብ እንደውም ተሳትፈው ደብዳቢም ነበሩ =_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_= ደሀ ስንቱን ይቻል የችግር ውርጅብኝ በላዩ ሲዘንብ ኑሮን ለማሸነፍ ቀን ከቀን ሲለፋ ስንቱ ወጥቶ ቀረ ድምፁን እያጠፋ ይሄ ሁሉ ሲደርስ በጎን የችግሩ በጎን ተወግቶ አርሶ አደሩ ነጋደው ሲቃጠል ቤትና ድንበሩ ተማሪው ተሳቆ መማርን ሲጠላ አትሌት፣ አርቲስት ሳይቀር ዜግነት ሲጠይቅ ወጥቶ ወደ ሌላ ማየት አልችል ብሎ ሰውን ሰው ሲበላ በጥይት ውርጅብኝ ሚስኪን እየሞተ ሲገበር ለሌላ ለሰማ ያሳምማል እንኳንስ ለአዬ ለሀሩ ኗሪ ሰው በዶዘር ሲዛቅ ጠፋና ቀባሪ ይሄንን የሰራ ከሰው ተፈጥሮ ከሰው ጋራ ኗሪ =_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_= እኔ የሚገርመኝ ሰው ለሰው ማሰቡ ቀረና መሞቱ መግደል ሲጀምር ማን ነበር መካሪው ለዚህ ፍላጎቱ ወድህ ወገኑ ነው የዘር ግንድ ያለበት ከመልክ እስቋንቋ አልፎም እስከ ቦታ ታድያ ምን አሰበ ደሀን ሲጨፈጭፍ አንቱን ሲመታ ማየትስ አስቻለው ከጎኑ ጋ ቆሞ መመልከት ለንዳፍታ ያሳዝናል በጣም ለሚመለከተው አእምሮ ላለው ሰው ማሰብን ለቻለ አውሬነትን ወርሰው ያስብላል ለሰማ ሰውነት የታለ =_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_= #አቡ_ዓብደረህማን_ሐሰን_ኢድሪስ Http://t.me/hassen_and_his_poemes
Показати все...
🇪🇹ሐሰን እና ግጥሞቹ (Channel)🇸🇦

"وَلَا تَجْعَلُوا مَعَ اللَّهِ إِلَٰهًا آخَرَ ۖ إِنِّي لَكُم مِّنْهُ نَذِيرٌ مُّبِينٌ" "ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አታድርጉ፡፡ እኔ ለእናንተ ከእርሱ (የተላክሁ) ግልጽ አስፈራሪ ነኝና፡፡" #ለአስያየትዎ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 http://t.me/Hassen_And_His_PoemsBot

ሰውነት ሲጠፋ =_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_= ለሰው ማሰብ ቀርቶ በአደባባይ ሲሞት ደሙ እየጎረፈ ይህንን ከማሰብ አልፎም ከመቃወም ማን ነበር ያረፈ እነዚያ ሲቀሩ ከድሀ ጀርባ ላይ ሲያርፍ ብትሩ ቆመው በማጨብጨብ እንደውም ተሳትፈው ደብዳቢም ነበሩ =_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_= ደሀ ስንቱን ይቻል የችግር ውርጅብኝ በላዩ ሲዘንብ ኑሮን ለማሸነፍ ቀን ከቀን ሲለፋ ስንቱ ወጥቶ ቀረ ድምፁን እያጠፋ ይሄ ሁሉ ሲደርስ በጎን የችግሩ በጎን ተወግቶ አርሶ አደሩ ነጋደው ሲቃጠል ቤትና ድንበሩ ተማሪው ተሳቆ መማርን ሲጠላ አትሌት፣ አርቲስት ሳይቀር ዜግነት ሲጠይቅ ወጥቶ ወደ ሌላ ማየት አልችል ብሎ ሰውን ሰው ሲበላ በጥይት ውርጅብኝ ሚስኪን እየሞተ ሲገበር ለሌላ ለሰማ ያሳምማል እንኳንስ ለአዬ ለሀሩ ኗሪ ሰው በዶዘር ሲዛቅ ጠፋና ቀባሪ ይሄንን የሰራ ከሰው ተፈጥሮ ከሰው ጋራ ኗሪ =_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_= እኔ የሚገርመኝ ሰው ለሰው ማሰቡ ቀረና መሞቱ መግደል ሲጀምር ማን ነበር መካሪው ለዚህ ፍላጎቱ ወድህ ወገኑ ነው የዘር ግንድ ያለበት ከመልክ እስቋንቋ አልፎም እስከ ቦታ ታድያ ምን አሰበ ደሀን ሲጨፈጭፍ አንቱን ሲመታ ማየትስ አስቻለው ከጎኑ ጋ ቆሞ መመልከት ለንዳፍታ ያሳዝናል በጣም ለሚመለከተው አእምሮ ላለው ሰው ማሰብን ለቻለ አውሬነትን ወርሰው ያስብላል ለሰማ ሰውነት የታለ =_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_=_= #አቡ_ዓብደረህማን_ሐሰን_ኢድሪስ Http://t.me/hassen_and_his_poemes
Показати все...
🇪🇹ሐሰን እና ግጥሞቹ (Channel)🇸🇦

"وَلَا تَجْعَلُوا مَعَ اللَّهِ إِلَٰهًا آخَرَ ۖ إِنِّي لَكُم مِّنْهُ نَذِيرٌ مُّبِينٌ" "ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አታድርጉ፡፡ እኔ ለእናንተ ከእርሱ (የተላክሁ) ግልጽ አስፈራሪ ነኝና፡፡" #ለአስያየትዎ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 http://t.me/Hassen_And_His_PoemsBot

ሚስትህን ልክ ወጯን (ቀለቧን) ለመሸፈን እንደምትጓጓው ሁሉ ለማስተማርም ጓጓ!! اِحـــرِص علىٰ تعليـــم زوجتــك كما تَحرِصُ علىٰ إطعامها قال عمرُو ابن قيس - رحمه الله تعالى - : ➴ አምር ኢብኑ ቀይስ((رحمه الله)) እንዲህ ይላል ◉«إنَّ المـرأة لَتُخاصِـم زوجها يوم القيامة عِندَ الله فتقول : إنّهُ كانَ لا يُؤدِّبُـني ولا يُعلِّمُني شيئًا كانَ يأْتِيني بِخُبزِ السُّوق» ~አሏህ ዘንድ የውመልቂያማ ባሏን እንዲህ በማለት የምትከራከር ሴት አለች‼️ ➛◉እርሱ (ባሏ)የተገዛ ዳቦ(ኹብዝ) ይዞልኝ ከመምጣት ውጭ ምንም አደብ አያስይዘኝም፣አያስተምረኝም ነበር ትላለች‼️ 📖 [تفسير السمعاني (٤٧٥/٥)]
Показати все...
📌ሁሉም ነፍስ ሞትን ቀማሽ ናት‼ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ እነዚህ የቁርአን አንቀፃች ስንቴ ቀርተን እናልፋቸዋል። በተገቢው መልኩ ያስተነተናቸው ሰው በቂ ተግሳፅ አላቸው። 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ◾️وَلَقَدْ خَلَقْنَا الْإِنسَانَ وَنَعْلَمُ مَا تُوَسْوِسُ بِهِ نَفْسُهُ ↪️ ሰውንም ነፍሱ የምትወሰውሰውን የምናውቅ ስንኾን በእርግጥ ፈጠርነው። ◾️وَنَحْنُ أَقْرَبُ إِلَيْهِ مِنْ حَبْلِ الْوَرِيدِ ↪️ እኛም ከደም ጋኑ ጅማት ይበልጥ ወደርሱ ቅርብ ነን፡፡ ◾️إِذْ يَتَلَقَّى الْمُتَلَقِّيَانِ عَنِ الْيَمِينِ وَعَنِ الشِّمَالِ قَعِيدٌ ↪️ ሁለቱ ቃል ተቀባዮች (መላእክት) ከቀኝና ከግራ ተቀማጮች ኾነው በሚቀበሉ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ ◾️مَّا يَلْفِظُ مِن قَوْلٍ إِلَّا لَدَيْهِ رَقِيبٌ عَتِيدٌ ↪️ ከቃል ምንም አይናገርም በአጠገቡ ተጠባባቂና ዝግጁ የኾኑ (መላእክት) ያሉበት ቢኾን እንጅ፡፡ ◾️وَجَاءَتْ سَكْرَةُ الْمَوْتِ بِالْحَقِّ ↪️ የሞትም መከራ (ስካር) በእውነቱ መጣች፡፡ ◾️ذَٰلِكَ مَا كُنتَ مِنْهُ تَحِيدُ ↪️ ይህ ያ ከርሱ ትሸሸው የነበርከው ነው ይባላል፡፡ ◾️وَنُفِخَ فِي الصُّورِ ۚ ذَٰلِكَ يَوْمُ الْوَعِيدِ ↪️ በቀንዱም ውስጥ ይንነፋል፡፡ ያ (ቀን) የዛቻው (መፈጸሚያ) ቀን ነው፡፡ ◾️وَجَاءَتْ كُلُّ نَفْسٍ مَّعَهَا سَائِقٌ وَشَهِيدٌ ↪️ ነፍስም ሁሉ ከእርሷ ጋር ነጂና መስካሪ ያለባት ኾና ትመጣለች፡፡ ◾️لَّقَدْ كُنتَ فِي غَفْلَةٍ مِّنْ هَـٰذَا ↪️ ከዚህ ነገር በእርግጥ በዝንጋቴ ውስጥ ነበርክ፡፡ ◾️فَكَشَفْنَا عَنكَ غِطَاءَكَ فَبَصَرُكَ الْيَوْمَ حَدِيدٌ ↪️ ሽፋንህንም ካንተ ላይ ገለጥንልህ፡፡ ስለዚህ ዛሬ ዓይንህ ስለታም ነው ይባላል፡፡ 📚 ሱረቱል (ق) ከ ①⑥–②② ➧አደራ ወንድም እህቶች ➖➖➖➖➖➖➖ 〰ሁሌም ተውበት እናድርግ ወደ አላህ እናልቅስ 〰የቀልባችን መድረቅ ሊያሳስበን ይገባል 〰ሰዎችን አሻግሮ ከማየት እራሳችንን እንምከር 〰አላህን በድብቅም በግልፅም እንፍራ 〰ሞት እንዳለብን እናስታውስ 🔺ሞት አለ 🔺ሀቂቃ ከፊት ለፊት ሞት አለ 🔺ሞት ሞት ያልመከረውና ያልገሰፀው ልፍ ወየውለት 〰የቀብር ጥያቄና ቅጣት አለ ያ አላህ በራህመትህ 〰ሲራጥ አለ አስበው ወንድሜ 〰የስራ ሚዛን አለ 〰ጀሀነም እያጓራ ከፊት ለፊታችን ድቅን የሚልበት ቀን አለ 📌ኧረ ስንቱ ልጥቀስ ይህ ሁሉ እያለብን ባልሰማ ላሽ ብለናል በወንጀል ላይ ወንጀል እንደርባለን መች ይሁን የምንነቃው ◾️ሀቂቃ ሁኔታችን ያሳዝናል ቆም ብለህ አስብ ነገ ዋጥፋቴ፣ መልሱኝ ወደ ዱንያ አንዴ ብለህ ከመጮህህ በፊት አሁን ጊዜው አለህ 🔺ጉድለትህን ጠግን 🔺 ከወንጀልህ ተመለስ 🔺 ከኢባዳ መዘናጋትን ተው 🔺 ግድ የለሽ አትሁን 🔺 የአሔራ ቤትህን በኢማን በተቅዋ በመልካም ስራ ገምባ እኖራለሁ ብቻ ሳይሆን እሞታለሁም በል ማረፊያህ ጀነት ይሁን ጀሀነም ገና አልተረጋገጠም አላህ ሆይ እኔንም ወንድም እህቶቼን ማረን ቀጥ ብለው ያንተን ትእዛዝ ከሚፈፅሙት አድርገን ..✒️አቡ አብደሏህ ኢብኑ ኸይሩ
Показати все...
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 المورد العذب الزلال رد على الإخواں المسدين وغيرهم من الفرق الضالة
Показати все...
المورد العذب الزلال 33.mp318.66 MB
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.