cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

የነብያት ታሪክ قصص الأنبياء

The lies

Більше
Країна не вказанаМова не вказанаКатегорія не вказана
Рекламні дописи
280
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

ነቢዩላሕ ሙሳ።3 @dinkadinkoch {(ድግምተኞቹ) በመካከላቸውም ነገራቸውን ተጨቃጨቁ፤ውይይትንም ደበቁ።}[ጣሃ፡62] ይሁን እንጂ አብዛኞቻቸው ከአቋማቸው ተመለሱና፦ {እነዚህ በእርግጥ ደጋሚዎች ናቸው፤ከምድራችሁ በድግምታቸው ሊያወጧችሁ፣በላጭቱንም መንገዳችሁን ሊያስወግዱባችሁ ይሻሉ አሉ። ተንኮላችሁንም አጠንክሩ፤ከዚያም ተሰልፋችሁ ኑ፤ዛሬ ያሸነፈም ሰው ምኞቱን አገኘ (ተባባሉ)።›[ጣሃ፡63-64] {ሙሳ ሆይ! ወይ ትጥላለህ፣ወይም በመጀመሪያ የምንጥል እንኾናለን፣(ምረጥ) አሉ። አይደለም ጣሉ፣አላቸው፤ወዲያውም ገመዶቻቸውና ዘንጎቻቸው ከድግምታቸው የተነሳ እነርሱ የሚሮጡ (እባቦች) ኾነው ወደርሱ ተመለሱ።}[ጣሃ፡65-66] ሙሳም u ሕዝቡ በድግምተኛ ጠንቋዮች እንዳይፈታትን ሰጉ። {ሙሳም በነፍሱ ውስጥ ፍርሃትን አሳደረ።}[ጣሃ፡67] ከአላህ (ሱ.ወ.) ዘንድም ትእዛዝ መጣላቸው፦ {፦ አትፍራ አንተ የበላዩ አንተ ነህና አልነው። በቀኝ እጅህ ያለችውንም በትር በጣል፤ያንን የሠሩትን ትውጣለችና፤ያ የሠሩት ሁሉ የድግምተኛ ተንኮል ነውና፤ድግምተኛ በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናውም (አልን)።}[ጣሃ፡68-69] {ወደ ሙሳም፦ በትርህን ጣል ስንል ላክን፤(ጣላትም) ወዲያውኑም የሚቀጣጥፉትን (ማታለያ) ትውጣለች። እውነቱም ተገለጸ፤ይሠሩት የነበሩትም (ድግምት) ተበላሸ።}[አልአዕራፍ፡117-118] ያልተጠበቀ ታምር ተከሰተ፦ {እዚያ ዘንድ ተሸነፉም፤ወራዶችም ኾነው ተመለሱ። ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ። አሉ፦ በዓለማት ጌታ አመንን፤በሙሳና በሃሩን ጌታ።}[አልአዕራፍ፡119-122] {ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፤በሃሩንና በሙሳ ጌታ አመንን፣አሉ።}[ጣሃ፡70] የፈርዖን ምላሽም የጅላጅል ማስፈራሪያ ብቻ ነበር። {(ፈርዖንም) ለናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለርሱ አመናችሁን? እርሱ በእርግጥ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ትልቃችሁ ነው፤እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን በማናጋት (ግራና ቀኝን በማፈራረቅ) እቆርጣችኋለሁ፤በዘምባባም ግንዶች ላይ እሰቅላችኋለሁ፤}[ጣሃ፡71] የድግምተኞቹ ምላሽ ለፈርዖን ዱብ እዳ ከመሆኑም በላይ እምነት በምእመናን ላይ የሚያሳድረውን ከባድ ተጽእኖም የሚያብራራ ነበር። {(እነርሱም) አሉ፦ ጉዳት የለብንም፤እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን። እኛ የምእመናን መጀመሪያ በመኾናችን፣ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለኛ ሊምር እንከጅላለን።}[አልሹዐራ፡50-51] ፈርዖን ምእመናኑን ማሰቃየት ሲቀጥል አላህ (ሱ.ወ.) እርሱንና ከርሱ ጋር ያሉትን ከሓዲዎች ቀጣቸው። {የፈርዖንንም ቤተሰቦች፣እንዲገሠጹ በድርቅ ዓመታትና ከፍሬዎችም በመቀነስ በእርግጥ ያዝናቸው። ደጊቱም ነገር (ምቾት) በመጣችላቸው ጊዜ፣ይህች ለኛ (ተገቢ) ናት፣ይላሉ፤ክፋትም ብታገኛቸው በሙሳና አብረውት ባሉት ገደቢስነት ያመካኛሉ፤ንቁ! ገደቢስነታቸው አላህ ዘንድ ብቻ ነው፤ግን አብዛኛዎቻቸው አያውቁም።}[አል አዕራፍ፡130-131] አላመኑም፤ከክሕደታቸውም ተጸጽተው አልተመለሱም። {(ለሙሳም)፦ በማንኛይቱም ታምር በርሷ ልትደግምብን ብትመጣብን፣እኛ ለአንተ የምናምንልህ አይደለንም አሉ፤ወዲያውም የውሃን ማጥለቅለቅ፣አንበጣንም፣ነቀዝንም፣እንቁራሪቶችንም፣ደምንም፣የተለያዩ ታምራት ሲኾኑ፣በነሱ ላይ ላክን፤ኮሩም፤ተንኮለኞችም ሕዝቦች ነበሩ።}[አል አዕራፍ፡132-133] ቅጣቱ ሲጸናባቸው፦ {በነርሱም ላይ ቅጣቱ በወደቀባቸው ጊዜ፦ ሙሳ ሆይ! ጌታህን ላንተ ቃል ኪዳን በገባልህ ነገር ለኛ ለምንልን፤ከኛ ቅጣቱን ብታነሳልን ለአንተ በእርግጥ እናምንልሃለን፤የእስራኤልንም ልጆች ከአንተ ጋር በእርግጥ እንለቃለን፤አሉ። እነርሱም ደራሾቹ እኾኑበት ጊዜ ድረስ ቅጣትን ከነሱ ላይ ባነሳን ጊዜ፣ወዲያውኑ እነርሱ ቃላቸውን ያፈርሳሉ።}[አል አዕራፍ፡134-135] የገቡትን ቃል ሲያፈርሱና ያሉትን ሳይፈጽሙ ሲቀሩም አላህ (ሱ.ወ.) ተበቀላቸው። {እነርሱ በታምራታችን ስለ አስተባበሉም፣ከርሷ ዘንጊዎች ስለኾኑም፤ከነሱ ተበቀልን፤በባሕርም ውስጥ አሰጠምናቸው።}[አል አዕራፍ፡136] የግብጽ ሰዎች ንጉሣቸውን ፈርዖንን በመከተልና የአላህን (ሱ.ወ.) ነቢይና መልክተኛውን ሙሳን u በመጻረር፣በክሕደታቸው በትዕቢታቸውና በእምቢታቸው በገፉ ጊዜ አላህ (ሱ.ወ.) የግብጽን ሕዝብ ኃያልና አስገዳጅ የሆኑ አስገራሚና አስደማሚ ታምራቶቹን አሳያቸው። ይህ ሁሉ ሆኖ ግን ሰዎቹ ከትዕቢታቸው የሚገቱና ከጥመታቸው የሚመለሱ አልሆኑም። ከፈርዖን ሕዝብ በጣም ጥቂቶች ብቻ እንጅ አላመኑም። ሁሉም ድግምተኞችና ሁሉም የእስራኤል ሕዝብ ያመኑ ሲሆን፣የፈርዖንን ግፍና ጭካኔ በመፍራት እምነታቸውን ይደብቁ ነበር። አላህን እንዲገዙባቸውና በሚታዘዙ ጊዜ ለጉዞ ዝግጁ ሆነው አንዱ የሌላውን ቤት ለይቶ አውቀው ይጠብቁ ዘንድ፣የተከታዮቻቸው ቤቶች ከፈርዖን ተከታዮች ቤቶች የተለዩ እንዲሆኑ አላህ (ሱ.ወ.) ለሙሳና ለሃሩን [የአላህ ሰላም በሁለቱም ላይ ይሁን] አሳወቀ። {ወደ ሙሳና ወደ ወንድሙ፦ ለሕዝቦቻችሁ በምስር ቤቶችን ሥሩ፤ቤቶቻችሁንም መስገጃ አድርጉ፤ሶላትንም በደንቡ ስገዱ፤(ለሙሳ) ምእመናኖቹንም አብስር ስንል ላክን።}[ዩኑስ፡87] ከዚያም አላህ (ሱ.ወ.) ለባሪያው ለሙሳ u ወሕይ አስተላለፈ፦ {ወደ ሙሳም ፦ ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፣እናንተ የሚከተሏችሁ ናችሁና ስንል ላክን።}[አል ሹዐራ፡52] የፈርዖን መልስ ግን የሚከተለው ነበር፦ {፦ ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፤ ፦ እነዚህ ጥቂቶች ጭፍሮች ናቸው። እነርሱም ለኛ አስቆጪዎች ናቸው። እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤(አለ)።}[አል ሹዐራ፡53-56] የአላህ (ሱ.ወ.) ፈቃድ ግን ሌላ ሆነ፦ {አወጣናቸውም፤ከአትክልቶችና ከምንጮች፤ከድልቦችም፣ከመልካም መቀመጫዎችም። እንደዚሁ፣ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም።}[አል ሹራ፡51] ፈርዖንና ሰራዊቱ የእስራኤል ልጆችን ይዘው ለመመለስ ተከተሏቸው። {ፀሐይዋ ስትወጣም፣ተከተሉዋቸው።}[አል ሹዐራ፡60] ሲደርሱባቸውም፦ {ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ፣የሙሳ ጓዶች እኛ (የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን፣አሉ።}[አል ሹዐራ፡61] የአላህ መልክተኛ የሙሳ u ምላሽ ግን በአላህ ላይ ሙሉ በሙሉ በመተማመን፣እርሱን በማወቅና በርሱ ብቻ በመመካት የተሞላ ነበር። {(ሙሳ)፦ ተውዉ!ጌታዬ ከኔ ጋር ነው፤በእርግጥ ይመራኛል፣አለ።}[አል ሹዐራ፡62] የአላህ መመሪያና እዝነቱ ለሙሳና ለተከታዮቻቸው ከተፍ አለ፦ {ወደ ሙሳም ባሕሩን በበትርህ ምታው ስንል ላክንበት፣(መታውና) ተከፈለም፤ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ። እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን። ሙሳንና ከርሱ ጋር ያሉትንም ሰዎች፣ሁሉንም አዳን። ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን። በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፤አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም። ጌታህም፣እርሱ አሸናፊው፣አዛኙ ነው።}[አል ሹዐራ፡63-68] በዚህ አስፈሪ ወቅትም አላህ (ሱ.ወ.) እንዲህ አለ፦ {የእስራኤልንም ልጆች፣ባሕሩን አሳለፍናቸው፤ፈርዖንና ሰራዊቱም ወሰን ለማለፍና ለመበደል ተከተሏቸው፤}[ዩኑስ፡90] እዚህ ላይም ፈርዖን ሞትና መስጠም አይቀሬ መሆኑን አረጋገጠ፦ Share share share Share share share Share share share Share share share @dinkadinkoch
Показати все...
ነቢዩላሕ ሙሳ። { {(ሙሳ) አለ፦ ጌታዬ ሆይ! እኔ ከነሱ ነፍስን ገድያለሁ፣ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፤ወንድሜም ሃሩን እርሱ ምላሱ ከኔ የተባ ነው፤እውነተኛነቴንም የሚያረጋግጥልኝ ረዳት ኾኖ ከኔ ጋር ላከው፤እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁና።}[አልቀሶስ፡33-34] ወንድማቸው ሃሩንን ረዳታቸው ያደርግ ዘንድም አላህን (ሱ.ወ.) ለመኑ፦ {ከቤተሰቦቼም ለኔ ረዳትን አድርግልኝ፤ሃሩንን ወንድሜን። ኀይሌን በርሱ አበርታልኝ። በነገሬም አጋራው። በብዙ እናጠራህ ዘንድ። በብዙም እንድናወሳህ። አንተ በኛ ነገር ዐዋቂ ነህና። (አላህም) አለ፦ ሙሳ ሆይ! ልመናህን በእርግጥ ተሰጠህ።}[ጣሃ፡29-36] ሙሳና ሃሩን ወደ ፈርዖን ሄደው አንድ አላህን ብቻ መግገዛትን፣በርሱ አለማጋራትን፣እስራኤላውያንን በፈለጉበት ቦታ አንድ አላህን ብቻ መግገዛት ይችሉ ዘንድ ከጭቆና አገዛዙ ነጻ መልቀቅን በተመለከተ የተላኩበትን የአላህን (ሱ.ወ.) መልእክት አደረሱት። ፈርዖንም በትእቢት ተወጥሮ በመኩራራት ሙሳን በንቀት ዓይን ተመለከተ። እንዲህም አለ፦ {(ፈርዖንም) አለ ፦ ልጅ ኾነህ በኛ ውስጥ አላሳደግንህምን? በኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን? ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን? አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ (አለ)።}[አል ሹዐራ፡18-19] ሙሳም u መልስ ሰጡት፦ {(ሙሳም) አለ፦ ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት።}[አል ሹዐራ፡20] ያን የፈጸምኩት የአላህ መልክት ሳይመጣልኝና ወሕይ ሳይገለጥልኝ በፊት ነው፣አሉት። {በፈራኋችሁም ጊዜ ከናንተ ሸሸሁ፤ጌታየም ለኔ ጥበብን ሰጠኝ፤ከመልክተኞቹም አደረገኝ።}[አል ሹዐራ፡21] በማሳደግና በመንከባከብ ስላደረገላቸው ውለታ ፈርዖን ሲመጻደቅ ሙሳ u መልስ ሰጡት። {ይህችም፣የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ናት።}[አል ሹዐራ፡22] መላውን የእስራኤል ሕዝብ በባርነት ይዘህ ጉልበታቸውን በመበዝበዝና በመጨቆን ለዘመናት የሰቆቃ ሕይወት እንዲመሩ እያደረግህ፣ለኔ ለአንዱ እስራኤላዊ ብቻ በዋልከው ውለታ አትመጻደቅ፣አሉት። በመቀጠልም ሙሳ ላከኝ የሚሉት ጌታ አምላክ የቱ እንደሆነ ፈርዖን ጠየቃቸው። {ፈርዖን አለ፦ (ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው?}[አል ሹዐራ፡23] አሳማኝ መልስም ተሰጠው፦ {(ሙሳ) ፦ የሰማያትና የምድር፣በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፤የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤አለው።}[አል ሹዐራ፡24] ፈርዖንም መሳለቅ ጀመረ። {(ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች፦ አትሰሙምን? አለ።}[አል ሹዐራ፡25] ሙሳም u ለማንም ቁብ ሳይሰጡ ጥሪያቸውን ቀጠሉ። {(ሙሳ)፦ ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው አለው።}[አል ሹዐራ፡26] ፈርዖን በትእቢቱ ገፋበት፦ {(ፈርዖን) ፦ ያ ወደናንት የላከው መልክተኛችሁ፣በእርግጥ ዕብድ ነው፤አለ።}[አል ሹዐራ፡27] {(ሙሳ)፦ የምሥራቅና የምዕራብ፣በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፣ታውቁ እንደ ኾናችሁ፣(እመኑበት) አለው።}[አል ሹዐራ፡28] ከማስረጃ ከአመዛዛኝ አእምሮም ሆነ ከአመክዮ የተራቆተው አምባገነኑ ትእቢተኛ ገዥ ፈርዖን ማስፈራራት ጀመረ። {(ፈርዖን)፦ ከኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ አለ።}[አል ሹዐራ፡29] በፈርዖን ሹፈትና በስላቁ ጥሪውን ያላቆሙት ሙሳ u፣በፈርዖን ማስፈራሪያም አልተበገሩም። መልስ ሰጡት፦ {(ሙሳ)፦ በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ? አለው። እንግዲያውስ ከውነተኞች እንደ ኾንክ (አስረጁን) አምጣው አለ። በትሩንም ጣለ፤እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች። እጁንም አወጣ፤ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች።} [አል ሹዐራ፡30-33] ሕዝቡ በሙሳ u እንዳያምን ፈርዖን ስጋት ላይ ወደቀ። {(ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት፣ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው፤አለ። ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ? (አላቸው)። አሉት፦ እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ፣ሰብሳቢዎችን ላክ። በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና።}[አል ሹዐራ፡34-37] ፈርዖን ሁሉንም አሳማኝ ማስረጃዎች ካየ በኋላም ማስተባበሉንና ክህደቱን በእብሪት ቀጠለ። {ታምራቶቻችንንም ሁሏንም (ለፈርዖን) በእርግጥ አሳየነው፤አስተባበለም፤እምቢም አለ። ከምድራችን በድግምትህ ልታወጣን መጣህብን? ሙሳ ሆይ! አለ። መሰሉንም ድግምት እናመጣብሃለን፤በኛና ባንተም መካከል እኛም አንተም የማንጥሰው የኾነ ቀጠሮን፣በመካከለኛ ስፍራ አድርግልን፣አለ። ቀጠሯችሁ በማጌጫው ቀን ሰዎቹም በረፋድ በሚሰበሰቡበት ነው አለ። ፈርዖንም ዞረ፤ተንኮሉንም ሰበሰበ፤ከዚያም መጣ።}[ጣሃ፡56-60] ሙሳ u በሕዝቡ ላይ የአላህ (ሱ.ወ.) ቅጣት እንዳይወርድ ፈሩላቸው። {ሙሳ ለነሱ አላቸው ፦ ወዮላችሁ በአላህ ላይ ውሸትን አትቅጠፉ፤በቅጣት ያጠፋችኋልና፤የቀጠፈም ሰው በእርግጥ አፈረ።}[ጣሃ፡61] የፈርዖን ድግምተኞች በሀሳብ ተለያዩ፤አንዳንዶቻቸው ይህ የድግምተኛ ጠንቋይ ንግግር አይደለም አሉ። Share share share Share share share Share share share Share share share @dinkadinkoch
Показати все...
ነቢዩላሕ ሙሳ። 2 ሙሳም u በግፈኛው ንጉሥ በፈርዖን ቤት አደገ፦ {ብርታቱንም በደረሰና በተስተካከለ ጊዜ፣ጥበብንና ዕውቀትን ሰጠነው፤እንዲሁም መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን። ከተማይቱንም፣ሰዎችዋ በዝንጋቴ ጊዜ ላይ ኾነው ሳሉ ገባ፤በርሷም ውስጥ የሚጋደሉን ሁለት ሰዎች አገኘ፤ይህ ከወገኑ ነው፤ይህም ከጠላቱ ነው፤ያም ከወገኑ የኾነው ሰው፣በዚያ ከጠላቱ በኾነው ሰው ላይ እርዳታን ጠየቀው፤ሙሳም በጡጫ መታው፤ገደለውም፤ይህ ከሰይጣን ሥራ ነው፤እርሱ ግልጽ ጠላት ነውና፣አለ። ጌታዬ ሆይ! እኔ ነፍሴን በደልኩ፤ለኔም ማር አለ፤ለርሱም ምሕረት አደረገለት፤እርሱ መሓሪ፣አዛኝ ነውና። ጌታዬ ሆይ! በኔ ላይ በመለገስህ ይኹንብኝ (ከስሕተቴ እጸጸታለሁ)፤ለአመጠኞችም ፈጽሞ ረዳት አልኾንም፣አለ።}[አልቀሶስ፡14-17] የራሱና የእስራኤላዊው ጠላት የሆነውን ግለሰብ ከገደለ በኋላ ግን፦ {በከተማይቱም ውስጥ ፈሪ፣የሚጠባበቅ ኾኖ አደረ፤በድንገትም ያ ትላንት እርዳታን የጠየቀው ሰው በጩኸት እርዳታን ይጠይቀዋል፤ሙሳ ለርሱ፦ አንተ በእርግጥ ግልጽ ጠማማ ነህ አለው። (ሙሳ) ያንን እርሱ ለሁለቱም ጠላት የኾነውን ሰው፣በኀይል ሊይዘው በፈለገም ጊዜ፣ሙሳ ሆይ! በትላንትናው ቀን ነፍስን እንደ ገደልክ፣ልትገድለኝ ትፈልጋለህን? በምድር ላይ ጨካኝ መኾንን እንጅ ሌላ አትፈልግም፤ከመልካም ሠሪዎችም መኾንን አትፈልግም፤አለው። ከከተማይቱም ዳርቻ አንድ ሰው እየሮጠ መጣ፤ሙሳ ሆይ! ሹማምንቶቹ ሊገድሉህ ባንተ ይመካከራሉና ውጣ፤እኔ ላንተ ከመካሪዎች ነኝና አለው። የፈራና የሚጠባበቅ ኾኖም ከርሷ ወጣ፤ጌታዬ ሆይ! ከበደለኞቹ ሕዝቦች አድነኝ አለ።}[አልቀሶስ፡18-21] ግብጽን ለቆ ወደ መድየን አቅጣጫ አመራ፦ {ወደ መድየን አግጣጫ ፊቱን ባዞረ ጊዜም፣ጌታዬ ቀጥተኛውን መንገድ ሊመራኝ እከጅላለሁ አለ። ወደ መድየንም ውሃ በመጣ ጊዜ፣በርሱ ላይ ከሰዎች ጭፍሮችን (መንጋዎቻቸውን) የሚያጠጡ ኾነው አገኘ፤ከነሱ በታችም (ከውሃው መንጎቻቸውን) የሚከለክሉን ሁለት ሴቶች አገኘ፤ነገራችሁ ምንድን ነው? አላቸው፤እረኞቹ ሁሉ (መንጎቻቸውን) እስከሚመልሱ አናጠጣም፤አባታችንም ትልቅ ሽማግሌ ነው አሉት። ለሁለቱም አጠጣላቸው፤ከዚያም ወደ ጥላው ዘወር አለ፤ጌታዬ ሆይ! እኔ ከመልካም ነገር ወደኔ ለምታደርገው ፈላጊ ነኝ፣አለ።}[አልቀሶስ፡22-24] ሁለቱ ሴቶች ሙሳ የሰራውን በጎ ሥራ ለአባታቸው ለነቢዩ ሹዐይብ u ተናገሩ። ሹዐይብም ሙሳን u ትጠራው ዘንድ አንደኛቱን ልጃቸውን ላኩ፦ {ከሁለቱ አንደኛይቱም ከሕፍረት ጋር የምትኼድ ኾና መጣችው፤አባቴ ለኛ ያጠጣህልንን ዋጋ ሊሰጥህ ይጠረሃል፣አለችው፤}[አልቀሶስ፡25] ሙሳም [የአላህ ሰላም በሁለቱም ላይ ይሁን] ወደ ሹዐይብ መጡ። {ወደርሱ በመጣና ወሬውን በርሱ ላይ በተረከለትም ጊዜ፣አትፍራ፤ከበደለኞቹ ሕዝቦች ድነሃል አለው።}[አልቀሶስ፡25] ልጅቱ የሙሳን u ታማኝነት ባስተዋለች ጊዜ፦ {ከሁለቱ አንደኛይቱም አባቴ ሆይ! ቅጠረው፤ከቀጠርከው ሰው ሁሉ በላጩ፣ብርቱው፣ታማኙ፣ ነውና አለችው።}[አልቀሶስ፡26] ሹዐይብም ለሙሳ [የአላህ ሰላም በሁለቱም ላይ ይሁን] ፦ {ስምንትን ዓመታት ልታገለግለኝ፣እኔ ከነዚህ ሁለት ሴቶች ልጆቼ አንዲቱን ላጋባህ እሻለሁ፤ዐሥርን ብትሞላም ከአንተ ነው፤ባንተ ላይ ማስቸገርንም አልሻም፤አላህ የሻ እንደኾነ ከመልካሞቹ ሰዎች ኾኜ ታገኘኛለህ አለው። (ሙሳም) ይህ፣(ውለታ) በኔና ባንተ መካከል (ረጊ) ነው፤ከሁለቱ ጊዜያቶች ማንኛውንም ብፈጽም፣በኔ ላይ ወሰን ማለፍ የለም፤አላህም በምንለው ላይ ምስክር ነው አለ።}[አልቀሶስ፡27-28] የተስማሙበትን የሥራ ጊዜ ካጠናቀቁ በኋላ ሙሳ u ቤተሰባቸውን ይዘው ተጓዙ፦ {ሙሳም ጊዜውን በጨረሰና ከቤተሰቦቹ ጋር በኼደ ጊዜ፣ከጡር ተራራ ጎን እሳትን አየ፤ለቤተሰቡ (እዚህ) ቆዩ፤እኔ እሳትን አየሁ፤ከርሷ ወሬን ወይም ትሞቁ ዘንድ ከእሳት ትንታግን አመጣላችኋለሁ አለ።}[አልቀሶስ፡29] በዚህን ጊዜ አላህ (ሱ.ወ.) ወሕይ ላከባቸው፦ {በመጣትም ጊዜ፣ከሸለቆው ቀኝ ዳርቻ፣ከዛፊቱ በኩል በተባረከችው ስፍራ ውስጥ ሙሳ ሆይ! እኔ የዓለማት ጌታ አላህ ነኝ በማለት ተጣራ። በትርህንም ጣል (ተባለ)፤እንደ ትንሽ እባብ ስትስለከለክ ባያትም ጊዜ፣ወደ ኋላ ዞሮ ሸሸ፤አልተመለሰምም፤ሙሳ ሆይ! ተመለስ፤አትፍራም፤አንተ ከጥብቆቹ ነህና (ተባለም)። እጅህን በአንገትጌህ ውስጥ አግባ፤ያለ ነውር ነጭ ኾና ትወጣለችና፤ክንፍህንም ከፍርሃት (ለመዳን) ወዳንተ አጣብቅ፤እነዚህም ከጌታህ የኾኑ ወደ ፈርዖንና ወደ መኳንንቶቹ የሚደርሱ ሁለት አስረጅዎች ናቸው፤እነርሱ አመጠኞች ሕዝቦች ነበሩና።}[አልቀሶስ፡30-32] Share share share Share share share Share share share Share share share @dinkadinkoch
Показати все...
አሪፍ ግጥም Share share share Share share share Share share share Share share share @dinkadinkoch
Показати все...
(النونيه).mp31.15 MB
ለቻናል ቤተሰቦች ይህ ቻናል ወደ ሀይማኖታዊ ነገር ስለተቀየረ ቅር ያለው ካለ መውጣት ይችላል @dinkadinkoch
Показати все...
Share share share Share share share Share share share Share share share @dinkadinkoch
Показати все...
ነቢዩላሕ ሙሳ። 1 እስራኤላውያን ከኢብራሂም u ሲወርድ ሲዋረድ በውርስ የደረሳቸውንና ከዝርያቸው መካከል በሚወለድ ልጅ እጅ የግብጽ ንጉሥ ጥፋት እንደሚከሰት በሚገልታ ትንቢት ላይ ይነጋገሩ ነበር። ይህ የብስራት ትንቢትም በእስራኤላውያን ዘንድ በስፋት የተሰራጨ ስለ ነበር በሹማምንቱ በኩል ነገሩ ወደ ፈርዖን ጆሮ ደረሰ። በዚህን ጊዜ ፈርዖን ትንቢቱን ለማክሸፍ ለእስራኤላውያን የሚወለድ ወንድ ልጅ ሁሉ እንዲገደል ትእዛዝ አስተላለፈ። እስራኤላውያንም ግብጽ ውስጥ የግፍና የሰቆቃ ሕይወት ይገፉ ነበር፦ {ፈርዖን በምድር ላይ ተንበጣረረ፤ነዋሪዎችዋንም የተከፋፈሉ ጓዶች አደረጋቸው፤ከነሱ ጭፍሮችን ያዳክማል፤ወንዶች ልጆቻቸውን በብዛት ያርዳል፤ሴቶቻቸውንም ይተዋል፤እርሱ ከሚያበላሹ ሰዎች ነበርና። }[አልቀሶስ፡4] አላህ (ሱ.ወ.) ለግፉአኑ የእስራኤል ልጆች ጸጋውን መዘርጋት ፈለገ፦ {በነዚያም በምድር ውስጥ በተጨቆኑት ላይ ልንለግስ፤መሪዎችም ልናደርጋቸው፣ወራሾችም ልናደርጋቸው፣እንሻለን። ለነርሱም በምድር ላይ ልናስመች፣ፈርዖንንና ሃማንንም፣ሰራዊቶቻቸውንም፣ከነሱ ይፈሩት የነበሩትን ነገር ልናሳያቸው፣(እንሻለን)።}​[አልቀሶስ፡5-6] እየዞሩ እርጉዝ ሴቶችን ሁሉ የሚከታተሉና መች እንደሚወልዱ የሚያጣሩ ሠራተኞችንና አዋላጆችን እስከማሰማራት ድረስ ፈርዖን ከሙሳ ለመዳን የተሟላ ጥብቅ ጥንቃቄ ቢያደርግም፣ተቆጣጣሪዎቹም ወንድ ሕጻናትን እንደተወለዱ ወዲያውኑ ሲያርዱ ቢቆዩም፣አላህ (ሱ.ወ.) ግን ለፈርዖን ለሹሙና ለሰራዊቶቻቸው የፈሩትን ማሳየት ፈቃዱ ሆነ። የሙሳ እናት በወለደች ጊዜም፦ {ወደ ሙሳም እናት፦ አጥቢው፤በርሱም ላይ በፈራሽ ጊዜ በባሕሩ ውስጥ ጣይው፤አትፍሪም፤አትዘኝም፤እኛ ወዳንቺ መላሾቹና ከመልክተኞቹም አድራጊዎቹ ነንና ማለትን አመለከትን።}[አልቀሶስ፡7] እንዳይገድሉት ስለፈራች ሕፃኑን ሳጥን ውስጥ አድርጋው ወደ ወንዝ ጣለችው፦ {የፈርዖን ቤተሰቦችም (መጨረሻው) ለነርሱ ጠላት ፣ሐዘንም፣ይኾን ዘንድ አነሱት፤ፈርዖንና ሃማንም፣ሰራዊቶቻቸውም ኀጢአተኞች ነበሩ።}[አልቀሶስ፡8] የፈርዖን ሚስት ልብም በሕጻኑ ሙሳ ፍቅር ተጠመደ፦ {የፈርዖንም ሚስት ለኔ የዓይኔ መርጊያ ነው፤ለአንተም፤አትግደሉት፤ሊጠቅመን ወይም ልጅ አድርገን ልንይዘው ይከጀላልና አለች፤እነርሱም (ፍጻሜውን) የማያውቁ ኾነው (አነሱት)።}[አልቀሶስ፡9] የሙሳ እናት ግን፦ {የሙሳም እናት ልብ፣ባዶ ኾነ፤ከምእመናን ትኾን ዘንድ በልቧ ላይ ባላጠነከርን ኖሮ ልትገልጸው ቀርባ ነበር። ለእኅቱም ተከታተይው አለቻት፤እርሱንም እነሱ የማያውቁ ሲኾኑ በሩቅ ኾና አየችው።}[አልቀሶስ፡10-11] {(ወደናቱ ከመመለሱ) በፊትም አጥቢዎችን (መጥባትን) በርሱ ላይ እርም አደረግን፤(እኅቱ) ለናንተ የሚያሳድጉላችሁን፣እነርሱም ለርሱ ቅን አገልጋዮች የኾኑን ቤተሰቦች ላመልክታችሁን? አለችም። ወደናቱም፣ዓይንዋ እንድትረጋ፣እንዳታዝንም፣የአላህም የተስፋ ቃል እርግጥ መኾኑን እንድታውቅ፣መለስነው፤ግን አብዛኞቻቸው አያውቁም።}[አልቀሶስ፡12-13] ሙሳም u በግፈኛው ንጉሥ በፈርዖን ቤት አደገ፦ {ብርታቱንም በደረሰና በተስተካከለ ጊዜ፣ጥበብንና ዕውቀትን ሰጠነው፤እንዲሁም መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን። ከተማይቱንም፣ሰዎችዋ በዝንጋቴ ጊዜ ላይ ኾነው ሳሉ ገባ፤በርሷም ውስጥ የሚጋደሉን ሁለት ሰዎች አገኘ፤ይህ ከወገኑ ነው፤ይህም ከጠላቱ ነው፤ያም ከወገኑ የኾነው ሰው፣በዚያ ከጠላቱ በኾነው ሰው ላይ እርዳታን ጠየቀው፤ሙሳም በጡጫ መታው፤ገደለውም፤ይህ ከሰይጣን ሥራ ነው፤እርሱ ግልጽ ጠላት ነውና፣አለ። ጌታዬ ሆይ! እኔ ነፍሴን በደልኩ፤ለኔም ማር አለ፤ለርሱም ምሕረት አደረገለት፤እርሱ መሓሪ፣አዛኝ ነውና። ጌታዬ ሆይ! በኔ ላይ በመለገስህ ይኹንብኝ (ከስሕተቴ እጸጸታለሁ)፤ለአመጠኞችም ፈጽሞ ረዳት አልኾንም፣አለ።}​[አልቀሶስ፡14-17] የራሱና የእስራኤላዊው ጠላት የሆነውን ግለሰብ ከገደለ በኋላ ግን፦ {በከተማይቱም ውስጥ ፈሪ፣የሚጠባበቅ ኾኖ አደረ፤በድንገትም ያ ትላንት እርዳታን የጠየቀው ሰው በጩኸት እርዳታን ይጠይቀዋል፤ሙሳ ለርሱ፦ አንተ በእርግጥ ግልጽ ጠማማ ነህ አለው። (ሙሳ) ያንን እርሱ ለሁለቱም ጠላት የኾነውን ሰው፣በኀይል ሊይዘው በፈለገም ጊዜ፣ሙሳ ሆይ! በትላንትናው ቀን ነፍስን እንደ ገደልክ፣ልትገድለኝ ትፈልጋለህን? በምድር ላይ ጨካኝ መኾንን እንጅ ሌላ አትፈልግም፤ከመልካም ሠሪዎችም መኾንን አትፈልግም፤አለው። ከከተማይቱም ዳርቻ አንድ ሰው እየሮጠ መጣ፤ሙሳ ሆይ! ሹማምንቶቹ ሊገድሉህ ባንተ ይመካከራሉና ውጣ፤እኔ ላንተ ከመካሪዎች ነኝና አለው። የፈራና የሚጠባበቅ ኾኖም ከርሷ ወጣ፤ጌታዬ ሆይ! ከበደለኞቹ ሕዝቦች አድነኝ አለ።}[አልቀሶስ፡18-21] see @dinkadinkoch
Показати все...
ከነቢዩላሕ ሙሳ እንጀምራለን
Показати все...
😎ሰዎች ላንተ የሚሰጡህ አክብሮት አንተ ለራስህ ከምትሰጠው ቦታ እና ከሁኔታህ ተነስተው ነው። ስለዚህ ሰዎች እንዲያከብሩህ ከፈለክ መጀመሪያ ራስህን አክብር፤ ግድ የለሽ አትሁን። በጣም የምታደንቃቸው የምታከብራቸው ሰዎች የሚያደርጉትን ተመልከት፣ ኮርጅ እንውም የእነሱን አሪፍ ልማዶች ስረቅ። ፖብሎ ፒካሶ ጥሩ አርቲስቶች ይኮርጃሉ፤ ምርጦች ግን ይሰርቃሉ ይለናል። የምናከብረው ሰው ቀጠሮ አክባሪ፣ አንባቢ፣ በጠዋት የሚነሳ፣ ላመነበት ጥግ ድረስ የሚሞክር ከሆነ እኛም ብዙ መልፋት ሳይጠበቅብን ያ ሰው ያደረገውን መድገም ነው። አስደሳች ምሽት ተመኘን🙏 @dinkadinkoch የእናንተ ምርጥ ጓደኛ
Показати все...
#አመስግነው አንድ ስጋ የምትጠብስ ሴት ስጋውን መጥበሻው ላይ ትጥድና ታገላብጠዋለች ። ከዛ መብሰል አለመብሰሉን በሹካ ወጋ ወጋ አድርጋ ታየዋለች ። ከበሰለ ታወርድና ለመዓድ ገበታ ላይ ታቀርበዋለች። ፈጣሪም እኛን እውቀት ይሰጡናል ያበስሉናል ብሎ ባሰባቸው በተለያዩ ነገሮች ላይ ይጥደንና ፍቅረኛ ማጣት ፣ ስራ ማጣት ፣ ገንዘብ ማጣት ... በተባሉ ሹካዎች ወጋ ወጋ አድርጎ መብሰል አለመብሰላችንን ያረጋግጣል። ችግር ውስጥ ሆነን ካመሰገንን በስለናል ካማረርን ግን ይቀረናልና በተለያዩ ችግር ውስጥ ጥዶ ያገላብጠናል። 1 ካሜራ ማን እኛን ፎቶ ከማንሳቱ በፊት ፈገግ በል ቀና በል ትንሽ ወደ ቀኝ ምናምን እያለ ያስተካክለናል ከዛ ያነሳናል ። ፈጣሪም እኛን በተለያዩ ችግሮች ውስጥ እያስገባ ነው ህይወታችንን ሚያስተካክለው። መከራ ፈጣሪ እኛን ወደሱ የሚጎትትበት ገመድ ነው። ዳይመንድን ውድ ካደረጉት ነገሮች መካከል አንዱ አቆራረጡ ነው ። ዳይመንድን የምናውቀውን ቅርፁን ያስያዘውና ከተለያየ አቅጣጫ እንዲያንፀባርቅ ያደረገው አቆራረጡ ነው ። እኛንም ዛሬ እየቆረጡንና እያማረርንባቸው ያሉ ችግሮች ነገ እኛን ዉድና የሚያበራ ማንነት ባለቤት የሚያደርጉን ናቸው ። ማዕበል ሲነሳና ባህሩን ሲያማስለው ሁሉም እንስሶች ይሸሻሉ። ንስር ግን በመሀሉ ገብቶ አሳ ይዞ ይወጣል ። ወዳጄ be like Eagle በችግር ውስጥ እራስህን አንፅ። ሸክላ የምትሰራ ሴት እንኳን ሸክላዋን ሰርታ ስትጨርስ እንዲጠነክርላት በእሳት ነው ምትጠብሰው ። ዛሬ የሚጠብሱህ ችግሮች ማንነትህን ነው የሚያጠነክሩልህ ። ስለዚህ ስለሆነው ስለሚሆነው እየሆነ ስላለው ፣ ስለተደረግልህ ስላልተደረገልህ ፣ ስለ ሰጠህ ስለ ነፈገህ ነገር ሁሉ እሱን አመስገነው ። እንዲ በለው " ደስታንም ሆነ መከራን ብትሰጠው ከኔ ይልቅ ለኔ አንተ ነህ ምትቀርበው " @dinkadinkoch
Показати все...