Al Quran online
አብደሏህ ኢብኑ መስዑድ እንዲህ ብለዋሉ፦ <<ዕውቀትን ከፈለጋቹ ቁርዓንን አሰራጩ፤ ምክኒያቱም በቁርዓን ውስጥ የመጀመሪያም የመጨረሻ እውቀት አለበት።>> ለማንኛዉም አስተያየት☞☞ @Alhamdu_Quran_Rectation_bot በዚህ ላይ ይድርሱን https://t.me/joinchat/AAAAAE3vQfUMPUaMGBOVJw
Більше- Підписники
- Перегляди допису
- ER - коефіцієнт залучення
Триває завантаження даних...
Триває завантаження даних...
እድሜህን በጭንቀት፣ በሀዘንና በትካዜ አትጨርስ። በረባ ባረባው በትንሽ በትልቁ እየተብሰለሰልክ ውስጥህን አትጉዳ። ከዛም አልፎ ለስኳር፣ ለደም ግፊትና ለሌሎች ተጓዳኝ በሽታዎች እራስህን አታጋልጥ። የሚያስከፋ የሚያሳዝንና ደስ የማይል ነገር ቢገጥምህ እንኳ ቀልብህ ላይ ቋጥረህ ይዘህ ነፍስህን አታስጨንቅ። ዱንያ አጭር ናት ቢደላህም ቢከፋህ ታልፋለች። ዘውታሪነት ለአላህ እንጂ ለማንም የለም። ስታገኝ አመስጋኝ ስታጣ ታጋሽ ውድ የአላህ ባሪያ ሁን። ከዛ በዘለለ ለዱንያ ብዙም ቦታ አትስጥ። እንደሚታወቀው ከሀዘን በኋላ ደስታ ከማጣት በኋላ ማግኘት እንዳለ ሆኖ የዱንያ መከራና ስቃይ የፈለገ ቢገዝፍና ቢበረታ በሶብርና በፅናት ትሻገረዋለህ። እጅግ ከከፋም በሞት ትገላገለዋለህ። ነገራቶች ሲስተካከሉልህ፣ ያሰብከው ሲሳካና ህልምህን እውን ሲሆን እንደምትደሰተው ሁሉ ነገራቶች በተቃራኒ ሲሆኑብህ የአላህ ውሳኔ ነውና ወደህ ተቀበል። ሲሳካለትና ሲያገኝ የሚደሰት ሲያጣና ሲቸገር የሚማረር ጥቅሙን ብቻ የሚያሳድድ ራስ ወዳድ አትሁን። ነገራቶችን ቀለል አድርገህ ኑር። የሁል ጊዜ ሀሳብና ጭንቅህ ከሞት በኋላ ስላለው ለዘልአለማዊ ህይወትህ ይሁን። ከዱንያው ይልቅ ለአሄራው ቤትህ አብዝተህ ልፋ ተጨነቅ። በትንሽ ትልቁ አትማረር። በዱንያ ላይ ስትኖር የበታችህን እንጂ የበላይህን አትመልከት። የሌሎችን እያየህ እራስህን በቅናት አትግደል። በአላህ ካመንክና በሱ ላይ ትክክለኛ መመካትን ከተመካህ በማጣት ውስጥ ሆነህ ማግኘትን ታያለህ። በችግር ውስጥ ሆነህ ደስታን ታጣጥማለህ።
🛑👉ዱንያ በባህሪዋ አጭርና ጠባብ ናት የባሰ ደግሞ አንተ አታጥባት። ሲጀመር ዱንያ የተፈጠረው ላንተ እንጂ አንተ ለሷ አይደለም። ነግደህ ስላላተረፍክ አትበሳጭ። ከትምህርት ስለወደቅክ የህይወትህ መጨረሻ አድርገህ አትመልከት። ህይወትህ ሊለውጡ የሚችሉ ከዛ ውጪ ሌሎች ብዙ አማራጮች አሉህ። አንዱ ካልተሳካልህ የግብህ መጨረሻ ያ አታድርግ። በጌታህ ታግዘህ ነገራቶችን ቀያይረህ ሞክር። እንደ ጋሪ ወደ አንድ አቅጣጫ ወደፊት ብቻ አትመልከት። በፍፁም ተስፋ አትቁረጥ። ተስፋ መቁረጥ የስኬት ግርዶሽ ነው። ማወቅ ያለብህ ያንተ ጥረትና ልፋት ሰበብ እንጂ ሌላ አይደለም። ሰጭውና ከልካዩ የበላይና የበታች አድራጊው አላህ ነው። ስለዚህ ሁሌም አመስጋኝ፣ ታጋሽ፣ ታታሪ፣ ጠንካራና ማራል ያለው ጀግና ሁን። ባጣኸው ነገር ውስጥ ሊደርስብህ የነበረ መጥፎ ነገር ስለማታውቅ ለምን አጣሁት ብለህ ችክ አትበል።
🛑👉ሁሌም ደስተኛ ሁን። ለሀዘን ለትካዜ በር አትክፈት። ደስታን ለማግኘት እሩቅ አትሂድ እጅግ በጣም ቀላል ነው። በአላህ ማመን እሱን በብቸኝነት መገዛትና መልካም መስራት ብቻ ነው የሚጠበቅብህ። ይህ ካደረግክ አላህ በዱንያም በአሄራ ደስተኛ ህይወት ሊያኖርህ ቃል ገብቷልና።
مَنْ عَمِلَ صَالِحًا مِّن ذَكَرٍ أَوْ أُنثَىٰ وَهُوَ مُؤْمِنٌ فَلَنُحْيِيَنَّهُ حَيَاةً طَيِّبَةً ۖ وَلَنَجْزِيَنَّهُمْ أَجْرَهُم بِأَحْسَنِ مَا كَانُوا يَعْمَلُونَ
ከወንድ ወይም ከሴት እርሱ አማኝ ኾኖ በጎን የሰራ መልካም ኑሮን በእርግጥ እናኖረዋለን፡፡ ይሠሩትም ከነበሩት ነገር በመልካሙ ምንዳቸውን እንመነዳቸዋለን፡፡
📚 ሱረት አን_ነህል 97➡️ በቻናላችን የሚሰጡ የትምህርት አይነቶች ➲የአቂዳ ኪታቦች ➲የፊቅህ ግንዛቤዎች ➲የሱና ኡለማዎች ፈትዋ ➲ወቅታዊ ምክሮች ➲የቁርአን ቂርአትና ሌሎችም http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
👍 ባመሸህም ጊዜ ነገ አለ እያልክ መልካም ስራና ወደ አላህ መመለስን ለነገ አታዘግይ። ምክንያቱም ነገን ላታገኘው ትችላለህና።
👍 ላንተ ይህን አሁን ያለህበትን እንጂ ነገ ማታ የምትለው ሰአት የለህም።
👇 ወደ ኸይር ተሽቀዳደም
➧ማንኛውም መልካም ስራን
➧ተውባ (ወደ አላህ መመለስን)
➧እስቲግፋር (አላህን መሀርታ መጠየቅን)
➬ለነገ ለማታ ለሌላ ጊዜ እያልክ አታዘግይ።
📚 [ "المنحة الربانية" (٢٨٧/٢٨٦) ]💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው። 👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው። 💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።
На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.